Get Mystery Box with random crypto!

ልዩ መረጃ ®

የቴሌግራም ቻናል አርማ leyumerga — ልዩ መረጃ ®
የቴሌግራም ቻናል አርማ leyumerga — ልዩ መረጃ ®
የሰርጥ አድራሻ: @leyumerga
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 50.90K
የሰርጥ መግለጫ

#ልዩ_መረጃ  |  #ቀዳሚ_ምርጫዎ
➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ
➠ወቅታዊ መረጃዎች
➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዜናዎች
➠ጠቃሚ ጥቆማዎች ይደርሶታል።
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን።
         PROMOTION
➥   
🎬  "ተመራጭ የዜና ምንጭ"
News & Media Channel®

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2023-01-16 20:34:11
#Tigray

የመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአፋጣኝ ስራ እንዲጀምር ለማድረግ እንደሚሰራ የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ አመራሮች ማረጋገጫ ሰጡ።

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አመራሮች ዛሬ በትግራይ ክልል ጉብኝት አድርገዋል።

አመራሮቹ ጉብኝት ያደረጉት በመዲናዋ መቐለ እና አካባቢው ሲሆን #ዓላማው ፦ በጦርነት ምክንያት በአምራች ዘርፎች ላይ የደረሰውን ውድመት ማእከል ያደረገ እቅድ ለማዘጋጀት እና በፍጥነት ስራ የሚጀምሩበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሆነ ተነግሯል።

ሚኒስቴሩ ፤ ጉብኝቱ ውድመት የደረሰባቸው እና በግብአት አቅርቦት እጥረት ስራ ያቆሙ አምራች ተቋማትን ስራ ለማስጀመር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጿል።

በዚሁ ጉብኝት በመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስፈላጊ የግብአት አቅርቦት እንደሚሟሉ እና በአፋጣኝ ስራ እንደሚጀምር አመራሮቹ ማረጋገጫ መስጠታቸው ተነግሯል።

በተመሳሳይ አመራሮቹ በውቅሮ ከተማ የሚገኙ ሸባ ሌዘር ኢንዱስትሪ እና ሰማያታ እምነ በረድ ፋብሪካ የደረሰውን ውድመት በአካል ተገኝተው መመልከታቸውንና ውድመቱ እንዳሳዘናቸው ድምፂ ወያነ ዘግቧል።

Photo Demtsi Woyane
1.9K views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-15 22:00:51
NGO በ0 አመት የወጣ የስራ ማስታወቂያ  በማንኛውም ፊልድ Amref Health Africa Vacancy Fresh Graduates

Deadline: January 23, 2022

Position: Intern

Requirements: Minimum of bachelor’s degree in health discipline, business, Accounting, social science or any related field of study.

Experience: Not required/ Zero years of work experience

How to Apply??
Click Here to Apply Online

https://abyssinajob24.com/amref-health-africa-vacancy-2023
share to your friends
2.5K viewsedited  19:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-15 14:25:23
በኔፓል አውሮፕላን ተከስክሶ የ40 ሰዎች ሕይወት አለፈ

72 ሰዎችን አሳፍሮ ከካትማንዱ ወደ ፖክሃራ ይበር የነበረው የየቲ አየር መንገድ አውሮፕላን የተከሰከሰው በማዕከላዊ ኔፓል አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ በማረፍ ላይ ሳለ ነው ተብሏል፡፡
በዚህም እስካሁን 40 አስከሬን መገኘቱን ነው ሬውተርስ የዘገበው፡፡

የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ፑሽፓ ካማል ዳሃል ካቢኔያቸውን ለአስቸኳይ ስብሰባ መጥራታቸው እና የአደጋ ጊዜ ሠራተኞችም በሥፍራው ተገኝተው የነፍስ አድን ሥራ እያከናወኑ መሆኑ ተመልክቷል፡፡

ከተጓዦቹ መካከልም÷ የሕንድ፣ ሩሲያ፣ የደቡብ ኮሪያ እና የአውስትራሊያ ዜጎች እንደሚገኙበት ነው የተጠቆመው፡፡
3.7K views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-14 22:44:19
★ አሜሪካን ኢምባሲ አዲስ የስራ ማስታወቂያ

Closing Date: January, 26 , 2023

American Embassy in Addis Ababa is seeking eligible and qualified applicants for the following job position

Position : Public Health Administrative Management Assistant

EDUCATION: Must have a bachelor’s degree in Management, Business Administration, International Development, Economics or Finance is required.

[ Salary: USD $12,764]

How to Apply Online??

https://abyssinajob24.com/embassy-of-united-state-vacancy-2023
4.4K views19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-14 10:31:32
የስራ ማስታወቂያ ከ at Ahadu Bank SC

Ahadu Bank Invites Interested and qualified applicants for the following job position.

Education Qualification: Accounting, Management, Business, Finance, Marketing, Economics, Banking, Business administration, Marketing Management, Banking and Insurance, Banking and Finance or another related field of study.

Position list

1: Customer Services Officer-I
2:Customer Service Officer II
3: Senior Customer Services Officer
4: Branch Manager I

Deadline: January 18, 2023

how to Apply Online
https://abyssinajob24.com/ahadu-job-new-vacancy
Share your friends
@leyumerga
4.8K viewsedited  07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 19:25:31
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ አውጥታው የነበሩ የማዕቀብ ሕጎችና ረቂቆች ተሰረዙ

በአሜሪካ የዴሞክራት 117ኛው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ላይ ህወሓትን በመደገፍ ወጥተው የነበሩ ማእቀቦችና ሌሎችም አስገዳጅ ህጎችና ረቂቅ ህጎች ሙሉ በሙሉ መሰረዛቸው ተገለፀ። ውሳኔውን የኢትዮ-አሜሪካዊያን ምክር ቤት ሰብሳቢ ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ ትላንት ለካውንስሉ አባላት በተደረገ ስብሰባ ይፋ ማድረጋቸው ነው የተጠቀሰው።

ማምሻውን በተሰማው በዚህ መግለጫ፤ አዲሱ የሪፐብሊካን 118ኛ ምክር-ቤት መላውን ኮንግረስ ሲቆጣጠሩ የነበሩት የዲሞክራቶች ረቂቅ ሕጎች ሙሉ በሙሉ ጊዜው ያለፈባቸው መሆናቸውን በይፋዊ ማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ካውንስሉ ገልጿል። ይህ እንዲዘገይ ለሰሩ የካውንስሉ አባላት እንዲሁም ለዩኒቲ ፎር ኢትዮጵያ ትልቅ ምስጋና አለን ብሏል።

ምክር ቤቱ አክሎም፤ አሁን በዜጎች ላይ እየተከሰተ ባለው የሰብኣዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ምን ማድረግ በሚኖርብን ጉዳይ ላይ ከአዲሱ የኮንግረስ መሪ ኬቨን ማካርቲ ሃላፊዎች ጋር ንግግር መጀመሩን አቶ አምሳሉ ካሳው ለአባላቱ አስታውቀዋል ሲል ገልጿል።
5.0K views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 16:38:57
ቻይና ለኢትዮጵያ 30 ሚሊዮን ዩዋን የእዳ ስረዛ አደረገች

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቼን ጋንግ ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት  የእዳ ስረዛውን እንደገለጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በተለያዩ ወቅታዊ የዲፕሎማሲ  ጉዳዮች መግለጫ ሰጥተዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋንግ ጉብኝት ወቅት ሁለት አበይት ስምምነቶች መፈረማቸውን የገለፁት አምባሳደር መለስ፣ በፖለቲካው ዘርፍ በጋራ ለመስራትና ከፊል የእዳ ስረዛ ስምምነት ተፈርሟል ብለዋል።
4.7K viewsedited  13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 14:57:05
#BelaynehKindie

ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ፤ በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገነቡት በዓመት 1 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መገጣጠም የሚያስችል የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከ3 ወራት በኋላ ሥራ እንደሚጀምር ገለፁ።

ይኸው በደብረ ብርሃን ከተማ ለተገነባው የኤሌክትሪክ መገጣጠሚያ ፋብሪካ 2 ቢሊየን ብር ወጪ እዳደረጉበት ተሰምቷል።

አቶ በላይነህ ፤ " ፋብሪካው ከሦስት ወር በኋላ ወደማምረት ሥራ ይገባል፡፡ " ያሉ ሲሆን " በዓመት 1ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የመገጣጠም አቅም አለው " ብለዋል።

ከሦስት ወራት በኋላ ወደ ሥራ ሲገባ በዚህ ዓመት ከ250 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እንደሚገጣጠሙ አቶ በላይነህ ተናግረዋል፡፡

ፋብሪካው #ለ500 ሰዎች #የሥራ_ዕድል እንደሚፈጥር መግለጫውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
4.7K viewsedited  11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 12:29:25
በ0 አመት አዲስ የስራ ማስታወቂያ
[Ababa gidey trading house PLC Vacancy Fresh Graduates
]

Deadline: jan 22, 2023


Position1: cashier

Education: BA Degree in Accounting and Finance or related

Experience: Not required/ 0 Years.

Position 2 junior Accountant

Education: Degree in Accounting and Finance or related

Experience: Not required/ 0
Years.

Position 3: Corporate Legal Service Head
Education: University degree or above in Law

How to Apply Online??

https://abyssinajob24.com/abebe-gidey-trading-plc-new-vacancy
4.7K viewsedited  09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 08:57:09
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ከብዘሃ ቋንቋ ካሪኩለም ጋር በተያያዘ ውሳኔዎችን አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው በ2ኛ አመት 8ኛ መደበኛ ስብሰባው ከብዘሃ ቋንቋ ካሪኩለም ጋር በተያያዘ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

ካቢኔው በመደበኛው ስብሰባ የብዝሃ የቋንቋ ስርዓተ ትምህርትን አስመልክቶ የኮተቤ ትምህርት ዩንቨርሲቲ ሲያስጠናው የቆየውን አዲሱን ካሪኩለም አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን ዩንቨርሲቲው ባስጠናው ጥናት ዙርያ ሰፋ ያለ የተለያዩ የህዝብ ( የተማሪ ወላጆችን ጨምሮ) ምክክሮችና ውይይቶች ሲካሄዱበት ቆይቶ በዛሬው እለት በጥናቱ በቀረቡት ምክረ ሃሳቦች ዙርያ ውሳኔውን አሳርፏል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

1ኛ:- በአዲሱ ስርዐተ ትምህርት ጥናት መሰረት በአፋን ኦሮሞ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ለሚማሩ ተማሪዎች አማርኛ እንደ ተጨማሪ (ሁለተኛ ) ቋንቋ እንዲሰጥ

2ኛ:- በአማርኛ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ለሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ አፋን ኦሮሞ እንደ ተጨማሪ (ሁለተኛ )ቋንቋ እንዲሰጥ

3ኛ:- ከ7ኛ ክፍል ጀምሮ በሁሉም የከተማው ትምህርት ቤቶች የአገር ውስጥ ቋንቋ መማራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ሁሉንም የትምህርት አይነቶችን በእንግሊዘኛ መማር እንዲችሉ እንዲደረግ

4ኛ:- ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎች አረብኛና ፈረንሳይኛ በሃይስኩል ደረጃ አማራጭ ትምህርት ሆኖ እንዲቀጥል፡፡

5ኛ:- የቅድመ አንደኛ ደረጃ የትምህርት መጀመሪያ እድሜ ከ4 ዓመት እንዲሆን
5.0K views05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ