#BelaynehKindie ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ፤ በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገነቡት በዓመት 1 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መገጣጠም የሚያስችል የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከ3 ወራት በኋላ ሥራ እንደሚጀምር ገለፁ። ይኸው በደብረ ብርሃን ከተማ ለተገነባው የኤሌክትሪክ መገጣጠሚያ ፋብሪካ 2 ቢሊየን ብር ወጪ እዳደረጉበት ተሰምቷል። አቶ በላይነህ ፤ " ፋብሪካው ከሦስት ወር በኋላ ወደማምረት ሥራ ይገባል፡፡ " ያሉ ሲሆን " በዓመት 1ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የመገጣጠም አቅም አለው " ብለዋል። ከሦስት ወራት በኋላ ወደ ሥራ ሲገባ በዚህ ዓመት ከ250 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እንደሚገጣጠሙ አቶ በላይነህ ተናግረዋል፡፡ ፋብሪካው #ለ500 ሰዎች #የሥራ_ዕድል እንደሚፈጥር መግለጫውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። 4.7K viewsedited 11:57