Get Mystery Box with random crypto!

ቅን ልቦች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ken_leboch — ቅን ልቦች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ken_leboch — ቅን ልቦች
የሰርጥ አድራሻ: @ken_leboch
ምድቦች: ቴሌግራም , ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 5.54K
የሰርጥ መግለጫ

ደግነት ለራስ ነው !!
❣❣ በፍቅር ከሆነ እንስማማለን❣❣
ለ አስተያየት @Tesfish2

@EgerKwasMeme
@YehabeshaTiktok
@ye90slijochfans
▶ YouTube 🔥
https://youtu.be/619clN81mFs

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-01 20:34:31 ሰላም ቅን ልቦች

እንዴት ናችሁ ?? በቅርቡ በአዲስ ታሪክ እንመለሳለን።

አስተያየት አላችሁ ? .. @Tesfish2 በዚህ ፃፉልኝ
2.0K viewsTesfa Desalegn, 17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 07:43:01 ያለፈውን መንገድ ያለፈውን የውሃ ጥም የምታስረሳው። የተጣላባቸውን ጊዚያቶች የምትስረሳው በመሆኗ ኤሴቅ ሲል ሰየማት። ሁላችንም የምንጣላው ተጣልተን የምናገኛትን ሕይወት ለማጣጣም ነው። ያቺ ሕይወት ተጣልተን ያገኘና ዋጋ ከፍለን ያገኘናት ስለሆነች ኤሴቅ ልንላት ይገባል። እኔ ልጄ የኔ የመጨረሻ ደስታዬ ናት። ከዚህ በላይ ደስተኛ ልሆን አልችልም። ልሆን የምችለው ድጋሚ ልጅ ስወልድ ነው። ስለዚህ እዚህ ሕይወት ለመድረስ በርካታ ውጣ ውረዶች በመኖራቸውና ከእናቴም ከእህቶቼም ጋር ተጣልቼ የሸሸሁት በእነሱ ግፍ ብቻ አይደለም። ይቺን የሕይወት ፍሬ ፍለጋ እንጂ!"አለ ቀዳማዊ ።ሐምራዊ አንገቷን ነቅንቃ አንገቱ ስር ተወሸቀች።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ተ.ፈ.ፀ.መ!!!!!!

ኤሴቅ ተከታታይ ታሪክ አልቋል!!! ለአመታት የቆየው ድርሰት ይህን ይመስል ነበር። በድርሰቱ ላይ ያላችሁን አስተያየት በ @Adwa_1888 እንድታደርሱኝ በትሕትና እጠይቃለሁ።

ስለ "ኤሴቅ" ድርሰት ያላችሁን አስተያየት ና ሐሳብ በ @Adwa_1888 ብቻ አድርሱኝ። ለአስተያየት መቀበያ ብዬ ከወራት በፊት የከፈትኩት የራሴ ሊንክ ስለሆነ በእሱ አድርሱኝ


###እንዲሁም ድርሰቴን በሌላ ቻናል ስትለቁ የነበራችሁ የቻናል ባለቤቶች ለአስተያየት የኔን የግል ዩዘር ኔም በመጠቀም ሀሳብና አስተያየት ለእኔ እንዲሰጡኝ እንድታደርጉ በአክብሮት እጠይቃለሁ። ምክንያቱም የአንባቢያን ሐሳብና አስተያየት ለእኔ በእጅጉ ይጠቅመኛልና!
የአስተያየት መስጫ ሊንክ

@Adaa_1888
@Adwa_1888
@ken_leboch
2.5K viewsTesfa Desalegn, 04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 07:43:01 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፴፬~ ( 234)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888


****
ሔዋን የሁላቸውንም ልብስ የቆሸሸውን ለሰራተኛዋ እየሰጠች ያልቆሸሸውን ደግሞ በስርአት እያስቀመጠች ነው። የሔመንን ክፍልም እያስተካከለች ሳለ አንድ የግል ማስታዎሻ የአልጋዋ ራስጌ ላይ አገኘች። ማስታወሻውን ለማየት ፈራ ተባ ብላ ከፈት አደረገችው። የማስታወሻው ደብተር መግቢያ ላይ በእጅ ፅሁፍ እንዲህ የሚል መልዕክት ሰፍሯል። "Irreversible Life "
A man who once walked as the wind blows.he let out a sigh of relief and put the blow to my heart. የምትል በእንግሊዝኛ የተፃፈች ቃል። ገፁን ገለጠችው። የቀዳማዊ ምስል አለ ከስሩ "the wing of my life"ይልና ገለጥ ስታደርገው "I fly with your wings! I am as far away as you have given me. But now my wings are weak.i can't go anywhere love.help me!! (በክንፎችህ በርሪያለሁ። በሰጠኸኝ ፍጥነት ልክ ርቂያለሁ። ነገር ግን አሁን ክንፎቼ ደክመዋል። አቅም አጥሮኛል የትም መሄድ አልቻልኩም ፍቅር። እርዳኝ!" የሚል ተማፅኖ የተቀላቀለበት ፅሁፍ ነበር። በርካታ ገፆችን ከምስል ጋር የሰፈረባቸውን የፍቅር መልዕክቶች በእንባ እየተሞላች አነበበቻቸው። ምንም እንኳ ሔመን ቀዳማዊን እንደምትወደው ብትገምትም ነገር ግን በዚህ ልክ በዚህ እርቀት ይሆናል የሚል ሀሳብ ፈፅሞ አልነበራትም።ሔመን ለአተመታት በቀዳማዊ ፍቅር ስትሰቃይ ብትቆይም ነገር ግን ሕመሟን ለራሷና ለራሷ ብቻ ነበር ይዛው የኖረችው። ሔዋን ያለችበት እስኪጠፋት ድረስ ተሰወረች።ራሷን ይዛ ለመቆም ሞከረች። ከዚህ ገፅ በላይ መሄድ አልቻለችም። የሔመንን የሕመሜ ቃላት መቀበል እስኪያቅታት ድረስ አመማት። በዚህን ጊዜ ሔመን በፈገግታ ታጅባ ስልክ እያወራች ወደ ቤት ገባችና ስትመለከት ማንም እንደሌለ ስትረዳ "ማንም የለም እንዴ ዝኑ?"አለች። "እትዬ ሔዋን አለች። ያንቺ ክፍል ውስጥ ናት"በማለት ጠቆመቻት። ሔመን ያቋረጠችውን ስልክ ቀጥላ እያወራች ወደ ክፍሏ ስትገባ ሔዋን የእሷን ማስታወሻ አቅፋ እያለቀሰች ነበር። ሔመን ስልኩን ዘግታ በቀስተ ተራመደችና ከእናቷ ጎን ጋደም አለችና እንባዋን አበሰችላት። ሔዋን ሔመንን ለደቂቃዎች ስትመለከታት ከቆየች በኋላ "ልጄ ለምን ይሄን ሁሉ ይሄን ያህል ጊዜ ይዘሽ?" አለች እንባዋን እያፈሰሰች። "ብታውቂ ምን ታደርጊ ነበር? አዎ ቀዳማዊ ላይ ተፅእኖ ትፈጥሪያለሽ። እኔን እንዲያገባ ጥረት ታደርጊያለሽ እሱንም ታስገድጅዋለሽ!"አለች ሔመን ፈገግ ብላ " ልጄ እንደዛ አይሆንም ቢያንስ ሁሉም ነገር በልክ ይሆን ነበር። በዛ ላይ ለእሱም ቢሆን አንቺ ነሽ የምትሻይው። ከማንም በላይ አብረሽው ኖረሻል አድገሻል"አለች ሔዋን። "አይ እማዬ ለእሱ ግን ከእኔ ይልቅ ሐምራዊ ትበልጥበታለች። እኔን ደግሞ በእህትነት ከሐምራዊ በላይ እንደሚወደኝ እንደሚሳሳኝ አውቃለሁ። እሱን ደስተኛ የሚያደርገው ሕይወት እንዲህ ሲሆን ነው። እኔም ቢያንስ በዚህኛው ደስተኛ እሆናለሁ። ባይሆን ኖሮ አንቺ እንዳልሺው ከመጀመሪያው እሱን እንዳገባ ብታደርጉ እሱ ለዘላለም እህት የሚባል ነገር አያውቅም። በእህቶቹ መጥፎ ጠባሳ አለበት። ስለዚህ ቀሪ እድሜውን ከሚሰቃይ እኔ ሕመሙን ብጋራው ይሻላል ብዬ ነው ለራሴ እንኳ ደግሜ ሳልናገር የያዝኩት። ቀዳማዊ ደስታ ብቻ ነው የሚገባው። እኔ ደግሞ የዛ ደስታው አጠልሺ መሆን አልፈልግም ። እኔን በሚገባ ሰርቶኛል። አሁን ያለሁበትን ስብዕናና ማንነት በእሱ ምስል የተገነባ ነው። ተመልከቺ እማዬ አሁን በጣም ጎበዝ ተማሪ ነኝ። ለዚህ ደግሞ ከፍተኛው ምሽጋና የሚወስደው ቀዳማዊ ነው። በሁሉም ነገር ጎበዝና ተፎካካሪ እንደድሆን፣ ሕይወትን በሌላ መነፀር መመልከት እንዳለብኝም ጭምር አስተምሮኛል። ስለዚህ ለዚህ ግብሩና ማንነቱ ደግሞ ሁሌም ሳፈቅረው እኖራለሁ። ነገር ግን የኔ ይሁን ማለቴ አይደለም። ፍቅር ፍቅር የሚሆነው ሁለቱም ተመሳሳይ ስሜት ሲኖራቸው ነው። ያንደኛው ብቻ ከሆነና የሌላኛው ሌላ ጋር ከህነ አይሰምርም። ቀዳማዊ ደግሞ የሚያፈቅራትን እሷም ስለምታፈቅረው ተገናኝተዋል። በነሱ መሀል ደግሞ መግባት ስላልፈለኩና የቀዳማዊ ደስታ ከእኔ ፍቅር ስለበለጠብኝ ሁሉንም ተውኩት"ብላ የእምባ ዘለላዎቿን በጉንጮቿ ላይ ጣለቻቸው። ሔዋን አቀፈቻትና "ለካ ያን ሁሉ ደስታ ስደሰት የነበረው በልጄ እንባና ህመም ኖሯል"አለች። "ተይ እማዬ እንደዛ አትበይ ቀዳማዊም ልጅሽ እኮ ነው። ምንም እንኳ እንዲህ ስትይ ባይሰማሽም ግን እኔ ይከፋኛል። ያራቅሽው ያህል ይሰማኛል። የእሱ ጥፋት ደግሞ ምንም ነገር የለም። የሆነ ነገር ጀምረን እሷን መርጦ ቢሄድስ እሺ ነገር ግን እንደማፈቅረው እንኳ የማያቅን ሰው መኮነን ተገቢ አይደለም እማዬ። ተረጋግተሽ አስቢና ለቀዳማዊ የነበረሽን ቦታ መልሺ። ትንሽ እንኳ ቅይር ብትይበት የምር እማዬ በጣም አዝንብሻለሁ ይከፋኛል። እኔ ቀዳማዊ ድጋሚ በቤተሰቦቹ እንዲያዝን አልፈፍግም። ለእሱ ያላችሁት ያለነው ብቸኛ ቤተሰቦቹ እኛ ነን። የኔ ሕይወት ይህ ጅማሮው ነው እንጅ መጨረሻው እንዳልሆነ በመረዳት ለእሱ ያላችሁ ቦታ እንዳይቀንስ አደራ እማዬ በእኔ ሞት ነው የምለምንሽ። እኔ እንደቀዳማዊ የማፈቅረውን ባይሆንም ምቾት የሚሰጠኝንና የሚያፈቅረኝን ወንድ መርጬ የእናንተን ደስታ እደግመዋለሁ እሺ እማዬ" ብላ ሔመን በልመና ጭምር ጠየቀቻት። "እሺ ልጄ ቃልሽን አከብራለሁ። ግን ደግሞ ይሄን መቀበል እንደሚከብደኝም እንድታውቂልኝ የኔ ቆንጆ"አለች ሔዋን መቋቋመም እያቃታት። ሔመን አባበለቻትና ወጥታ ወደ መናፈሻው ሄደች። ሔዋን አንድ በአንድ የሔመንን ሁኔታ ማስታወስ ጀመረች። የሰርጉ ጊዜ ራሱ ብዙም አልታየችም። ሰፊውን ጊዜ ክፍሏ ውስጥ ነበር ያሳለፈችው። ቀዳማዊን ቤት ስታጣው የምትነጫነጨው ነገር። ስታየው ደግሞ በስስትና በፍቅር አይኗ አይኖቹ ላይ የሚንከራተተውን ነገር አስታወሰች። እንደውም አቶ ሙሉሰው አንድ ጊዜ "ይቺ ልጅ ያለ ቀዳማዊ ሁሉንም ማድረግ አትፈልግም። እኔ አሁን አሁን እያሳሰበችኝ ነው። ያለ እሱ መኖርን የምትለምደው አይመስለኝም! "ብሎ ነበር። "እንዴት አይገባንም? የማንረባ እኛን ቢሉ ወላጆች። እኔን ቢሉ እናት? እንዴት ሁኔታዋን አይቼ ስሜቷን መረዳቴ ያቅተኛል?"አለችና ሔዋን በራሷ ተበሳጨች።
ሔዋን ያለውን ነገር ሙሉ በሙሉ እውነቱን ለሙሉሰው ነገረችው። ሙሉሰው በነገሩ ብዙም አልተገረመም። "እኔ አኳኋኗ አላማረኝም ነበር። ያው ብገምትም ደግሞ የቀዳማዊ ሁኔታ እንደ እህቱ ስለነበር የሚያያት ጉዳዩ በአጭር ይቋጫል ብዬ ነበር። ለማንኛውም ይሄ ያለፈ ምዕራፍ ነው። ሔሚ እንዳለችው ራሷን ለራሷ ነገ ታዘጋጃለች። አሁን ልጅ አይደለችም። ሁሉንም ነገር ግራና ቀኝ ታስተውላለች። ስለዚህ ለራሷ እንተውላት። ራሷ መፍትሔ ትስጥበት"አለ ሙሉሰው።
*
"ግን ቀዳ ኤሴቅ ማለት ምን ማለት ነው?"አለች ሐምራዊ። ቀዳማዊ ትንሽ አሰብ አደረገና ጉሮሮውን ጠራርጎ "የኔ ፍቅር #ኤሴቅ ማለት #የተጣላሁብሽ ማለት ነው። ይቺን ስም ያወጣት በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የአብርሃም ልጅ ይስሀቅ ነው። በፍልስጤሙ ሀገረ ገዥ በንጉስ አበሜሌክ ጊዜ የሆነ ታሪክ ነው። ይስሀቅ እየተገፋ እየሄደ በመጨረሻ ላይ ከሁሉመሰ ጋር ተጣልቶ ያገኛትን የውሃ ጉድጓድ ለእሱ ተስማሚ የሆነችለትን የውሃ ጉድጓድ ሰላማዊ ኑሮ እየኖረባት ያለችውን የውሃ ጉድጓድ የሰየማት "ኤሴቅ "ብሎ
ነው። ይቺ ጉድጓድ
1.8K viewsTesfa Desalegn, 04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 21:44:40 ሰላም እንዴት ናችሁ ?
ኤሴቅ በነገው እለት የመጨረሻው ክፍል 234 ይቀርባል። እንዴት ነበር ወደዳችሁት ?
1.4K viewsTesfa Desalegn, 18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 07:39:01 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፴፫~ ( 233)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
"እንደዛ ማድረግ አልነበረብሽም።ይሄ ትልቅ ነውር ነው። በዛ ሁሉ ሰው ፊት የማይሆን ነገር ነው ያደረግሺው።በዛ ላይ የእናንተንና የእናታችሁን ስራ ሁላቸውም ያውቃሉ።ይበልጥ ነውራችሁን ነው በአደባባይ የገለጣችሁት "አለ የማለፊያ ባል። "ውይ አንተ ደግሞ ተወኝ በሀዘኔ ላይ ሌላ ነገር አትጨምርብኝ"አለችውና ገላመጠችው። ባለቤቷም ትኩር ብሎ ከተመለከታት በኋላ "እኔማ እተውሻለሁ ስራሽ እንዲተውሽ ነው እንጅ ራስሽን መለመን"ብሏት ትቷት ወጣ
***
ቀዳማዊ ያለው ሁኔታ ምቾት ባይሰማውም በዚህ ጊዜ መሄዱን አልፈለገውም። ነገር ግን ሐምራዊ የሰሞኑ ሁኔታዋ ልክ ስላልሆነ። ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ተነሳ። "ትንሽ ብትቆዩ ደስ ይለን ነበር"አሉ ዳሳሽና ሙሉቀን እንደተለመደው ቅር ተሰኝተው። "እኛም ደስ ይለን ነበር። ግን ደግሞ"አለና ቀዳማዊ ወደ ሐምራዊ በመዞር የሚሄዱበትን ምክንያት ለማስረዳት ሞከረ። ሙሉቀን የቀዳማዊ የአይንን ጥቅሻ በሚገባ ስለተረዳ "እሺ ዛዲያ ምን እናደርጋለን እንኸዳለን ካላችሁማ"በማለት ተረታ። ዳሳሽም የሙሉቀንን ሀሳብ ከደቂቃዎች በፊት ተከትላ እንዳይሄዱ ስትለምን እንዳልቆየች አሁን ደግሞ የሙሉቀንን ሀሳብ እየደገፈች። "እሺ እንግዲህ መልካም መንገድ ይሁንላችሁ። በሰላም ያስገባችሁ"አለችና ተገናኝታቸው ተለያዩ። መልካሙ (አቤል) መኪናውን አስነስቶ ወደ ሐመረ ኖኅ ጉዞ ጀመሩ።
ሁላቸውም ለየብቻቸው የራሳቸውን ወሬ እያወሩ። ቀዳማዊና ሐምራዊም አፍ ለአፍ ገጥመው እየተጫወቱ ሀመረኖኅ ደረሱ። "እንግዲህ ወንድሜ አቤል ላደረከው ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ። በደንብ እንጫወታለን። ያው እንግዳ ስለያዝኩ ነው እንጅ በሰፊው ብንጫወት ደስ ይለኝ ነበር። ነገር ግን እንደምታየው ነው"አለ ቀዳማዊ በትሕትና። "ኧረ ወንድሜ በሚገባ እረዳለሁ። በስልክም በምንም እንጫወታለን። እናንተ በሰላም ግቡ። ሙሽሪትም በሰላም ተገላገይ ማርያም በሽልም ታውጣሽ። ወንድሜ እንዳትረሳ ስትወልድ ወዲያው ንገረን"አለ መልካሙ (አቤል)። ቀዳማዊ አቀፈው። መልካሙም መልሶ አቅፎ ጀርባውን መታ መታ አደረገውና "እንኳንም አገኘንህ። አሁን በጣም ደስተኞች ነን።"ብሎት ሁላቸውንም በየተራ እጂ ነስቶ ተሰናበታቸው።
***
"በጣም ይቅርታ ጋሼ! ከባለቤቴ ጋር ሆነን ልንመጣ ነበር ያሰብነው። በመሀል ያው እሷ ትንሽ አመም ሲያደርጋት ቀጥታ ወደዚህ መጣን። ያው ነፍሰጡር ስለነበረች"አለ ቀዳማዊ "አውቃለሁ የኔ ልጅ የሆነ እክል ኤንደገጠመህ ገብቶናል። ትሕትናም ስትነግረኝ ነበር። ግዴለም ልጄ መገናኛ ዘዴ አናጣም። እኔ እንደውም አደዋወሌ እንኳን ደስ አለህ። ባባትህ ስም ትምህርት ቤት መክፈትህ ትልቅ ነገር ነው። አሁን ከመቼውም በላይ አስተዋይና ብልህ ልጅ መሆንህን ተረድቻለሁ"አለ ደረጄ ኩራት እየተሰማው። "አመሰግናለሁ ጋሼ ያው መሠረታችንን ካላጠበቅነው መቆም አንችልም። ምንም ያህል በደል የደረሰብኝ ቀዬ ቢሆንም ነገር ግን መሠረቴም መነሻዬ ነው። አባቴ ደግሞ የኔነት ሰሪ ነው። ስለዚህ ያን ውሳኔ ወሰንኩ"አለና ቀዳማዊ ሀሳቡን በትንሹም ቢሆን ጠቅለል አደረገ። "በጣም ጥሩ ነው ያደረከው"አለና ደረጄ አበረታታው።
ሐምራዊ ብዙም ሳትጨነቅ በሰላም ተገላገለች። ተስረቅራቂ የህፃን ልጅ ድምፅ ተሰማ። ሁሉም በእፎይታ ተነፈሱ። ቀዳማዊ የሆስፒታሉን ኮሪደር ወዲያና ወዲህ እያካለለ ሳለ የሐምራዊን የመውለድ ዜና ሰማ። "እንኳን ደስ አላችሁ ሐምራዊ ሴት ልጅ በሰላም ተገላግላለች።"አለ አዋላጁ። ቀዳማዊ ልቡ በሀሴት ተሞላ። ጭንቀቱ ከመቅፀበት ሄዶ በደስታ ተተካለት። "ተመስገን አምላኬ!"አለ ጮክ ብሎ።
***
ከወራቶች በኋላ የሆኑ የፊልም ኢንዱስትሪዎች በቀዳማዊ የመስሪያ ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ጠቋሚነት ስለ ቀዳማዊ የሚያትተውን ዶክመንተሪ ፊልም በአጭር ጊዜ አጠናቀው ለምርቃት ቀረበ። በዚህ የሕይወት ዘጋቢ ፊልም ላይ ቀዳማዊ የነካቸውና ከቀዳማዊ ጋር ተያያዥነች ያላቸው ቦታዎች ተዳሰዋል። በዚህ ዘጋቢ ፊልም ምርቃት በርካታ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ተገኝተዋል። እንዲሁም በቀዳማዊ ተጋባዥነት የመጡ መሀንዲሶች ዶክተሮችና ሌሎችም ተገኝተዋል። የዘጋቢው ፊልም ዋና ዳይሬክተር ንግግር ካደረገ በኋላ ባለታሪኩን ለንግግር ቀዳማዊን ጋብዞ ወረደ። "ሕይወት መልከ ብዙ ቀለም አላት።በጣም ብዙ። ወድቀን ስንነሳ ይዘነው የምንነሳው ቀለም፣ እንዲሁም ከወደቅንበት ተነስተን አራግፍን የሚታየው የሕይወት ቀለም ሌላኛው ደግሞ ያንኑ ልብስ አቧራውን አራግፈን የነበረውን ልብስ አጥበን ስንለብስ የሚታየው የሕይወት ቀለም ነው። የመጨረሻው ያን ልብስ ቀይረን በሌላ ልብስ ራሳችንን የምናሳየው የሕይወት ቀለም ነው። በቅደም ተከተልና በሂደት የምንሰራው ራሳችንን መጨረሻችንን ይናገራል። ሰው ራሱን በሂደት እየሰራ የተሻለ ያደርጋል። እኔ በእኔ ፅናት ብቻ ነው እዚህ የደረስኩት ብዬ አላምንም። እግዚአብሔር ነው ለዚህ ሁሉ ያደረሰኝ። ያለ ፈጣሪ እርዳታ ምንም አልሆንም የትም አልደርስም ነበር። ምክንያቶችን እየፈጠረልኝ ሕይዎቴን የተሻለ እንድናደርግ ረድቶኛል።ለዚህም ክብርና ምስጋና ይግባው።ፈጣሪ ማስተማሪያ እንድሆን ከእኔ ሕይወት በርካቶች እንዲማሩ ለማስቻል ደግሞ እነዚህን ወንዶሞቼን በማነሳሳት ይሄን ዶክመንተሪ እንዲያዘጋጁ አድርጓቸዋል። እኔም ለእሱ ክብር ይግባውና ይሄው ስላለፈው ሕይወቴ የተደረሰን ፊልም አስመርቄ እየተናገርኩ ነው። በጣም እድለኝነት ይሰማኛል"ብሎ በርካታ የሕይወት ምሳሌዎችንና እውነታዎች አንስቶ ለታዳሚዎች አቅርቦ አመስግኖ ወረደ።
"የኔ ፍቅር እንኳን ደስ አለህ።በጊዜ አለቀ እንዴት ነበር"አለችና ሐምራዊ ሳመችው። "አመሰግናለሁ የኔ ፍቅር ጥሩ ነበር። እስኪ "ኤሴቅን ስጪኝ ልቀፋት"አላትና ሕፃኗን ተቀበላት። "ምንድን እሱ የኔ አበባ አባትሽን ታውቂዋለሽ?"እያለ ከኤሴቅ ጋር ይጫዎት ጀመር። "እንዴት ነው አባቷን የማታቀው በዚህ እድሜዋ አባቷን ካላወቀችማ ምኑን ልጅ ሆነችው"አለችና ሐምራዊ ሳቀች። "የአባቷን ጠረን የምታውቀው አሁን ነው"ብሎ ኮስተር አለ። "እሺ ይሁንልህ ተጃጃል!"አለችና እየሳቀች ወደ ኪችን ሄደች።
@amba88
@ken_leboch
1.5K viewsTesfa Desalegn, 04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 07:38:01 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፴፪~ ( 232)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
"የሐመረ ኖህ ወረዳ አስተዳዳሪ ና ልዑካቸው እየተዟዟሩ ትምህርት ቤቱን ከጎበኙ በኋላ ወደ ተዘጋጀላቸው የክብር ወንበር ሄደው ተቀመጡ። "ጥሩ አድርጎ ነው ያሰራው። በሚገባ የተደከመበት ስራ ለመሆኑ ህንፃው ይናገራል"አለ የሐመረ ኖኅ ከተማ ከንቲባ። "በትክክል ከእኛ የሚጠበቀው ጥሩ ጥሩ መምህራኖችን መቅጠር ነው። በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ተማሪዎች ትምህርት ተመዝገበው እንዲማሩ ይደረጋል። ማንኛውም ከሰባት አመት እድሜ ከፍ ያለ ልጅ ካለ በግዴታም ቢሆን ገብተው መማር አለባቸው። ይሄን ስራ ደግሞ እናንተ መስራት አለባችሁ"አለና የወረዳው አስተዳዳሪ ወደ ቀበሌው ሊቀመንበር ዞረ። "በትክክል እንጅ እኛ እየዞርን ቤተሰቦቻቸውን በማስፈራራት ትምህርት እንዲጀመሩ አሰናደርጋለን"በማለት መለሰ።
*
የትምህርት ቤቱን መመረቅ ተከትሎና የነ ቀዳማዊን መምጣት ተመልክቶ ጥሩ ድግስ ተደግሷል። ዘመድ አዝማድና ጎረቤትም ተጠርቷል። ከወይዘሮ አትጠገብ ልጆች በስተቀር ሁላቸውም መጥተዋል። ሙሉቀን ጨዋታውም ምኑም እንዲደራ ከአንድ ቀን በፊት ለሊቀ መኳስ መልዕክተኛ ልኮበት ነበር። "እንደምን አለህ ሊቀመኳስ ተቻልህ እና ቶሎ ከደረስክ ነገ ጠዋት ታልሆነልህ ደግሞ ወደ ማታ አካባቢ እንድትደርስ። የደጃዝማች ታረቀኝ ልይ ቀዳማዊ መጥቷልና እንዳትቀር አደራ "የሚል መልዕክት ነበር የሰፈረበት ደብዳቤው ላይ።
"ውሸት በፍርቃ ግንድ
ሲታጠን እንድታይ ጧት እንዳታረፍጂ
ታይቷል አምሮ ከብሮ
በደጃዝማች እውነት ጊዜ ሆይ ስገጂ"ሊቀመኳስ እንጉርጉሮውን ጀመረ። "እየው እየው ይሄ መናጢ ጨዋታዋን ጀመራት። አጀብ ነው እንዴት ነው ወጓን የሚፈጥራት"አለ አንድ ሽማግሌ በፈገግታ የዳሱ ኮርና ላይ ተቀምጦ ጠጁን እየጠጣ ከሌላኛው አጠገቡ ከተቀመጠ ጎረቤቱ ጋር እየተያያ። "አዎ በደንብ እንጅ ወጓንም እውነቷንም ወዋታዋንም ሽሙጧንም በደንብ ነው የሚችልባት"አለ ሌላኛው።
"አዝማሪ ያደረጉለትንና ያደረጉበትን አይረሳምና ዛሬ በአካል ባይኖርም ደጃዝማች ታረቀኝ የሁላችንም አባት ነው። ማንም የማይሰጠኝን ክብር ነበር እሱ የሚሰጠኝ። አዝማሪነቴ ጥበበኝነት እንደሆነና መዝናኛ እንደሆነ ነበር ሁሌም የሚነግረኝ"አለ ሊቀመኳስ ማሲንቆውን ለአፍታ አቁሞ። ሔዋንና ሙሉሰው ራሳቸውን በአግራሞት ነቀነቁ።
ሕይወት በብዙ መልክ ሆና በስኬት ካባ ተከናንባ በሌላ የድል ምዕራፍ ሕይወቷን ሀ ብላ ትቀጥላለች። ቀዳማዊ በሊቀመኳስ የግጥም ስንኞች ትላንቱን እንደ ገብስ እህል በሀሳብ መንሽ እየበረበረ በልጅነት ዛላ የረሳውንም እያስታወሰ ያስታወሰውንም እያጣጠመ አመሸ። ሊቀመኳስም ክፉዎችን በስንኙ እየጎሸመ መልካሞችን እያሞገሰ ከበርካታ የብር ሽልማቶች ጋር አመሸ። በሕይወቱ ተሸልሞ የማያቀውን የብር መጠን በአንዲት ጀንበር አጋብሶ አመሸ።
***
"እባካችሁ ልጆቼ አንድ ነገር ብቻ ልለምናችሁ ልጄን ለመጨረሻ ጊዜ ልዬው ጥሩልኝ። ቢያንስ ለነፍሴ ጥሩ ስንቅ ይሆናታል። እንደዚሁ መሄድ አልፈልግም "አለች ወይዘሮ አትጠጠብ ዙሪያውን የከበቧትን ልጆች እየተማፀነች። ግራ ተጋብተው ተያዩ "ይቺ ሴትዮ ምንድን ነው የምትለው?"አለችና አድና በንዴት ተነስታ ወደ ስርጡ(ጓዳ) ገባች። "በቃ እህቶቼ እየደከመች ነው ቀዳማዊን እናስጠራላት።ምንም ቢሆን የእኛ ፍላጎት ከእናታችን አይበልጥም"አለች ርብቃ። በርብቃ ሀሳብ ተስማምተው ለቀዳማዊ መልዕክት ተላከ። ሙሉቀን ዙሪያ ገባውን ጋራና ሸንተረሩን ከምሽቱ አናሳ የጨረቃ መጠን ጋር እያስተያየ ውጪ ላይ ተቀምጦ የርብቃ ልጅ እያለከለከ መጣ "ጋሻዬ ሙሉቀን!"አለ "አቤት ምን ሆነህ ነው የምታለከልከው? እየሮጥኩ ስለመጣሁ ነዋ!" "ምን ሆነህ ነው እየሮጥክ የመጣኸው?"ሙሉቀን እየደነገጠ ጠየቀው። "አያቴ ደክማለይ እና ቀዳማዊን መገናኘት ትፈልጋለች። አጎቴን እንዲመጣ ጥሩ ብላ ነው። እንድጠራው ተልኬ ነው።"አለ ሙሉቀን በፍጥነት ወደ ቀዳማዊ ጋር ሄደና በሹክሹክታ በጆሮው ሁሉንም ነገረው።"እሺ አንድ ጊዜ ጠብቀኝ ላስተኛት"አለ ጭኑ ላይ የተኛችውን ሐምራዊ እየተመለከተ። ሐምራዊን ደገፍ አቀፍ አድርጎ መኝታቸው ጋር ካስተኛት በኋላ ከሙሉቀን ጋር ህፃኑን ተከትለው ሄዱ።
ቀዳማዊ እንደደረሰ ሁላቸውም በፀጥታ ተዋጡ። ዙሪያ ገባውን አማተረ። ያ ምድጃ አሁንም አለ። በብርድ ተመትቶ ለመሞቅ የሚቀመጥበት የምድጃው ጠርዝም መልኩን አልቀየረም። የመከራ ስቃይ በልቶ የሚተኛባት ደመደም የምትመስለዋ መደብም ያለምንም ልዩነት አለች። ቀዳማዊ አይኖቹ እንባ አርግዘው ሁሉንም ተመለከተና ዝቅ ሲል ሌላኛው መደብ ላይ ወይዘሮ አትጠገብ ተኝታለች። ሙሉቀን ቀዳማዊን ደገፍ አድርጎ ወደ ወይዘሮ አትጠገብ አስጠጋው። ርብቃ የእናቷን ወገብና አንገት ደገፍ አድርጋ "ይሄው መጥቷል"ብላ በአጠጯ ወደ ቀዳማዊ ጠቆመቻት። አይኖቿን እያርገበገበች ቀዳማዊን ለማየት ጥረት አደረገች ነገር ግን አይኖቿ ብዥታ ውስጥ ስለነበሩ ቀዳማዊን በትክክል ለመመልከት አልቻለችምና አይኖቿ ወደነበረበት ተከድነው ሰውነቷ እየቀዘቀዘ ሄደ። ወይዘሮ አትጠገብ ለዘላለም ይቺን ምድር ተሰናብተዋት ሄዱ። ርብቃ ዋይታዋን አቀለጠችው። ሌሎቹ እህቶቿም ተከትለዋት እሪ አሉ። ፊታቸውን እየነጩ ደረታቸውኝ መድቃት ጀመሩ።
"ምንድን ነው ወዲያ ማዶ ግድም ዋይታ አለሳ እልፍነሽ "አለ አባወራው "አይይ አትጠገብ አረፈች ማለት ነው። በጣም ተቸንፋ ነበር። ሰሞኑን አታልፍም እያለ ነበር ሰው። አየ ጉድ አዬ ጉድ በመጨረሻ ወደማይቀረው ሄደይ!"አለችና በሀዘን እንደመተከዝ ብላ ለነገሩ ለእሷ እንኮ ሞቱ ይሻላታል። በጣም እየተሰቃየች ነበር"አለችና እንደመተከዝ አለች።
ቀዳማዊ በለቅሷቸው ደንዝዞ ቆመ። ለማን እንደሚያለቅሱ ማን እንደሞተ ግራ የገባው ይመስላል። ፊቱ ላይ የእንባ ርዝራዥም ሆነ የሀዘን ጥላ አጥልቶ አልታየበትም። ሙሉቀን ይዞት ወጣና ወደ ቤት መለሰው። ቀዳማዊ አልተቃወመውም ምንም ነገርም ደግሞ አላለውም።
"ልጄ የምን ለቅሶ ነው?"አለች የሙሉቀን እናት ""ወይዘሮ አትጠገብ እኮ አረፈች"። እነ ሙሉሰውና ሔዋን በድንጋጤ ተያዩ። "ኧረ እግዚኦ ምን አይነት ማዕት ነው!"አለችና ብድግ ብላ ወጣች። "ምነው ምን ሆና ነበር?"አለች ሔዋን ሙሉቀንን "አይ ከታመመች እንኳ ቆይታለች። እርጅናውም ምኑም ተጨምሮባት አባበሰባት። ቀዳማዊን ለማየት አስጠርታው ነበር። ልክ ቤት ስንደርስ ጉልበትም ምንም አንሷት ነበርና ትንሽ ሳትቆይ ወዲያው አረፈች"አለ። ቀዳማዊ ሁለታቸውንም ሲያዳምጣቸው ከቆዬ በኋላ ወደ ቤት ውስጥ ገብቶ ሐምራዊን እቅፍ አድርጎ ትኝት አለ። ሙሉቀን ተከትሎት ሊገባ ሲል "ተወው ልጄ የፈቀደውን ያድርግ ሕመሙ ሲዘልቀው ተነስቶ ያለቅሳል። ያዝናል"አለች ሔዋን። ዋይታውና እሪታው እየጨመረ መላው መንደሩን አዳረሰው።
ብሰንት ልመናና ጉትጎታ ቀዳማዊ ቀብር ላይ እንዲገኝ ተደረገ። በተለይ ሐምራዊ ባልተወለደው ልጇ ሁሉ ለምናዋለች። ሔዋን የበርካታ ታቦቶችን ስም በመጥራት ለምናዋለች። በመጨረሻ በሁላቻውም ጥረት ቀብር ላይ ለመቆም ወሰነ። ማለፊያ ቀዳማዊን ስታየው እንደ አራስ ነበር አደረጋት። "አንተ ነህ እናቴን የገደልካት። አንተ ወደዚህ ባትመጣ ኖሮ አትሞትም ነበር። አንተ የተረገምክ ሕይወታችንን ስቃይ አደረከው"እያለች ደረቷን ትደቃበት የነበረውን ድንጋይ ይዛ ወደ ቀዳማዊ እየገሰገሰች ስትመጣ ለቀስተኞች ይዘው አስቀሯት። ድግጋውንም ከእጇ በቀስታ በመንጠቅ ወረወሩት። ቀዳማዊ በነ ሔዋን ታጅቦ ዝም ብሎ ስርአተ ቀብሩን አስፈፀመ።

@amba88
@ken_leboch
1.3K viewsTesfa Desalegn, 04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 07:38:02 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፴፩~ ( 231)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
ይሄ ስራ በትክክል ተሰርቶ ለዚህ ደረጃ እንዲበቃ ጠዋትና ማታ ከእንቅልፍ ስአታቸው በመቀነስ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በአንድ አይነት ሀሳብ በመቀናጀት ተናበው ሲሰሩ ለነበሩ መሀንዲሶችና ግንበኞች የቀን ሰራተኞች ከፍ ያለ ምስጋናዬን ማቅረብ እፈልጋለሁ። እንዲሁም ይህን ትልቅ ፕሮጀክት ለማሰራት ሙሉ ገንዘቡንና ሀሳቡን ያወጣው ኢንጂነር ቀዳማዊ ታረቀኝ በእኔና በማህበረሰቡ ስም ከፍ ያለ ምስጋናዬን ማቅረብ እፈልጋለሁ። " ስራው በጣም የተለፋበትና የተደከመበት ስለመሆኑ የወጣበት ገንዘብና ጊዜ ብቻም ሳይሆን ስራው ራሱ ይመሰክራልና አቶ አቤል በእውነት ጥሩ ስራ ነው ለዚህ ትልቅ ምስጋና ሊቸረው ይገባልና ሞራል ስጡልኝ" በማለት መድረክ መሪው አቤልን ወደ ቦታው በጭብጨባ እንዲሸኙት አደረገ። "ግን እኮ እሱ የምንም ነገር እውቀት የለውም። እንዴት ይሄን ያህል ፕሮጀክት ሊያሰራ ይችላል?"አለ አንድ ወጣት ከስብሰባው መሀል ለሌላኛው ጓደኛው። "አዎ ግን እሱ እኮ ተቆጣጣሪ ነው። የስራውን ሂደት የሚከታተለው ግን ቀዳማዊ ነበር። ዋና መሀንዲሶች ነበሩ። እነሱ ናቸው ስራውን በደንብ ሲሰሩ የነበረው። ያው መልካሙ ከአሻንጉሊት ያልተናነሰ ስራ ነው ያለው"አለ "የሚገርም እኮ ነው ግን ቀዳማዊ እንደዚህ ይሆናል ብሎ የገመተ ማን ይኖራል?" "ምን ታደርገዋለህ? ፈጣሪ እድለኛ አድርጎ ሲፈጥርህ እኮ እጣህ እንዲህ በሀብት ላይ ሀብት በዝና ላይ ዝና መጨመር ነው"። መድረክ መሪው በመቀጠል በርካታ መልዕክቶችን ካስተላለፈ በኋላ የወረዳውን የስራ ሀላፊዎችንና ቀዳማዊን ወደ መድረክ በመጥራት የምርቃት ስነስርአቱ ተጀመረ።ሶስት ልጆች በእምነ በረድ የተፃፈውን ፅሁፍ አምጥተው ዳርና ዳር ከተሰራ ባላ አጋድመው ተከሉት። በትልቅ ወረቀት ተሸፍኖ ስለነበር ቀዳማዊ እንዲቀደው ተደረገ። ሰው ውስጡ ላይ ያለውን ፅሁፍ ለማየት በጣም ጓጉቷል። ቀዳማዊ በእርጋታ አዟዙሮ ከተመለከተ በኋላ በዳርና በዳር ወረቀቱን ቀዶ ፅሁፉን ለሕዝቡ ክፍት አደረገው "ደጃዝማች ታረቀኝ የሺዋስ መታሰቢያ ትምህርት ቤት"የሚል ፅሁፍ እምነበረዱ ላይ ተቀርጿል።
" ይህ ትምህርት ቤት በአባቴ ስም ያደረኩት። አባቴን እኔ ከማውቀው በላይ የዚህ ቀበሌ ነዋሪ በደንብ ያውቁታል። እኔ ልጁ ነኝ በቃ ስለ አባቴ እናንተ በነገራችሁኝ መሰረት ነው። የእናንተ አስታራቂ አስተማሪ እንደሆነ ብዙዎቻችሁ ነግራችሁኛል። ይህን ደግሞ በሚገባ ይዣለሁ። አንዳንድ ጊዜ ልጆች በወላጆቻቸው መጥፎ ሀጢያት እንደሚሰቃዩት ሁሉ እኔ ደግሞ በአባቴ ደግነት ምክንያት አንገቴን ቀና አድርጌ በእናንተ ፊት ቆሜያለሁ ሄጃለሁም። ከብዙ አመት በኋላ ስመጣ የአባቴን ደግነትና የአባቴን መልክ እኔ ፊት ላይ ለመስራት የጣራችሁትን ጥረት ያደረጋችሁትን ሙከራ በሚገባ አውቃለሁ። ስለዚህ ይህ ትምህርት በአባቴ ስም ተሰይሞ በአባቴ ግብር መልክ ትምትናን እውነተኛነትን ግብረገብነትን ፍቅርን መቻቻልን ልጆቻችሁ እንድንማር ተከፍቷል። የአባቶቻችንን መልካም ስራ ለማስቀጠል ደግሞ በትምህርት የታገዝን መሆን እንዳለብን ስላመንኩ ነው ትምህርት ቤቱን ለማሰራት የወሰንኩት። አባቴ ለእኔ ካደረገልኝ በላይ ለእናንተ ያደረገው ይበልጣልና ይሄው ይህ ትምህርት ቤትም በእኔ በልጁ ለእናንተ የተሰጠ ስጦታ ሆኗል። ልጆቻችሁን አስተምሩ። አለም በምሁራን እየተጥለቀለቀች የፈጠራ ባለሞያዎች እንደ ጉንዳን የሚፈለፈሉባት ሆናለች።ስለዚህ ወላጆች ልጆቻችሁን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ አታቅማሙ ልጅችም ወደ ትምህርት ቤት ላለመሄድ ማሰብ የለባችሁም። እናንተ ስትማሩ ቤተሰባችሁን አካባቢያችሁን ታስተምራላችሁ። እናንተም ተምራችሁ ራሳችሁንም ኑሯችሁንም ትለውጣላችሁ። እና በመጨረሻ አንድ ነገር ብዬ ልውረድ። እኔን ከማሳደግና ከማስተማር ጀምሮ ትልቅ መስዋዕትነት ለከፈሉት ለአቶ ሙሉሰውና ለወይዘሮ ሔዋን ምስጋናየን በእናንተ ፊት ልገልፅላቸው እወዳለሁ። እነሱ ባይኖሩ እኔ እዚህ ደረጃ የመድረሴ እውነት አጠራጣሪ ነበር። እግዚአብሔር አባቴን ወስዶ እናትም አባትም ሰጥትኛልና ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን። እንዲሁም ባለቤቴ ሐምራዊ ሱራፌል። ስራዎቼ ላይ የራሷንም ሀሳብ በመጨመር በማበረታታት ትደግፈኝ ነበር። ይህ ትምህርት ቤት እስኪጠናቀቅም ሙያዊ እርዳታ ከማድረግ ጀምሮ ብዙ ነገሮችን ከአጠገቤ ሆና ከውናልኛለችና አመስግኑልኝ። በመጨረሻ እዚህ ትምህርት ቤት ላይ ጉልበታችሁንና ጊዜያችሁን ለሰጣችሁ የዚህ ቀበሌ ወጣቶችና ጎልማሶች በጣም ላመሰግናችሁ እፈልጋለሁ። አቶ አቤልን የማመሰግንበት ቃል ስላጠረኝ ምንም ልለው አልችልም። ይሄን ፕሮጀክት ከጥንስሱ ጀምሮ እየተከታተለ ለዚህ አብቅቶታልና እባካችሁ አመስግኑልኝ"በማለት ምክር ሀሳቡንም ምስጋናውንም በማቅረብ ንግግሩን ጨርሶ ማይኩን ለመድረክ መሪው ሰጠ። "ኢንጂነር ቀዳማዊ በዚች ትንሽ የገጠር ቀበሌ ተፈጥሮ። የአባቱን ደግ ልብ በመውረስ እሱም የአባቱን ፈለግ በመከተል የዘላለም ቅርስ ተክሎልናል። ከእኛ የሚጠበቀው በእንክብካቤ መያዝና የተሰጠንን ስጦታ ተቀብለን መማር ነው። እንግዲህ ሁላችንም ከቀዳማዊ ሕይወት በመማር ራሳችንን ለትልቅ ደረጃ ማብቃት ይኖርብናል ማለት ነው። ስለሆነም ኢንጂነር ቀዳማዊን ልናመሰግነው ይገባል። ይህን የመሰለ ትምህርት ቤት ሰርት ስለሰጠን"ብሎ ቀዳማዊን በጭብጨባ ወደ ቦታው እንዲመለስ አድርጎ ንግግሩን ቀጠለ። "የኔ ፍቅር ጥሩ ንግግር ነበር ያደረከው"አለች ሐምራዊ "በእውነት?" "አዎ እያንዳንዷን ነገር በጥንቃቄ ለቅመህ ነው ያነሳኸው!"አለች ሐምራዊ ጉንጩን ሳም እያደረገች። "አመሰግናለሁ እናት!"
"በእርግጠኝነት ወይዘሮ አትጠገብ ይሄን ጉድ ስትሰማ በንዴትና በጭንቀት ትሞታለች"አለ አንደኛው ባላገር "እንዴት አትሞት ይሄን ሁሉ መአት ሲወርድባት"አለ ሌላኛው። "ቄሶች ጥሩ ስራ ለራስ ነው። ዋጋው ለእራስ እንጅ ለእግዜርም ለሌላኛው ሰውም አይደል። ደግ መሆን መጀመሪያ የሚጠቅመው ለራስ ነው። መጥፎነትም ሚጎዳው ራስን ነው። ብለው የሚያስተምሩን እኮ ለዚህ ነው። ወይዘሮ አትጠገብም ሴት ልጆቿን መርጣ ነው ይህን ልጅ ገና በህፃንኑቱ ምንም በማያውቀው ሀጢያት ከፋይ እንዲሆን የፈረዱበት ስለዚህ ብትሞትም ምንም አይደል። የእንጀራ እናት እራሱ እንደ እሷ ክፉ አይደለም። አይሆንም። ግን ይሄው በትልቅ ቁና ስራዋ ተሰፍሮላታል። ያመነቻቸው ሴት ልጆቿ ቁም ስቅሏን እያበሏት ነው።የምረቃ ስነስርዓቱ በልዩ ልዩ ግብዣ ደምቋል። ለትምህርት ቤቱ ማስመረቂያ ተብሎ ሁለት ሰንጋ በሬ ታርዷል። በርካታ ሰዎች ደግሞ ፍየል በግ አቅርበዋል። ልዩ የሆነ መሰናዶ ነበር። ትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥ የተሰራው ሰፊ ዳስ የምርቃት ዝግጅቱን ለመታደም መጡ ሰዎች ተሞልቷል። ድግሱ ለጉድ ነበር። መለስተኛ ሰርግ ነበር የሚመስለው። ሁሊም የየራሱን ወግ በጎንዮሽ እያወሩ ይጠጣሉ ይጫወታሉ ቢራም ወንይንም ጠጅም ጠላም ሁሉም በአይነት ነበር።

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 07:36:44 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፴~ ( 230)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
ወገሜት ቅቤው የወጣ ወተት አጓቱ በእሳት ተሙቆ የሚጠጣ ነው። ወተቱ ወደ አይብነት ተቀይሮ ውሃው ለሰውነት ተስማሚ በመሆኑ አመሻሽ ላይ ተሙቆ ይጠጣል። እነ ሔዋን ግን በጭራሽ አይሆንም ምንም ነገር አንጨምርም ብለው አሻፈረኝ አሉ። ቀዳማዊም "በቃ ተዋቸው ሁላችንም በሚገባ ጠግበናል። በዛ ላይ እርጎ ጠጥተናል"ብሎ የነ ሔዋንን ድምፅ አስተጋባ "ወገሜቱ እኮ ጥሩ ነው። ስለደከማችሁም ለእንቅልፍ ጥሩ መቅኔ ይሆናል። "አለ ሙሉቀን ቅር እያለው። "አይ ወንድሜ እባክህ አትቸገር!"አለ ቀዳማዊ "አይይ የአንተ ነገር ደግሞ የምን መቸገር አመጣህ! ለማንኛውም ጥሩ ይሁን እሺ እንግዲህ አይሆንም ካላችሁ በግድ አልግታችሁ ነገር"አለና ወደ ዳሳሽ ዘወር ብሎ "ውሃው ለብ ብሏል አይደል?"አዎ ሞቅ ብሏል ለሰስ ብሏል"አለች ዳሳሽ "በይ ይዘሽው ነይ!" ለሰስ ያለውን ውሃ በቆርቆሮው ይዛ መጣች ከጎኑ ትንሽ ቀዝቃዛ ውሃ በባልዲ አስጠጋችና ሰፋ ያለ የእግር መታጠቢያ ገበታ አቅርበው የሙሉሰውንና የሱራፌልን እግር ያዙ። ሱራፌልና ሙሉሰው "በጭራሽ አይሆንም ብለው አሻፈረኝ አሉ" "ነገር ግን ሙሉቀንና ዳሳሽም ኮስተር ብለው "አይሆንም። ለእኛ የምታስቡ ከሆነ በረከቱን አትንፈጉን እንግዳን እግሩን ማጠብ በረከት ነው"በማለት ሞገቷቸው። ሙሉሰውና ሱራፌል ወደ ቀዳማዊ አንድ ላይ ዞረው በአይናቸው እንዲያስቆምላቸው ቢጠይቁትም "ይሄ እንኳ ግዴታ ነው"በማለት ለነ ሙሉቀን ወግኖ ቆመ። የግድ ሲሆንባቸው እግራቸውን ሰጥተው ታጠቡ። አጥበው ሲጨርሱ የእግር አውራ ጣታቸውን ስመው ምርቃት ተቀበሉ። በተመሳሳይ ሔዋንና ፊደላዊትም ታጠቡ። በመጨረሻ ሐምራዊን ዳሳሽ ቀስስ አድርጋ እግሮቿን አጣጥባ እንዳይደነዝዛት በደንብ ማሳጅ አድርጋ ጨረሰች። ቀዳማዊ ግን አይሆንም በማለት ዳግማዊ እንዲያጥበው አደረገ። በየ ማረፊያቸው አረፍ ብለው ይጨዋወቱ ጀመር።"ፍፁም ትሑቶች ናቸው። እነዚህ የክርስቶስ አምሳያዎች ናቸው። እነሱ ቃሉን ሳያውቁት ያደርጉታል ይኖሩታል። እኛ ግን ምን እንደሚደረግ እናውቃለን ነገር ግን ምንም ነገር አናደርግም። ስለዚህ ትክክለኛ ሐይማኖተኞች እነሱ እንጅ እኛ አይደለንም"ሲል ሱራፌል ደመደመ።ፊደላዊትም በሀሳቡ ሙሉ በሙሉ እየተስማማች "ነገር ግን ጥሩ የሚሆኑት አዲስ እንግዳ ለሆነባቸው ሰው ነው። ሲበዛ ደግ እንደሆኑት ሁሉ ጨካኝም ናቸው። በርግጥ እነ ሙሉቀን ችክክለኛዎቹ የዋሆች ናቸው"ብለዋ እነ ሙሉቀን ወደ እነሱ ሲሄድ ንግግራቸውን አቁመው ሌላ ወሬ ያዙ።
ጠዋት ላይ ሁላቸውም አንድ ላይ ቀርበው በሞሰብ ቁርሳቸውን በልተው ልብሳቸውን ቀያይረው ወደ ራስ አምባ ለመሄድ ተነሱ። ሐምራዊ ዘግየት ብላ ስለነበር ከእንቅልፏ የነባችው ለብቻዋ ቁርስ ልትበላ ስትል ቀዳማዊ አብሯት ቀረበና እያጎረሰ በደንብ አበላት። "ቀዳማ እንደው ምን ቢሰራላት ጥሩ ነው። ምንም እኮ አልጠየቅናትም ትውደደው ትጥላው?"አለ ሙሉቀን ሐምራዊን በስስት እየተመለከተ። "ምንም ሙሌዋ ችግር የለውም።ቢኖር አሳውቅህ ነበር። ሐምራ ብዙ ይሄ ቢሆን ያ ቢሆን ብላ አታማርጥም እንዲሁ ያገኘችውን ትመገባለች። ከሚገርምህ እኔ ታዲያ አንዳንድ ጊዜ አንቺ ልጅ ያረገዝሺው ልጅ ነው? ወይስ ቦርጭ ነው? ብዬ እቀልዳት ነበር"አለ ቀዳማዊ። "ግን የምር ሐምራ ማርም ከፈለግሽ ንፁህ ማር አለ እሺ?"አለ ሙሉቀን ሐምራዊን በስስት እየተመለከተ" "እሺ ሙሉቀን እንደ እንግዳ ዝም አልልም ችግር የለውም የምፈልገውን እናገራለሁ"አለችና ሐምራዊ የእለቱን ልብሷን ለመልበስ ወደ ጓዳ ገባች።
****
"ስም ተመቃብር በላይ እንደ ሰው ቆሞ ሲሄድ እንዲህ ነውይ! አይ ደጃዝማች ታረቀኝ ምናለ ልጅህን ለአፍታ ቀና ብለህ ብታየው"እያሉ የመንደሩ ሰው የቀዳማዊን ደረጃ በመመልከት ይናገራሉ። "ሁላቸውም ግልብጥ ብለው አይደል እንዴ የመጡት። የሚስቱ እናትና አባት ራሱ መጥተውየለ እንዴ!"አለ ሌላኛው። "ወትሮስ ሊቀሩ ኖሯል። ሀተጋቡ በኋላ እኮ የእሷ ቤተሰብ የእሱ ቤተሰብ ሚባል ነገር የለም"አለ አንደኛው የመንደሩ ነዋሪ "እሱማ ልክ ነህ" "ስለዚህ በይህ የስራ ምርቃት ጊዜ ያልመጡ በያውም የቀዳማዊን አካባቢ ማየትና የማን ዘር ነው የሚለውን ማየት ይፈልጋሉ። የኸተማ ሰው እኮ እንደራሱ ሀፍታምና የደህና ሰው ልጅ ታልሆነ ሊያፋቱ ሁሉ ይችላሉ!!!" ያን እንኳ ስለ ቀዳማዊ በደንብ ያውቁ ይሆናል። ልጆቹ ተከጃጅለው ነው የሚሆን ብቻ እስቲ ቀድመን እንሂድና ቦታ እንያዝ። ለጉድ ነው ድግሱኮ"ተባብለው ወደራስ አምባ እየተጠራሩ ሄዱ።
*
"ያ መንገድ ዳር ያለው ወደ ገበያው ስንሄድ" "እሺ " "እሱ ጋር በቆርቆሮ ተከብቦ ሲሰራ የነበረው ሕንፃ የቀዳማዊ ነው አሉ።እሱን ለማስመረቅ ነው ሁላቸውም ግልብጥ ብለው የመጡት"አለች አድና ለማለፊያ እያስረዳች። "ያነ ሁሉ የእሱ የው?"አለች ማለፊያ በመደነቅ "አዎ እህቴ እኔም የሆኑ የቀን ሰራተኛ ሲሰሩ የነበሩ የባሌ ዘመዶች ሲናገሩ ነው የሰማሁት"አለች አድና። ማለፊ ዝም አለች። "ሚስቱ በጣም ነው የምታምረው ደግሞ እርጉዝ ናት!"አለችና አድና ንግግሯን ቀጠለች። ወይዘሮ አትጠገብ ጉልበቷ ከድቷት አቅም አንሷት አልጋ ላይ ሆና የሚያወሩትን ትሰማለች። ምንም እንኳ የአልጋ ቁራኛ ባትባልም ነገር ግን በእድሜ መግፋት የመጣ ችግር ገጥሟታል። ጉልበቷን ይይዛታል። የቀዳማዊ ሚስት ነፍሰጡር መሆኗን ሲያወሩ ስትሰማ እንባዋን መቆጣጠር ተሳናት። አለቀሰች "እንግዲህ ይቺ አሮጊት ደግሞ ጀመራት። ልታላዝንብን ነው"አለች ማለፊያ እናቷን ዞር ብላ በንቀት እየተመለከተች። "አሁን ይሄ ምኑ ነው የሚያስለቅስሽ?"አለች አድናም የማለፊያ ሀሳብ ላይ የራሷን ሀሳብ እየጨመረች። ወይዘሮ አትጠገብ ትንፋሿን ዋጥ አደረገችና ጋቢያዋን ለብሳ ታለቅስ ያዘች።
****
"የተከበሩ የሀመረ ኖህ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተከበራችሁ የሐመረ ኖኅ ከተማ ከንቲባ እንዲሁም የራስ አምባ ቀበሌ አስተዳዳሪና ስራ አስፈፃሚዎች እንዲሁም ኢንጂነር ቀዳማዊ ታረቀኝ እንኳን ደህና መጣችሁ"መድረክ አጋፋሪው ተናገረ። ታዳሚው አጨበጨበ። "እንግዲህ ላለፉት ሁለት አመታት ገደማ በጥንቃቄና በትልቅ ሀላፊነት ሲሰራ የነበረው ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይመረቃል። ነገር ግን እስኪ ከማስመረቃችን በፊት ስለ ፕሮጀክቱ ስራ ጠቅለል አድርጎ እንዲነግረን ይህንን ፕሮጀክት በበላይነት እያስተባበረ ሲያሰራ የነበረውን አቶ አቤልን ወደ መድረክ ልጋብዝ" አለና መልካሙን (አቤልን)ወደ መድረክ ጋብዞት ወረደ። " እሺ በብዙ እንግዶችና አዋቂዎች ፊት ሆኜ ስናገር ይህ የመጀመሪያዬ ነው"በማለት ሳቅ ብሎ ታዳሚውንም በሳቅ ፈገግ አሰኛቸው። "ያው ይሄን ለመስራት ስናቅድ ሀሳቡን በማበረታታትና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ከቦታ አመራረጥም ጋር አብረውን ሆነው ለደገፉን የሐመረ ኖህ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቢሻው ሳህሌን በእናንተ ና በእኔ ስም ላመሰግናቸው እፈልጋለሁ። በመቀጠል........

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 14:13:01 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፱~ ( 229)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
****
"ልጆች በሕይወታችሁ ልክ እንደ ንስር ከፍ ብላችሁ መብረር ከፈለጋችሁ በወጀብ የሚናጥ የንፋስ ሀይልን መቋቋም አለባችሁ። ዛሬ ከትምህርታችን በተለዬ መልኩ ስለ ሕይወት እነግራችኋለሁ። መቼም ከዚህ በፊት ሌሎች መምህራኖችም ነግረዋችሁ ይሆናል ስለ ቅዱስ ያሬድ ታሬክ ትሏ ሰባት ጊዜ ወድቃ በስምንተኛው ግንዱን ስትወጣ በተማረው መሠረት አሁን ሀይማኖታዊ የዝማሬ ዜማዎችን ደርሰውልናል። አለም ላይ ገናና እና ትልቅ አሻራ የሚያስቀምጡ ተፅእኖ ፈጣሪ ሰዎች እንደ ወርቅ ተፈትነው ከመሞት አምልጠው ወድቀው ተነስተው ነው ለጥሩ ደረጃ የሚበቁት። መቼም ይሄን ያለነገር አላነሳሁላችሁም።አሁን የምነግራችሁ ታሪክ እውነተኛ ነው። እኔም የማቀው ነው"አለና መምህር ደረጄ የቀዳማዊን ታሪክ አንድ በአንድ ነገራቸው። ተማሪዎች በተመስጦ አንገታቸውን ጠንዘል አድርገው ያድምጡታል። ከመሀል አንዳንድ ተማሪዎች ቀዳማዊ የደረሰበትን በእህቶቹ የደረሰበትን ስቃይ በእናቱ የተደረገበትን ግፍ ሲናገር ያለቅሱ ነበር። "በመጨረሻ ያ ሁሉ አልፎ አሁን በአለም ላይ በስራው አንቱታን ካተረፈና እውቅናን ከተቸረ ሎሳንጄለስ ኮንስትራክሽን ድርጅት ውስጥ በዋና መሀንዲስነት እየሰራ በሺህ የሚቆጠር የአሜሪካን ዶላር እየተከፈለው በደስታና በስኬት እየኖረ ነው" "መምህር በቅርቡ በቴሌቪዥን ቀርቦ መምህር ደረጄን አገናኙኝ ያለው ነው?" ብሎ አንዱ ተማሪ ንግግሩን አቋረጠው። "አዎ በትክክል አይተኸዋል። እሱ ነው ቀዳማዊ ማለት። ልጁ እንደስሙ ቀዳማዊ ነው። አሻራዎቹ በሙሉ በስኬት የተሞሉ በገዛ ቤተሰቦቹ እኖደ እሳት የተፈተነ ልጅ ነው። እኔን ያፈላለገኝ በወቅቱ ምንም አድርጌለት ሳይሆን ግን በሀሳብ እደግፈው ስለነበር ነው። የተወሰኑ ቀናትም ከእኛ ጋር ሆኖ ለመማር ሞክሮ ነበር ያው እንደነገርኳችሁ እናቱ የማስተማር አቅም ከሌላት በሚል ሀሳብ። እና ያቺን እንደ ትልቅ እገዛ ቆጥሯት ነው እኔን ለምስጋና ያፈላለገኝ። ስለዚህ እናንተም በየራሳችሁ እስካሁን ምን አይነት ሕይወት እንደገጠማችሁ እና እንዳልገጠማችሁ አላውቅም። ግን የምነግራችሁ ነገር ያሻውን በሕይወታችሁ መከራ ቢበዛ ተስፋ ቆርጣችሁ የሰይጣን መጫወቻ እንዳትሆኑ። የሕልማችሁ ተራራ ጫፍ ላይ እስክትደርሱ መታገል መፍጨርጨር አለባችሁ።" አለ መምህር ደረጄ እንባው በአይኑ እየሞላ። በዚህ ጊዜ ነበር የእሱ ክፍለ ጊዜ አልቆ የሌላኛው መምህር ክፍለጊዜ ደርሶ ሌላኛው መምህር በሩን ያንኳኳው። "በሉ የዛሬውን ክፍለጊዚያችን በሌላ ጊዜ እናካክሰዋለን መልካም ትምህርት ይሁንላችሁ "ብሎ ትቷቸው ወጣ። መምህር ደረጄ ለተማሪዎቹ ስለቀዳማዊ በመናገሩ ኩራት ተሰማው። ከቀዳማዊ የሕይወት ታሪክ ተምረው ራሳቸውን ለተለያዩ ስኬትች እንደሚበቁ አመነ። በሌላ በኩል ደግሞ ቀዳማዊ ያን ሁሉ ፈተና ተቋቁሞ ለዚህ ለሌሎች ሕይወት ማስተማሪያ በመሆኑ ፍፁም ደስታ ተሰማው።
***
ከአንድ አመት በኋላ
ራስ አምባ የገጠር ቀበሌ ከወትሮው ልዩ ሆና አሸብርቃለች። ኮረኮንች መንገዷ ሁሉ ተስተካክሏል። መልካሙ በቀዳማዊ የተጣለበትን ኃላፊነት ስለመወጣቱ ስራው ምስክር ሊሆነው ይሄው ሁሉንም ነገር አጠናቆ የእንግዶቱን መምጣት ብቻ ይጠባበቃል። በርካታ ገንዘብና ጉልበት የወጣበት ፕሮጀክት ስራው ተጠናቆ ለጎብኝዎቾና ለተጠቃሚዎች ክፍት ሊሆን በእንግዶች ተመርቆ በይፋ መከፈት ብቻ ይቀራል።ቀዳማዊ፣ሐምራዊ ወይዘሮ ሔዋንና አቶ ሙሉሰው ወይዘሮ ፊደላዊትና አቶ ሱራፌል ሐመረ ኖኅ የአየር ማረፊያ ወርደው በተዘጋጀላቸው መኪና ወደ ራስ አምባ ቀበሌ ያመሩ ጀመር። ቀዳማዊ ፈገግ ብሎ "ይችን ትመስላለች እንግዲህ የተወለድኩባት አካባቢ"አለ ለሁላቸውም እያሳዬ። መልካሙ (አቤል) ሳቅ አለና "ያው ተወለድክባት እንጅ ብዙም አታውቃትም"አለ "አይ ወንድሜ ከዛ በላይ እንዴት ልወቃት ለአስራ ሁለት አመት ነው ለአስራ ሶስት አመት ኖሬባታለሁ "አለና "ያው ኑሮ ከተባለ"አለ በለሆሳስ ማናቸውም ሳይሰሙት "አይ በጣም ገጠር ነች። እኔ እኖደውም አንተ ያጋነንክ መስሎኝ ነበር። በጣም ገጠር ነች ስትለን"አለች ሔዋን። " "አዎ እትዬ በጣም እንጅ አሁን ነው እንጅ መብራት ምናምን የተገጠመላት በእኛ ጊዜ መብራት አናውቅም። ስናጠና ራሱ በኩራዝ ነበር"አለ ቀዳማዊ። ሐምራዊ ትንሽ ደከም ብሏት ቀዳማዊን ተንተርሳ የሚያወሩትን በጥሞና ታዳምጥ ስለነበር " የትም ይሁን የትም ዋናው ራስን ለትልቅ ደረጃ ማብቃቱ ነው ትልቁ ቁምነገር"አለች የቀዳማዊን ስኬት በመተማመን ፊደላዊት የልጇን ሀሳብ በመደገፍ "ልክ ነሽ ሐምራ ግን ተመችቶሻል?"አለች "አዎ እማዬ እኔም ልጄም የቀዳማዊን ሰውነት ተንተርሰን ምን እንሆን ብለሽ"አለች። ሐምራዊ ልትወልድ በቢዛ የወር እድሜ የቀራት ነፍሰጡር ነች። ቀዳማዊ አብራው እንዳትመጣ ብዙ ጠይቋት ነበር። ብቻህን አልልክህም ብላ እምቢ ስላለችውና በዚህ ትልቅ ቀንህ ከጎንህ መሆን እፈልጋለሁ ብላው ነው አብራው ለመምጣት የቆረጠችው። ወይዘሮ ፊደላዊትና አቶ ሱራፌልም በዚህ ልዩ ቀንህ አብረንህ ልንሆን ይገባል"ብለው ወዲህም ሐምራዊን ለመንከባከብ አብረው ለመምጣት የወሰኑት። ሔዋንና ሙሉሰውም ልጃችንን ብቻውን አንልከውም በማለትና ያሰራውን ስራ በአይን ለመመልከት እዚሁ ራስ አምባ ድረስ ለመምጣት የወሰኑት። ቀዳማዊ በሁላቸውም አብረውት ስለመጡ በጣም ደስ ብሎታል። ቀዳማዊ ሐምራዊን በፍቅር እየተመለከተ ከቆዬ በኋላ "ልጃችን እንዴት ነው"በማለት በቀኝ እጁ ሆዷን እየዳበሰ ጠየቃት። "ልጃችን በጣም ደህና ነው የኔ ፍቅር"አለችና አንገቱ ስር ሳም አደረገችው።
ከራስ አምባ ቀበሌ ደርሰው ከወረዱ በኋላ ቀጥታ ወደ ቀይ አፈር የገጠር ቀበሌ አመሩ። ሙሉቀን ከዳስሽ ጋር ሆነው ቀኑን ሙሉ ቤቱን ሲያስተካክሉና ሲያስውቡ እንዲሁም የእንግዶቹን ማረፊያ መደቦች በፍራሽ ሲያነጥፉ ነበር።ቤቱ በጭራሽ የገጠር ቤት አይመስልም ነበር። ቀዳማዊ የቤት ማሰሪያ ብሎ የሰጠውን ሀምሳ ሺህ ብር በጥሩ ሁኔታ በድንጋይና በጭቃ እንዲሁም በቆርቆሮ ጣሪያ ሰፊ ደርብ ቤት ሰርተዋል። ለአቶ ሱራፌልና ፊደላዊት አንድ የጠፍር አልጋ ላይ አዘጋጁላቸው። ለወይዘሮ ሔዋንና ለአቶ ሙሉሰውም እንደዚሁ የጠፍር አልጋ። ለእነ ሐምራዊና ቀዳማዊ ደግሞ ሰፊ መደብ ላይ ፍራሽ አንጥፈው አሳረፏቸው። ገና ከመግባታቸው ሙሉቀንና ዳሳሽ የተሰራውን የምግብ አይነት ካልበላችሁ ብለው ሲሞግቷቸው ቆዩ። ምንም እንኳ የቻሉትን ቢበሉም ነገር ግን ለነ ሙሉቀን መብላታቸው አልታያቸውም ነበርና በሞቴ አፈር ስሆን እያሉ ከእርጎውም ከስጋውም ከሁሉም እያቀረቡ ይለምኗቸው ጀመር። ሔዋንና ሙሉሰው ተገርመው ዝም ብለው ይመለከቷቸዋል። ፊደላዊትና ሱራፌል በደስታ እየበሉ እየተጨዋወቱ ነው። በመጨረሻ ጠግበው ማዕዱ ተነሳ። "እስኪ ዳሳሼ ወገሜት አሙቂላቸው እሱን ትንሽ ቢጠጡ "አለ ሙሉቀን።
@amba88
@ken_leboch
1.0K viewsTesfa Desalegn, 11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 12:09:01 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፰~ ( 228)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
ሐምራዊ ገና በውል ከእንቅልፏ ሳትነቃ አይኖቿን በስሱ እንደገለጠች "ፍቅሬ ደወሉልኝ እኮ"አለ ቀዳማዊ "እነማን ናቸው እነሱ"ብላ ተገላብጣ ተኛች። "እነ መምህር ደረጄ ናቸዋ!" "መምህር ደረጄ ማነው?"ሐምራዊ አይኖቿን ከድና ከንፈሯን እያሸራመጠች ጠየቀችው። ሳቅ ብሎ ቀዳማዊ በዚህን ጊዜ ነበር ሐምራዊ በትክክል እንዳልነቃች ያወቀው።"አይይ ዝም ብዬ እለፈልፋለሁ አይደል"አለና የስፖርት ቱታውን ለብሶ የቤቱ ጊቢ ውስጥ ቀለል ያለ ስፖርት ይሰራ ጀመር።
***
የሌሊቱ ጨለማ በርኖሱን ከምድር አላነሳ ብሎት፣ አይኖቹ እንቅልፍ በአጠገባቸው ሳያልፍ ከቤቱ ጣራ ጋር እየተነጋገሩ ነው ያነጉት። ከአንድ ጊዜም ሁለት ጊዜ እየወጣ የሰማዩን ምስራቃዊ ክፍል ገላ ይመለከታል። ፅሐይ በስታው እንድትወጣ እየተመኘ የሰማይን ሽንቁር ገላ ከመቅፅበት ለመመልከት እየቋመጠ ቢቆይም ሰማዩ ግን በከዋክብቶቹ ደምቆ የፅሐይን መውጫ ስአት ያዘገየው ጀመር። ቢጨንቀው የክፍሉ በረንዳ ጋር ሆኖ ሰማዩ ላይ እንደ ዛር ቆሎ የተበተኑትን ከዋክብቶችን ይመለከትም ይቆጥርም ጀመር። ታሮስ የኮከቦችኖ ብዛት ለማወቅ አይደለም የመቁጠር ግቡ.. ምን አልባት አስር ኮከቦችን ሲቆጥር አስር የሌሊት ደቂቃዎች ቢያልፉልኝ ብሎ እንጅ። ሆዱ በፍርሀት ኮረኮንች እንደበዛበት መንገደኛ የሕዝብ አውቶብስ እየተንገጫገጨ ያስቸግረዋል። ልቡ ልትወጣ ቀዳዳ የምትፈልግ ይመስል በሁሉም የሰውነት ክፍሉ ትመታለች።
ፍቅር ውስጥ ስንሆን እያንዳንዷ ነገር ትነካናለች። ሆደ ቡቡ እንሆናለን። ፍቅራችንን ብቻ እያሰብን እንኖራለን።የአንድ ደቂቃ ርዝማኔ ያስለፈልፈናል ያፈላስፈናል።ለሁሉም ነገር እንቸኩላለን በፈጥነት እንዲሆንልንም እንመኛለን! ነገ ያጓጓናል። ሁሉም ነገር በበጎ ምልከታ ብቻ ይታየናል።
***
"ፍቅር በምሽት ውስጥ በጨለማ ውስጥ ለተቀመጠ ሰው የሚታይ የተስፋ ጭላንጭል ብርሃን ነው። ብዙዎች ስላፈቀሩ ብቻ ነገን መኖር ይጓጓሉ። መፈቃቀር የሁለት ጥንዶች የልብ ቋንቋ አንድነት ምስጢር ሲሆን! ማፍቀር ደግሞ የተፈጥሮ እውነትና የልብ ቅፅበታዊ ድርጊት የሚፈጥረው ደስ የሚል ስሜት ነው። አሁን በፍቅር ከትላንቱ የተሻለ ዛሬን ከዛሬ የተሻለን ነገ መኖር ያስችላል። በፍቅር ውስጥ ሙሉነት አለ።"አለ ኪሩቤል የታሮስን የሰርግ ሱፍ ገዝተው ሻይ ቡና እያሉ ተቀምጠው ሳለ። "ከሚገርምህ አንተ ብቻ አይደለህም ከምታፈቅራት ሴት ውጪ ሌላ አለምን ማየት የማትፈልገው። ሁሉም የራሱ የፍቅር ጠባሳ አለው። ተመልከት ይሄ ሁሉ ተጓዥ መንገደኛ የራሱ የሆነ ሕመም ቁስል የፍቅር ችግር ይኖርበታል። አንተ ከጤፍ እህል ብዛት ነጥረህ ወጥተህ የምታፈቅራትን ሴት ልታገባ ነው። በዚህ ልትደሰት እንጅ ልታዝን አይገባም። በምንም ታዕምር አንተን ቀዳማዊን ለመርሳት ብቻ የምታገባህ መስሎህ ከተሰማህ ችግሩ የአንተ እንጅ የእሷ አይደለም!! አምናለሁ ቀዳማዊን ትወደዋለች ግን ያለፈ ታሪክ ነው። አሁን ሁለታችሁም ሌላ አለም የራሳችሁን ድንቅ የፍቅር ፕላኔት ልትፈጥሩ ነው። ከዚህ በላይ ደግሞ ደስታ የለም"ብሎ ትከሻውን መታ መታ አደረገው። ታሮስ በጥሞና ሲያዳምጠው ከቆዬ በኋላ "አመሰግናለሁ ኪሩዬ ከዚህ በላይ ምን ልልህ እንደምችል አላውቅም። ሁሌም ከጎኔ ሆነህ የሚበጀኝን ሀሳብ ትሰጠኛለህ። ብቻየን እንዳልሆን አድርገኸኛልና አመሰግናለሁ!!!" በእኔና ባንተ መሀል ያለምስጋና የሚሰበር ድልድይ የለም። እኔና አንተ በመነጋገር እና የግል ችግሮቻችን ላይ በጋራ እልባት መስጠት እንጅ መመሰጋገን የለብንም። ካልሆነማ ምኑን ጓደኛሞች ሆነነው?"ብሎ በጥያቄ መልስ ሀሳቡን ገለፀለት።
**
"ሁሌም ካፋችን ጠፍተህ አታውቅም! በተለይ ደሬ እንደው የት ሀገር ሆኖ ይሆን እያለ ያብሰለስል ነበር"አለች ትሕትና "አውቃለሁ እትዮ መቼም ከውስጣችሁ እንደማልወጣ። በዛ situation (ሁኔታ) ውስጥ ሆኜ ራሱ ሁሌም ነበር የማስበው። በእውነት እናንተን ለማግኘት ያላደረኩት ጥረት አልነበረም። አሁን ራሱ በቃ ግራ ግብት ሲለኝ ነው ባለቤቴ በቴሌቭዥን ና በሬዲዮ እናፈላልጋቸው ስትለኝ ሀሳቧን የተቀበልኩት" "በጣም ጥሩ ነው። ማግባትህነም በዛው ቃለመጠይቅ ስታደርግ ሰማን። በጣም ነው ደስ ያለን ልጄ እንኳን ደስ አለህ!"አለች ትሕትና ፍፁም ትሕትና በተሞላው አነጋገር!!! "አመሰግናለሁ እትዬ ቀደም ብለን ብንገናኝ ኖሮ የደስታዬ ተካፋይ ትሆኑ ነበር። ግን እግዚአብሔር አልፈቀደም" "አዎ ሁሉም ነገር የሚሆነው እሱ ሲፈቅድ ብቻ ነው። ስለዚህ ከዚህ በኋላ ብዙ የምንካፈላቸው የደስታ ጊዚያቶች አሉን"አለች ትሕትና "እውነት ነው እሱስ ገና መች ጀመርነው። እኖደው እዚህም ብትገኙልኝ ብዬ ነው እንጅ። የት ነው የምትኖሩት አሁን?"" ኮምቦልቻ ነን ወደዚህ መጥተናል!" በጣም ጥሩ በቃ መጥቼ እጠይቃችኋለሁ!! እስከዛው ግን እንደዋወላለን"አለ ቀዳማዊ ተባብለው ጨዋታቸውን ጨርሰው ሲዞር ሐምራዊ ከጀርባው ቀስ ብላ እየተራመደች ልታስደነግጠው ስትል አያት። "ኤጭ ሳታስበው ላቅፍህ ነበር ቀረብህ" "አይ አይቀርብኝም እርግቤ"አለና ግራ እጇን ሳብ አድርጎ ስሞ ጭኑ ላይ አስቀመጣት።"አሁን ስታወራ እየሰማውህ ነበር። በእንቅልፍ ልቤ ቢሆንም ቅድምም ሰምቼሀለሁ። በጣም ነው ደስ ያለኝ የኔ ፍቅር! አሁን ሁሉንም አግኝተሀል አሳክተሀል!!! ስለዚህ ከዚህ በኋላ ትንሽ አትጨናነቅብኝ"አለችና አቅፋ ወደ አንገቷ ሸጎጠችው። አንገቷን ሳም አደረገና "በትክክል ሁሉንም አግኝቻለሁ ግን አንድ ነገር ብቻ ነው የቀረኝ። ግን ምን እንደቀረኝ እንዳትጠይቂኝ!"አለ ቀዳማዊ "እንዴ የኔ ፍቅር ካልፈለክማ ለምን እጠይቅሀለሁ። ነገር ግን ብትነግረኝ ደስ ይለኛል!"አለች ሐምራዊ እየተቅለሰለሰች "ፍቅር ሲሳካ እነግርሻለሁ"
***
"በጣም ልዩ ሁነሻል የኔ ወርቅ!!"አለች ትዮቢስታ ደሐብን ትኩር ብላ ስትመለከታት ከቆየች በኋላ። ደሐብ ፈገግ አለችና "አዬ እማዬ ልጅ ሁሌም ለእናትና አባቱ በጣም ቆንጆና ልዩ ነው። ግን የትንንንሾች ውበት ከቤተሰብ አይን አልፎ በሌሎች አይንም ያርፋል!" አለች ደሐብ በመስታውት ራሷን እየተመለከተች። "እኔ ልጄ ስለሆንሽ አይደለም ቆንጆ ነሽ ያልኩሽ ቆንጆ ስለሆንሽ ነው። ውበትሽንና ቁንጅናሽን ደግሞ ያየ ሁሉ የሚመሰክረው ነገር ነው" አለች ትዮቢስታ ከጀርባዋ በኩል ያለውን ቀሚሷን እያስተካከለችላት። ደሐብ ምንም አልመለሰችላትም። በዝምታ ውስጥ ሆና ራሷን ታስውብ ጀመር። ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ጓደኞቿ፣ ሚዜዎቿ እና ሜካፕ የሚሰሩት ልጆች አንድ ላይ መጡ። ወደ ደሐብ ክፍል ገቡና ሜካፕ ሰሪዎቹ ተከፋፈሏት። አንደኛዋ የእግር ጥፍሯን ሌላኛዋ የእጇን ጥፍር ሌላኛዋ ደግሞ ፊቷን ተከፋፍለው ያስውቧት ጀመር።
'የፉክክር ሰርግ አስመሰለው' ተብሎ እስኪታማ ድረስ እዮሲያስ ሰርጉን ከሰርግነት ደረጃ አስወጣው። በጣም ቅንጦት የተቀላቀለበት ድግስ ነበር። ሙሽራዋም ውዱን የሙሽራ ቬሎ ለብሳለች። እዮሲያስና ትዮቢስታ ለአንድ ልጃቸው ያላቸውን ጉልበትና ገንዘብ ሁሉ አውጥተው ሞሽረዋል።

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ