Get Mystery Box with random crypto!

ቅን ልቦች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ken_leboch — ቅን ልቦች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ken_leboch — ቅን ልቦች
የሰርጥ አድራሻ: @ken_leboch
ምድቦች: ቴሌግራም , ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 5.54K
የሰርጥ መግለጫ

ደግነት ለራስ ነው !!
❣❣ በፍቅር ከሆነ እንስማማለን❣❣
ለ አስተያየት @Tesfish2

@EgerKwasMeme
@YehabeshaTiktok
@ye90slijochfans
▶ YouTube 🔥
https://youtu.be/619clN81mFs

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-19 14:02:37 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፯~ ( 227)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
"ጥሩ እንግዲህ አንተን የመሰለ የተማረ ኃይል ሀገራችን አብቅታለችና ባንተ ትጠቀማለች ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ"ብሎ ቀጥሎ ሌሎች ጥያቄዎችን እያነሳ እያለ። ወይዘሮ ትሕትና የምታየውን ነገር ማመን ከበዳት "እውነት ያ ትንሽዬ ልጅ ቀዳማዊ ነው?"አይኖቿን ጨፈን ከደን አደረገችውና "ዮአኪን ሂድና አባትህን ጥራው"ብላ ላከችው "አባዬ እማዬ እየጠራችህ ነው!" "እሺ ትንሽ ቆይቼ እመጣለሁ የሆነች ነገር እየሰራሁ ነው"አለ ደረጄ የማንበቢያ ክፍሉ ውስጥ ሆኖ። ዮአኪን አባቱ ያለውን ሳይጨምር ሳይቀንስ ለትሕትና ተናገረ። እምር ብላ ተነሳችና ደረጄ ጋር ሄደች። "ደሬ " ብላ ገና ሳትጨርስ "እራት ደርሶ ነው ትሑቴ? እመጣለሁ ትንሽ ጠብቂኝ" "ኧረ አይደለም እ ቀ ቀ ቀዳማዊ በቴለቪዥን ቀርቧል!" ትሕትና ተንተባተበች። "ቀዳማዊ ቀዳማዊ? ቀዳማዊ የእኛ?" "አዎ" ተስፈንጥሮ ተነሳና ሳሎኑ ጋር ደረሰ። ነገር ግን የቀዳማዊ ቃለመጠይቅ አልቆ ስለነበር። የመጨረሻ የጋዜጠኛውን ንግግር ነበር የሰማው "ክቡራን እንግዶቻችን ከኢንጂነር ቀዳማዊ ጋር የነበረን ቆይታ ይሄን ይመስል ነበር። በርግጥ የዛሬ ቆይታችን አንድ የቀደመ መምህሩን ለማግኘት በጠየቀን መሠረት በዛው አንዳንድ ጥያቄዎችን ብጠይቀው ጥሩ ነው ብዬ ስላሰብኩ እንጅ ተፈላልገን በደንብ ተዘጋጅተን አይደለም የተገናኘነው።በሌላ ጊዜ በሰፊ ዝግጅት የምንገናኝ ይሆናል። መምህር ደረጄንና ወይዘሮ ትሕትናን የምታውቁ ወይም ራሳችሁ ካላችሁ ከታች በሚታየው ስልክ ለኢንጂነር ቀዳማዊ ልትደውሉለት ትችላላችሁ"በማለት ከቀዳማዊ ጋር ሰላምታ ተለዋውጠው ተሰነባበቱ።
"ወይ ቀዳማዊ! እንዲህ ትልቅ ሰው ሆነ።በእውነት ፈጣሪ ክበር ተመስገን።"አለ አቶ ደረጄ እጆቹን ወደ ላይ ዘርግቶ። "ቁምነገረኛው የኔ ጌታ። አሁን ያቺንም እንደ ትልቅ እርዳታ ቆጥሯት እኮ ነው!"አለ ደረጄ ወደ ትሕትና ዘወር ብሎ "በጣም እንጅ በጊዜው ልጅ ስለነበር ሁሉም ጭንቅላቱ ላይ ይቀመጣል። ባለፈው ሲናገር አልሰማኸውም? "አለች የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናን ከሀገሪቱ ከፍተኛ ውጤት አምጥቶ በቴለቪዥን ቀርቦ ቃለ መጠይቁን እያስታወሰችው። "አዎ ልክ ነሽ ከአስር አመት አመት በፊት ነው አይደል?"አለ ደረጄ የአመቱን ርዝመት ለማስታወስ እየሞከረ "አዎ ልክ ነህ አስር አመት መስከረም አለፈው!"አለች ትሕትና "ይሄን ሁሉ አመት ውጪ ነበር ማለት ነው?"አለ ደረጄ "ይመስለኛል። ግን በቅርቡ ነው የተሞሸረው ለሰርጉ መጥቶ ይሁን አላውቅም!!" "እውነትሽን ነው አገባ?" "አዎ አንተን እያስጠራውህ እያለ ጋዜጠኛው ስለ ትዳር እየጠየቀው ነበር!" "ወይ ፈጣሪ። በእውነት ይሄን ስላሰማኸኝ በጣም ደስ ብሎኛል አምላኬ" ብሎ ደረጄ "በቃ እንደውልለት"አለ "አሁንማ መሽቷል ነገ ባይሆን እንደውልለታለን" "ኧረ ችግር የለም። አሁን በዚህ ስዐት ምሽት አይባልም እኮ"ብሎ ደረጄ የቀዳማዊ ስልክ ነው ተብሎ የተለጠፈውን ስልክ ቁጥር ስልኩ ላይ ፅፎ ደወለ
****
ሐምራዊ የቀዳማዊ ጭን ላይ በጀርባዋ ተኝታ እንቅልፍ ወስዷታል። በግንባሯ የወረዱትን ፀጉሮቿን እያስተካከለ የተከደኑ አይኖቿን እያዬ በስስት ይመለከታታል። ሐምራዊ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ነው የወሰዳት። "አንዱን ከአንዱ በሀሳብ እያላተመ ስልኩ ጠራ።ቀዳማዊ ስልኩን ለማንሳት ቢፈልግም ሐምራዊ ከኤንቅልፏ ልትነቃ ትችላለች ብሎ ስላሰበ ስልኩን ማንሳቱን ተወው። ሁለት ጊዜ ያህል ሲደወልለት ሐምራዊን አቅፎ አነሳትና መኝታ ክፍል አስገብቶ በስርዓት አስተኝቷት አለባብሷት ወደ ሳሎን መጥቶ ስልኩን አንስቶ ማን እኖደደወለለት ሲመለከት አዲስ ቁጥር ነው። "ምን አልባት መምህር ደረጄን የሚያውቅ ሰው ሊሆን ይችላል።"አለና መልሶ ደወለ። "አላልኩህም መሽቷል። ነገ እንደውልለት ስልህ አትሰማም "አለች ትሕትና "ምን ላጅርግ ብለሽ ነው አላስችል ብሎኝ አየሰደል..."በመሀል ስልኩ ጠራ "ይሄው ደወለ"አለ ደረጄ። "ሔሎ ጤና ይስጥልኝ" "አብሮ ይስጥልን"የሚል ምላሽ ሰጠው መምህር ደረጄ "ምልክት አግኝቼ ነበር"አለ ቀዳማዊ "ልጄ እኔ ደረጄ ነኝ!" "ም ም ም ምን?ቀዳማዊ አፉ ተያያዘ "አዎ መምህር ደረጄ ነኝ!! አሁን ቴሌቪዥን ላይ ስልክህን ወስጄ ነው"አለ "አ አዎ አዎ ጋሼ " ቀዳማዊ የሚለው ሁሉ ጠፋበት።"እንዴት ነህ" " እኔ በጣም ደህና ነኝ። ሁሌም ነው የማስባችሁ" "እናውቃለን ልጄ። እኛም እናስብህ ነበር። ወደ ዩኒቨርሲቲ ልትሄድ ስትል ቴሌቪዥን ላይ ነበር ያየንህ። ያው ወደ ውጪ ልትሄድ እንደምትችል ጠቆም ስላደረክ ሄደሀል ብለን አሰብን" "አዎ እዛው ነው ተምሬ የጨረስኩት ስራም እዛው ነው የጀመርኩት። ገና የዛሬ አመት ነው የመጣሁት" "ጥሩ ልጄ እንኳን ደስ አለህ! እዚህ ደረጃ እንደምትደርስ በአንተ ሙሉ እምነት ነበረን!!" "አመሰግናለሁ ጋሼ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እዚህ ደርሻለሁ! አሁን ተመስገን ነው ያለኝ ብዙ ነው" አለ ቀዳማዊ "ጥሩ ልጄ እንግዲህ በድምፅ ከተገናኘን በአካል ደግሞ ፈጣሪ ሲፈቅድ እንገናኛለን።አሁን በዚህ ምሽት የደወልኩት እስኪ ነጋ ስላላስቻለኝ ነው"አለ ደረጄ "እሺ ጋሼ ስላገኘኋችሁ ደስ ብሎኛል ነገ ራሴ እደውላለሁ። እትዬ ትሕትናንም ማግኘት እፈልጋለሁ!!" አለ ቀዳማዊ "እሺ ልጄ ታገኛታለህ ደህና እደርልኝ" "አሜን ደህና እደርልኝ ጋሼ!!!!
"አንቺን ማውራት ፈልጎ ነበር ።ግን የተኛሽ ስለሐሰለው ነገ ላውራት አለ። ስርአቱ አሁንም እንደድሮው ነው። ሲያወራኝ ድምፁ ውስጥ መቅለስለሱ ቀና ብሎ አለማየቱ ይታየኛል። እትዬ አባባሉ ላይም የድሮው ራሱ ትዝ ይለኛል።አንዳንዴ ሰዎች ቦታ ሲቀይሩ አብረው የሚቀየሩት ነገር አለ። ነገር ግን ቦታ አይደለም ሰውን የሚቀይረው።ራሱ ሰውየው ለመቀየር ካልፈለገ በቀር" አለ ደረጄ። ትሕትና ስታዳምጠው ከቆየች በኋላ "ቀዳማዊ ምይ ደርሶበት እዚህ እንደደረሰ ያውቀዋል። የስዎችን ደግነትም የሰውን ክፋትም ጠንቅቆ ያውቃል። በእርግጠኝነት እስካሁን እናቱን እና እህቶቹን እንደማያያግራቸውና ይቅር እንደማይላቸው"አለች "አዎ ልክ ነሽ በጭራሽ አያገኛቸውም ጠባሳዎቹ ናቸው። ይሄን ስኬቱን ሲያዩ እንደው የእግር እሳት ነው የሚሆንባቸ ግን እስካሁን ያልተረዳኝ ነገር ትሑቴ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ? ያን ያህል በደል እንዴት አስችሏት ልጇ ላይ ታደርለች?ልጁ ህፃን ነው። በዛ ላይብቸኛ ወንድ ልጅ። አንድን ኤኮ እንዲህ ማድረግ ከባድ ነው። ደግሞ ጉዳዩ በወለዱት ላይ ሲሆን ያስጨኝቃል" ብለው እያወሩ እራታቸውን ይበሉ ጀመር።
ቀዳማዊ የሚይዘው የሚጨብጠው አጣ። ዜናውን ለሐምራዊ እንዳይነግራት ድብን ያለ እንቅልፍ ይዟታል።"ይሄ ሁሉ ሀሳብ የአንቺ ስለሆነ አድናቆት ይገባሻል የኔ ፍቅር"አለና ግንባሯን ሳም አደረጋት። "ተመስገን አምላኬ አሁን የምፈልጋቸውን ሰዎች አግኝቻለሁ። ልመናዬንም ሰምተህ ሰጥተኸኛልና ክብር ተመስገን ፈጣሪዬ ከዚህ በኋላ እድሜና ጤና ብቻ ስጠኝ። እሱም አንተን እያመሰገንኩ የምኖርበት ነው።"አለና አባታችን ሆይን ፀልዮ ተኛ።

@amba88
@ken_leboch
1.0K viewsTesfa Desalegn, 11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 13:51:13 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፮~ ( 226)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
ደሐብ ከታሮስ ጋር በሰከነ መንፈስ ስለ ሁሉም ነገር በግልፅ ካወሩ በኋላ ለሰርጋቸው ቤተሰቦቻቸው እንዲዘጋጁ ለመናገር ተስማሙ። "እኔ አንተን የማገባህ ቀዳማዊን ለመርሻነት አይደለም። የማገባህ ቆሜ እንዳልቀር ፈርቼ አይደለም። የማገባህ እናትና አባቴ ማግባት ይኖርብሻል ብለው ስላስገደዱኝ አይደለም። የማገባህ የእኔን እውነተኛ ፍቅር በአንተ ልብ ውስጥ ስላገኘሁት ነው። ፍቅር በሰጡት ልክ መስጠት እንዳልሆነ አሳይተኸኛል። አንተ ስትሰጠኝ የነበረው በሰጠውህ ልክ አልነበረም። እንደው በተቃራኒው ነው። በራኩህ ቁጥር እየቀረብክ በጠላውህ ጊዜም እየወደድክ ዝም ባልኩህ ጊዜም እያወራህ ፍቅርህን አሳይተኸኛል።ለእኔ የሚያስፈልገኝ እሱ ነው። አንተ የእኔ እውነተኛ አፍቃሪ ነህ። እሱን ደግሞ ድርጊቶችህ ሁኔታዎችህ ነግረውኛል። ስለዚህ አንተ የልጆቼም አባት የእኔም ባልና ጠባቂ መሆን ስለምትችል ከአንተ ጋር በፍቅር ኑሮ መመስረት እፈልጋለሁ"አለች ደሐብ የታሮስን የግራ እጅ መዳፍን እያሻሸች። ታሮስ ስቦ ወደ እቅፉ አስጠጋትና "በቅርቡ የራሳችንን ቤተሰብ እንመሰርታለን"አለና ግንባሯን ሳማት። ደሐብ ልስልስ ኩርምት ብላ ዝናብ መትቷት ከብርድ ለማምለጥ ዋሻ ውስጥ እንደ ተሸጎጠች ፍየል ደረቱ ውስጥ ሰርስር አድርጋ ተሸጎጠች።
በደሐብ መወላወል ምክንያት የተቆረጠው ቀን ከአንድ ጊዜም ሁለቴ ስለተቀየረ የታሮስ ቤተሰቦች ትንሽ ቅር ተሰኝተው ነበር። "ልጃችንን እንዳትጎዳብን እንጅ ብለው እስከመጨነቅም ደርሰው ነበር። በዚህም ምክንያት ሽማግሌዎቹን ደግመው በመላክ ያለውን እውነት እንዲያጣሩ ቢልኩም አጥጋቢ መልስ አላገኙም ነበር። ታዲያ አሁን በድጋሚ ያለውን ነገር ሲነግራቸው እንደማቅማማት ቢሉም ደግሞ የእሱን ደስታ ማክበር ስለነበረባቸው ተቀበሉትና ለመጨረሻ ጊዜ ሽማግሌ ልከው ቀኑ ተቆረጠ። ይህም ቀን ከሁለት ወር የማይበልጥ ርዝማኔ ያለው ነበር።
****
የድንጉዛዋ እመቤት የፍቅር መለይካዋ የምድር ገነቷ አርባ ምንጭ የፍቅሯን ሞሰብ ለመክፈት ለመጡ ሁሉ በደስታ ከፍታ ማዕዷን በበረከት የምታቋድስ ብዙ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ ለመጣ እንግዳዋ ቤቷን ክፍታ አድርጋ እጆቿን ዘርግታ ከምድር እስከ አርያም በሚልቅ ባልተበረዘና ከልብ በመነጨ ንፁህ ፈገግታዋ "ሀሹ ሳሮ ይዴታ"ብላ ተቀብላለች። ዛሬም ፍልቅልቋን ሐምራዊና ገራገሩን ቀዳማዊ ከማይነጥፈው ማድጋዋ ፍቅሯን በአንደበቷ ሞልታ ተቀብላቸዋለች አርባምንጭ እንደደረሱ ቀጥታ አዲስአበባ ሆነው ከያዙት ሆቴል አረፉ። በሁለት ሀይቆች ተከባ የፅሀይን መዳረሻ ከሰማይ አርቃ ለምድር ያቀረበችው ሞቃታማዋ አርባምንጭ በብዙ የተፈጥሮ መስህቦች የተሰበዘች ሰበዝ ሆና ሙቀቷን እስከ ማስረሳት ታደርሳለች
በጥቅጥቅ ደኖቹ መሀል ከፈለቁት ምንጮች ስር እንደ አሳ ሁሪት እየተስለከለኩ ይዋኛሉ። የዛፉቹ ኮሽታና ቅጠሎቹ ከዛፉ ሲወርዱ የሚያሰሙት የለሆሳስ ድምፅ ከጫካ ወቹ የወፎች ጫጫታ ተዳሞሮ ነፍስን የገነት በር እያደረሰ ይመልሳል። ሊያስጎበኟቸው የመጡ ሁለት የሰማይ ስባሪ የሚያህሉ ወጥማሻ ባለ ፈርጣማ ክንዶች ዙሪያ ገባውን እያማተሩ ከምንጮቹ ዳር ካለ አንድ ዛፍ ስር ተቀምጠዋል። ሙሽሮቹ ምንጩ ውስጥ እንደ ህፃን ልጅ እየተደፋፈቁ እስኪበቃቸው ከዋኙ በኋላ ራሳቸውን አደራርቀው ልብሳቸውን ለባብሰው ወደ ሌላ የሚጎብኝ ስፍራ ጉዟቸውን ጀመሩ። በያገኙበት ስፍራ ሁሉ ፎቷቸውን እየተነሱ የእግዜር ድድልድይን የነጭሳር ብሔራዊ ፓርንክን የአዞ እርባታን በየተራ ሁሉንም አንድ በአንድ ሲጎበኙ ቆይተው ተመለሱ። አስጎብኝተው ለጠበቋቸው ሰዎች ከጉርሻ ጋር ጨምረው አመስገነዋቸው ተለያዩ። የአርባምንጭ ቆይታቸውን አጠናቀው ሐዋሳ ደግሞ ድንቅ ጊዚያትን አሳልፈው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ።

**
ታሮስና ደሐብም ለመጋባት ሽር ጉድ እያሉ ነው። አቶ እዮሲያስ ሰርጉን የተለዬ ለማድረግና ከማንም የተሻለ ሰርግ እንዲሆን እየጣረ ነው። በርካታ የሚያውቁት ሰዎችና የስራ ሸሪኮቹ ብዙ አውራጅ ይዘው ቀርበዋል። በርካታ ሰንጋ ለእርድ ቀርቧል። አቶ እዮሲያስ ደደሐብ በምንም ታዕምር ያነሰች፣ የተጣለች፣ የተገፋች፣ እንዳይመስላት በበርካታ መንገዶች ሊሸፋፍን ይጥራል። የጥሪ ካርድ ለሁሉም ተብትኗል ከሚታወቁ ሰዎች ካልተጠሩት መካከል አቶ ሙሉሰው አንዱ ነው። ይህን ያወቀው ሙሉሰው ሳቅ አለና "ከሚገርምሽ እኔ ቢጠራኝም አልሄድም ነበር"አለ " እንዴት ጠርተኸው ሳይመጣ የቀረ ሰው ለልጁ ሰርግ ይጠራኛል ብለህ ታስባለህ"አለች ሔዋን "ኧረ በእውነት መጥራትስ ይጠራኛል ብዬ ገምቼ ነበር። ግን ይሄን ያህል ይወርዳል ብዬ አላሰብኩም ነበር!"አለ ሙሉሰው
****
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የምሽት ሁለት ስአቱን ዜና ጨርሶ በርካታ ማስታወቂያዎችን እየተመለከቱ እያለ የሆነ ቃለመጠይቅ ሲመጣ ዮአኪን አሳለፈው "ተወው እንጅ መልሰው እስኪ ቃለመጠይቁ ምንድን ነው እናዳምጠው "አለች ትሕትና "እስኪ ወቅቱን ንገረን መቼ ነው?" ጋዜጠኛው ይጠይቃል "ልጅ ነበርኩ የስምንተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነው ተቀይሮ ሌላ ቦታ የሄደው። በእኔ ምክንያት ነው ስራ የለቀቀው!!" አለ ቀዳማዊ "እስኪ ማስተላለፍ የምትፈልገውን መልዕክት ተናገር"ብሎ ጋዜጠኛው ለቀዳማዊ እድል ሰጠው። "መምህር ደረጄ ይባላል አስተማሪዬ ነበር ባለቤቱ ወይዘሮ ትሕትና ትባላለች። እኔ ቀዳማዊ ታረቀኝ እባላለሁ ይህን ቃለመጠይቅ ይምታዩ ሁሉ እነ መምህር ደረጄን አገኝ ዘንድ እርዱኝ! ከዚህ ቀጥሎ በሚገኘው ስልክ ብትደውሉ ታገኙናላችሁ"አለ ቀዳማዊ እንደ ሕንዶች ሰላምታ እጆቹን አገናኝቶ ወደ ግንባሩ አስጠጋ። እንግዲህ ይህን መልዕክት የምታዩ ሁሉ እንድትተባበሩት እኔ በአክብሮት እጠይቃለሁ። እኔና አንተ በዚሁ ጨዋታችንን እንቀጥልና "በቅርቡ ነው ትዳር የመሠረትከው ትዳር እንዴት ነው?" "ትዳር በጣም ጥሩ ነገር ነው። በተለይ ሁለት የሚፋቀሩ ሰዎች ትዳር ሲመሰርቱ ጎጆ ሲቀልሱ ይበልጡን ከወትሮው በበለጠ ይፋቀራሉ ይግባባሉ።ስለዚህ በእኔ እይታ ትዳር የላላ የፍቅር ገመድን የሚያጠብቅ ሲባጎ ነው ማለት ነው። እኔና ሐምራ አሁን ገና ትዳርን እየጀመርን ነው። የሁለታችንም የትዳር ሞዴሎች አሉን እነሱን እያየን ስለሆነ እኛም ሞዴሎች የማንሆንበት ምንም ምክንያት አይኖርም።" ጥሩ አሜሪካን ሀገር የምትሰራበት የኮንስትራክሽን ድርጅትም እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ቅርንጫፍ ከፍቷል። የዚህ ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅና ዋና መሀንዲስ አንተ እንደሆንህ መረጃው አለኝ እና ምን ለመስራት አቅደሀል?" "ያው ሀገራችን በርካታ የምህንድስና ወለድ ድጋፎች እንደሚያስፈልጓት እሙን ነው። አሁንም መንገዶች ሆስፒታሎች ትምህርት ቤቶች የህዝብ መኖሪያቤቶች ያስፈልጋታል ከጠቀስኩልህ ውጭም ጊዜን የሚቆጥቡ ድልድዮችና ግድቦች ያስፈልጓታል። እና ሀገራችን በሚያስፈልጋት ሁሉ እኔም እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሚጠበቅብኝን የምወጣ ይሆናል ማለት ነው" .....

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-17 07:30:52 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፭~ ( 225)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
#ከትውስታ መልስ አሁን
ኤሊያና እየሮጠች ሄዳ አባቷ ላይ ወጣችበት። "አቤት የኔ ወፍ ምን ፈልገሽ ነው?" "ምንም አልፈለኩም ተመልከት አባቴ ሁሉንም ትምህርት ደፍኜዋለሁ። መምህሯ ራሱ በጣም ጎበዝ ተማሪ ነሽ በርቺ እንቺ ሳይንቲስት ነው የምትሆኚው"አለችኝ እኔ ግን እንደ ቀዳማዊ ነው የምሆነው"አልኳት። ሙሉሰው ከሀዘን ወዲያው ባይወጣም በኤሊያና አነጋገር ፈገግ ብሎ "አንቺማ ከቀዳማዊም ትበልጫለሽ እንጅ የኔ ጀግና" "እንዴ አባዬ ተሳሳትክ ከቀዳማዊ በላይ እኮ ጎበዝ አይኮንም።እሱ ሁሉንም ይበልጣል እንጅ ማንም አይበልጠውም"አለች። አሁን ሙሉ በሙሉ ሳቀና "እሺ የኔ ቆንጆ በቃ እንደ ወንድምሽ ጎበዝ ሁኝ!" "አዎ እንደሱ ነው የሚባለው። ዋንጫ አመጣለሁ ወርቅ እሸለማለሁ።አሜሪካ ሄጄም አንደኛ እሆናለሁ" "አምንብሻለሁ የኔ ጣፋጭ" አለና ጉንጯን እያዟዟረ ሳማት። በኤሊያና ሁኔታ የነበረበትን የማህደሬ ትውስታ አጠፋው። ሁሌም የሆነ ጥሩ ነገር ባልተሰማው ጊዜ ኤሊያና ወይም ሔመን መጥተው ፈገግ ያደርጉታል። ይህ ነገር በጣም ይገርመዋል። ለኣ ሀዘናቸውን የሚረሱበት የሌላቸው ሰዎችም አሉ"ይልና ፈጣሪውን ያመሰግናል። እንደቤተሰብ ደስተኛ መሆኑ እፎይ ያስብለዋል። ደግሞ አሁን ከልጆቹ ራሱ አስበልጦ የሚወደውን ልጅ በመዳሩ ኩራትም ደስታም ተሰምቶታል።
****
"ሰርግ ቢሉሽ ሰርግ መሰለሽ እናቴ አገር ምድሩ አልቀረ። የእንግዳው አበዛዝ እንዳለ የተጠራው በሙሉ ሀፍታም ነው። የምግቡ አበዛዝ ትንሽ ከዛም ከዛም ስታነሽ ገና ሶስት አይነት እንዳነሳሽ ሳህንሽ ይሞላል። ኧረ ምኑ ቅጡ እታተዬ አለም ነበር አልኩሽ። ዘፋኞችም አሉ። የሚቀርጡም አሉ ይሄ ፎቶ ማንሻቸውን ይዘው በየቦታው ቆመው ቦግ ቦግ ቦግ ያደርጉታል። ብቻ ሰርጉ የአንድ ሰው አይመስልም የሶስት አራት ሰው ነው የሚመስለው"አለ ሙሉቀን የሰርጉን ሁኔታ ለመግለፅ ቃላት እያጠረው "እሰይ እሰይ እልል ነው። ወትሮስ እሱ የሁሉ ጌታ ሁሉንም ይመለከት የለ" " እነዛ ያስተማሩትን ሰዎች ብታያቸው አናቴ እንዴት የተባረኩና የተቀደሱ ሰዎች እንደሆነ። እኛን ራሱ እንዴት ሲያጣውቱን ና ሲንከባከቡን እንደነበሩ ብታይ" "እኔ ከተሜ ለያውም የአዲስአበባ ሰው እንደዛ ደግና ሩህሩህ ይሆናል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር። እንዴት ያሉ ደግ ሰዎች እንደሆኑ። አይፀየፉ ሁሉንም እኩል ነው የሚያዩት። እዚህ ተኛ ራስ አምባ ገበያ ስንሄድ ያሉት ሰዎች እንዴት እንዴት ነው የሚሆኑት ይቺም ከተማ ሆና። እና ሰዎቹ የጠባይ ሀብታም ና አዛኞች ናቸው"ብላ ዳሳሽም የሙሉቀን ሀሳብ ላይ ሀሳቧን ጨመረች። የሙሉቀን እናት በጣም ተደሰተች። "የኔ ከርታታ ልጅ እንኳን አባት የለኝሞ ብሎ እንዳይሰማው ተንከባከቡት። "የተጠሩት ሰዎች ራሱ አቤት ሰርግ ብለው እጃቸውን በግርምት አፋቸው ላይ ከድነው ነው የሄዱት። እኛ የማናውቀው መጠጥ ሁሉ አለ። ውስኪ ነው ጉደር ነው ያሉት?" ውስኪ ነው እንጅ"አለች ዳሳሽ "አዎ ውስኪ ብቻ እናቴ ምን አለፋሽ ድብልቅልቅ ያለ ሰርግ ነበር። ሙሽራይቱም ሸጋ ናት የተወለወለይ ቅቤ ቅል ነው ምመስለ። አይ ባህሪ አዬ ጠባይ ከቀዳማዊ ጋር ሆነው ነበር በመኪናቸው ወደ አየር መነሻው የሸኙን ብቻ የወንድሜን አለም አየሁት። አሁን በጣም ደስ ብሎኛል"ብሎ ሔዋን የሰጠቻቸውን እቃ ከሻንጣው እያወጣ ለእናትህ ስጥ የተባለውን እየመረጠ ከሰጣት በኋላ "ይሄን የላከችልሽ የቀዳማዊ እናት ናት"አለ ሙሉቀን "ኧረ ትባረክ ምነው ይሄን ሁሉ ልብስ መቼ ልለብሰው ነው የቀዳማዊን ራሱ ለብሼ መቼ አዳረስኩት?" "እንግዲህ ወደ በተስኪያን ስትሄጅ አንደኛውን ትለብሽና ሌላኛውን በፌስታል ሀይዘሽ ልክ ቤተስኪያን ስመሽ ስትጨርሽ ደግሞ ቀይረሽ ትመጫለሽ"አለና ሳቀ። ዳሳሽም ሳቀች። ሁላቸውም አንድ ላይ ተሳሳቁ።
*
"ጋሼ ለጫጉላ ሽርሽር ለአንድ ሳምንት ወይ ሁለት ሳምንት ወደ አርባምንጭ ሄደናል"አለ ቀዳማዊ "ጥሩ ነው። በሉ በደንብ ተዝናኑ ልጄ። ታዲያ ተጠንቅቃችሁ"አለ ሙሉሰው እንደማንኛውም ወላጅ ልጆቹ እንዲጠነቀቁ በማሳሰብ "እሺ ጋሼ እንጠብቃለን። ለእትዬም ንገረልኝ ስልኳን አላየችውም መሰል ስደውላት አታነሳም" "አይ ልጄ የእሷን ነገር ታውቀው የለ ለይስሙላ እኮ ነው ስልክ የምትይዘው። ልትደውል ስትፈልግ ብቻ ነው ስልክ እንዳላት ትዝ የሚላት"አለ ሙሉሰው።
ሐምራዊም ለእናትና ለአባቷ አሳወቀቻቸው። ደስ አላቸው እንደውም አባቷ ቀዳማዊን እንድታገናኘው ጠየቃትና አገናኘቻቸው። "ልጄ እንግዲህ ልጃችንን አደራ ሰጥተንሀል። እኛ ሀሳባችንን በአንተ ጥለናል። ከእንግዲህ ከአንተ በላይ ለእሷ እናስብላታለን ማለት አንችልም። ከአንተ በላይ ለእሷ የሚያስብ ማንም የለም። ስለዚህ እርስ በእርስ ተጠባበቁ ተንከባከቡ"አለ ሱራፌል። ቀዳማዊ በእሺታና በአክብሮት ሲያወራው ቆይቶ በመጨረሻ ስልኩን መልሶ ለሐምራዊ ሰጣት።
"አባዬ ግን በጣም ነው የሚወድህ። ከእኔ እንደውም ወደ አንተ ሳያመዝን ይቀራል። እኔም ቅልል ይሉኛል ሳወራቸው። ኮከባችን ተገጣጥሞ ይሆናል። አንዳንድ ጊዜ ሰውን ምንም ሳያደርገን እንዲሁ አይተን ልንወድ እንችላለን ልንጠላ እንችላለን። እና አባትሽም እንዲሁ ስለወደዱኝ ይሆናል" "እሪ ቀዳማ ግን እኔ ስለምወድህና የእኔ ባል ስለሆንክ ቢሆንስ የወደደህ?"አለች ሐምራዊ "እኔ በእሱ ግብረመልስ እወደዳለሁ ብዬ አላስብም። የራሱ መውደጃ ምክንያት ይኖረዋል ብዬ እንጅ የማስበው አንቺ ስለወደድሽኝ ብቻ ይወደኛል ብዬ አላስብም። ምን አልባት አንቺ ባልሽው መንገድ ወዶኝ ቢሆን እንኳ እኔ በዛ መንገድ እንደወደደኝ ማሰብ የለብኝም። እኔ አሁን የሚሰማኝ አንቺ ጋር እንኳ ብንጣላ ከእኔ ጋር የማይጣላ አድርጌ ነው ያሰብኩት" "አቤት አቤት ይሁንልህ አለችና ከንፈሩን ሳም አደረገችው።
*
መልካሙ (አቤል)"ቶሎ ቶሎ መስራት ይኖርብናል በዚህ አመት መጨረሻ ማለቅ አለበት"አለ ሁሉንም ሰራተኞች ከአናፂዎች እስከ ቀን ሰራተኞች ሰብስቦ። " አንዳንድ ጊዜም ከስራ መውጫችን ስአት ዘግየት ከስራ መግቢያችን ስአት ቀደም ብለን ሰርተን ብንጨርስ ለእኛም ደስ እንሰኛለን። ስራው አይጓተትም ማለት ነው። ይሄ የመጨረሻ ስብሰባችን ነው ከዚህ ቀኋላ ሁላችንም ሳንለግም በቅንነት እንሰራለን። ለራሳችሁ ስትሉ ለእናንተው ስትሉ ትሰራላችሁ "አለና ኮስተር ብሎ ተናግሮ ወደ ስራ ተሰማሩ።
**
"ቤርሲ ይሄ ነገር መብቃት አለበት። ደሐብ ከዚህ በላይ መሰቃየት የለባትም አንቺ እንደ ጓደኛ ማድረግ ካለብሽ በላይ አድርጊ። እያት በአንድ ጊዜ ነው ጥውልግ ያለቺው። በጣም ታሳዝናለች። ታሮስም እሷ በተጎዳችው ለሰክ ነው እየተጎዳ ያለው። ተስፋው እሷ ነች። እርግጠኛ ነኝ ታሮስ በጣም እንደሚንከባከባት"አለ ኪሩቤል "አዬ ኪሩ እንደሚንከባከባት ለእኔ ነው የምትነግረኝ እንኳን እኔ እሷም በደንብ ታውቃለች ግን አንዴ ልብህ ሲጎዳ ለሌላ ዝግ ይሆን የል ለዛ ነው......ትንሽ ትረጋጋና አናግራታለሁ"አለችና ቤርሳቤህ በዝምታ አቀረቀረች።

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 04:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 19:09:49 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፬~ ( 224)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
"ምንም አትሆኝም ሌላ ሕይወት ሌላ ባል ይኖርሽ ነበር። መቼም የማታቂውን ሰው ስትፈልጊ አትኖሪም!" አለ ቀዳማዊ "እሱስ ልክ ነህ። ግን የምር የሚደንቅ ነው። በዚህ ልክ አንተን ኬር ያደርግህ እንደነበር ስትነግረኝ በጣም ነው የገረመኝ" "አዎ ግን እስካሁን ቅር የሚለኝ በአንድ ነገር ብቻ ነው። አንድ እስካሁን ላገኘው ያልቻልኩት ባለውለታዬ አለ"አለ ቀዳማዊ "ማነው እሱ አባትዬ?" "የቀድሞ መምህሬ ነው። ለእኔ ሲል በእኔ ምክንያት ከስራው ተባሯል። እኔ ከእናቴ ጋር ተጣልቼ እያለ እሱ ጋር ሆኜ ለተወሰነ ጊዜ እየተማርኩ እያለ እናቴ ከሊቀመንበራችን ጋር በመመሳጠር እንዲከሰስ አደረጉት ከዛም የሰው ልጅ በማባለግ ተብሎ ከስራው ተባረረ። ባለቤቱ ራሱ እንዴት አይነት መልካም ሴት ነበረች መሰለሽ። ደረጄ ነው የሚባለው እንደው እናትዬ እሱን ካገኘሁት ደስታዬ እጥፍ ይሆናል። አግኝቼው እንደዚህ ትልቅ ሆኜ ያለሁበትን ደረጃም አይቶ ምን ያህል ደስ እንደሚለው ባይ ደስ ይለኛል" "በቃ ታገኘዋለህ የኔ ፍቅር። የምታገኝበትን መንገድ እናመቻቻለን። ያው መቼም በአሁኑ ጊዜ ከተማ ገብተው ይሆናል። ስለዚህ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች እንፈልገዋለን ለምሳሌ በሬዲዮም ሆነ በቴለቪዥን ብናስነግር መፍትሔ ይኖረዋል!"አለች ሐምራዊ። "እንዴት እስካሁን ይሄን አላሰብኩትም በቃ ይሄን መንገድ ነው እንጅ የምንጠቀመው"አለ ቀዳማዊ ከልቡ ደስ ብሎት። "እሺ በሚገባ እንጠቀመዋለን እንጅ የኔ ፍቅር"አለችና ቀበቶዋን አወለቀች። የቤታቸው ጊቢ ደርሰዋል። ቤታቸው ቅንጡ የሚባልና ሰፊ መሬት ላይ የተንጣለለ ግሩም ቤት!
ቤት ተቀምጠው እየተጨዋወቱ ሳለ ሙሉቀን ደውሎ በሰላም እንደገቡና ወደ ራስ አምባ ቀይ አፈር እየሄዱ እንደሆነ ነገራቸው። "ፍቅሬ አሁን በቀጣይ ምንድን ነው የምናደርገው?" "ጫጉላችንን አርባምንጭ ወይም ሐዋሳ እናሳልፍና በሁለተኛው ደግሞ ደስ ያለሽ ቦታ እንዝናናለን!!! ወይም ደግሞ በአንቺ ምርጫ እኔ ብቻ አንቺ አጠገቤ እስካለሽ ድረስ የትም ቦታ ሄጄ መዝናናት እችላለሁ"አለ ቀዳማዊ እያቀፋት።"አይ እኔም የተለዬ ሀሳብ የለኝም ፍቅሬ እንዳልከው መጀመሪያ አርባምንጭና ሐዋሳ እናሳልፍ"ብላ ሐምራዊም በአንድ ሀሳብ ተስማሙ።
*
"እንዴት አንጀት የሚበላ ልጅ ነው ሙሉዬ? እኔማ አሳዘነኝ ቀዳማዊን አይቶ አይጠግበውም። ጓደኛው ሳይሆን እኮ ወንድሙ ነው የሚመስለው። በል እስኪ ለቀዳማዊ ደውልልለትና በሰላም መግባታቸውን ጠይቀው"አለች ሔዋን። ሙሉሰው በሀሳብ ሄዶ ስለነበር በሔዋን ጣት ሲገካ ወደ ራሱ ተመለሰና "ምን አልሽኝ ሔዋኔ?" "እስኪ እነ ሙሉቀን በሰላም እንደገቡ ቀዳማዊን ደውለህ ጠይቀው ነው ያልኩህ" "እሺ እሺ "አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለለት "አቤት ጋሼ"ቀዳማዊ ከወዲያኛው የስልክ ጫፍ ፈጣን ምላሽ "ልጄ ወንድምህ ደወለልህ? በሰላም ገብተዋል?" "አዎ ጋሼ አሁን ከደቂቃዎች በፊት ደውሎልኝ ነበር በሰላም ገብተዋል"አለ ቀዳማዊ "ጥሩ እንኳን በሰላም ገቡ። እናንተስ እንዴት ናችሁ ቤታችሁን ተላመዳችሁት?" "አዎ ጋሼ በደንብ ተላመደናል" "ጥሩ በሉ የወንድምህን ዜና ለመጠየቅ ነው የደወልነው። እናትህም ሰላም እያለችህ ነው መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ" "አሜን አሜን ለእናንተም መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ ጋሼ። እትዬን ሰላም በልልኝ" "እሺ እልልሀለሁ"
ሙሉሰው ከቀዳማዊ ጋር አውርቶ ከእንደገና በሀሳብ ንውዝ አለ። "ሙሉዬ የሆንከው ነገር አለ? ፍዝዝ ትክዝ እኮ አልክብኝ"አለች ሔዋን አጠገቡ እየተቀመጠች። "ቀዳማዊን በመዳራችን በጣም ነው ደስ ያለኝ። ግን መጀመሪያ እድራታለሁ ወግ ማዕረጓን አያለሁ ብዬ የነበረው የእህቴን ነበር"ብሎ የእንባ ዘለላዎቹን በጉንጮቹ ቦይ አፈሰሳቸው። "ያው ምን ታደርገዋለህ ፈጣሪ አልፈቀደልንም። የፈቀደልንን አድርገናል"አለች ሔዋን እሷም አይኖ እምባ ሞልቶ። ሙሉሰው በትውስታ ተመለሰ።
#ትውስታ "ኮሚሺነር መላኩ በጣም ተናዶ ጠረንጴዛውን በቡጢ እየነረተ እያንዳንዱን ታራሚ እየጮኸ ጠየቃቸው። እርስ በእርስ የት እንደነበሩ። ሰላማዊትን ለመጨረሻ ጊዜ ከማን ጋር እንደነበረች። ሁሏንም ነገር አንድ በአንድ በጥንቃቄ በመጠየቅ ሁላቸውንም አንድ በአንድ። የብዙዎቹ ታራሚዎች መልስ ለመጨረሻ ጊዜ ሰላማዊትን ያይዋት ከ ስርጉቴ ጋር እንደሆነ መሰከሩ። የሁሉም ጣት እና ነገሮች ሁሉ ወደ ስርጉት ሲወስድ ኮሚሺነር መላኩ ጊዜ ሳያጠፋ ስርጉትን ለብቻዋ የምርመራ ክፍል ይዟት ገባ። ለትንሽ ጊዜ ካናዘዘችው በኋላ እውነቱን ተናገረች። ዳዊት ብር እንደከፈላት ውጪ ላይ ካለ የእሱ ሰው ጋር እየተገናኙ እያንዳንዱን ነገር ሲያደርጉ እንደነበር ቀን በቀን ስታደርገው የነበረውን የቀን እንቅስቃሴዋን ሳይቀር አንድ በአንድ ተናዘዘች። "ከእኛ በተጨማሪ አቤልንም በተመሳሳይ ያስገደለው ራሱ ዳዊት ነው" አለች ስርጉት። ኮሚሺነር መላኩ ስርጉትን ባለችበት ትቷት ቀጥታ ወደ ወንዶች እስር ቤት ዳዊት ጋር አመራ
"ኮሚሺነር ዞረህ ዞረህ እኔ ጋር መጣህ ደግሞ ?" አለ ዳዊት ያስጠራው እንግዳ ኮሚሺነር መላኩ መሆኑን ሲመለከት። "አዎ ዞሬ ዞሬ መጣሁ። በርግጥ በመዞር ደከምኩ እንጅ መድረሻዬ መነሻዬ ነበር። መነሻዬ ላይ በትክክል መንገዴን አላሰብኩም ነበር መሰል የተነሳሁበት ቦታ ደረስኩ"አለ ኮሚሺነር ዳዊን ትክ ብሎ እየተመለከተ። "እና አሁን እኔ ምን ልርዳህ"አለ ዳዊት እግሩን እግሩ ላይ አነባብሮ። "የወንጀል ድርጊትህን ደርሰንበታል። ወይዘሮ ሰላማዊትንና አቶ አቤልን አንተ እንዳስገደልካቸው ደርሰንበታል"አለ ኮሚሺነር መላኩ። "ምኑን ነው የምትደርሱበት? ይሄ እኮ በጣም ተራ ነገር ነው። ትልቅ ነገር እኮ አይደለም ያገኛችሁት። እንደውም ይሄን ያህል ጊዜ እንደምትቆዩ ባውቅ ቀድሜ እኔ እንዳደረኩት እነግራችሁ ነበር። ግን እስኪ ትንሽ ጭንቅላታቸውን ይጠቀሙበት ፖሊስነታቸውን በሚገባ ይወጡ"ብዬ እንጂ ቀድሜ እነግራችኋለሁ እንኳን እንደዚህ አይነት ተራ ወንጀል ቀርቶ በበርካታ እንቆቅልሽ የታጀበ የወንጀል ድርጊት እንኳ ይደረስበታል"አለ ፈገግ እያለ። "እና አመንክ ማለት ነው?"አለ ኮሚሺነር መላኩ። "እንዴት አላምን!"ሰው የሰራውን ስራ ካላመነ ምኑን ሰው ሆነ ታዲያ?" " ጥሩ የአቃቤ ህግ ቢሮ እንሄዳለን የእምነት ክህደት ቃልህን ትሰጣለህ"ብሎ አብረው ተነሱ። ዳዊት ሳይጨምር ሳይቀንስ ለአቃቤ ህጉ ለኮሚሽኑ የነገረውን መልሶ ነገረው። አቃቤ ህጉ ተገርሞ ቃሉን እንዳለ አንድ በአንድ።አቃቤ ህግ የዳዊትን ቃል በደንብ ከመዘገበ በኋላ በድጋሚ የወንጀል ከስ መሠረተ።
"እንግዲህ አቶ ሙሉሰው ለሁሉም ነገር ፅናቱን ይስጥህ የእህትህን ገዳይ ይዘን ለፍርድ ማቅረብ አልቻልንም ነገር ግን የእህትህን ገዳዮች ገዳይን አጎኝተነዋል። የነ አቤልና ሰላማዊት ገዳይ ወንድምህ ዳዊት ነው። ይሄንን እውነት እሱሙ አረጋግጦልናል። ክሱን አልተቃወመም በደስታ ነው የተቀበለው። እንግዲህ በድጋሚ ፈጣሪ ያፅናህ "ብሎት ሙሉሰውን ተሰናብቶት ወደ ቢሮው ገባ። ሙሉሰው ራሱን ይዞ ሲያስብ ከቆየ በኋላ መኪናው ውስጥ ገብቶ ወደ ቤት ተመለሰ።"ዳዊት ስለተበቀላቸው ደስ ብሎኛል "አለች ሔዋን። ሙሉሰው ምንም አይነት መልስ አልመለሰላትም። ቀጥታ ወደ መኝታ ከፍል ገብቶ ነበር የተኛው

@amba88
@ken_leboch
1.0K viewsTesfa Desalegn, 16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 13:16:27 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፫~ ( 223)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
"እና ደሐብ ስለ ዶስቶቭስኪ ልንገርሽማ በእርግጠኝነት ስለ እሱ ታውቂያለሽ። በጣም የሚገርምና በአለም ላይ የሚታወቅ ከያኒና ደራሲ ነው። በዛ ላይ የምትወጃት ሀገር የሩሲያ ፍሬ ነው"አለና ወሬ በማስቀየር የታሮስን ሀሳብ እንድትረሳው አደረጎ ታሮስን ከእግር እስከራሱ እየገላመጠ። ታሮስ ጥፋት እንደሰራ የገባው ኪሩቤል ሲገላምጠው ነበር። "አዎ በደንብ አውቀዋለሁ እንጅ የሩሲያው ሼክስፔር የስነፅሁፍ ራስ አይደል። የፅሁፎቹን ይዘት ሁሌም ሳነብ በጣም እገረማለሁ። በተለይ "notes frome the underground "የሚለው መፅሐፉ ይበልጥብኛል"ብላ ስለ መፅሐፉ አጠር ያለ ማብራሪያ ሰጠች። "አዎ ልክ ነሽ እኔም እንደ ዳዊት ሁሌ ነው የምደጋግመው ሲያልቅብኝ እናደዳለሁ"አለና ኪሩቤል እዛው የመፅሐፍ ሙድ ውስጥ እንዳለች የሌላኛውን አስገራሚ የስነፅሁፍ ሰውና ተዋናይ ኮሜዲ ቻርለስ ቻፕሊንን ቃኘት አደረገላት። "ቻርሊ በጣም ቀልደኛ ነገር ግን በዛው ልክ ደግሞ ቁምነገረኛ ነው"ብሎ ሀሳቧን እንድትሰጥ በር ከፈተላት። "በተለይ ኪሩ እሱ ሰውዬ አልፎ አልፎ የሚፅፋቸው ግጥሞች በጣም ነው የሚገዙኝና የምወዳቸው አሁን ለምሳሌ "the mask"በሚል አርዕስት የፃፋት ግጥም ግሩም እኮ ነች።#The_Mask የምትለዋ
First I say,
“How do you do?"
And lift my hat
and wink at you
.
But you mustn't
clap too loud
I'm so modest
in a crowd."ብላ ደሐብ በቃሏ አነበበቻት። ኪሩቤል በዚህ ጊዜ ፈገግ አለና በነገርሽ ላይ ይቺን ግጥም እኔው በራሴ አገላለፅ ወደ አማርኛ ቀይሪያታለሁ"አለ "እና አታነብልኝም?"አለች። "ሳትጠይቂኝ ነበር የማነብልሽ ማስታወሻዬ ጋ ነው። ስልኬ ላይ አላሰፈርኳትም። ዝም ብዬ ቢሮ በሆነ ሀሳብ ውስጥ ሆኜ ግጥሟን እያነበብኳት ከሰውየው ባህሪም ጋር በተወሰነ መልኩ በማናፀር ነው የተረጎምኳት""ዋው ደስ ይላል"አልችና ወደ ቤርሳቤህ ዞር ብላ "የኔ ቆንጆ በጣም አምሮብሻል ኪሩቤል አፈር አይንካሽ እያለ ነው መሰል የሚንከባከብሽ?"አለች ፈገግ ብላ "አዎ በደንብ ነዋ። ይሄው መሬቱን በእግሯ ከረገጠችው ቆይታለች። በስንት ጊዜ በቃ በእግሬ መሄድ እፈልጋለሁ መራመድ ናፍቆኛል ባለችው መሠረት ነው ዛሬ በእግሯ ያመጣኋት"አለ ኪሩቤል እየሳቀ "ኧረ ባክህ ወሬኛ አልቀረብህም። ከሚገርምሽ ስራውን ብነግርሽ ታፍሪበት ነበር። የሚያቅፈኝ እኮ የሆነ ነገር ሲያምረው ነው። ልክ ክፉ ላስ ወይ ቤት የሄድን እንደሁ እግራችን ቤቱን እንደረገጠ እቅፍ አድርጎ ቀጥታ ወደ አልጋ ነው የሚወስደኝ"አለች። "ይሄም ጥሩ ነገር ነው። እሱ ስለሆነ ነው ያደረገው ሌላ ቢሆን ማን ያደርገዋል?"አለችና ደሐብ በፈገግታ ኩም አድርጋ አቀፈቻት። ታሮስ ባደረገው ነገር እንደ መሸማቀቅ ብሎ በዝምታ ይመለከታቸዋል "የኔ ፍቅር ምነው ዝም አልክ?"አለች ደሐብ የታሮስን ፂም እየነካካች። "እ ምንም እንዲሁ እናንተ ወሪያችሁን እስክትጨርሱ እየጠበኩና የማነሳውን ሀሳብ እያሰብኩ ስለሆነ ነው"በማለት ቆጠብ ብሎ ተናገረ። "ዝም ስትል ይጨንቀኛል። ፈታ በል በደንብ ተጫወት እሺ ጌታዬ"አለችና ጉንጩን ሳም አደረገችው። ኪሩቤልና ቤርሳቤህ ተያዩ።
**
"እንዲህ ያለም የለ። በጣም ነው የምናመሰግነው እትዬ። ይሄን ያህል ቀን ተስማምቶን ነው የቆየን እግዚሐር ይስጥልን"አለ ሙሉቀን ጎንበስ ብሎ። ሙሉሰው በነ ሙሉቀን ስርአትና የቃላት ጥንቃቄ እየተገረመ "እናንተ ቤተሰቦቻችን ናችሁ እኛም እንደዛው። ቀዳማዊ አስተሳስሮናል። ስለዚህ በክፉም በደጉም አብረን ነን። እኛም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መጥተን እንጠይቃችኋለን"አለ ሙሉሰው። ሔዋን ሻንጣ ሙሉ ልብስና አንዳንድ የሚያስፈልጉ ነገሮችን አዘገጃጅታ "ልጃችሁን ሳሙልኝ። ወላጆቻችሁንሞ ሰላም በሉልን"አሉና ተሳስመው መኪና ውስጥ አስገቧቸው። "በቃ አይዟችሁ እንዴ በቅርቡ መሄዳችን አይቀርም የሆነች ነገር የምንጎበኛት ነገር አለች"አለ ቀዳማዊ እነ ሙሉቀንንና ሔዋንን በየተራ እየተመለከተ" በሉ እሺ በሰላም ግቡ ፈጣሪ ከእናንተ ጋር ይሁን"አለና ሙሉሰው እጁን አውለበለበላቸው። ሔዋንም መልካም ምኞቷን ገልፃላቸው ተሸኛኙ። ቀዳማዊ እና ሐምራዊ እነ ሙሉቀንን እያጫወቱ ኤርፖርት አደረሷቸው።"ወንድሜ በዚህ የደስታ ቀኔ አብረኸኝ ስለሆንክ በጣም ደስ ብሎኛል።"አለና ቀዳማዊ አቀፈው። "እኔም ወንድሜ በጣም ተደስቻለሁ። ሰርግህ በጣም ግሩም ነበር። እነ ጋሽ ሙሉሰው ጥሩ አድርገው ነው የዳሩህ የነሱ ውለታ አለብህ ቀዳም በርግጥ አንተ ያደረጉልህን የምትረሳ አይደለህም። ግን ተንከባከባቸው በነዚህ ጥቂት ቀናቶች ምን አይነት ሰዎች እንደሆኑ አስተውለናል። እና አምላክ የልብህን አይቶ ወደር የማይገኝላቸው እናትና አባት ሰጥቶሀል"። "አንቺም እህቴ እንግዲህ ተዛምደናል። ቶሎ ወልዳችሁ ደግሞ ደስታችንን እጥፍ እናድርገው።"ብሎ ሐምራዊንም አቅፎ ሳማት። በናፍቆት ተለያዩ።
*
"ወንድሜ ሲልህ አንጀቴን አላወሰው። ውይ አነጋገሩ እንዴት አንጀቴን እንዳላወሰው"አለች ሐምራዊ እነ ሙሉቀንን ሸኝተው ሲመለሱ።ቀዳማዊ ፈገግ ብሎ "አዎ ከልቡ ነው እንደዛ የሚለኝ። ምድር ላይ ከእሱ በላይ የሚወደኝ ያለ እስካይመስለኝ ድረስ ነው የሚገርመኝ። በእኔ ጉዳይ በጣም ስስ ነው። እኔን ሲነኩኝ አይወድም። ከልጅነቴ ጀምሮ በጣም ነው የሚሳሳልኝ። ከሚገርምሽ እሱ ከትምህርት ይቀርና እኔ እንድማር የኔን ግልገሎች ይጠብቅልኝ ነበር። እናቴ ያው ከትምህርት ቤት የምታስቀረኝ ጊዜ ስለሚበዛ እሱ እኔ እጠብቅለታለሁ ብሎ ከትምህርት ቤት እስክመለስ በደንብ ይጠብቅልኛል። ምን አልባትም ምሳ ላይበላ ይችላል ብሎ ስለሚያስብ እሱ ቤቱ በልቶ ከእንደገና እናቱን በአገልግል ያስቋጥራትና እንበላለን። ብቻ የቱን አንስቼ የቱን ልተውልሽ የእናት ልጅ እንደዛ ማድረጉን እጠራጠራለሁ። ሁሌም የሚለኝ አንተ የተማርህ ምሁር ነው የምትሆን እኔ እጣፈንታዬ ገበሬነት እንደሆነ አውቀዋለሁ።ስለዚህ አንተ ተማር ጎበዝ መምህር ትሆናለህ ነው የሚለኝ። ያው በዛን ጊዜ በእኛ እይታ ትልቅ ስራ መምህርነት ነው የሚመስለን። ከእኛ የተሻለ ከተሜዎች ስለሆኑ እንደነሱ መኖር ነው የምንፈልገው። ትልቁ ራዕያችን እንደ ጋሼ እንትና ጎበዝ አስተማሪ መሆን ነው።ከዛ ቀጥሎ ደግሞ ወታደር መሆን። እና ታዲያ የኔን ጎበዝ ተማሪ መሆንን ይኮራበታል። ወንድሜ እኮ አንደኛ አንደኛ ነው የሚወጣው የሚሸለመው ደፍተር እኮ ብዙ ነው። እያለ በእኔ ይኮራል። በኤረኞቹ ፊት ደረቱን ነፍቶ ይቆማል ይጀበንባቸዋል። ብቻ ምን አለፋሽ እኔ እዚህ ለመድረሴ ትልቁን ሚና የተጫወተው እሱ ነው። ለመጥፋት ባሰብኩ ጊዜ እንኳ ራሱ እናቱ ያስቀመጠችበት የብር ቅል ገብቶ ብር ሰርቆ ነው መሳፈሪያ የሰጠኝ። ከዛ በኋላ በዛች ብር ፈጣሪ እረድቶኝ አዲስአበባ ገብቼ ለዚህ በቃሁ ማለት ነው።እንግዲህ ከብዙ በጥቂቱ ይሄን ይመስላል ፍቅሬ"አለ ቀዳማዊ እንባ ያቀረሩ አይኖቹን በፈገግታ ለመሸፈን ፈገግ እያለ። "የኔ ጌታ እንኳን መጣህልኝ። ለእኔም ባለውለታዬ ነው። አንተን ከዛ ባያስወጣህ ኖሮ ይሄኔ ምን እሆን ነበር?"አለች ሐምራዊ

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 07:30:57 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፪~ ( 222)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
****
አይኖቿ ለመሟሸት የተጣደ የሸክላ ድስት ቂጥ መስሏል። ከደምነት ቀለም ወደ ጥቁርነት ቀለም የተለወጠና ሁለቱንም ቀለማት የቀላቀለ ውህድ። በዘመናት ለቅሶ የማይመለስ በይቅርታም ሆነ በሌላ ግብረ መልስ የማይሽር በስህተት የታተመ የፍቅር ማህተብ። ከልቧ የማትፍቀው በእልህና በአልሸነፍ ባይነት የእድሜ ዘመኗ የሰነቀችው የፍቅር ስንቅ፤ ማዕበሉ በሚያናውጣት የተስፋ ወጀብ ውስጥም ሆና የምትናፍቀው ካፒቴኗ። ጀልባው መልህቋን ስትጠል በከዋክብት ታጅቦ በልቧ ሰማይ ላይ የሚሳል ውብ ድንቅና ማራኪ ቀለም። በልቧ ሸራ ላይ እያንዳንዱ ድርጊቱና ስኬቱ የተሳለ ብቸኛ የሕይወቷ ገጠመኝ ቀዳማዊ። አሁን የማይታመነውን አምናለች። እውነት በገሀድ ወጥታ መርዶዋን ነግራታለች። ቀዳማዊ በበረሃ ጋመን እንደሚሸሽ የዝናብ ጉም በደቂቃዎች ተኗል። የሕልሟ ካብ ተንዷል። ደሐብ ከዚህ በኋላ የምትኖረውን የገሀነም አለም አሰበችው። ጣዕሙ አልጣጣማት አለ። ውበቱ አልታያት አለ። ቀዳማዊ እስከወዲያኛው በሐምራዊ ልብ የሚዋኝ ዓሳ መሆኑን ለማመን ተገደደች። እስከመጨረሻው የሰርግ ስነስርአት ድረስ ተስፋ አልቆረጠችም ነበር። ምንም እንኳ ተስፋ የጣለችበት ነገር ተስፋ ባይኖረውም ግን እውነቱን ሳይሆን የልቧን እምነት ብቻ በተስፋ ትጠብቅ ነበር። ብቻ የማታውቀው ነገር ግን ሰርጉን የሚያስቀር ሐምራዊን የሚያስተው ታዕምር እንዲኖር ታስብ ነበር። በሞት ውስጥ ተስፋ የሚደረግ እምነትም ነበራት። ነገር ግን ሁሉም ነገር ከቅዥት ያለፈ አልነበረምና አንዱም ከእሱ ጋር ልትሆንበት የምትችልበት መንገድ አልተፈጠረም። አንዳንድ ጊዜ ከሚታየን እውነት ለመራቅ በሸሽን ቁጥርና ባለማመን መንፈስ ከተገትርን ሕይወት በሌላ የሕይወት አዙሪት ውስጥ አስገብታ ታጥረናለች።
በእንባ የራሰ አንሶላዋን ቀስ አድርጋ አጠፈችና ከአልጋዋ ተነሳች። ስልኳን ስትመለከት በርካታ ሚስኮሎችን አየች። ደዋዮቹ ቤርሳቤህ ኪሩቤልና ታሮስ ናቸው።ነገር ግን ታሮስ በርካታ ጥሪዎችን አድርጎ ነበር። የማናቸውንም ጥሪ አልሰማችውም።ሕይወት ለካ እንዲህ ጣዕሟ ይጎመዝዛል። መኖርም ጣዕም የሚኖረው ለካ በራሳችን ሕይወት የሚኖረን ተስፋና ሰው ሲኖር ነው። ለካ ሰው ራሱን የሚያጠፋው ሌላ የተሻለ አለም ፍለጋ ኖሯል። ለካ ዘመንም የምሽቱን አድማስ በጨለማ የሚተካው ከፅሐይ አንዳች መፍትሔ ሲያጣ ነው። ለካ ጭንቅላት ማረፊያ ዋርካ ሲያጣ ነው ያገኘው ሀሩር ላይ ተሰጥቶ እንደ ቅቤ የሚቀልጠው። ለካ የሚወዱትን የሚናፍቁትን ገላ እንደ ነፋስ ሽው ብሎ ሲያልፍ ልብም እንደ ቃየል መሄጃ እስክታጣ ትቅበዘበዛለች።
*
"እኔ ሁኔታዋ አላማረኝም። ብቻ ፈጣሪ ይርዳኝ እኔ እሷን አጥቼ መኖር አልችልም"አለ ታሮስ ሆድ ቁርጠት እንደ ተያዘ ሰው ሆዱን በእጁ ታቅፎ እየተቁነጠነጠ። "ታሮ ተረጋጋ ምንም አትሆንም ይሄን ያህል ጅል አይደለችም። በደንብ የምታስብና የምታሰላስል ብልህ ሴት እኮ ነች። ለማይረባ ስሜት ብላ ነገዋን የምታበላሽ ሴት አይደለችም" "የማይረባ ስሜት አትበል ኪሩቤል!!!!"ታሮስ በድንገት ጮኾ ኪሩቤል ላይ አንባረቀበት። "ፍቅር ነው የያዛት ገባህ ፍቅር ነው። ይሄ ደግሞ የማይረባ ስሜት አይደለም። ፍቅርን ማጣት ስሜቱን አታውቀውም። በርግጥ እንደዛ የምትሆንለት ሰው እኔ ብሆን ደስ ይለኝ ነበር ግን አይደለሁም በቃ እኔ አይደለሁም። እሱ ብቻ ነው ለዚህ የታደለው "አለ ታሮስ ስቅስቅ ብሎ እያለቀሰ። ኪሩቤል የታሮስ ሁኔታ አብሰከሰከው"ወንድሜ እመነኝ። እሱ የራሱን ሕይወት መርጦ ጀምሯል። ደግሞ እሱ ፈልጎ እኖዳላደረገው ታውቃለህ። በቃ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው። አውቆ ሁለቱም እንዲወዱት ቢያደርግ ኑሮ ያው የምናደርገውን እናደርግ ነበር። ግን እሱ የራሱን ኑሮ ሲኖር በተፈጠረ ነገር ተወቃሽ ልናደርገው አይገባም። በዛ ላይ አሁን እስከወዲያኛው ከሕይወታችሁ ይጠፋል። በምንም ታዕምር ልታገኙትም ሆነ ልትገጣጠሙ አትችሉም" በማለት ኪሩቤል ሊያባብለው ሞከረ። "አዎ አሁን ጠንክረህ እሷንም የምታጠነክርበት ጊዜ ነው። በጭራሽ እጅ አትስጥ እሱን እንድታስበው ለማድረግ ቦታ መስጠት የለብህም። ጊዜህን ስጣት። እኛ ሴቶች ከምንም በላይ የምንፈልገው ጊዜውን የሚሰጠንን ወንድ ነው። ገንዘብ ብትሰጣት ገንዘቡን መልሰህ ታገኘዋለህ። ሌላም ነገር ብትሰጣት መልሰህ የምታገኝበት እድል ሰፊ ነው። ጊዜ ግን አንዴ ከሄደ ሄደ ነው። የማይመለስ ጊዜውን የሰጠ ወንድ ደግሞ ፍቅሩን በቃላት ከሚገልፅላት በላይ ይገልፅላታል። ስለዚህ ጠንከር በልና አጠንክራት ጓደኛዬን በሚገባ አውቃታለሁ። ለጊዜው ነው እንጅ የምትጎዳው በደንብ ምቾት ከሰጠኻትና ከተንከባከብካት ትረሳዋለች......."ብላ ቤርሳቤህ ልትቀጥል ስትል "ቆይ አንድ ጊዜ እሷ ናት መሰል"ብሎ የሚጠራ ስልኩነሰ ከኪሱ አውጥቶ ተመለከተው እውነትም ደሐብ ነበረች። "አቤት የኔ ፍቅር አስጨነቅሽኝ እኮ የት ነሽ የት ልምጣ?"አለ ታሮስ። "የትም አትምጣ እኔ እዛው ያለኽበት እመጣለሁ "አለችና ያለበትን ጠይቃው ስልኩን ዘጋች። "አላልኩህም! እሷ ምንም አትሆንም ደሐብ ነገዋን የምታበላሽ ሴት ሳትሆን በፈራረሰው የትላንት ትዝታዋ ዛሬዋን የምታሰማምር ነገዋን ደግሞ የምታስውብ ሴት እንጅ ተሸንፋ ከሜዳ የምትወጣ ሴት አይደለችም። እና ወዳጄ ደስ ልትሰኝ ይገባል የእሷ ባል በመሆንህ አሁን ደስታችሁን የምታከብሩበት ቀን ሩቅ አይደለም"አለና ኪሩቤል በፈገግታ የታሮስን ትከሻ መታ መታ አደረገው።
**
"በሉ ሁሉንም እርሱት። የራሳችንን የወሬ ርዕስ ፈጥረን ነው እንጅ መጫወት ያለብን ሕመሟን የሚያስታውስ ወሬ ማንሳት የለብንም። ታሮስ በጣም ተጠንቀቅ ነግሬሀለሁ በምንም ታዕምር ስለ ቀዳማዊ ምንም ነገር እንዳታነሳ"ብሎ ኪሩቤል አስጠነቀቀው። "እሺ ምንም አታስብ ጓደኛዬ በጭራሽ አላነሳባትም"አለ ታሮስ። "እሺ ክቡራንና ክቡራት እዚህ ተሰብስባችሁ የየአዲስ አበባን ድንቅ ተፈጥሮ ትቋደሱልኛለችሁ አይደል?"አለችና ደሐብ የምፀት ፈገግታዋን ፈገግ ብላ ሁላቸውንም ስማ ታሮስ ቆሞ ያዘጋጀላት ወንበር ላይ ስባ ተቀመጠች። "እንዴት ነው እዚህ ሆናችሁ ስትመለከቱት የአዲስ አበባን ውብ ገፅታ?"አለች ደሐብ " እንግዲህ እንደ አስተያየታችን ነው። በመሀንዲስ አይን ካየናት ህንፃና መንገድ እንዲሁም በርካታ ፋብሪካዎችና የኤሌክትሪክ መብራቶች ይታያሉ። በዶክተሮች እይታ ደግሞ ታካሚዎችና በርካታ የታካሚዎች አስታማሚዎች ሲታዩ ሒሳብ ባለሞያዎች አይን ደግሞ። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እምብርት መሆኗንና በርካታ ገንዘቦቸሰ የሚንሸራሸርባት የንግድ ማዕከል ሆና ስትታየው። ሁሉም እንደየ ሰው አይንና እንደሚስማማው ወይም እንዲሚሰራው ስራ ቆጥሮ ያላትንና የሚጎላትን ይተነትናል"አለ ታሮስ ኪሩቤል እግሩን በእግሩ መታ አደረገው። ኪሩቤል የታሮስ ወሬ አጀማመር አላማረውም መዳረሻው ቀዳማዊን ማሳሰብ እንዳይሆን ሰግቷል። ታሮስ የኪሩቤል ጉሽምታ በሚገባ ተረድቶታል ወሬ ለመቀየር ብሎ "ፍቅሬ ምን ያህል እንደማፈቅርሽ ታውቂያለሽ አይደል? ቅድም አሁን ስልክ ሳታነሺ ስትቀሪ በጣም ጨንቆኝ ነበር"አለ ታሮስ ደሐብ ለታሮስ ልትመልስለት ስትል ኪሩቤል ፊቱን አጨፈገገና በንዴት ታሮስን እየተመለከተ.........

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 04:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 07:30:03 ቅን ልቦች pinned Deleted message
04:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 07:36:20 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳፩~ ( 221)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
ወይዘሮ አትጠገብ እንዲሁ እየተብሰለሰለች ቁጭ ብላ የባጡን የቆጡን ከእንደገና ብቻዋን ስታወርድ ስትሰቅል የቀኗ ፅሐይ ጥላዋን እያጠላች እግሮቿን ወደ ምስራቅ ዘርግታ አንገቷን ወደ ምዕራብ አቅጣች እያሰገገች ነው። የሰውን ክፋት ገመና በብርሀኗ ስታጋልጥ ውላ በመጨረሻ በጨለማ ተረትታ ጉሟ ውስጥ ተሸጎጠች። አንድ የከፋው እና የናፈቀ ህፃን ተንደርድሮ የእናቱን ጡት ይዞ ጉያዋ ውስጥ እንደሚደበቀው ነው የጀንበሯ ቀይ ጉሙ ላይ አሸጓጎጧ። ይህን የምሽት የተፈጥሮ መስተጋብር ቆሞ ላስተዋለ ሰው ብዙ ነገር ይማራል። አንዳንድ ጊዜ በየዋህነትም ሊሆን ይችላል ወይም በጊዜው በማይሆን ስሜት የፈጠርነው ችግር አድጎ እኛ የምንደበቅበት እስክናጣ ድረስ ያደርገናል። ሰው ልክ እንደ ፅሐይ ይወጣል። እድሜው የፅሕይን አስራ ሁለት ስዐት ሲያክል ደግሞ ይመሽበታል። ከመሸ በኋላ ጠዋቱን ማግኘት ቢፈልግ አያገኝም በፀፀት ቢናውዝም በጭራሽ። ስለዚህ ሕይወታችንን በጥንቃቄና በብስለት መኖር ካልቻልን የምንጥላቸው የነገር ቃሎች እሾህ ሆነው በቅለው ሲወጉንና እርምጃችንን በሰቀቀን እንድንሞላው ያደርጉናል። ሰው የዘራውን ነው የሚያጭደው ማለት ጤፍ ከዘራ ጤፍ እንጅ ማሽላ አያጭድም እንደማለት ብቻ ሳይሆን መጥፎ ነገር ካደረግን ምላሻችን ሊሆን የሚችለው መጥፎ ነገር ነው ለማለት ነው። መቼም ነገር በምሳሌ ጠጅ በብርሌ ነውና የሚባለው።
በሀሳብ ሰጥማ ስትነሳ የተቀደደው የጎዳዋ ጫፍ የእግር ጣቷን ጠልፎ ከእንደገና ወደቀች የጎዳዋ ቀዳዳ ውስጥ የገባችው ጣቷ ትንሽ ወለም ብሏት አመማትና ይዛት ተቀመጠች። በጣም ስላመማት ሕመሟን እንደምንም እየዋጠች ቀስ አድርጋ በባዶው እየነካካች ታሻት ጀመር። ወይዘሮ የአትጠጠገብን አኳኋን የተመለከተ በጭራሽ መጥፎ ነገርን መስራት አይደለም ለማሰብ እርም ያስብላል። ከልቧ ነው ብሶቷና ኃጢያቷ ገንፍሎ አይኗን በእንባ ያጠበው።
***
ሁሉም ነገር ዝግጁ ሆኗል። ሮሃ ባንድ የተዘጋጀለትን ቦታ ቀድሞ ይዞ ዝግጅቱን አጠናቆ የፕሮግራሙን ቅደም ተከተል ብቻ ይጠባበቃሉ። ካሜራ ማኖቹ በየቦታውና መውጫ መግቢያው ካሜራቸውን አስቀምጠው እያንዳንዷን ነገር ይለቅማሉ። የሙሽሮቹ ስቴጅ በደንብ ዲኮር ተደርጓል። እንግዶች እና ጥሪ የተደረገላቸው ሰዎች ቀድመው ቦታ ቦታቸውን ይዘዋል። ድንኳኑ በሰዎች ተጥለቅልቋል በየ ድንኳኑ ኮሪደር የቀዳማዊና የሐምራዊ ፎቶ ተሰቅሎ ዙሪያው በዲም ላይት ይበራል ከፏቷቸው ስርም " የአቶ ቀዳማዊ ታረቀኝና የወይዘሪት ሐምራዊ ሱራፌል የጋብቻ ስነስርዓት"የሚል ወርቃማ ፅሁፍ ሰፍሮበታል። የሰርግ ፎቷቸውን የተመለከተ እንግዳ ሁሉ "እትፍ እትፍ ከአይን ያውጣችሁ! ትዳራችሁ በፍቅርና በረድኤት የተሞላ ይሁን!"ብሎ የማይመርቅ የለም።
ጠጁ፣ጠላው፣ቢራው ወይኑ፣ውስኪው ሁሉም በአይነት በየጠረንጴዛው ተደርድሯል። ምግቡም በአይነት ከአትክልት እስከ ዶሮ አሩስቶው በአልጫም በቀይ ተሰርቶ በጎዶጓዳ ሳህን ተቀምጧል አንግዶችም በሰልፍ የሚፈልጉትን ምግብና መጠጥ እያነሱ ይስተናገዱ ጀመር። የምሳ ስነስርአቱ እየተካሄደ እያለ ሙሽራውን ይዘው ሚዜየዎቹና አጃቢዎቹ ወደ ሙሽሪት ጉዞ ሄዱ።ሆታውና ጭፈራው እንደ ጉድ እየኖጋ ጉዞ ሙሽሪት ጋ። ሙሽሪት ጋር የነበረው ድግስ አጀብም ለጉድ ነው። የሁለት ኃብታሞች ሰርግ በመባል የተሰየመው የአቶ ሙሉሰውና የአቶ ሱራፌል ሰርግ በብዙ ክዋኔዎች የተሻለ ና የተመሰገነ አቅርቦትና ድግስ ነው። ከብዙ እልህ አስጨራሽ ጭፈራና ጥያቄ በኋላ ወደ ሙሽሪት ክፍል ሚዜዎቹና ሙሽራው ገቡ። የሙሽሪት ሚዜዎች በተራቸው ደግሞ ሙሽራተውን ሸፍነው በጭፈራ የወንዱን ሚዜዎችን አደከሟቸው። ትዕይንቱ ደስ የሚልና የባህልን ይዘት የተላበሰ በመሆኑ በሁለቱም ወገኖች ምንም አይነት ቅሬታ አይፈጥርም። የሴቷ ሚዜዎችም በባህል መሠረት ነው የሚያደርጉት ወንዶቹም የሚጋፉት በደስታ ነው። ባህልና ወግ ለአንዲት ሀገር ምሰሶዎችና መሠረቶች ናቸው። ባህል ሐይማኖት ወግ የሌላት ሀገር ሀገር አትመስልም። የራሷ መገለጫ ሊኖራት ይገባል።አሁን በርካታ የአለም ሀገራት የራሳቸው ወግና ባህል የላቸውም። ለረጅም አመታት በቅኝ ግዛት የተያዙ ሀገሮችም ቋንቋቸውም ባህላቸውም ወጋቸውም በቅኚ ገዥዎች ሀሳብና ተፅዕኖ ጠፍቶ የሌላ ሀገር ወግና ባህል ለምደው እናያቸዋለን።ይህ እንዳይሆን ትልቅ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግኖች አያትቻችን ይግባና እንዲህ ውብ በሆነ የባህል ትውፊት ትዳር ሲመሰረት ደግሞ በጥሩ ሁኔታ ያማረና ለየት ያለ ይሆናል።
በሽማግሌዎችና በቄሶቹ መሀል ቃለ መሀላ ፈፅመው ምሳ ከበሉ በኋላ ወደ ሙሽራው ቤት ተመለሱ። "በሀዘንም በደስታ ጊዜም አብረው ሊሆኑ ላይለያዩ ሚስቱን ሊያከብር ሊንከባከብ እርሷም ባሏን ልትንከባከብ ልታከብ እስከ እድሜ ማብቂያቸው ላይለያዩ በአጋቢ ቄሳቸው ፊት ተማምለው ባልና ሚስተነታቸውን አሳወጁ።ቤተዘመዱም ለሙሽሮቹ ደስታ ወገቡን ፈትሾ በውዝዋዜ አጅበው እንኳን ደስ ያላችሁ የሚል መልዕክት በጭብጫቦና በእልልታ አስተላልፈው ሙሽሮቹን ወደ ወንዱ ቤት ለመሸኘት አንድ ላይ ግልብጥ ብለው ከድንኳኑ ወጡ። ሙሽሮቹን እየዞሩ ሚዜዎቹ ከጨፈሩ በኋላ ለሙሽሮቹ ወደ ተዘጋጀችው ቅንጡ መኪና ሙሽሮቹን አስገብተው ከፊታቸው በፒካፕ ካሜራ ማኖቹ እየቀረፁ አጃቢዎቹ መኪኖችን በሰልፍ ይቀርፁ ጀመር።አጃቢዎቹ መኪናቸውን በንፋፊት ለጣጥፈው በጋራ እየጨፈሩ ጉዟቸውን ወደ ደጃች ውቤ ሰፈር አደረጉ። ከቦሌ የተነሳው ሰርገኝ በፍላሚንጎ መስቀል አደባባይ አድርጎ በጊዮን አልፎ አንባሳደርን በመተው የቸርቸልን መንገድ አቅንተው ወደ ውቤ በረሃ ገቡ። የወንዱ ሙሽራ ቤተሰቦችም ሙሽሮቹ እስኪመጡ አሰፍስፈው እየጠበቁ ነበርና የመምጣታቸውን የመኪና ጡርንባ ሲሰሙ ሁሉም ነገር ጀመረ። ደጂው የሰርግ ሙዚቃ ከፍቶ ይዘፍኑ ጀመር። ሰርግ ብዙ ሰዎች ባይወዱም ነገር ግን አንዳንድ ወላጆች የልጃቸውን ሰርግ ከማየት በላይ ለእነሱ ድል የለም። ተመርቀው ከሚያይዋቸውና በሌላ የስራ መስኮት ዝነኛ ሆነው ከሚረኩት በላይ በልጆቻቸው ሰርግ ይረካሉ ፍፁም ደስተኛ ይሆናሉ። ብዙ የተለፋበትን ድግስም ዘመድ አዝማድ የሩቅ እንግዳ ተጋብዞ ሲሄድ ወላጆች ደስ ይሰኛሉ።ቀዳማዊና ሐምራዊ በዚህ ውብ የአሰራረግ ስነስርዓት ተድረው ኤርስ በእርስ ተዛምደው ወላጆች ከወላጆች በልጆቻቸው ደስታ ተደስተው ሰርጉን ቋጩ። ልጆቻቸውንም እስከወዲያኛው በልጅ የታጀበ ደስታ እንዲሆንላቸው መርቀው ወደ ቤታቸው አስገብተዋቸው። በነ ቀዳማዊ ቤት የተዘጋጀላቸውን ግብዣ ተጋብዘው ተሳስቀው ተጨዋውተው ሙሽሮቹን ጥሩ ጫጉላ እንዲሆንላቸው በመመኘት ተሰናብተዋቸው ወጡ። ቀዳማዊና ሐምራዊ ቤተሰቦቻቸውን ሸኝተው ተቃቅፈው ሶፋው ላይ ተቀመጡ። "የኔ ፍቅር ይቺን ቀን በተስፋና በትዕግስት ለአመታት ስጠብቃት ነበር አሁን ይሄን ቀን በሕይወቴ መቼም አልረሳውም። ይሄው እድሜ ልኬን ደስተኛ ሆኜ እንድኖር ፈጣሪዬን አንተን የልቤን ንጉስ ሰጥቶ አንግሶኛልና ሁሌም የእሱ አመስጋኝ ሆኜ እኖራለሁ"አለችና አይኑን ሳም አደረገችው። እሱ ዝም ብሎ በፍቅር ይመለከታት ነበር ዝምታው በቃል የማይሰፈር አስተያየቱ በምን የማይገለፅ የፍቅር አተያይ ነበር።

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 13:10:40 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፳~ ( 220)
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
#ራስ አምባ
"እሱ ቅቤ ነው አንድ ጊዜ ተገፍቶ የወጣ"አለች አትጠገብ። የግንባሯ ቆዳ ተሸብሽቦ የፊት ፀጉሯ ውስጥ ተደብቋል። በንግግሯ ውስጥ ቁጭት ፀፀት እንደ ስምንት ወር ፅንስ ይገላበጣል። የተቆጠበ የተመጠነች ንግግር ነበረች። ሌላ አንድም ቃል አልተነፈሰችም። ከወትሮው ወጣ ያለ አነጋገር ነበር። ማለፊያ የእናቷ ቃል አጥንቷን ሰርስሮ ዘልቆት የገባው ይመስላል። "ምን ሆነሽ ነው እታተዬ እንደዚህ የምትይው?"አለች ማለፊያ የአትጠገብን ጉንጭ በእጆቿ እየዳበሰች። "እንዳይረፍድባችሁ ልጄ! እንደኔ የማትመልሱት ነገር እንዳይገጥማችሁ ፍጠኑ። እኔ ልጅ ሆኜ በማይሆን እልህ እናንተን እዚህ ገደል አብሬ አስገብቻችኋለሁ። እንግዲህ ለዚህ በደሌ በምድርም በሰማይም እቀጣበታለሁ። እናንተ ግን ጊዜ አላችሁ ንስሃ የምትገቡበት ኃጢያታችሁን በንስሃ የምታጥቡበት ጊዜው አሁን ነው። አሁን ቀዳማዊን እርሱት። እሱ እረስቶናል። የራሱን ቤተሰብም መስርቷል። ሊያገባ ነው። ሕይወቱ ውስጥ የለንም። እሱም እስከ ወዲያኛው ከበደላችን ጋሬ አስፈንጥሮናል። እውነት ምን ጊዜም እንደ ጉልጭማ ፍም እሳት ነች። የፈለገ ብታዳፍኗት እሳትነቷ እንደማይጠፋ ሁሉ እውነትም የፈለግነውን ያህል ብናዳፍናት አንድ ቀን ትወጣለች ግብረ መልሷም የከፋ ይሆናል። ስለዚህ አሁን ኤንደ እናትም በእድሜ እንደገፋ ሰውም የምመክራችሁ እስከዚህ እድሜያችሁ ድረስ ያሻችሁን ስታደርጉ ነበር። ከዚህ በኋላ ግን በተቻላችሁ መጠን ክፉ ላለመሆን ሞክሩ። ካልሆነ እንደ እኔ በደለኞች ሆናችሁ የሰይጣን መጫዎቻ ሆናችሁ ትኖራላችሁ። እዩ ውስጡ ንፁህ የሆነውን ልጅ እጣ ፈንታ ተመልከቱ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ። እኔና እናንተ ግን ያለንበትን አልነግራችሁም። በውል ጥሩ ምርት ከማያስገኝ አፈር ተቀምጠን አፈር እያነሳን ነው። ኑሯችን ሳይሻሻል እዛው ከአፈር ወደ አፈር ሆኗል። ልጆቼ አሁን የምናገራችሁ ነገር ምን አልባት አሁን አይገባችሁ ይሆናል። ምክንያቱም ገና ያልበረደ ወጣትነት ውስጣችሁ ላይ ነገር ግይ እናት ናችሁና ዘግይታችሁም ቢሆን ትረዱኛላችሁ። ግን ሲገባችሁ ምን ማድረግ እንዳለባችሁ ምክር ስትፈልጉ እኔን አታገኙኝም። ገመዜ ሳይቀድማችሁ ቅደሙት እያልኳችሁ ነው ስስቶቼ"አለች የአይኗ ጭራ ላይ የደረሰውን እምባዋን ወደ ውስጧ እየሳበች። ሁላቸውም የንዝ ቃል የሚሰሙ እስኪመስላቸው ድረስ የእናታቸውን ንግግር ሳያቋርጡ በጥሞና አዳመጧት።
"እሺ እታተዬ አታስቢ በሚገባ ተረድተንሻል ነገር ግን አሁን ያልገባኝ ነገር ለምንድነው እንደዚህ በድንገት እንደዚህ አይነት ንግግር የምትናገሪው?"አለች አድና። ወይዘሮ አትጠገብ የጣራውን ቡጥር እየተመለከተች "ጥሩ ጠይቀሻል ልጄ። እንዲህ የምላችሁ ከዚህ በኋላ ለወንድማችሁ የነበራችሁን አመለካከት መቀየር አለባችሁ። ከዚህ በኋላ ለእሱ መጥፎ መሆን የለባችሁም። እንደውም በተቃራኒው ይቅርታ ብትጠይቁትና እሱም ይቅር ብኋችሁ ትንሾ ጊዜም ቢሆን የወንድምና የእህት ጊዜ ብታሳልፉ ብዬ ነው። በጣም ይጠቅማችኋል። ደግሞ ደግ ነው በእርግጠኝነት ይቅር ይላችኋል። ይቅር የማይል የእግዚአብሔር ሰው አይደለም።እስኪ ተመልከቱት ሙሉቀንን እንኳ ቀዳማዊ ከመጣ በኋላ ነው ኑሯቸው የተለወጠው። ያቺ የማትረባ እናቱ እንኳ በእኔ ልጅ እርዳታ የገዛላትን ቀሚስ ለብስ ቤተርኪያን ላይ ስታገኘኝ እንዴት እንድት እንደምትሆንብኝ። ሙሉቀንስ በአንድ በሬ አልነበር እንዴ የሚኖረው መቀናጆ ገብቶ። አሁን ግን እንደምታዩት ማንም የሌላቸውን አይነቶች በሬዎች ገዝቶ ጥንድ ጥንድ በሬ አለው። ኧረ ምኑ ቅጡ "ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ማለፊያ አቋረጠቻትና "እና ሆን ብሎ እኛን ለማናደድ ብሎ እኮ ነው ይሄን ሁሉ ያደረገለት። እያ ደግሞ ይቅርታ ያደርግላችሀዠኋል ያልሺውን አልስማማበትም። ምክንያቱም መጥቶ ምን ምን አድርጎ እንደሄደና ምን እያሰበ እንደሆነ በደንብ እናውቃለን።በርግጥ እንደሱ የተማሪ ተንኮለኛ ላንሆን እንችላለን። ነገር ግን በጭራሽ እኛም ከእሱ የበለጥን ነን ሊሸውደን አይችልም"አለች እጇን እያወራጨች። ርብቃም "የማለፊያን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ እስማማበታለሁ። እታተይ በርግጥ አሁን ላይ በዚህ እድሜሽ ፍራቻሽን ነውና የመከርሽን ምክርሽን ሰምተነዋል ተረዴተሻልንም ግን ይቅር ተባባሉ የሚለው ሀሳብ ማዘናጊያ ነው። ቀዳማዊ ያን ሁሉ አድርገነው ረስቶት ይቅርታ ብሎን ጥሩ ወንድምና እህት እንሆናለን ብዬ አላስብም"አለች። "እኔ ግን የእታተይን ሀሳብ እደግፋለን። እየውላችሁማ በደንብ አስቡት።እታተይ እንደለትው ይቅርታ ብንጠይቀው ይቅር ሊለን ይችላል። ደግሞ ከተማ ነው ያደገው ይቅርታ ከተጠየቀ ሁሉንም ነው የሚረሳው። ነገ ጠዋት በብዙ ነገሮች መገናኘታችን አይቀርም። ልጆቻችንም ከእኛ ክፋትንና ቂምን መውረስ የለባቸውም። ለልጆቻን ይህንን መተው የለብንም። ከአሁኑ ካልቆረጥነው የችግሩ ሰንኮፍ እያደገ ይሄዳል። ደግሞም ይቅር ብለን ብንጠይቅ እኛ እንጅ ሸክማችን የሚቀል እሱ የምንም የሚለው ነገር አይኖርም"በማለት የእናቷን ሀሳብ ደገፍ ከጎኗ መሆንዋን አስመሰከረች። ኤርስበርስ ሲጨቃጨቁ ቆዩ። የነ ማለፊያ እና እርብቃ ቡድንበጭራሽ ይቅርታ አንጠይቀውም ብለው አሻፈረኝ ሲሁ። የነ አድና ቡድን ደግሞ ሁሉንም እንተወው በማለት ለሁለት ተከፈሉ። "በሉ አሁን አትጨቃጨቁብኝ። በቃ እንደፈለጋችሁ እርስ በርስ ተጣልታችሁ ደግሞ መሳቂያ እንዳትሆኑ።
"ፐ ከወለዱ አይቀር እንዲህ ነው እንጅ እነሙሉቀንን እኮ የአየር ትኬት የቆረጠላቸው ራሱ ነው። መቼም ትልቅ ሰርግ ቢሆን ነው መሬት አይንካችሁ ብሎ በአየር ያስወሰዳቸው"አለ አንድ የአካባቢው ነዋሪ "ልክ ብለሀል ጃል የሙሉቀንን ኑሮ እኮ በድንገት ነው ያሻሻለለት ሀሰማይ የመጣ ነው የሚመስለው። እንደዛ ለምኗን እየተንቆሻቆሸ እንዳላረሰ አሁን ግን ተጀንኗል"አለ ንቀት ባዘለ አነጋገር። "አንተው እሱ ከተሜ ከተሜ ሸቷል ተይየይ በኋበላማ ጭራሽ ጉዳችን ፈላ። ወጉ ሁሉ አየር ነው የሚሆነው።"አለ ሌላኛው የበግ ለምዱን እያስተካከለ። "አንተው የእሱን ጉራ ተወውና ግን ጥሩ ልይ ነው ድምጡ እኮ አይሰማም። እንደ ድህነቱ አይደለም ዝቅ ብሎ ነበር የሚሰራው። ፈጣሪ ያን ቆጥሮለት ነው አቦ እንዲህ አይነት ሲሳይ የሰጠው። ችግር የለም የሰራ ሰው እንኳ ያግኝ ቁጭ ብሎ ባቱን እያጠበ የሚውል ሞላጫ አይደል። ይጥራል ይለፋል። በያ ላይ ለእኩ ክፋት የለውም ደግ ነው። እንዲህ አይነት ሰው ደግሞ ማግኘቱ ደግነቱን ይጨምርለታል እንጅ አይቀንስበት።ምክንያቱም ማግኘትንም ማጣትንም በሚገባ ያውቀዋል"በማለት የሙሉቀንን ጥሩ ማግኘት ደገፈ። "ግን አንድ ቀንም አስበኸው ታውቃለህ ቀዳማዊ እንደይህ ይሆናል ብለህ?" "ኧረ በጭራሽ ጎድ እንደው አንዱ የከተማ ሰው ዱርዬ አርጎ ወያላ ይሆናል ነው እንጅ ብዬ ያሰብኩ እንደይህ ትልቅ ሰው ይሆናል ብዬ እንኳ በህልሜም አላሰብኩት እንኳን በውኔ" "አይ የጌታ ነገር እሱ እኮ ማንሳትም መጣልም ይችልበታል። እንደዛ መከራውን አይቶ እኛ ራሱ ይቺ ሴትዮ በእውነት ይሄን ልጅ ወልዳዋለች? ብለን እስክንጠይቅ ድረስ እንዳላሰብነው ከዛ ወጥቶ ይሄን ያህል ማረግ ሲያገኝ እኛስ እኛ ነን እንደ ው እነ ወይዘሮ አትጠገብ ምን ይሉ?" ብሎ በመገረም ጠየቀ።

@amba88
@ken_leboch
1.0K viewsTesfa Desalegn, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 07:33:26 " ኤሴቅ "
ክፍል ~፪፻፲፱~ ( 219 )
በአምባዬ ጌታነህ @adwa_1888
" መቸገር አልነበረባችሁም እኮ ሙሌ"አለ ቀዳማዊ። "ኧረ አይባልም። እዛ ብትዳር ጥሩ ነበር በደንብ እድርህ ነበር። ደግሞ አዝመራው ለጉድ ነበር የያዘው። ያመረትነው እህል ብዙ ነበር። ከምግቡ እስከ ሰላሱቱ ድረስ ተመርቶ ነበር።"አለና ሁለቱን አቁማዳ የነጭ ጤፍ ዱቄት ለወይዘሮ ሔዋን ሰጡ። ሌሎቹ ልጆች ደግሞ የጠላ ድፍድፉን ይዘው ተከተሉ። "እግዚኦ ይሄን ሁሉ ነገር ተሸክማችሁ?"አለችና ሔዋን ሙሉቀንናና ዳሳሽን ስማ በዝና እንደምታውቃቸው ነግራቸው ወደ ቤት አስገብታ አስቀመጠቻቸው። ቀዳማዊም አብሯቸው ተቀመጠ። ዳሳሽ ብድግ አለችና "እትዬ የሆነ በርሚል ነገር ይስጡኝ ጠላውን ልጥመቅ"አለች። "ኧረ ምነው ልጄ መጀመሪያ አረፍ በይ እንጅ አሁን አይደል ከመንገድ የመጣችሁት ትንሽማ አረፍ በሉ የሚጠጣም የሚበላም ቀማምሱ እስከዛው ተጫወቱ እኔ የሚበላ ይዤ ልምጣ ብላ ወጣች ቀዳማዊም ተከተላት "እንግዶቹን ትተኻቸው ለምን መጣህ?" "እነሱ እንግዳ አይደሉም ወንድሞቼ ናቸው ስለዚህ ለትንሽ ደቂቃ ብቻቸውን ብተዋቸው ምን ይሆናሉ ብለሽ ነው! እትዬዋ" "እሺ እንዳልክ በል ሳህንና ይሄን ይዘህ ሂድና አስይዛቸው እኔ ወጡን ይዤ እመጣለሁ" "እሺ "ብሎ ይዞ ወጣ
እነ ሙሉቀን ምግብ በልተው በደንብ ከተስተናገዱ በኋላ ወደ ስራ ለመግባት ተነሱ "ምን ልትሰሩ ነው የምትነሱት?"አለ ቀዳማዊ "እህ አዴጌር ያለበት ቤት ስራ ይጠፋዋል ብለህ ነው? የተገኘውን መስራቴ ነውይ ዳሳሽም ጠላውን ትጥመቅ ወንጠፍትና ገለገይት አምጥተሻል አይደል?"አለ ሙሉቀን ወደ ዳሳሽ ዘወር ብሎ "አዎ የከተሜ ሰው መቼም በቢራና በጠጅ ነው የሚያደርገው ጠላ ከጠመቁ ዝልሉን እንጅ ይሄን የገብሱን አያውቁትም ብዬ ሁሉንም ይዣለሁ። እኔ ምፈልገው ጋን ወይም በርሚል ብቻ ነው። እሱን እንዲያመጡልኝ ንገራቸው"አለች ለቀዳማዊ "እሺ እንግዲህ ካልሽ!" አለና ለሔዋን ዳሳሽ የምትፈልገውን እንድታቀርብላት ነግሯት ከነ መልካሙ ጋር ሻይ ቡና ለማለት ወደ ውጭ ወጡ።
"ቀዳማ እንደው ይቺ ሴትዮማ እናት ማለት አይደለች"አለ ሙሉቀን "ከእናትም ትበልጣለች ወንድሜ ሕይወቴን ምቹና ጣፋጭ ያደረገችልኝ ሴት ነች። ባለቤቷን ደግሞ ይበልጥ ብታየው ትገረማለህ?"አለ "ወትሮም እኮ እሚባለው እልፍ ሲሉት እልፍ ይገኛል ነው!"አለ መልካሙ(አቤል) "እውነት ነው። በእሱ እኔም አምናለሁ። ተመስገን በአንድ በኩል እንደዛ ባይሆኑብኝ ኑሮ ይሄን አለም አላየውም ነበር ብዬ አስባለሁ። እግዚአብሔር ሰዎችን የሚያስጨክነውም የሚያራራውም በምክንያት ነውና እኔ በበጎ ጎኑ አይቼዋለሁ"አለ ቀዳማዊ "ሙሽሪትን የሰርጉ ቀን ነው የምናያት ቀዳ?"አለ ሙሉቀን ወሬውንም ለመቀየር ያህል "አዎ እንግዲህ የእለቱ እለት ማየታችሁ ነው። ያውም ኤኮ መች ነው ምንተዋወቀው እያለችኝ ነበር። አሁን እንዳልደውልላት ከጓደኞቿ ጋር እየተዘገጃጀች ነው።" "ኧረ ችግር የለም ቀስ ብለን እንተዋወቃለን"አለ ሙሉቀን። "ለምንድነው ግን ዳግማዊን ያላመጣችሁት ሙሌ"አለ ቀዳማዊ "ልጅ ይዞ መንገድ ጥሩ አይደለም። በዛ ላይ አያቱ ልጄማ ከእኔ ጋር ነው ሚቆየው ብላ ከረሚላ እሰጥሀለሁ ስትለው እሺ ብሎ አልቀረም መሠለህ" "አይ ጥሩ አላደረጋችሁም ይዛችሁት መምጣት ነበረባችሁ ማርያምን"አለ ቀዳማዊ "ችግር የለም የሚመጣባቸው ገና ብዙ ጊዚያቶች አሉን ስለዚህ ብዙ ቅር አይበልህ
***
"ልጄ ደከምሽ እኮ። ደግሞ ብዙ ነው ያመጣችሁት"አለች ሔዋን ለዳሳሽ ከልቧ እያዘነች። "ኧረ ይቺማ ምን አላት እትዬ አውራጅማ ብዙ ነበር የሚያዝ"አለች ዳሳሽ እየተቅለሰለሰች "አይ ይሄን ሁሉ ይዛችሁ ጭራሽ ትንሽ ነው? አይ ከበቂ በላይ ነው። የሚያግዝሽ እንዳልጠራ ይሄን አጠማመቅ የምትችል ሴት ያለች አይመስለኝም" "ኧረ ችግር የለም ይሄው እየጨረስኩ ነው። ትንሽ ነው የቀረኝ"አለች ለማስተባበል ነገር ግን አንድ ሙሉ ማዳበሪያ ድፍድፍ ነበር የቀረው። ግን ጉሹን ቅመሺው እስኪ እትዬ መወፈሩንና መቅጠኑን"አለችና በመቀነሻ ቀንሳ ሰጠቻት። ጥጥት አድርጊው ገብስ ነው። ጌሾ ትንሽ ነው ያለው" ሔዋን ጠጣችው። በጣም ይጥማል ጭልጥ አድርጋ ጠጣችና እቃውን ሰጠቻት " በጣም ጥሩ ነው። ከዚህ በላይ መወፈርም መቅጠንም ያለበት አይመስለኝም"አለች ሔዋን አፏን እየጠራረገች። "እሺ "አለችና ዳሳሽ መጥመቋን ቀጠለች።
"እንዴት አይነት ግሩም የሆነ ጠላ ነው! እንዴት አድርጋ እንዳዘጋጀችው ብታይ"አለች ሔዋን ለሙሉሰው "እኔ ርኮ የወሎን ባህላዊ ጠላ በጣም ነው የምወድላቸው እስኪ ይዘሽልኝ ነይ ሔዋኔ "አለ ሙሉሰው። ሔዋንም ሂዳ አመጣችለት።
"ይሄ ሰርግ በቃ እንደፈለግሽው ሆነልሽ። ኧረ እንደውም ከፈለግሽው በላይ ነው የሆነው ከመጠጥም ብዙ አይነት ሆነልሽ "አለ ሙሉሰው "እንዴታ የመጀመሪያ ሰርጌ እኮ ነው። ለቀጣዮቹ ልጆቼ ልምድም ይሆነኛል። በል እንዲጨመርልህ ከፈለክ ንገረኝ ወይም ሄደህ በሀይላንድ አስቀድተህ ጠጣ" ብላው ወጣች። ሙሉሰው የኮረፌውን አይን እያዬ "እንዲህ ነው እንጅ ሴትነት የቱባው ባለሞያ ሲሆን ይጥማል"እያለ እያጣጣመ ሳለ "እስኪ አባዬ እኔም ልጠጣ ስጠኝ"አለች ኤሊያና "አይሆንም ትሰክሪያለሽ "አለች ሔመን ድንገት ከመኝታ ቤቷ ብቅ ስትል ኤሊያና ከአባቷ ልትቀበል የነበረውን ኮረፌ በመመልከት "ሔሚዬ ይሄ እኮ አያሰክርም ቡቅሬ በይው ንፁህ ገብስ ነው። እና ማርማር ነው የሚለው ከፈለግሽ አንቺም ልትጠጪ ትችያለሽ"አለ። "እሺ አባዬ በርግጥ ከአንተ በላይ ለኤሊ አስቤ ሳይሆን እንዲሁ ከአፌ ስለመጣ ነው ይቅርታ"አለች ሔመን ሀዘኔታ በተሞላ አነጋገር። "ችግር የለም የኔ ማር እኔም የምፈልገው ይሄን ያህል ለእህትሽ እንድትጠነቀቂላትና እንድታስቢላት ነው። እናንተ እርስ በእርስ ስትዋደዱና ሰትተሳሰቡ ሁሉም ነገር ቀናና የተደላደለ ይሆናል። እርስበርስ መጠባበቅ አለባችሁ አንዳችሁ ለአንዳችሁ ምርኩዝ ነው መሆን ያለባችሁ። መቼም እኛ ለዘላለም አብረናችሁ አንኖርም"አለና ሙሉሰው ሁለቱንም አቅፎ ሳማቸው

@amba88
@ken_leboch
1.1K viewsTesfa Desalegn, 04:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ