Get Mystery Box with random crypto!

#Tigray የመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአፋጣኝ ስራ እንዲጀምር ለማድረግ እንደሚሰራ የኢፌዴሪ ኢን | ልዩ መረጃ ®

#Tigray

የመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአፋጣኝ ስራ እንዲጀምር ለማድረግ እንደሚሰራ የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ አመራሮች ማረጋገጫ ሰጡ።

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አመራሮች ዛሬ በትግራይ ክልል ጉብኝት አድርገዋል።

አመራሮቹ ጉብኝት ያደረጉት በመዲናዋ መቐለ እና አካባቢው ሲሆን #ዓላማው ፦ በጦርነት ምክንያት በአምራች ዘርፎች ላይ የደረሰውን ውድመት ማእከል ያደረገ እቅድ ለማዘጋጀት እና በፍጥነት ስራ የሚጀምሩበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሆነ ተነግሯል።

ሚኒስቴሩ ፤ ጉብኝቱ ውድመት የደረሰባቸው እና በግብአት አቅርቦት እጥረት ስራ ያቆሙ አምራች ተቋማትን ስራ ለማስጀመር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጿል።

በዚሁ ጉብኝት በመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስፈላጊ የግብአት አቅርቦት እንደሚሟሉ እና በአፋጣኝ ስራ እንደሚጀምር አመራሮቹ ማረጋገጫ መስጠታቸው ተነግሯል።

በተመሳሳይ አመራሮቹ በውቅሮ ከተማ የሚገኙ ሸባ ሌዘር ኢንዱስትሪ እና ሰማያታ እምነ በረድ ፋብሪካ የደረሰውን ውድመት በአካል ተገኝተው መመልከታቸውንና ውድመቱ እንዳሳዘናቸው ድምፂ ወያነ ዘግቧል።

Photo Demtsi Woyane