Get Mystery Box with random crypto!

ልዩ መረጃ ®

የቴሌግራም ቻናል አርማ leyumerga — ልዩ መረጃ ®
የቴሌግራም ቻናል አርማ leyumerga — ልዩ መረጃ ®
የሰርጥ አድራሻ: @leyumerga
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 50.90K
የሰርጥ መግለጫ

#ልዩ_መረጃ  |  #ቀዳሚ_ምርጫዎ
➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ
➠ወቅታዊ መረጃዎች
➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዜናዎች
➠ጠቃሚ ጥቆማዎች ይደርሶታል።
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን።
         PROMOTION
➥   
🎬  "ተመራጭ የዜና ምንጭ"
News & Media Channel®

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2023-01-12 23:06:57
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መቼ ይገለፃል ?

በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሁለት ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ የሚደረግበትን ቀን እየጠየቁ ይገኛሉ።

የፈተናው ውጤት መዘግየቱን የሚገልፁት ተማሪዎች እና ወላጆች ትምህርት ሚኒስቴር ውጤቱ መቼ ይፋ እንደሚደረግ እንዲያሳውቅ ጠይቀዋል።

" የትምህርት ዓመቱ እየገፋ ነው ፤ ገና ከውጤት በኃላ ምደባ አለ ፤ ልጆቻችን ከመደበኛ ትምህርት ርቀው ቤት ከሆኑ በርካታ ሳምንታት አልፈዋል ፤ የሁሉም ውጤት ከ2ኛ ዙር ተፈታኞች ጋር ይገለፃል ቢባልም ዛሬም ድረስ ቀኑ መቼ እንደሆነ አይታወቅም ፤ የተማሪዎችን የትምህርት ዓመት ታሳቢ በማድረግ ቀኑ ቢገለፅ " ሲሉ ወላጆች መልዕክታቸውን ልከዋል።

መልዕክት የላኩልን አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር ፤ ምንም እንኳን ቁርጥ ያለው የውጤት መግለጫ ቀን ባይታወቅም ነገር ግን ከጥር 15 ጀምሮ ባሉት ቀናት ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ930 ሺ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው መገለፁ የሚዘነጋ አይደለም።
@leyumerga
6.1K viewsedited  20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 21:12:05 እናት ባንክ አዲስ የስራ ማስታወቂያ በ0 አመት እና በልምድ


Enat Bank S.C invites fresh Graduates and qualified applicants for the following vacant position.

Position 1: Junior Customer Service Specialist
Position 2: Customer Service Specialist
Position 3: Senior Customer Service Specialist
Position 4: Branch Accounts Administrator Grade B
Position 5:Branch Manager Grade C
Position 6: Legal Aid
Position 7: Credit Workout Officer
Position 8: Senior Marketing & Communications Officer

Professions: Accounting, Accounting & Finance, Banking & Finance, Economics, Business Administration, Management, Sales, Marketing, Economics, Law, and any other related fields

How to apply
https://abyssinajob24.com/enat-bank-2023
5.7K viewsedited  18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 14:31:26
ኤሎን መስክ በዓለም ታሪክ ከፍተኛው ኪሳራ የደረሰበት ግለሰብ ሆነ

ኤሎን መስክ በአጭር ጊዜ ውስጥ በግል ሀብቱ ላይ በታሪክ ከፍተኛው ኪሳራ የደረሰበት ግለሰብ በመሆን የዓለምን ክብረወሰን መስበሩ ተነገረ።

የዓለም ክብረ ወሰኖችን የሚመዘግበው ‘ጊነስ ዎርልድ ረከርድስ’ በድረገጹ ላይ እንዳሰፈረው መስክ በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 165 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ሀብት በኪሳራ አጥቷል።  

ይህ የኪሳራ አሃዝ የተገኘው ፎርብስ የተባለው መጽሔት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት ሲሆን፣ ጊነስ እና ሌሎች ምንጮች እንደሚሉት ግን መስክ የገጠመው ኪሳራ ከዚህም ከፍ ሊል ይችላል።

መስክ በተጠናቀቀው የፈረንጆች ዓመት ላይ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኩን ትዊተርን መግዛቱን ተከትሎ የኤሌክትሪክ መኪና አምራች ኩባንያው የቴስላ የአክሲዮን ዋጋ ወድቋል። በዚህም ነው ከፍተኛው ኪሳራ የተመዘገበው።

መስክ 44 ቢሊዮን ዶላር በመክፈል ትዊተርን ሲገዛ በዘመናዊው መኪና አምራች ድርጅቱ ቴስላ ውስጥ ያሉ ባለድርሻዎች፣ መስክ ለኩባንያው የሚያስፈልገውን ትኩረት አይሰጠውም የሚል ስጋት ፈጥሯል። ይህም የቴስላ የአክስዮን ዋጋው ላይ ኪሳራ እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል።
5.6K views11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 10:59:16 ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፖ ማስታወቂያ በ0 አመት

Trainee Marketing Officer
#midroc_investment_group
#business
#Bishoftu
BA Degree in Marketing, Business Administration, Economics, or related fields
Position tasks:
- Contribute to the implementation of marketing strategies. Supporting the marketing manager in overseeing the department's operations.
- Organize and attend marketing activities or events to raise brand awareness.
Quanitity Required: 1
Minimum Years Of Experience: #0_years

Trainee Machine Operator
#midroc_investment_group
#manufacturing
#Bishoftu
TVET Level 3 or 4 in General Mechanic, Electrical Technology, Industrial Machine Drive, Electrical Instrumentation, or related fields
Position tasks:
- Responsible for ensuring the machine produces high-quality products, runs smoothly and at capacity, and is properly maintained.
Quanitity Required: 1
Minimum Years Of Experience: #0_years

Trainee Electrician
#midroc_investment_group
#engineering
#Bishoftu
BSc Degree in Electrical engineering, Electricity, Industrial electricity, Power instrumentation, Electronics, or related fields
Position tasks:
- Install and repair electrical wiring, systems, and fixtures in buildings.
- Install circuit breakers and other electrical hardware and connects wiring to them.
Quanitity Required: 1
Minimum Years Of Experience: #0_years

Trainee Mechanic
#midroc_investment_group
#engineering
#Bishoftu
BSc Degree in Mechanical Engineer, General Mechanic, Auto Mechanic, or related fields with similar work experience
Position tasks:
- Inspecting the vehicle's mechanical components and engine, diagnosing problems with vehicles, and performing maintenance and repair work on cars, trucks, and other vehicles.
Quanitity Required: 1
Minimum Years Of Experience: #0_years
Deadline: January 16, 2023

How To Apply:
Send your Curriculum Vitae only via email:unlimitedPhrm@midrocinvestmentgroup.com or unlimitedbishoftu@gmail.com For further information contact Tel.0114371267
@leyumerga
5.3K viewsedited  07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 08:48:19
የዓለም ባንክ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክትን በፋይናንስ ለመደገፍ ግምገማ እያደረገ ነው

በሙከራ ደረጃ በአዲስ አበባና በተወሰኑ የክልል ከተሞች የተጀመረውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ወደ ሙሉ ትግበራ ለማስገባት የሚያስችለውን ፋይናንስ ለመደገፍ፣ የዓለም ባንክ ሒደቱን እየገመገመ እንደሚገኝ ታወቀ፡፡

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ዜጎች፣ በተለይም ሁሉን አካታችና ተዓማኒ አገልግሎቶችን በሥርዓት ለመስጠት ያስችላል ተብሎ ወደ ሥራ የገባውን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ  አገልግሎትን የገንዘብ ድጋፍ ለመልቀቅ፣ የተቋሙን የቦርድ ውሳኔ እየተጠባበቀ እንደሚገኝ ተሰምቷል፡፡

በገንዘብ ሚኒስቴርና በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ሥር በባለቤትነት የሚመራውን ይህንን ፕሮጀክት፣ የዓለም ባንክን ጨምሮ ሌሎች የፋይናንስ ምንጮች እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር ፈሰስ ሊያደርጉበት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ እየተጤነ እንደሚገኝ የዓለም ባንክ መረጃ ያሳያል
5.2K views05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 15:53:34
Vacancy for fresh graduate Ethiopian Electric power

Jobs Requirement

Education Qualification:1st degree in Geology or related field from a recognized with zero years of experience

Experience: not request / 0-year

salary: 8,417.00 birr

Quantity: Three (3

Location: Koisha Water Power Project Site

Year of graduate from 2012 up to now

How to apply?

Interested applicants should submit their CVs as prescribed in the employment notification. Along with supporting documents (educational) in person in Mexico City, Keker Building Electric Power Head Office.
5.9K views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 15:08:12
ቻይና ለኢትዮጵያ የዕዳ ስረዛ ለማድረግ ስምምነት ፈረመች

ከተሾሙ ገና አንደኛ ወራቸውን ያስቆጠሩት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የመጀመሪያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸውን በኢትዮጵያ በማድረግ፣ ከኢትዮጵያ አቻቸው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር የዕዳ ስረዛን ጨምሮ የተለያዩ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ተፈራረሙ።

ከአቶ ደመቀ መኮንን ጋር ከተወያዩ በኋላም ኢትዮጵያ ከቻይና ከተበደረችው ውስጥ የተወሰነውን ዕዳ ለመሰረዝ የሚያስችል ስምምነት በሁለቱ ሚኒስትሮች መካከል እንደተፈረመ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

ይሁን እንጂ በዕዳ ስረዛ ስምምነቱ ቻይና ምን ያህል የዕዳ ስረዛ እንደምታደረግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቢሮ ያለው ነገር የለም። 

ኢትዮጵያ ባለፉት አስርና ከዚያ በላይ ዓመታት ከቻይና መንግሥት ተበድራ ያልከፈለችው ከ14 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዕዳ እንዳለባት የሚታወቅ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያ ካለባት አጠቃላይ 27.9 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ውስጥ ወደ ግማሽ የሚጠጋ ነው። 
@leyumerga

ethiopianreporter
5.2K viewsedited  12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 11:48:58
ነዳጅ

ወደ ትግራይ ክልል #ነዳጅ መግባት መጀመሩን የክልሉ የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ፤ ወደ መቐለ 10 ቦቴ ነዳጅ መግባቱን ያመለከተ ሲሆን ወደ ኩዊኃ እና ዓጉላም ነዳጅ መግባት መጀመሩን ጠቁሟል።

ከፌዴራል መንግስት ጋር ጥሩ ትብብር እየተደረገ ነው ያለው ቢሮ " እናተ ጋር ካለው ችግር አንፃር ቅድሚያ እንሰጣለን " ተብለናል ሲል ገልጿል።

ጦርነት ለመፈጠሩ በፊት በወር 12 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ ይገባ እንደነበር የገለፀው ቢሮው አሁን እየገባ ያለው ነዳጅ ከሚፈለገው አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው ብሏል።

መቐለ ውስጥ ካሉት 15 ማደያዎች ነዳጅ የገባው በ4ቱ ላይ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል።

ነዳጅ ለማግኘት እነማን ቅድሚያ አላቸው ?

አሁን እየገባ ያለው ነዳጅ በተወሰነ መልኩ ስለሆነ ፦

- አምቡላንስ
- እሳት አደጋ
- ውሃ አቅራቢ ቦቴዎች
- የመንግስት ተሽከርካሪዎች
- የእርዳታ አከፋፋይ አካላት
- ባንክ፣ ቴሌ፣ መብራት ኃይል
- በትራንስፖርት ቢሮ ታሪፍ የወጣላቸው ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ቅድሚያ እንደሚያገኙ ተመላክቷል።

የፋይናንስ እጥረት በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እንዳይገባ እንቅፋት መሆኑን ያሳወቀው ቢሮው ችግሩን ለማፍታት ከባንክ ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

ቤንዚን እና ናፍጣ ስንት እየተሸጠ ነው ?

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከፌዴራል መንግስት ለክልሉ እንደተላከ ለመረዳት ተችሏል።

በመቐለ #ቤንዚን በሊትር 60 ብር ከ57 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን #ናፍጣ 66 ብር ከ58 ሳንቲም እየተሸጠ መሆኑን ከክልሉ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

Photo Credit : Tigrai Television

@leyumerga
5.3K viewsedited  08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 11:10:29
የፌዴራል መንግስት በስምምነቱ መሰረት ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ከህወሓት መረከብ ጀመረ

በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት አመራሮች መካከል በደቡብ አፍሪካ እና በኬኒያ የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ በትናንትናው ዕለት የመጀመሪያ ዙር ከባድ መሳሪያ ርክክብ ተደርጓል።

ርክክቡ ከመቐለ ከተማ 36 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አጉላ ካምፕ የተከናወነ ሲሆን፤ በርክክቡ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ ታዛቢዎችም ተገኝተዋል።

በቀጠናው የተሰማራው ሠራዊት አመራር ሌተናል ኮሎኔል አለሜ ታደለ በመንግሠታችንና በህወሓት አመራሮች መካከል በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት የተለያዩ ዓይነት ከባድ መሳሪያዎችን መረከባቸውን ገልፀዋል።

ህወሓት ለመከላከያ ሠራዊታችን ያስረከባቸው የመሳሪያ ዓይነቶችም ብረት ለበስ ታንኮች፣ የተለያዩ ሚሊ ሜትር መድፎች፣ ሮኬቶች፣ ዙዎች፣ ሞርታሮች እና ፐምፐን ያጠቃለለ መሆኑን ሌተናል ኮሎኔል አለሜ ታደለ ተናግረዋል።

የርክክብ ሥነ-ሥርዓቱን ለመታዘብ የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ አረካካቢ ኮሚቴዎች የተገኙ ሲሆን፤ ከአረካካቢዎች መካከል ብርጋዴር ጄነራል አድዋ ልቡካን ፒተር በሁለቱም ወገኖች በኩል እየተደረገ ያለው የከባድ መሳሪያ ርክክብ የተጀመረውን የሰላም ጉዞ የሚያጠናክር መሆኑን ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰው ሰላምን የማስፈን ተግባር ዓለምን የሚስደንቅ መሆኑን ጠቅሰው ለመላው ህዝብና ስምምነቱን ተግባራዊ እያደረጉ ላሉ አካላት ምስጋና ማቅረባቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@leyumerga
@leyumerga
5.2K viewsedited  08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ