Get Mystery Box with random crypto!

LEYU NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ leyu_news — LEYU NEWS L
የቴሌግራም ቻናል አርማ leyu_news — LEYU NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @leyu_news
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 527
የሰርጥ መግለጫ

#ልዩ_መረጃ  |  #ቀዳሚ_ምርጫዎ
➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ
➠ወቅታዊ መረጃዎች
➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዜናዎች
➠ጠቃሚ ጥቆማዎች ይደርሶታል።
አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን።
         PROMOTION
➥   
🎬  "ተመራጭ የዜና ምንጭ"
News & Media Channel®

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-28 12:42:44 በናይሮቢ በታገተው ኢትዮጲያዊ ዙሪያ ለኬኒያ መንግስት ሁለት ጊዜ ደብዳቤ ፅፈናል ሲሉ አምባሳደር መለሰ ተናገሩ

የኬኒያ መንግስት ለደብዳቤው ስለሰጠው ምላሽ ግን አምባሳደሩ የሰጡት ማብራሪያ የለም


በኬኒያ ናይሮቢ ማንነታቸው ባልታወቁና የደንብ ልብስ በለበሱ አምስት ግለሰቦች የታገተው ኢትዮጲያዊ ሳምሶን ተክለሚካኤል ያለበት ሳይታወቅ አንድ ዓመት ከስድስት ወራት አስቆጥሯል። ይህንኑ ተከትሎ የኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የኬንያ ኤምባሲ ላይ ክስ መመሥረታቸውን የታጋች ባለቤትና ጠበቃቸው ማስታወቃቸው ይታወሳል።

የአቶ ሳምሶን ባለቤት ወ/ሮ ሚለን ሐለፎም፣ አቶ ሳምሶን በኬንያ ፖሊሶች ታፍነው ከተወሰዱ አንድ ዓመት ከስድስት ወራት ቢሆናቸውም፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ስለጉዳዩ ምርመራ እያደረጉ መሆናቸውን ከመግለጽ ባሻገር፣ ያሉበትን ሁኔታ ለማሳወቅ እየተንቀሳቀሱ ያለበት ሁኔታ ቸልተኝነት ታይቶበታል ማለታቸው አይዘነጋም።

ይህንኑ ተከትሎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለቀረበበት ቅሬታ ምን ምላሽ አለው በሚል ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦለታል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃለአቀባይ አምባሰደር መለስ አለም ጉዳዩ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱንና አሁንም እያደረገ መሆኑን በማንሳት ለኬኒያ መንግስት ሁለት ጊዜ ደብዳቤ ጽፈናል ማለታቸውን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።የኬኒያ መንግስት ለደብዳቤው ስለ ሰጠው ምላሽ ግን አምባሳደር መለሰ አለም ከመግለፅ ተቆጥበዋል።

በፌዴራል መንግሥትና በኦሮሚያ ክልል በማንኛውም ፍርድ ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ የሆኑት ጠበቃ ዳባ ጩፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ‹‹ደንበኛዬ በኬንያ በደረሰባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከአንድ ዓመት በላይ ያለበት አይታወቅም፤›› ብለው፣ መታሰራቸው ወይም መሞታቸው አለመነገሩ አሳሳቢ እንደሆነ መግለፃቸውን ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል።
‹‹ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመጣበት ምክንያት እነዚህ የተከሰሱ አካላት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው ነው፡፡ ፍርድ ቤት በሕግ አግባብ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማስገደድ የሚችል በመሆኑ እንደሚያስገድዳቸው እንጠብቃለን፤›› ሲሉም ጠበቃው ተናግረዋል፡፡
ዳጉ ጆርናል

@Leyu_News
@Leyu_News
3.9K views09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 12:42:09
3.5K views09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 11:32:26
በጋሞ እና በጎፋ ዞኖች በተዛመተው ኮሌራ ሰዎች እየሞቱና በብዛት እየታመሙ ናቸው!

በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በተከሠተው የኮሌራ ወረርሽኝ፣ ስምንት ሰዎች መሞታቸውን የዞኑ ጤና መምሪያ ሲያስታውቅ፣ በጋሞ እና በጎፋ ዞኖች፣ እስከ ትላንት ድረስ በጥቅሉ ከ430 በላይ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን፣ የየዞኖቹ ባለሥልጣናትና ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።

የፌዴራል እና የክልል መንግሥታት፣ እንዲሁም መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች፣ ድጋፍ እያደረጉ ቢኾንም፣ የመድኃኒት እና የሕክምና ቁሳቁሶች እጥረት መኖሩን አመልክተዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(OCHA)፣ ሰሞኑን በአወጣው ሪፖርት፣ እ.አ.አ. ካለፈው ዓመት ነሐሴ ወር አንሥቶ፣ የደቡብ ክልልን ጨምሮ በሌሎች ክልሎችም በተከሠተው ወረርሽኝ፣ ከአራት ሺሕ በላይ ሰዎች መያዛቸውንና 71 ሰዎች መሞታቸውን አስታውቋል።

[VoA]

@Leyu_News
@Leyu_News
3.8K views08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 09:00:39 አብን

አብን በአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈጸመው ግድያ "የአገሪቱን ሰላምና መረጋጋት አደጋ ላይ የሚጥል የዜሮ ድምር ፖለቲካዊ ሽብር ውጤት" መኾኑን ገልጧል።

አብን ቀደም ሲል በክልሉ አመራሮች ላይ የተፈጸመው የግድያ ወንጀል "ተሸፋፍኖ መቅረቱና ተጠያቂነት አለመስፈኑ"፣ አኹንም የአመራሮች ግድያ "ተባብሶ እንዲቀጥል" ምክንያት መኾኑን አምናለኹ ብሏል።

አብን ግድያው ሳይጣራና የገዳዮች ማንነት ሳይታወቅ፣ ከድርጊቱ "ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት ሲባል በአደባባይ የሚደርጉ ፍረጃዎችንና መግለጫዎችን" እንደሚያወግዝም ገልጧል።

የግድያው ፈጻሚዎች ማንነት እንዲጣራና ተጠያቂዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ አብን ጨምሮ ጠይቋል።

@Leyu_News
@Leyu_News
4.3K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 08:17:55
ሰበር..!

ትላንት ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ የኛ ባስ በአሮምያ ክልል መተሀራ አካባቢ ሙሉ ሰው እንደያዘ በኦነግ ታግቶ ተወሰደ።

ምንጭ ፡ ዘሐበሻ

@Leyu_News
@Leyu_News
4.4K views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 20:26:54
እስካሁን የአምስት ሰዎች ሕይወት አልፏል!

የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በአቶ ግርማ የሺጥላ እና በግል ጥበቃዎቻቸው በተፈፀመ ጥቃት እስካሁን የአምስት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡

ጥቃቱ የተፈፀመው ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየመጡ በነበረበት ሰዓት መንዝ ጓሳ መሆኑን ለማረጋገጠት ችለናል።

@Leyu_News
@Leyu_News
4.9K views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 20:14:50
ሰበር ዜና

አቶ ግርማ የሺጥላ ላይ በተቃጣው ጥቃት ከእርሳቸዉ ጋር ሌሎች 4 ሰዎችም ህይወታቸውን አጥተዋል

ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረብርሃን በመጓዝ ላይ ሳሉ ጥቃቱ መፈጸሙን የክልሉ መንግስት አስታዉቋል


በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በተከበሩ አቶ ግርማ የሺጥላ፣ በግል ጥበቃዎቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ላይ የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በአካባቢው ላይ ሠርተው ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየመጡ በነበረበት ሰዓት መንዝ ጓሳ ላይ በታጠቁ ኢ-መደበኛ ኃይሎች ጥቃት ተፈጽሟል፡፡

በዚህም አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ እስካሁን በደረሰን መረጃ የአምስት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ በደረሰው ልብ ሰባሪ ጥቃት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰማውን መሪር ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል፡፡

እንዲህ አይነት አጥፊዎች እያደረሱት ያለው መረን የለቀቀ የሽብር ድርጊት ክልሉን እየመራ ያለውን መንግሥትና መላውን ሕዝብ የበለጠ ሊያጠናክር እንጂ በጥፋት ሃይሎች ሴራና ፍላጎት የሚሳካ ምንም አይነት ተልዕኮ የለም፡፡

ስለሆነም ይህንን የሽብር ሥራ እየሠሩ ያሉ እንዲህ አይነት ኃይሎች ላይ የክልሉ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል፡፡ የጥቃቱን አድራሾችም ለሕግ ያቀርባል፡፡ ማንኛውም በእንደዚህ አይነት ድርጊት የተሳተፉ ኀይሎችንንና ተባባሪዎችን ሁሉ ከያሉበት ለሕግ በማቅረብ አስፈላጊው ፍትሕ እዲረጋገጥ ይደረጋል ሲል የክልሉ መንግስት አስታውቋል።

@Leyu_News
@Leyu_News
5.0K viewsedited  17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 16:14:09 መረጃ

ለሦስተኛ ቀን በቀጠለው የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ልዩነታቸውን በሰላም ለመቋጨት በሚያደርጉት ውይይት ኬንያ እና ኖርዌይ በዋነኛ የአሸማጋይነት ሚና እየተጫወቱ እንደሆነ ተጠቆመ። ቢቢሲ ለድርድሩ ቅርበት ካላቸው ምንጮች እንደሰማው የፌደራሉ መንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በታንዛኒያ ራስ ገዝ አስተዳደር በሆነችው ዛንዚባር እያደረጉት ባለው ውይይት የኬንያ እና የኖርዌይ አሸማጋዮች በስፍራው ተገኝተዋል።

@Leyu_News
@Leyu_News
4.9K views13:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 13:17:57 በታይላንድ ገንዘብ ያበደሯትንና ፍቅረኛዋን ጨምሮ 12 ጓደኞቿን መርዛ የገደለችዉ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች

የታይላንድ ፖሊስ 12 ጓደኞቿን በሲአናይድ መርዝ ገድላለች የተባለችውን ሴት በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታዉቋል፡፡ሳራራት ራንጊሱታፖርን የተባለችዉ ተከሳሽ በባንኮክ ከተማ የተያዘች ሲሆን የቅርብ ጓደኛዋ ሞት ጥያቄ ማስነሳቱ በቁጥጥር ስር እንድትዉል ምክንያት ሆኗል።በዚሁ ወር መጀመሪያ ላይ ከሳራራት ጋር በጉዞ ላይ እያለች ህይወቷ ማለፉ በተጎጂ ቤተሰቦች ላይ ጥርጣሬ አድሮባቸው ነበር።ፖሊስ ሳራራት የቀድሞ የወንድ ጓደኛዋን ጨምሮ ሌሎች 11 ሰዎችን እንደገደለች ይፋ አድርጓል፡፡ፖሊስ ድርጊቱን የፈጸመችዉ በገንዘብ ምክንያት መሆኑን ገልጿል፡፡ ሳራራት የቀረበባት ክሶች በሙሉ ግን ውድቅ አድርጋለች። የታይላንድ ፍርድ ቤት ግን የዋስትና መብቷን ዉድቅ አድርጓል፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት ከጓደኛዋ ጋር ከባንኮክ በስተ ምዕራብ ወደምትገኘው ራትቻቡሪ ግዛት በማቅናት የቡድሂስት ሀይማኖት ስነስርዓት በማቅናት ተሳትፈዉ ነበር ሲል ፖሊስ ተናግሯል።ብዙም ሳይቆይ ጓደኛዋ በወንዙ ዳርቻ ህይወቷ አልፎ ተገኘች፡፡የአስከሬን ምርመራ ሲደረግ በሰውነቷ ውስጥ የሳያንይድ መርዝ መገኘቱን ፖሊስ ተናግሯል። ወድቃ በተገኘችበት ወቅት ስልኳ፣ ገንዘብ እና ቦርሳዋ ጠፍቷል።

ሌሎች ተጎጂ ናቸው የተባሉት ሰዎች በተመሳሳይ ሁኔታ መሞታቸውን የገለጹት ባለስልጣናት፣ ተጨማሪ መረጃ ግን አልገለጹም። ግድያውን ሳራራት በ2020 መጀመሯን ተናግረዋል።ከሟቾቹ መካከል የሳራራት የቀድሞ ፍቅረኛዋ እና ሁለት ሴት የፖሊስ መኮንኖችን አሉበት፡፡

ፖሊስ በዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሰዉ ሳራራት ከአንዲት ሴት ጓደኛዋ 250,000 ባህት ወይም 7,300 ዶላር ትበደራለች፡፡ታዲያ ጓደኛማቾቹ አብረዉ ምሳ ከበሉ በኋላ ግን አበዳሪዋ ራሷን ስታ ትወድቃለች፡፡ግን በህይወት ትተርፋለች የዚህችዉ ወጣት ቤተሰቦች ወድቃ በነበረ ጊዜ ጌጣጌጥ እና ገንዘብ መጥፋቱን ተናግረዋል ሲል ፖሊስ ለምርመራዉ ዱካ ሆኖታል፡፡ነገር ግን የጓደኛዋ ቤተሰቦቿ ሳራራት እንዲህ አድርጋለች ብለዉ ፈጽመዉ አልጠረጠሩም ነበር ያሉት የፖሊስ መኮንኖቹ፣ ይህንን ማስረጃ መሰብሰብ ፈታኝ እንደነበረበት ገልጿል፡፡አንዳንድ አስክሬኖች ተቃጥለዋል ሲል ፖሊስ ተናግሯል።

ሲአናይድ የተሰኘዉ መርዝ በከፍተኛ መጠን ጥቅም ላይ ከዋለ ከአስክሬን ላይ ሊታወቅ ይችላልለ፡፡መርዙ የልብ ድካም ሊያስከትል የሚችልና የሰውነት ኦክሲጅን ከሴሎች ላይ በመዉሰድ የመግደል አቅም አለዉ፡፡በታይላንድ ከፍተኛ ቁጥጥር የሚደረግበት ሲአናይድ ያለ አግባብ ይዞ የተገኘ ሰዉ የሁለት ዓመት እስራት ይጠብቃቸዋል።

ዳጉ_ጆርናል
@Leyu_News
@Leyu_News
5.0K views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 13:17:35
4.3K views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ