Get Mystery Box with random crypto!

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomerejaa — 💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomerejaa — 💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️
የሰርጥ አድራሻ: @ethiomerejaa
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.98K
የሰርጥ መግለጫ

24 Hour News

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-02-02 22:48:02
1.0K views19:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 22:47:56 ኢትዮ ቴሌኮም ግብርን በቴሌ ብር ለመክፈል የሚያስችል አሰራርን ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም ገንዘብን በቀላል ፣ፈጣን ፣ ምቹ እና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ግብርን በቴሌ ብር ለመክፈል የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በዛሬው እለት ተፈራርሟል ።ደንበኞች ግብርን መክፈል የሚችሉበት የተለያየ መተግበሪያዎች መኖራቸው ተጠቁሟል።

ከነዚህም ውስጥ የቴሌ ብር የደንበኛ መተግበሪያ፣ የደንበኞች መተግበሪያን፣ እንዲሁም *127# በመጠቀም የብሄራዊ ባንክ ህግን በማክበር ግብርን መክፈል እንደሚቻል ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ።ግብር ከፋዮች ኢ ታክስ ሲስተምን መጠቀም የሚችሉበት አሰራር ሲሆን የአጋርነት ስምምነቱ ለገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ግብርን እና የግል ሰራተኞች የጡረታ መዋጮ ፣ የፌደራል ታክስ ክፍያዎችን በወቅቱ ለመሰብሰብ እና ለማሳለጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገልጿል ።

ቴሌ ብር አገልግሎት እስካሁን 28.2 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን ፣112 ዋና ወኪሎች ፣ ከ98 ሺህ በላይ ወኪሎችን እና ከ25 ሺህ በላይ ነጋዴዎችን ማፍራት ችሏል።በቀጣይም ጊዜያት ኢትዮ ቴሌ ኮም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባባር የክፍያ ስርዓትን በቴሌ ብር የሚተገብርበት አሰራር በማመቻቸት ደንበኞችን የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራም የኢትዮ ቴሌ ኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል ።
1.1K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 16:04:57
611 views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 16:04:52 በሸዋሮቢት ከተማ ከዛሬ ጀምሮ የሚተገበሩ የሰዓት ገደብ እላፊና ሌሎች ክልከላዎች ታወጁ

ሐሙስ ጥር 25 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት ከዛሬ ጥር 25/2015 ጀምሮ የሚተገበር የስዓት ገደብ እላፊና ሌሎች ክልከላዎች ማውጣቱን አስታውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ከአገር መከላከያ ሰራዊት፣ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከአማራ ልዩ ሀይል እና ከከተማው የፀጥታ መዋቅር የተውጣጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

እንደ ኮማንድ ፖስቱ ገለጻ ከሆነ፤ በቀጠናው የተፈጠረውን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል በርካታ የሰላምና የጸጥታ ሥራዎች ለመስራት ያስችል ዘንድ የፀጥታ መዋቅሩ በተለይም ደግሞ አከባቢውን የተቆጣጠረው የአገር መከላከያ ሰራዊት ለሥራ ምቹነት ሲባል የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት የሚከተሉትን ክልከላዎች ማስቀመጡን አስታውቋል፡፡

ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ካወጣቸው የሰዓት ገደብና ክልከላዎች መካከል ፡-

1ኛ. ባጃጅ እና ሞተር ሳይክል ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን፣

2ኛ. በመንግስት እውቅና ወይም ፍቃድ ያልተሰጠው ስብስባ ማድረግ፣ ግጭት መቀስቀስ እና በማህበራዊ ሚዲያ ህዝብን ወደ ሁከት የሚያጋልጡ ምስሎችን እና ድምጾችንና ጹሁፎችን ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው፣

3ኛ. አገልግሎት ሰጪና ንግድ ተቋማት እንዲሁም የሰው እንቅስቃሴ ከምሽቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ የተከለከለ መሆኑ፣

4ኛ. ሲቪል ሆኖ የተለያዩ የፀጥታ መዋቅር ማለትም የአማራ ልዩ ሀይል፣ የአገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ አልባሳት መልበስ የተከለከለ ነው፣

5ኛ. በሰርግና ሌሎችን ሁነቶችን ምክንያት በማድረግ ርችትና ተቀጣጣይ ነገሮችን መተኮስ የተከለከለ መሆኑ፣

6ኛ. ከተፈቀደለት የፀጥታ መዋቅር ውጪ በከተማው ዘጠኙም ቀበሌዎች የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን ኮማንድ ፖስቱ ገልጿል።

እነዚህን ድንጋጌዎችና ክልከላዎችን በማክበርና በማስከበር እንዲሁም በኮማንድ ፖስቱ አማካኝነት የሚሰሩ የሰላምና የጸጥታ ሥራዎችን ውጤታማ እንዲሆኑ እና የቀጠናው ሰላም ዘላዊነት እንዲረጋገጥ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲል ኮማንድ ፖስቱ ባወጣው መግለጫው አሳስቧል፡፡
612 views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 15:04:23
656 views12:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 15:04:18 በቁጫ እና በዛይሴ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት እዲቆም ተጠየቀ

ሐሙስ ጥር 25 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በቁጫ እና በዛይሴ አካባቢዎች ምርጫ 2013 ውጤትን መነሻ በማድረግ "ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን መርጣችኋል" በሚል በሁለቱም ምርጫ ክልሎች ሕዝብ ላይ የአስተዳደር በደል እንዲሁም የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶች እየደረሱ ነው ሲሉ በኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ ክልል ም/ቤት የቁጫ ምርጫ ክልል ሕዝብ እና የዛይሴ ምርጫ ክልል ተወካዮች አስታወቁ።

ተወካዮቹ ወቅታዊ የአካባቢያቸውን ሁኔታ አስመልክተው ትናንት ጥር 24 ቀን 2015 በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በኹለቱ ምርጫ ክልሎች በሚገኙ ሕዝቦች ላይ እየተፈፀመ ያለው ሕገ መንግሥታዊ ጥሰት እንዲቆም መንግሥት የሕግ የበላይነትን ያስከብር ሲሉ ጠይቀዋል።

መግለጫውን የሰጡት ረ/ኘሮፌሰር ገነነ ገደቡ ከቁጫ ምርጫ ክልል፣ አብርሃም አሞሼ ከዛይሴ ምርጫ ክልል እንዲሁም የመቶአለቃ ማሴቦ ማዳልቾ እና አማኒያስ ጉሽና ሲሆኑ፤ በመግለጫቸውም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል የቁጫ እና የዛይሴ ሕዝብ ያለፈውን የምርጫ ውጤት ተከትሎ በመንግሥት መዋቅር የታገዘ ጥቃትና ለልዩ ልዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መጋለጡን ተናግረዋል።

በዚህም በአካባቢዎቹ ሰዎችን ያለምክንያት ድብደባ፣ ማሰር፣ ማሳደድ፣ ማዋከብ፣ ንብረት መቀማት፣ ከሥራ ማፈናቀልና ማሳደድ ከመድረሱም በላይ ምክንያታዊ ያልሆኑ የገንዘብ ቅጣቶችን በሕዝቡ ላይ በመጣል በኢኮኖሚ የማዳከም ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት የአካባቢዎቹ ማህበረሰብ ከፍተኛ የሆነ የደህንነት ስጋት እንደተደቀነበት ተወካዮቹ አብራርተዋል።

በተጨማሪም፤ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎችን አቅፎ አዲስ ክልል ለመመስረት ሰሞኑን ሊካሄድ የታቀደው ሕዝበ ውሣኔ ላይ እንዳይሳተፉ በርካታ ሰዎች የመራጭነት ካርድ መከልከላቸውን የገለጹት ተወካዮቹ፤ ለምርጫው አማራጭ እየቀረበ አለመሆኑን እና ገለልተኛ ምርጫ አስፈፃሚዎች፣ ታዛቢዎች በሌሉበት ሁኔታ የሚካሄድ መሆኑን በመጥቀስ ሒደቱ አግባብ አለመሆኑን አስረድተዋል።

ከቁጫ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዩ ረ/ኘሮፌሰር ገነነ በመግለጫው፤ አብዛኛው የቁጫ ሕዝብ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን መርጠሃል ተብሎ እንዲፈናቀል፣ እንዲሰደድና እንዲታሰር ተደርጓል ያሉ ሲሆን፤ ጥቃቱ በአዲስአበባ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጃች ላይ ጭምር ያነጣጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

የዛይሴ ሕዝብ ተወካይ የሆኑት አብረሃም በበኩላቸው፤ በጋሞ ዞን እና በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ የገዥው ፓሪቲ ባለስልጣናት በሚያደርጉት ክልከላና በሚያደርሱት እንግልት ምክንያት፤ ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር ተገናኝተው ዉይይት ለማድረጎ አለመቻላቸውን ገልጸዋል።

አክለውም ከ1987 ጀምሮ የዛይሴ ብሔረሰብና ሕዝብ የወረዳ እና የዞን አስተዳደራዊ መዋቅር ይፈቀድልን ጥያቄ በማቅረባቸው ብቻ የአካባቢው ሕዝብ የአገር ሽማግሌ፣ ሕጻናትና ሴቶች ሳይቀር እጅግ አሰቃቂ የጅምላ ድብደባ፣ እስር፣ ማሳደድና ማፈናቀል ወንጀል በአካባቢው የአስተዳደር አካላት ተፈፅሞባቸዋል ብለዋል።

በተጨማሪም በጋሞ ዞን ውስጥ የዛይሴ፣ የጊዲቾ እና የጋሞ እና ሌሎችም ብሔር ብሔረሰቦች ባሉበት ሁኔታ ሦስቱንም የማይወክል የዞን ስያሜ መኖሩ የአንድ ብሔረሰብ የበላይ እንዲሆን አድርጓል በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም ሕዝቡ በመረጧቸው ይተዳደሩ ዘንድ በ2015 ሊደረግ የታቀደው የሟሟያ ምርጫ እንዲደረግ የጠየቁ ሲሆን፤ ይህ ባለመሆኑ የዛይሴ ሕዝብ በመረጠው ሳይሆን ባልመረጠውና በማይፈልገው ተወዳድረው በወደቁ ግለሰቦች ያልተገባ እንግልት እየደረሰበት ሊቀጥል እንደማይችል አስረድተዋል።

ተወካዮቹ በመግለጫቸው በቁጫ እና በዛይሴ ሕዝብ ላይ እየደረሰ የሚገኘው የአስተዳደር ፣ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ በደሎች በአስቸኳይ ይቀረፉ ዘንድ የፌደራል እና የክልሉ መንግሥታት የሕዝባችንን ቅሬታ ይስሙልን ሲሉም ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።
631 views12:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 15:03:13
520 views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 15:03:09 ንግድ ባንክ በግማሽ አመቱ 13 ቢሊየን ብር አተረፈ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በግማሽ አመቱ የ102.4 በመቶ እድገት ማስመዝገቡን ገለፀ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ6ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርቧል። በዚህም የባንኩ የግማሽ አመት ትርፍ 13 ቢሊየን ብር መድረሱን ገልጿል።

ባንኩ የተደራሽነት እና የአገልግሎት ተደራሽነትን መሰረት በማድረግ ሲሰራ መቆየቱን ያነሱት የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቤ ሳኖ በዚህም በግማሽ አመቱ 55 አዳዲስ ቅርንጫፎችንና 99 ATM ማሽኖችን በተለያዩ አካባቢዎች ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ተናግረዋል። ባንኩ የአገልግሎት አድማስን ከማስፋት በዘለለ ለስራ እድል ፈጠራ ልዩ ትኩረት በመስጠት በሰራው ስራም አጠቃላይ የሰራተኛውን ቁጥር ወደ 39ሺህ ከፍ ማድረጉን እንዲሁ ያስታወቀ ሲሆን በተለይም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው ለሚወጡ አዳዲስ ስራ ፈላጊዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት ሰርቷል ነው የተባለው።

የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በሚመለከትም የእቅዱን 111 በመቶ ማሳካቱና ለገቢ ንግድና ሌሎች የውጭ ምንዛሬ ለሚያስፈልጋቸው የንግድ እንቅስቃሴዎች 3.9 ቢሊዮን ዶላር ማቅረቡ ተመላክቷል። የደንበኞቹን የሂሳብ ደህንነት ከመጠበቅ ረገድ ከፍተኛ የጥንቃቄ እየሰራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከኤጀንቶች ጋር በሰራው ስራም የአገልግሎት ተደራሽነት አድማስን ማስፋት እና የደንበኞችን አገልግሎት ማሟሟላት መቻሉ ተመላክቷል፡፡

እንደ አጠቃላይ በግማሽ አመቱ የባንኩ ጠቅላላ ሃብት 1.2 ትሪሊየን ብር መድረሱም እንዲሁ ተገልጿል፡፡
587 views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 09:29:38 የሕወሓት ታጣቂዎች በኮረምና አላማጣ አካባቢ ስጋት ፈጥረዋል ተባለ

ሐሙስ ጥር 25 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የማይጨው አካባቢዎች የሚገኙ የሕወሓት ታጣቂዎች የሚነዙት ፕሮፖጋንዳ በኮረምና አላማጣ አካባቢዎች ትልቅ ስጋት መፍጠሩን ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ፡፡

ታጣቂዎቹ ከኮረም 40 ኪሎሜትር ገደማ እርቀት ላይ በማይጨው የሚገኙ ሲሆን፤ በየጊዜው ኮረምና አላማጣ እንገባለን የሚሉ ዛቻዎችን እየሰነዘሩ ይገኛሉ ነው ያሉት፡፡

በዚህም ነዋሪዎቹ ትልቅ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸው፣ አሁንም ከስድስት ያላነሱ ቀበሌዎች በህወሓት ቁጥጥር ውስጥ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በቀበሌዎቹ የሚገኙ ነዋሪዎች ገንዝብ እንዲሁም ቀለብ አምጡ በሚሉ የህወሓት ታጣቂዎች በደል ውስጥ መሆናቸውንም ከእነዚህ አካባቢዎች ወደ ኮረም ለገበያ ከሚመጡ ሰዎች አረጋግጠናል ብለዋል፡፡

በጦርነቱ ወቅት ከኮረምና ለአለማጣ ወደ ትግራይ ሄደው የነበሩ የትግራይ ተወላጆች አሁን ላይ ብዙዎቹ ወደ ቦታቸው እየተመለሱ ነው ያሉት ነዋሪዎቹ፣ ነገር ግን ከተመለሱ በኋላ የተወሰኑት ለህወሓት ታጣቂዎች መረጃ በማድረስና በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በቅርቡ ከመቀሌ ወደ ኮረም የተላከን እርዳታ ቁሳቁስ፣ ማህበረሰቡ እኛ እየተዳደርን ያለነው በአማራ ክልል ስለሆነ በትግራይ ክልል በኩል የሚመጣን እርዳታ አንቀበልም በማለት የመጣውን መልሶ መላኩን ተናግረዋል፡፡

መሰል ድርጊቶችም የማህበረሰቡን የደህንነት ስጋት ከፍ እንዲል አድርጎታል ነው ያሉት፡፡

በትናንትናው ዕለት ከቆቦ ወደ አላማጣ የሚወስደው መንገድ የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ መስተጓጎሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ለዚህም አንዱ ምክንያት ቁጥራቸው የማይታወቅ በርካታ የአማራ ተወላጆች በትግራይ ክልል ባሉ እስር ቤቶች እየተሰቃዩ በመሆኑ ወደክልሉ የሚያልፍ ነገር መኖር የለበት በሚል እንደሆነነ ተመላክቷል፡፡

የትግራይ ታጣቂዎች በጦነቱ ወቅት ከአማራ ክልል የወሰዷቸውን በርካታ ሰዎች በየእስር ቤቶች አጉረው እያሰቃዩ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

በዚህም ማይጨው ላይ ብቻ 250 የአማራ ተወላጆች ታስረው የሚገኙ ሲሆን፣ ሶረም ወረዳ ውስጥ ደግሞ ቁጥራቸው የማይታወቅ ብዙ ሰዎች በከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ነዋሪዎቹ አክለዋል፡፡
1.0K views06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 08:33:28
1.0K views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ