Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Electric Utility

የቴሌግራም ቻናል አርማ eeuethiopia — Ethiopian Electric Utility E
የቴሌግራም ቻናል አርማ eeuethiopia — Ethiopian Electric Utility
የሰርጥ አድራሻ: @eeuethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.11K
የሰርጥ መግለጫ

EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-05-09 21:10:45
4.8K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 14:15:49 አገልግሎቱ ለ35 የመስኖ ፕሮጀክቶች የኤሌክትሪክ ኃይል ዳግም ተደራሽ ማድረጉን ገለፀ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትግራይ ክልል ኤሌክሪክ አገልግሎት በ2015 በጀት ዓመት በክልሉ ለሚገኙ ለ35 የመስኖ ፕሮጀክቶች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገለፀ፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል ዳግም ካገኙት 35 የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል 26ቱ የግብርና ኢንቨስትመንቶች ሲሆኑ የተቀሩት ደግሞ በልማት ስራ ላይ የተሰማሩ የአርሶ አደር ማህበራት ናቸው፡፡

የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ቀድሞ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የነበሩ ሲሆን በአካባቢው በተካሄደው ጦርነት ምክንያት ተዘርግቶ የነበረው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ጉዳት ስለደረሰበት አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡

በመሆኑም ፕሮጀክቶቹ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳግም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ 65 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ጥገና፣ 35 የተቃጠሉ ትራንስፎርመሮች ቅየራ እንዲሁም 45 ጉዳት የደረሰባቸው ቆጣሪዎች ጥገና በማድረግ ወደ ልማት እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል፡፡

ባለፈው በጀት ዓመት በክልሉ 59 የመስኖ ፕሮጀክቶች ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

በተመሳሳይ አገልግሎቱ በነባር የመካከለኛ መስመሮች ላይ የመልሶ ግንባታ ለማካሄድ ስራ የጀመረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የኮንክሪት ምሰሶ ተከላ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡

በ32 መጋቢ መስመሮች ላይ በቅርቡ የተጀመረው ይህ ግንባታ የሚከናወነው 14 በግንበታ ላይ በተሰማሩ ማህበራት አማካኝነት ነው፡፡

የማሻሻያ ግንባታው ከሚከናወንባቸው መስመሮች መካከል ውቅሮ-አዲግራት-ብዘት፣ አቢአዲ ወርቅ አምባ፣ አክሱም - ሽረ፣ አድዋ - አክሱም፣ ሽቅሩማሪያም - ጭላ የመሳሰሉ መስመሮች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በዚህ የመካከለኛ መስመር የማሻሻያ ግንበታ ከዘጠኝ መቶ የማያንሱ ዜጎች በግንባታው የስራ እድል ተጠቃሚ ይሆናሉ የተባለ ሲሆን በግንባታው 12 ሺ የኮንክሪት መሰሶዎችን ለመትከል ዕቅድ ተይዟል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
5.7K views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 14:14:45
5.0K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 16:35:34
ባለፉት 9 ወራት ከ2 ሚሊየን በላይ ደንበኞች የዲጅታል ክፍያ ስርአትን ተጠቅመው ክፍያ መፈፀም ችለዋል

ባለፉት 9 ወራት ተቋሙ በዘረጋቸው የዲጅታል የክፍያ ስርአትን ተጠቅመው ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳባቸውን የፈጸሙ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች 2 ሚሊየን 258 ሺህ 643 ሺህ መሆናቸው በዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ተገለፀ፡፡

በበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት 51 በመቶ የሚሆኑ ደንበኞች ዲጅታል የክፍያ ስርአት ተጠቅመው ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳባቸውን መፈጸም እንደቻሉ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 2 በመቶ በቴሌ ብር፣ 10 በመቶ በሞባይል ባንኪንግ፣ 12 በመቶ በሲቢኢ ብር እና 27 በመቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባሉ ቅርንጫፎች በአካል በመሄድ ክፍያቸውን የሚፈጸሙ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡

የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ከሀምሌ 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳባቸውን ሙሉ በሙሉ በዲጅታል በተዘረጉ አማራጮች ብቻ እንደሚፈጸሙ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

ተቋሙ ባለፉት 9 ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ከታቀደው 20 ነጥብ 67 ቢሊየን ብር ውስጥ 19 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 93 በመቶ ማሳካት መቻሉ ተጠቅሷል፡፡

ይህም ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነጻጸር 4 ነጥብ 61 ቢሊየን ብር ወይም በ24 ፐርሰንት ጭማሪ መሳየቱ ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችን በማስወገድ 117 ሚሊየን 68 ሺህ 772 ብር መሰብሰብ እንደተቻለ ተገልጿል፡፡
2.1K views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 11:10:33
አገልግሎቱ የዘጠን ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማ መካሄድ ጀመረ
*****************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀም ግምገማን ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡

ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ የዘጠኝ ወር ዕቅድ አፈጻጸም የግምገማ ትኩረት የሚያደርጋቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል አዳዲስ ኃይል ፈላጊ ደንበኞችንና የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ፣ ከኢነርጅ ገቢ ሽያጭ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ እና ለደንበኞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ከማረጋገጥ እንዲሁም ደንበኛ ተኮር አገልግሎት ከመስጠት አኳያ ውይይት በማድረግ የቀጣይ አቅጣጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

በግምገማው ላይ የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር፣ የዲስትሪክት ዳይሬክተሮችና የመሠረታዊ ሠራተኞች ማህበር ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
2.9K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 10:23:05
በዳውሮ ዞን ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል
ዳግም ወደ አገልግሎት ተመለሰ

በደቡብ ምዕራብ ክልል በዳውሮና ኮንታ ዞኖች ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ አገልግሎት ተመለሰ፡፡

በዳውሮ ዞን አባ ከተማ ላይ በሚገኝ የማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በደረሰ የቴክኒክ ብልሽት በዞኖቹ የኤሌክትሪክ ኃይል ከመጋቢት ወር መጀመሪያ ጀምሮ መቋረጡ ይታወቃል፡፡

በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ተከስቶ የነበረው የቴክኒክ ብልሽት በአሁኑ ወቅት ተጠግኖ በመጠናቀቁ ከትናንት ሚያዚያ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
22 views07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 20:26:03 የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ ኃይል አግኝቷል

በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል የተቋረጠበት የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ በአማራጭ መስመር ኃይል አግኝቷል።

ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ከቆቃ በአማራጭ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት በማስገኘቱ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞች ኃይል ማግኘት ችለዋል።

በዚህ አጋጣሚ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን እና በጥገናው ስራ ላይ ለነበራችሁ ባለሙያዎች ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን ፡፡
2.0K viewsedited  17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 17:45:04 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የዒድ-አልፈጥር በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

2.7K viewsedited  14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 16:39:07
ለቅድመ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በሙሉ

ተቋማችን የኢድ-አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የቅድመ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በበዓሉ ዕለት በመላው አገሪቱ በሚገኙ በተመረጡ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ካርድ መሙላት እንዲችሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡ በዚህ መሰረት

#ከ2_እስከ_6 ሰዓት ድረስ አገልግሎት የሚሰጡ

በአዲስ አበባ ከተማ፡- ጉርድ ሾላ፣ ካዛንችስ፣ ቱሊ ዲምቱ፣ አያት፣ ለቡ ቁ.10 እና ቤቴል ቁ.4 ማዕከላት፣
በኦሮሚያ ሪጅን፡- አዳማ፣ ጅማ፣ ሻሸመኔ እና ፊንፊኔ ዙሪያ ዲስትሪክት ስር ያሉ የተመረጡ ማዕከላት፣
በአማራ ሪጅን፡- ባህርዳር፣ ደብረማርቆስ፣ ጎንደር፣ ደብረብርሃን፣ ወልደያ ዲሰትሪክት ስር ያሉ የተመረጡ ማዕከላት፣
በሲዳማ ሪጅን፡- አዋሳ ቁ. 2 ማዕከል፣
በድሬዳዋ ሪጅን፡- ድሬዳዋ ቁ.2 ማዕከል፣
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ሪጅን፡- አሶሳ ማዕከል፣
በደቡብ ሪጅን፡- አርባምንጭ፤ ወላይታና ሆሳዕና ዲሰትሪክቶች ስር አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ሁሉም ማዕከላት፣
በደቡብ ምዕራብ ሪጅን፡- በሪጅኑ ስር የሚገኙ ሁሉም ማዕከላት፣

#ከ2_እስከ_11 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጡ

በሐረር ሪጅን፣ የሀረር ቀ.1 ማዕከል፣
በሶማሌ ሪጅን፡- በጂግጂጋ ከተማ በሚገኙ ቁ.1 እና 2 ማዕከላት እንዲሁም
በአፋር ሪጅን፡- በአዋሽ 7 ኪሎ፣ ሎጊያ፣ ሰመራ፣ ዱብቲና አሳይታ ማዕከላት፣
የካርድ መሙላት አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸው አውቃችሁ አገልግሎቱን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
2.7K viewsedited  13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 13:35:22
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!

ሽፈራው ተሊላ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
760 viewsedited  10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ