Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.34K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-25 08:32:35 በሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሰባት ዓ/ም ? የአማርኛ ሙዚቃ ንግሰ ነገስቱ ጥላሁን ገሰሰ አዲስ አልበሙን ከለቀቀ ገና የአንድ ሰንበት ዕድሜ ላይ ነበረ፡፡ ይሀ ሲሆን የሙሀባ ይመር ልጅ ዚነት ሙሀባ የመጀመሪያ አልበሟ ለብርሃን ሲበቃ በጥላሁን እንደሚዋጥ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ሆነ፡፡ ለጊዜው የተባ ተስፋ አልነበረም፣ ውቅያኖሱ ባህሪቱን የሚውጣት ይመስል ነበር፡፡ ግን ባህሪቱ ውቅያኖስ ሆነች፡፡ ለቅጽበት እንኳ ልትደበዝዝ ዕድል አልጠመመባትም፡፡ የተፈራው አልሆነም፡፡

ስጋት የሆነው ጥላሁን በፈገግታ የሚታቀፍ ውበት እንጅ ዚነትን ሰልቅጦ የሚያጠፋ እሳተ ገሞራ እንዲሆን የሙዚቃ አማልክቱ ላሎ አልፈቀደም፡፡ ልጁ ኩርማን ጋፋ ላሎም ቢሆን ለጠይሟ እመቤት አዳልቶ በአውሎ ዘንግ ላይ የምትውለበለብ ሰንደቅ አደረጋት እንጂ አሳልፎ ለቀባሪ አልሰጣትም፡፡ እናቷ አርፋ ቀድሞ ለተደገሰ ለሙዚቃ ድግስ በቃሏ የምትገኘዋ ዚነት በማራቶን ሙዚቃ ቤት በኩል ነገሰች፡፡ ሕይወት የራሷ ሕግና ስርዓት አላት፤ ዘመንም የራሱን ጀግና ይፈጥራል ማለት እንዲህ ነው፡፡ በዘመኑ የህዝብ ለህዝብ ኮንሰርትን አሰናድተው (ባልሳሳት) የአማርኛ ሙዚቃ ልዑሎችና አበጋዞች በዓለም ዙሪያ ቀድሞ በሀገራችን ለተከሰተው ድርቅ እርዳታ ላረጉ ሀገራት ምስጋና ለማቅረብ በሙዚቃ ድግስ ሲዟዟሩ የሀበሻ ምድር ከዚነት ሙሀባ አንደበት ጣዝማ ሲዝቅ ነበር፡፡ እነዚያ ፊውታራሪዎች ከበጎ ተግባራቸው መልስ አገር ቤት ሲገቡ ግን ያልተገመተ ክስተት ጋር ተፋጠጡ፡፡ አዎ…. አንዲት ጠይም ልዕልት የመዲናይቱን ጭፈራ ቤቶች አጥልቅልቃዋለች፡፡ በየሸክላ ማጫወቻው ዚነት ሙሃባ ይሏት ሸጋ የወሎ ለዛዋ ባጣፈጠው ድምጧ ተስረቀረቀችበት፡፡ አውራጃው ሁሉ ስሟ ናኘ፡፡ አልበሟ ካገር ባህር ማዶ ተሻግሮ ተደመጠ፡፡ ያኔ ታዲያ የህዝብ ለህዝብ ቄሳሮችን ‹‹ከየት የመጣች ተኣምር ነች!›› አሰኝታለች፡፡ በቦረከና ወንዝ ዳር ያደገችው ያች እንቡጥ አበባ ገና በልጅነት በሰርግና በማህበረሰባዊ በዓሎች ላይ የጀመረችው የሙዚቃ ሕይወት እንዲህ ሀገር አቀፍ ጣዕም ለመሆን አበቃት፡፡ ይህ እንግዲህ ኩርማን የዚነት ሙሀባ ዜና መዋእል ነው!!

ከውዴታ በመነጨ ቅን ስሜት ተከተበ፡፡
የሳትኩት በአፈ ሊቃውንት ይታረምልኝ!!

ጋሻው የኋላሸት (ዘቢደር)
922 views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-25 08:32:35 ጠይሚቱ ልዕልት
ባለሙሀባይቱ የሸኽ ሙሀባ ይመር ልጅ!!
÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷
(ጋሻው የኋላሸት (ዘቢደር)

አየዋ… ልቤን በንሻጤ የሚንጣት እልፈ ነገረ ኪን በጎሰመኝ ልክ የነፍስያዬን ጣዕመ-ዜማ ላዜምልህ እየከጀልኩ የዘመኑ መንፈስ አስሮ ይለጉመኛል፡፡ አየህ ቀን ሲበላሽ እንዲህ ያደርጋል፡፡

እመዋ… የውበትን ትርታ ምት ልቀኝልሽ፣ ለዛ ያለውን የሚያንስፍስፍ የፍቅር ጨዋታ ላሰማሽ ውስጤ እየወደደ ጌዜው አንደበት ይነሳኛል፡፡ አየሽ ለስላሳዬዋ የሰው ጠይም እንጂ የጊዜ ጠይምነት አያምርም፡፡

የምወዳችኹ ሆይ እስቲ ዛሬ'ኳ በድፍረት ዘማሪ ልሳኔ ወደ እዝነ ልቦናችሁ የሥን ቅኝቱን ያስረቅርቅ፡፡ መቸስ የወደደ… ውዴታውን አምጦ መውለጃ አፍታ አያጣም!

ወዳጆቸ… ጦሳ ሲባል በጦስኝ፣ በአደስ፣ በጠጅ ሳር አበባ የተቀመመ ጥዑም መዓዛ ያለው አየር ካለሁበት ድረስ ነፍሶ ያውደኛል፡፡ ጦሳ እንደ ገልአድ ተራራ ለምስል ከሳች ስንኝ የተመቸ ነው፡፡ ጦሳ እንደ ኢቨረስት ውሃ የሚረጋበት፣ እንደ ብሶተኛ ሰው በሆዱ ባህር እልፍ ሚስጥር የፀነሰ ዝምታ ነው፡፡ እነደ ቄርሜሎስ ተራራ ሱባዔ ቢይዙበት ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያገናኛል፡፡ ይህን ስንል ራስ ዳሽንን ማሳነሳችን አይደለም፡፡ የሶሎዳ ተራራን ማናናቃችን እንዳይመስላችሁ፡፡ ይልቅስ ትከሻ ለትከሻ እያደጋገፍናቸው ነው፡፡ ጦሳ እንኳን ላገር ቤቱ ለባህር ማዶ አምባዎችም የቅርብ ተጠሪ ወዳጅ ነው፡፡ አዎ ጦሳ ለዓይን ሳይሞላ ለልብ የደረሰ ሰራጺ ሚስጥር ነው፡፡ ከጦሳ ተራራ ግርጌ ደግሞ ገጻቸው ደም-ግባት ያጋተ ሸጋ ሸጋ ሳዱላዎች ቀን ተቀን ይፈልቁበታል፡፡ የውበት ዥረት በደርባባይቱ ወሎ ጉያ ይገማሸራል፡፡ ለነገሩ ወሎ የነመስቀለ ለክብራ፣ የነቴጌ መነን ሀገር አይደለ'ዴ ልባም እና ሸጋ መች ይጎድልበታል፡፡ የነዳና መስገጃ፣ የነላሊበላ መቀደሻ አይደል'ንዴ በምን ሒሳብ ኢማነኛና ባለኢልም ሊርቀው ከቶ!! ያጋምሳዎች አድባር፣ የራያዎች አዋይ፣ የየጁዎች መንበር፣ የላስታዎች መናገሻ ወሎ ምን ጎድሎባት ትታማለች? እንደው በደፈናው ከእያንዳንዱ የወሎ ደፍ የቁንጂና ሰብል አሽቷል፡፡ የነባህሩ ቃኘ ጎራ የሙሀባ አዝመራ አፍርቷል፡፡ ኸይርያዬን ይንሳኝ ስላቹሁ! ወሎ የልብ ምት፣ የግልገሎች ሙቀት ናት፡፡

እንግዲህ ይህን ሁሉ የምዘባርቅባችሁ ስላንዲት የወሎ ልዕልት ለማዜም ነው፡፡ እሷስ የሀበሻ ምድር ጣፋጪ ድምጥ ናት፡፡ አዎ! የኢትዮጵ እንቆጵ ነች እሷ፡፡ ይህች ድምጸ መረዋ እዚች አቢሲኒያ ውስጥ በአማርኛ የሙዚቃ ሰገነት ላይ ንግስና የማያንሳት ልዕልት ነበረች፡፡ እሲ ልተዝታት፡፡ እሷ'ኳን ዘካሪ፣ አደግድጎ አስተዋሽ ሎሌ ብትፈልግ ከ'ኔ በላይ የሚራቀቁትን አታጣም ነበር፡፡ ልቤ ግን ለገዛ ራሱ ደስታ ይቺን የስለት ልጅ፣ ይቺን ገና በእናቷ ማህጸን ሳለች የነብይ ዓይን የፈሰራትን ደርባባ አወዳሽ ሁኛለሁ፡፡ ያ የምስራቁ ነገረ-ፈጅ ኦሾ ከስም ሁሉ ለአፍ የሚጣፍጥ ስም እያለ ጂብራን ኻህሊል ጂብራንን ያወሳል፡፡ እኛም ባገራችን የስም ባለጸጋዎች ነን፡፡ ሸግዬ! የተኳኳለ ግብሩን የሚሻረክ ስም በየእልፍኙ አናጣም ብንፈልግ፡፡ ግን ደሞ ዚነት ሙሀባ የሚሉት ሁለት ቃሎች ነፍስ አንደበት ቢኖራት ደጋግማ የምትጠራው ልብ አጥጋቢ ስም ነው፡፡

‹‹የንጋት ኮከብ›› እያለች ገና በንጋት እድሜዋ የጣዝማ ድምጧን ወለላ ያቋደሰችን ያች የጣዕም መለኪያ ልዕልት ሲያደምጧት ልብ ታለመልማለች፡፡ ‹‹አንድ ቡቃያ ልጅ በሚስጥር ወድጀ›› እያለች ስትብሰከሰክ በግርምት ታጠምዳለች፡፡ ‹‹ምን ይሻላል››ን ስታዜመው እልፉን ነገረ-ሕይወት በንቃት ዓይን ለመቃኘት ያነሳሳል፡፡ ‹‹ና ሽሽጌ›› እያለች ስትጣራ ትንፋሽ ታሳጣለች፡፡ ‹‹እንደው ከንበል ደፋ›› በሚል የውበት መወድሷ የሕይወት መልካም ገጽ ጋር ታላትማለች፡፡

ዚነት ሙሉ ኪነት፡፡ ዚነት ጠይም ውበት፡፡ ከሸኽ ሙሀባ ይመር አስራ ሶስት ልጆች ብቸኛዋ እንስት ናት፡፡ ወትሮም ልባም ሴት በወንዶች መሀል አማልክት ሁና መከሰት ተፈጥሯዊ ስሪቷ ነው፡፡ ባለሙሀባይቱ ዚነት ሙሀባ በዚያች በጦሳ ግርግጌ ከሚገኙ የገጠር መንደሮች መንጪታ በሀገራችን አድማስ ላይ የሚያጥበረብር ብርሃን ፈንጥቃለች፡፡ በእዝነ-ልቦና አፀድ የጸደቀች አበባ ሁናለች፡፡

ወሎ የትሕትና ምግባረ-ቤት ናት፡፡ ወሎ የመተናነስ አስኳል፣ የመከባበር ሉል ናት፡፡ ወሎ መታበይን የምትጸየፍ፣ ወዴታን ማተቧ ያደረገች ያይናማዎች ምኩራብ ናት፡፡ ስለዚህ ነው የወሎ ልዑላን በያደባባዩ እዩን እዩን የማያበዙት፡፡ ስለዚህ ነው የወሎ ሁረል ዐይኖች ከታዋቂዎች ይልቅ ለአዋቂዎች ያሚያዳሉት፡፡ ወሎ የእብሪትን እብጠት፣ የሸፍጥን ቡግንጅ፣ የንቀትን ላህጪ ከጡሀራ ልቧ ጠራርጋ ያስወገደች የቅዱስ መንፈስ ማደሪያ ናት፡፡ ስለዚህ ነው ልጆቿ ፀሓይ ግዙፍ ሳሉ እንደ ኮከብ አንሰው የሚታዩት፡፡ ወሎ ዝቅ በማለት ውስጥ ለላቀው ከፍታ የምትታደም ናት፡፡ ወሎነት ደግሞ አንድ ሆኖ ሁሉንም መሆን ነው፡፡ ሁሉን ሆኖ በአንድነት መሰየም ነው፡፡ ወሎ እመ ብዙሀን ናት፡፡ ትራራለች፡፡ ስለዚህ ነው ማንም የሚወዳት፡፡ ወሎ አቅፋ ታከብራለች እንጅ ገፍትራ አትጥልም፡፡ ወሎ አፍቅራ ታገዝፋለች እንጅ ጠልታ አታኮሰምንም፡፡ ለዚህም ነው ከቅኝቶቿ ዜማ የጨለፈ፣ ሰነ-ቃሏን የጨለፈ ሁሉ ስሙ በኸይር ሀውዛ የሚጠመቀው፡፡ ዚነት የወሎ ውጤት ናት፡፡ ዘለስ ያለች ናት በትግስት፡፡

የዚነት ሙሀባ ወላጆች ሴት ልጅ ተርበው ሴት አማልክት ተሰጥተዋል፡፡ ዚነት የተጸነሰችበት አብራክ በወንዶች ጋጋታ ቢሞላም ደርዘን ወንድ የምታስንቅ አንዲት ፍሬ ልዕልት ሲያሸት ግን በዓይናማዎች እይታ ስር ውሏል፡፡ ‹‹ይህቺ ልጅ ስሟ በሰፊው አድማስ ላይ ይናኛል›› የተባለላት ናት ገና በአባቷ ወገብ ስር ሳለች፡፡ ይህች ያይን ማረፊያ እንቁ ተወልዳ የተነገረላትን ትንቢት በገሃድ ለመግለጥ ዕድሜ አልፈጀባትም፡፡ ገና በለጋነት ወቅቷ የላሊበላን የባህል ቡድን ለመቀላቀል፣ የወሎ ባህል አምባ ውስጥ ንግስተ ንግስት ለመሆን በብርሃን ፍጥነት ነበር የተምዘገዘገችው፡፡ ግጥምና ዜማዎችን ከማንም ቀድማ ቀብ የማድረግ ጸጋዋ ድንቅ ነበር፡፡ የአዘፋፈኗ አገረኛ ለዛ እዝን ጠላፊ ነበር፡፡ ጠይሚቱ ልዕልት ብትወዛወዝ የባህር ዌቭ፣ ብትዘፍን የማዕበል ዳንስ ነበረች፡፡

ዚነት ሙሀባ… ቀረብ ሲሏት በውበት ሙሀባ የምትጠልፈው የስህበት እሳቷ በፍቅር የተለከፈባት በሽጉጥ እስኪስታት ድረስ የተፈቀረች የደስ ደስ ያላት ጠይም እንኮዬ ናት፡፡ ገና በልጅነት እድሜዋ በቤተሰብ የታጨላትን የማታውቀውን ባል እቢኝ አሻፈረኝ ብላ እጅ መንሻ የወርቅ ጥሎሹን ያስመለሰች ልባም እንስት ናት፡፡ ፈገግታ የማይርቃት፣ የፍካት ወጋገኗ የሚጋባ ፍልቅልቅ የቁንጅና ሙዳይ ነበረች ስትወሳ፡፡ ገና በአፍላ ዕድሜዋ፣ የብርሃኗ ወጋገን ባልደበዘዘበት ቀትር ባጭር የቀረችው ዚነት ሰው መውደድ ያለስስት የተቸራት ነበረች ይላሉ አብሯ አደጎቿ፡፡ በስራዋና በዝናዋ ኩራትና ተኣቢዮ የማይነካት ልባም መሆኗ ዛሬም ይመሰከርላታል፡፡ ግልጽና ከሁሉም ጋር ተላማጅ በመሆኗ በልብ ትታማለች።

የነመሐመድ አቦል ሀገር ኢልምና ሙሀባ በግፍ ተችሮታል፡፡ የነአሰፋ አባተ፣ የነማሪቱ ለገሰ ቀየ ዜማና የኪን ሜሮን ነጥፎበት አያውቅም፡፡ የነሙሉጌታ ተስፋዬ አድባር ደም ግባታም ስንኝ ተዝቆ አይጎድልበትም፡፡እነሆ ዛሬም በተተኪዎቹ እያበበ ነው!
790 views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-25 08:31:21
554 views05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-25 08:26:03 "
ትልቅ የሄግል ተጽዕኖ ያረፈበት ማርክስ ከሄግል የወረሰውን የታሪክ አረዳድ ከራሱ materialism ጋር አዋህዶ እና አዋድዶ ይህንን የመሰለ የታሪክ አረዳድ ቀመረ። ይህ ለኮሙኒዝም ፍልስፍናው መሠረት የሆነው የማርክስ የታሪክ አረዳድ historical materialism ይሰኛል።
"
ብዙ ጊዜ «ካፒታሊዝም ነጻ ገበያ ነው፤ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ነው» ሲባል እንሰማለን። ሄግል የዳበረ የነጻነት ፍልስፍና አለው፤ ነገር ግን የነጻነት ፍልስፍናው ከካፒታሊቶች የነጻነት ብያኔ ጋር አብሮ የሚሄድ አይደለም። ማርክስም የሄግልን የነጻነት ፍልስፍና ይከተላል። የሄግል የነጻነት ፍልስፍና መነሻው የታላቁ ፈላስፋ የኢማኑኤል ካንት ፍልስፍና ነው።"

ዘርዓያዕቆብ የፍልስፍና ት/ቤት
567 views05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-25 08:26:02 ማርክሲዝም በአጭሩ
=============
ክፍል 1: የሄግል የታሪክ አረዳድ ማርክስ ላይ ያሳደረው ተፅዕኖ
* Dialectic of history
=================
Biruk Mesfin
============
የፈላስፎችን ሀሳብ፣ በተለይ ደግሞ የcontinental ፈላስፎችን ሀሳብ ለመረዳት በጊዜያቸው የነበረውን ገዢ ፍልስፍና መረዳት ቁልፍ ጉዳይ ነው። ምክንያቱም አብዛኛው ፍልስፍናቸው በጊዜአቸው ከነበረው ገዢ ፍልስፍና ጋር በሚደረግ ግጭትና ፍጭት የሚወለድ ነው። በማርክስ ዘመን የነበረው ገዢ ፍልስፍና የሄግል ፍልስፍና ነው። ማርክስ ራሱ በአንድ ወቅት ሄግሊያን ነበር። በኋላ idealistic ከሆነው የሄግል ፍልስፍና ወደ materialism በማዘንበል ከወጣት ሄግሊያንስ ማህጋር ራሱን አገለለ። ሆኖም የሄግልን ፍልስፍና መሉ በሙሉ ጠቅልሎ አልተወም።
"
ስለዚህ ሄግልን ቃኘት አድርገን እንመለስ። የሄግል ፍልስፍና ከውስብስብነቱም በላይ እጅግ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ ለመረዳት አዳጋች ነው። ስለዚህ ከፍልስፍናዎቹ መሀል ከማርክስ ፍልስፍና ጋር የሚያያዙትን ክፍሎች ብቻ ነጥለን በጥቂቱ እንመለከታለን።
"
ማርክስን እና ሄግልን ከሚያመሳስሏቸው ወሳኝ ጉዳዮች አንዱ ለታሪክ የሚሰጡት አጽንኦት ነው። ለሄግል ታሪክ የራሱ የሆነ ግብ እና ትርጉም ያለው ምክንያታዊ ሂደት(process) ነው፤ ትርጉም አልባ የሆነ የክስተቶች ጥርቅም አይደለም። ለአንድ የዚህ ዘመን ኢአማኒ ታሪክ ማለት ባለፉት ዘመናት የኖሩ ሰዎች የሰሯቸው ስራዎችና ክስተቶች ጥርቅም ከመሆን ያለፈ ትርጉም ላይኖረው ይችላል። ለአንድ ክርስቲያን አማኝ ግን ታሪክ ማለት ጅማሬው፣ ሂደቱ እና ፍጻሜው በአምላክ ቁጥጥር ስር ያለ፣ ግብ አላማ እና ትርጉም ያለው ነገር ነው። “በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው የእግዚአብሔር ሀሳብ በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።” እንዲል መጽሐፉ።
"
የሄግል የታሪክ እይታም ከክርስቲያኖቹ ጋር ይመሳሰላል። ነገር ግን ታሪክ ትርጉም አልባ ስላለመሆኑ ያላቸው አቋም ነው የሚያመሳስላቸው። በዝርዝሩ ይለያያሉ። ሄግል የታሪክን ጅማሬ፣ ሂደት፣ ፍጻሜ እና ግብ የሚቆጣጠረው ከአለም የተነጠለ የራሱ ኑባሬ ያለው አምላክ ነው የሚል አቋም የለውም።
"
በምን መሠረት ነው ታድያ ሄግል ታሪክ ትርጉምና ግብ ያለው ሂደት ነው የሚለው? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። ተገቢ ጥያቄ ነው። ነገር ግን ይህንን ጥያቄ በሙላት መመለስ ውስብስብ የሆነውን የሄግል ፍልስፍና በስፋት መተንተንን የሚጠይቅ ይመስለኛል፤ ስለዚህ ከያዝነው ርዕስ ጋር ተያያዥነት ያለውን ክፍል ብቻ መዝዘን እንመልከት።
"
በምን መሠረት ነው ታሪክ ትርጉምና ግብ ያለው ሂደት ነው የሚሆነው? ታሪክ ወደ ግቡ የሚያደርገውን ጉዙ የሚቃኘው እና የሚገዛው ሀይል ምንድነው? ለዚህ ጥያቄ 'dialectic of history' የተሰኘው የሄግል ፍልስፍና መልስ ይሰጣል። dialectic of history ውስጥ thesis, antithesis እና synthesis የተሰኙ ሶስት ቁልፍ ሀሳቦች አሉ።
"
ይህንን ትንሽ አስቸጋሪ የሆነ ሀሳብ በቀላሉ ለማስረዳት ያህል፦ Thesis ማለት አንድ ጭብጥ ነው፤ antithesis ደግሞ ከዚህ ጭብጥ ጋር የሚቃረን ሌላ ጭብጥ ነው፤ synthesis ማለት በthesis እና antithesis ተቃርኖ የሚወለድ አዲስ ጭብጥ ነው፤ synthesisም በተራው thesis ይሆንና ሌላ antithesis ይነሳበታል፤ ከዚያም ሌላ synthesis ይወለዳል። በዚህ ሁኔታ ሀሳብ ወደ ፊት ይጓዛል።
"
የታሪክን ሂደት ወይም ጉዞ ከጀርባው ሆኖ የሚዘውረው ሀይል ይህ thesis, antithesis and synthesis የተሰኘ የሀሳብ ኡደት ነው ይላል ሄግል፤ ከቅድመ ታሪክ ጀመሮ እርሱ እስከኖረበት ዘመን ድረስ የተከሰቱ ዋነኛ የአለም ታሪኮችን አንድ በአንድ አጣቅሶ ይህንን ሀሳቡን ለማስረገጥ ይሞክራል፤ ታሪክ ከጊዜ ጊዜ እንዴት እየተሻሻለ እና ወደ ግቡ እየቀረበ እንደመጣ ያሳያል። ሄግልን ማንበብ ከፍልስፍና ባለፈ ታሪክንም ማንበብ ነው የሚባለው ለዚህ ነው።
"
የታሪክን ሂደት ወይም ጉዙ ከጀርባው ሆኖ የሚዘውረው thesis, antithesis እና synthesis የተሰኘው የሀሳብ ኡደት እንደሆነ ተመልክተናል። ይህ የሀሳብ ኡዱት እንዴት ነው በዘመናት መካከል ባለማቋረጥ እያውጠነጠነ ሊቀጥል የቻለው? ይህንን የሀሳብ ሁደት በቋሚነት ከጀርባው ሆኖ የሚዘውረው ሀይል ምንድነው? ሀሳቦች ያለማቋረጥ እየተፋጩ፣ እየታደሱ እና ደግሞ እንደገና እየተፋጩ ወደፊት የሚቀጥሉ ከሆነ የሚያውጠነጥኑበት አንድ ቋሚ ጉዳይ አለ ማለት ነው፤ ይህ ጉዳይ ነጻነት ነው። የነጻነት ጥያቄ ነው ይህንን የሀሳብ ኡዱት በዘመናት መካከል ባለማቋረጥ እያውጠነጠነ ወደፊት እንዲቀጥል የሚያደርገው።
"
ሄግል ታሪክ ትርጉም እና ግብ ያለው ሂደት ወይም ጉዞ ነው የሚል አቋም እንዳለው ከላይ ተመልክተናል፤ ይህ የታሪክ ግብ ነጻነት ነው። ታሪክን ከጀርባው ሆኖ የሚዘውረው የሀሳብ ኡደት ታሪክን ወደ ነጻነት ነው የሚነዳው። የባርያ ንግድን ክላልኝ እያለ፣ ፊውዳሊዝምን ወግድልኝ እያለ፣ ፍጹም ነጻ ወደ ሆነ የማህበረሰብ ስርዓት ነው ታሪክ የሚያንደረድረው። ይህ የሄግል ሀሳብ dialectic of history ይሰኛል። ነጻ የሆነ ማህበረሰብ ምን አይነት ነው ለሚለው ጥያቄ የሄግል መልስ የምትጠብቁት አይነት ላይሆን ይችላል። በዚህ ጉዳይ ማርክስም ከሄግል ጋር ተቀራራቢ አቋም አለው።"

ማርክሲዝም በአጭሩ
==============
ክፍል 2: ሄግላዊ የማርክስ የታሪክ አረዳድ Historical Materialism
"
Biruk Mesfin
===========
ክፍል 1 ላይ ሄግል «ታሪክ ግብ እና ትርጉም ያለው ሂደት ነው፤ ግቡም ነጻነት ነው።» የሚል አቋም እንዳለው ተመልክተናል። የማርክስም የታሪክ አረዳድ ከሄግል የተቀዳ ነው፤ ሆኖም ማርክስ materialist፣ ሄግል ደግሞ idealist ስለሆኑ የታሪክ አረዳዳቸውም በዛው ልክ ይለያያል።
"
ሄግል «የታሪክን ጉዙ ከኋላው የሚዘውረው የሀሳብ ፍጭት ነው፤ የታሪክ ግብ ደግሞ ነጻነት ነው» የሚል አቋም ሲኖረው፣ ማርክስ ደግሞ «የታሪክን ጉዙ ከኋላው የሚዘውረው የማህበረሰብ የኢኮኖሚ ሁኔታ ነው፤ የታሪክ ግብ ደግሞ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት ነው» ብሎ ይከራከራል።
"
ማርክስም ልክ እንደ ሄግል የራሱ የሆነ thesis, synthesis and antithesis አሉት። ለምሳሌ፣ ፊውዳሊዝም ጠቅላላውን ሀብት ለንጉሡ ሰጥቶ ሰፊውን ህዝብ ጭሰኛ የሚያደርግ ጨቋኝ ስርዐት ሲሆን፣ እንደ thesis ወሰዱት። በከበርቴው መደብ እና በሰፊው ህዝብ መሀል ባለው ሰፊ የኢኮኖሚ ልዩነት ምክንያት የሚፈጠረውን የተዛባ የኢኮኖሚ ሁኔታ ደግሞ እንደ antithesis ውሰዱት። በthesis እና በantithesis ግጭት ምክንያት የተወለደው ካፒታሊዝም ደግም synthesis ነው።
"
ካፒታሊዝም ደግሞ በተራው thesis ሆነ። ይህንን በዝባዥ ስርዐት ተቃውሞ የተነሳውና የብዝበዛው ሰለባ ሰራተኛው መደብ ደግሞ antithesis ነው። በthesis እና antithesis ተቃርኖ የሚወለደው communism ደግሞ synthesis ነው።
734 views05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-25 08:22:59
769 views05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 17:07:24 አቅም ሲኖርህ የመደራደር አቅምህ ይጨምራል፡፡ የለመድነው ስኬታማ ወንድ እና submissive የሆነች ሴት ስለሆነ በድራማው ውስጥ የሴቷ ስኬታማ መሆን፣ ተደራድራ ጥቅሞቿን የምታስከብር ሴት መሆኗ፣ ኢፍትሃዊ የመሰላትን ነገር ለማስተካከል በመሞከሯ፣ ድምጿ ጎላ ብሎ የሚሰማ ሴት መሆኗ፣ ባሏን/ወንድን ለማኮሰስ ሆን ተብሎ የተሸረበ ሴራ ይመስለናል፡፡

ሂሩት የምትደነቅ፣ ባሏን የምትወድ፣ ልጆቿን የምትወድ፣ ቤተሰቧን የምትወድ ለፍቶ አዳሪ ሴት ናት፡፡ ልንረዳት የምፈልገው ግን እኔ ብቻ ያልኩት እንደምትል እንደ ጨቋኝ፣ ከመሬት ተነስታ ወንድን/ባሏን እንደማታከብር ስድ ሴት ነው፡፡ በስንቱንም ክብር እንዳጣ፣ እንደተበደለ፣ እንደተናቀ ሰው ልናየው አእንጣጣራለን፡፡

በብዙ ቤቶችና ትዳሮች፣ ከሴቷ በታች የሚሰራ ወንድ (የስራ ጫና ያለበት ወንድ)፣ ከሴቷ የተሻለ ትርፍ ሰአት ያለው ወንድ ቁጭ ብሎ ቲቪውን እያየ ሚስቱ ከስራ መጥታ ምግብ አስክትሰራ ይጠብቃል፡፡ ይሄ ሊቀፈን፣ ሊያንገሸግሸን ይገባል፡፡

በስንቱ ለኔ ምርጡ ድራማ ነው፡፡ እያዝናና፣ እያሳቀ፣ አንዳንዴም እያናደደም ቢሆን የጾታ እኩልነትን ለማስረጽ ምርጡ ድራማ ሆኖ ነው ያገኘሁት፡፡

ዘመናዊው ትዳር፤ ሴቶች ሰራተኛ የሆኑበት ትዳር፤ የተማሩና የራሳቸው ገቢ ያላቸው ሴቶች ሚስት የሆኑበት ትዳር እንዴት መመራት እንዳለበትበት የሚያሳይ እንጂ ፤ ሴቶችን የሚክብ ወንዶችን የሚያዋርድ ነገር አይቼበት አላውቅም፡፡

Embet Teshome (comment)
1.6K views14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 17:07:24 "በስንቱ" እንቃጠል ?!
A Blasphemy on Masculinity or / and/ Vs Empowering Feminism ?.
ቤ.ማ.ተ
-------------------------------
ምድረ ሐበሻ አባወራ ( በተለይ ዘመናዊው ) ከ "በስንቱ" ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ጋር እልህ የቀላቀለ ፍቅር ይዞታል።
( በጣም እርግጠኛ ነኝ!) ።

ምድረ ዘመናዊ አባት ከእያንዳንዱ የድራማው ክፍል በሗላ ለሰው የማይነግረው፣ ለራሱም በቅጡ የማይገባው ድብልቅልቅ ስሜት ይዞ "እየሳቀ" ( እንደ ፋንዲሻ ) ወደ መኝታው ይሔዳል።

በዛች ምሽት ግን የሚስቱ እና የሴት ልጆቹ "ሳቅ" ከሌላው ግዜ ለየት ይልበታል።

በማይካደው የተዋናዮቹ ድንቅ የትወና ብቃት እና በድራማው የተዋጣለት የዝግጅት ጥበብ ተዋዝቶ የሣቅ ጭንብል የሸፈነው ስሜቱ በሁለት ባልተረዳቸው ተቃራኒ ፅንፎች መሐል ይንዠዋዠዋል ።

ውሎ አድሮ ከኑሮ የውጣ ውረድ ወከባው ቆጥቦ ባስተረፋቸው ብጥስጣሽ የቡና ሰአቶቹ መሀል ሳይፈልግ ስለ "በስንቱ" ያሰላስላል ። የሚስቱ እና የሴት ልጁ የለበጣ ሳቅ ትዝ ይለዋል። በየሀሳቡ መሀል "እምምም በስንቱ ልቃጠል!" ይላል።

የገፀባህሪያቱን ወጥ የሆነ ባህሪ ሲያስብ፣ ተያይዞም ሊተላለፍ የታሰበውን መልእክት ሲጠረጥር የሆነ የተጠና ስውር ደባ ነገር ይሸተዋል።

የትውስታ ማሕደሩን ሲበረብር ግልፍ ግልፍ ለሚለው ስሜቱ የአመክንዮ ታኮ ሊሽጥለት ይታገላል።

፩-የበስንቱ ድራማ ወንድ ገፀባህሪያት በሙሉ ስለምን እንዲያ ተሳሉ? ።

፪-በድራማው ላይ "ወንድነትን" የወከሉ አባትነት፣ አያትነት ( ወንድ አያት) ፣ አጎትነት ፣ ወንድ ልጅነት እንዲሁም በየታሪኩ ገደምዳሜ ብልጭ የሚሉ ወንድ ገፀ ባህሪያት በሙሉ ስለምን እንዲያ በዘቀጠ እና ሀላፊነትን ሊሸከም በማይችል ስብእና ተሳሉ?
በአጋጣሚ ወይንስ... ?

፫-በተቃራነው በድራማው ውስጥ የተወከሉ "ሴትነትን" የሚወክሉ ገፀባህሪያት በሙሉ በአስተዋይ፣ አዋቂ እና ሀላፊነታቸውን በቅጡ መወጣት የተሳናቸውን ጅላጅል ተባእት ገፀ ባህርያትን እየተከታተሉ በማረም ( በማረቅ ) ስራ የተጠመዱ፣እንዲሁም "በባህላዊው" አባታዊ ስርአታችን
( patriarchal system) ላይ ሙድ በመያዝ ባተሌ በሆኑ እና ውስጥ ለውስጥ በደንብ የሚናበቡ "smart" ሆነው ተሳሉ?
በአጋጣሚ ወይንስ .....?

የሚሉ ጥያቄዎች ይሞግቱታል ።

ለዘመናት የተከተልነውን ወንዳዊውን ስርአት (patriarchal system) ለመሞገት ከታሰበስ ያን ያክል እርቀት መሔድ ተገቢ ነው ወይ?።

ነባሩን እና ባህላዊውን አባታዊ ስርአታችንን ለመተቸት እና "በዘመናዊው" (ከምእራባውያኑ በተዋስነው ስርአት) "ሊያድግ ይገባዋል ፣ ትኩረት እና እውቅና ተነፍጎታል" የሚባልለትን እያደገ የመጣውን የሴቶችን ጉልህ ድርሻ ለማሳየትስ ተባእትነትን ( አባትነትን) ያን ያክል ማንጓጠጥ ተገቢ ነው ወይ?።

Betemariam Teshome (post)



(የልጥፉን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ኮሜንቱ የመለሰ ባይሆንም የዘመናዊውን ትዳር ምን መምሰል እንዳለበት የራሷን ምልከታ አጋርታለች።)



አንድ ግልጽ መሆን ያለበት ነገር አለ፡፡ የለመድናቸው Gender roles እየተቀየሩ ነው፡፡ ሴቶችን ከሚስነት እና ከእናትነት አልፈው፤ ገቢ በሚያስገኙ የሙያ ስራዎች ላይ እየተሳተፉ ነው፡፡ መሳተፍ ብቻ አይደለም ከወንዱ የተሻለ ገቢ እያመጡ ነው፡፡ በትምህርት፣ በእውቀት፣ በልምድ የተቀሸረ የራሳቸው ሃሳብ ባለቤት እየሆኑ ነው፡፡ ወንዱ የፈለገውን ሃሳብ አምጥቶ ሊያራግፍባቸው የማይችሉ አይነት ስብዕና ባለቤት እየሆኑ ነው፡፡ ድህነት እና ምርጫ ማጣት ከሚጥልባቸው የጭቆና፣ የባርነት፣ የግርድና፣ የጥቃት ትዳር ማምለጥ የሚችሉበት አቅም በተለይም የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠሩ ነው፡፡ እኚህን ሴቶች አግብተህ፣ እንደ አያትህ በበታችነት እና በተገዢነት፤ በንቀት እና ምንም አያውቁም አይነት ጨዋታ አእየተጫወትክ ልታኖራቸው አትችልም፡፡ አቅም የፈጠረች ሴት፤ የራሷ ድምጽ የሌላት፤ ሁሉን እሺ የምትል፣ እራሷን እላፊ ጎድታ ልጆቿን እና ባሏን የምትንከባከብ፣ ለቤተሰቧ ብላ ሁሉን ጥቃት፣ ሁሉን ውርደት፣ ሁሉን ጫና በዝምታ የምትሸከም ሚስት ልትሆን አትችልም፡፡ መታገል ትጀምራለች፡፡

“Working mom” የሆነች ሚስት ያለችው እንደ በስንቱ ያለ ወንድ... የሚከተሉትን የማድረግ እድሉ የመነመነ ነው፡፡

በፈለገው ሰአት ልጅ ማስወለድ አይችልም፡፡ ልጅ መውለድ የጋራ ውሳኔ የሚፈልግ ነገር ይሆናል፡፡ ስገባ ስወጣ ጎንበስ ቀና በይልኝ፤ ልብሴን እጠቢ፣ እግሬን እጠቢ፣ ምግቤን ከሽኚ፤ ተነጠፊ ተዘርጊ ማለት አይችልም፡፡ እሷም ስትሰራ ውላ፣ ደክሟት ነው የምትገባው፡፡ የሚያዝንላት፣ የሚያግዛት፣ የሚንከባከባት ባል ትፈልጋለች፡፡ እኔ ሳልፈቅድልሽ ከቤት መውጣት አትችይም ማለት አይችልም፡፡ ስራው በራሱ ከቤት መውጣቷን ግዴታ ያደርገዋል፡፡ እኔ ሳልፈቅድልሽ ገንዘብ ማውጣት አትችይም ማለት አይችልም፡፡ ሰርታ የምታገኘው ገንዘብ ነው፤ ነጻነት ያስፈልጋታል፡፡ የሀይል ሚዛኑን ለማስጠበቅ በሚል ሲወጣ ሲገባ ሚስቱን መቀጥቀጥ አይችልም፡፡ የዛሬዋ ሚስት የባልነት እና የሚስትነት መብትና ግዴታን በቅጡ የተረዳች ስለሆነች ከቧላ ስድብን፣ ዱላን፣ ንቀትን፣ ማን አለብኝነትን በጸጋ አትቀበልም፡፡ የዛሬዋ ሚስት የምትወደው የሚወዳት፤ የምታከብረው የሚያከብራት፤ የምታምነው የሚያምናት፤ ዋጋ የምትከፍልለት ዋጋ የሚከፍልላት፤ የምትንከባከበው የሚንከባከባት፤ የምታደምጠው የሚያደምጣት፤ ባል ትፈልጋለች፡፡

ዘመናዊው ትዳር በሁሉም ነገር የጋራ ውይይት እና ውሳኔ ይፈልጋል፡፡ ከሁለቱም ወገን ፍቅርን፣ መከባበርን፣ መረዳዳትን፣ መተሳሰብን ይፈልጋል፡፡ እኔ ወንድ ስለሆኑኩ አእንዲህ ይደረግልኝ፤ ሴት ነሽ እንዲህ አድርጊ ብሎ የሚነሳ ክርክር ካለ... ውሃ አይቋጥርም፡፡ ግጭትን እንጂ ሰላምን አይፈጥርም፡፡ መናናቅን እንጂ መከባበርን አያጎለብትም፡፡

ሂሩት ሰራተኛም ሆናም... ከወንዱ አንጻር ሲታይ የቤቷን የእለት እለት አስተዳደር በመምራት የሚስተካከላት የለም፡፡ ቤትን በአግባቡ ማስተዳደር ለሴት የተሰጠ መክሊት እስኪመስል ድረስ... ወንዶቹ ላይ መዝረክረክ ይታያል፡፡ መሰልቸት ይታያል፡፡ መማረር ይታያል፡፡ለአንድ ሳምንት ፊልድ ብትሄድ የተከሰተውን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡ የሂሩት ቤተሰቦች ውስጥ ብንገባ፣ በጡረታ እድሜ የሚገኙት የሂሩት እና እና አባት .... ሴት በሚል የወል ስም ምግብ የሚያበስለው ማነው? ቤት የሚጸዳው ማነው? በሌላ በኩል ወንድ በሚል ማእረግ ቁጭ ብሎ የሚቀለበው ማነው? ሆዱ ሲሞላ ደግሞ ወጣ ብሎ ቢራ የሚጠጣ፣ ኳስ የሚያይ፣ ከሰው ጋር የሚገናኝ ማነው?

ወንዱ Bread winner ስለሆነ፣ ባህሉ ስለሚደግፈው፣ ሀይማኖቱ ስለሚደግፈው፣ ... የቤቱ ራስ፣ የሴቷ አዛዥ ተደርጎ የሚቆጠር፣ ውጭ ሰርቶ ሲመጣ ቤት ውስጥ የንጉስ አይነት መስተንግዶ የሚገባው፣ እረፍት የሚገባው፣ መፈራት፣ መከበር የሚገባው፣ ምርጥ ምርጡ ሁሉ ሊቀርብለት የሚገባው፣ እሱ የሚለው ብቻ የሚደመጥለት ... ካልሆነ ደግሞ ሚስቱን በመደብደብ ጭምር አባወራነቱን የሚያረጋግጥበት ትዳር ነው የለመድነው፡፡ በተለይም ሴቷ ሙሉ በሙሉ የኢኮኖሚ ጥገኛ የሆነችበት፣ የመደራደር አቅሟ ዝቅተኛ የሆነበት ትዳር ነው የለመድነው፡፡
1.4K views14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 16:58:07
1.3K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 16:13:05
"ራሴን ልፈልግ" ብሎ
ሲብሰለሰል ሲብሰለሰል
አበደ
አገኘው መሰል

Rediet Asefa
red-8
1.5K views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ