Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.28K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-05-16 15:20:36
1.2K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 23:01:44
እግዜር…
ለሰው ሁሉ ያበደረውን
የህዝቡን ሁሉ ዕዳ…
በየቤቱ እየሄደ ሰረዘለት…
ከእኔ በቀር…

ያንተስ?

የኔንም ሊሰርዝልኝ
ቤቴ መጥቶ ነበር
ግን አጣኝ፣ አላገኘኝም።

የት ሄደህ?

ለሰው ያበደርኩትን
ልቀበል ሄጄ ነበር።

Rediet Assefa
red-8
1.2K views20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 21:28:15 እንግሊዝ ህንድን በቅኝ ግዛት ስታስተዳድር በነበረበት ጊዜ ነው። መርዛማ ኮብራዎች በዋና ከተማዋ ዴሊ እጅግ በጣም በዝተው አስቸገሩ። ከዛ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የእንግሊዝ መንግስት ኮብራ እየገደለ ላመጣ ሰው ሽልማት እሰጣለሁ ብሎ ተናገረ።

ከዛማ ምን ይጠየቃል ህዝቡ ኮብራዎችን የመግደል ዘመቻ ጀመረ። ይሄ እንግልጣር ያመጣው ዘዴ ለጊዜውም ቢሆን መፍትሄ ያመጣ መሰለ። ችግሩ የተከሰተው ግን በኋላ ነው።

ኮብራዎቹ እያለቁ መሆኑን የተረዱት የቢዝነስ ሰዎች ኮብራዎቹን ማራባት ጀመሩ።

ይህንን የሰሙት ህጉን ያወጡት ሰዎች ኮብራ ለገደለ እሰጣለሁ ያሉትን ሽልማት ማቆማቸውን አሳወቁ።

ይሄን ጊዜ ኮብራ አርቢዎቹ ሽልማቱ ከቆመማ ኮብራዎቹ ምን ያደርጉልናል ብለው እጃቸው ላይ ያሉ ኮብራዎችን ከተማው ላይ ለቀቋቸው። ይሄኔ ከቀደመውም የበለጠ የኮብራ ቁጥር በከተማው ላይ ተበተነ። ይህ ክስተት Cobra effect በመባል ይታወቃል።

አንድን ችግር እፈታለሁ ብሎ ችግሩን ማባባስ ማለት ይሄ ነው። ችግርን እንደገና አዋልዶ አዙሪት ውስጥ መዘፈቅ። ፖለቲካው ይሄ ደዌ አለበት።

ይህ ክስተት አንድን ችግር ለመፍታት የምንወስደው እርምጃ ምን ያህል ችግሩን ለዘላቂው ይቀርፈዋል የሚለውን የሚያሳይ ይመስለኛል።

ይህ እንዳይሆን የሚፈጠሩ ችግሮችን አይቶ በርቀት አልሞ ፣ በደምቡ ተልሞ እርምጃ መውሰድ ከመሰል ስህተት የሚያድነን ይመስለኛል !!

Altayeh Kidane
1.2K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 21:27:12
1.0K views18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 20:43:14

“ሠርቅ ማለት ከገዛ ሥሜ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ ጎበና ማለት በኦሮምኛ ሙሉ ጨረቃ ማለት ነው፡፡ ሠርቅ ቃሉ ግዕዝ ሲሆን፣ ወደ አማርኛ ስንመልሰው የጨረቃ ብርሃን ሠረቀብርሃን ማለት ነው፡፡ ለዚህ ነው ሠርቅ የሚለውን ሥም የተጠቀምኩት፡፡”



“የብዕር ሥም የምትጠቀምበት ምክንያት አንዱ ሕይወትህ ከሌላኛው ሕይወትህ ጋር እንዳይደባለቅ ነው፡፡”



“ራሴን እንደማንኛውም ደራሲ አይደለም የማየው፡፡ ደራሲ ነኝ የሚል ስሜት አይሰማኝም፡፡ ድርሰት መጻፍ ስጀምር ደራሲ ነኝ ብዬ አይደለም፡፡ አሁንም ደራሲ ነኝ ብዬ አልልም፡፡ ሥነ-ጽሑፍን ውስጡ ጠልቄ አይቼው አይደለም የምጽፈው፡፡ እንደማንኛውም ተራ ሰው ዝም ብዬ ውስጤ ያለውን እንጂ የማወጣው፡፡ ስለዚህ ተራ ሰው ነኝ፡፡”



“ሰውን በሳይንስ ሕግ አየውና ‹‹ሰው እንደዚህ ነው እንደዚህ›› እላለሁ፡፡ በስሜት ሰውን ስትገልፀው ሥነ-ጽሑፍ ጥሩ መንገድ ነው፡፡ ደረቅ ሳይንስ አይደለም እንጂ ሥነ-ጽሑፍ ራሱ ሰውን የምታይበት ነው፡፡”



“ሥነ-ጽሑፍ በተፈጥሮ እያንዳንዳችን ውስጥ ያለ ነገር ነው፡፡ ሳስበው ሁሉም ቁጭ ብሎ አለመጻፉ እንጂ እያንዳንዱ ሰው ውስጥ ሥነ-ጽሑፍ ያለ ይመስለኛል፡፡ ምንም አዲስ ነገር የለውም፡፡ ለኔ ሥነ-ጽሑፍ እንደማውራት ነው፡፡”



“<<ቆንጆዎቹ>>ን ስጽፍ ዕድሜዬ 22 ነበር . . ."



"[ሥነ ጽሑፍና ሥነ ልቡና] ... የሚደጋገፉ ነገሮች ናቸው፡፡ … ሥነ ጽሑፍ ስለሰው ሕይወት፣ ስለኑሮ፣ ስለማንነታችን ነው የሚገልፀው፡፡ ሥነ ልቦናም ስለሰው ማንነት ነው የሚያጠናው፡፡ ሁለቱም አቅጣጫቸው ይለያይ እንጂ ተመሳሳዮች ናቸው፡፡"



"... በ14 ወይም በ15 ዓመቴ ገደማ የጻፍኩትና ወደ 40 ገጽ የሚሆን ልብ ወለዴ አሁንም አለ፡፡ ያኔ የጀመርኩትን አሁን እንኳ መጨረስ አልቻልኩም፡፡ ስጀምረው ጠማማ ስለነበር ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ የተሻለ ጽሑፍ የጻፍኩት ዩንቨርስቲ 2ኛ ዓመት ተማሪ ሆኜ ነው፡፡ . . . ስለዚህ መጻፍ ጀመርኩ ማለት የምችለው ያኔ ነው፡- በ19 ዓመቴ አካባቢ፡፡ ከዛ ወደ 3 መጽሐፎች፣ አጫጭር ልብ ወለድ ጻፍኩ፡፡ ከነሱ በኋላ ‹‹ቆንጆዎቹ››ን … ከረዥም ዓመት በኋላ ‹‹የቃየን መስዕዋት››ን ጻፍኩ፡፡"



"... እውነትና ሀሰት ምን ይለያቸዋል?
ማለት አንድ ሰው አገሩን ብሎ ቤተሰቡን በትኖ ሄዶ ሲሰዋ፣ ቤተሰቡን መስዕዋት አቅርቧል፡፡ ያን ሰውዬ ጀግና አልነው፡፡ ሌላው ደግሞ ፅላት ሸጦ ቤተሰቡን ሲያኖር ለምን እንወቅሰዋለን? ኃጢአትና ጽድቅ የምንለው ነገር የት ላይ ነው መስመሩ?
እግዚአብሔር ኢየሱስን አሳልፎ ሲሰጥ፣ ‹‹ዓለምን ወደደ›› አሉ!... አብርሃም ይስሐቅን ሲሰዋ፣ ‹‹እግዚአብሔርን አፈቀረ››… ቃየን አቤልን ሲሰዋ ደግሞ ‹‹ርኩሰት›› ነው፡፡ እንዴት ነው? በማን ዕይታ ነው ይህ ፍርድ የሚወሰነው? ይሁዳ ኢየሱስን አልክድም አልሸጥም ቢል ኖሮ ክርስቲያን ሁሉ ምን ይውጥሽ ነበር...? ንገሩኝ! ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን የይሁዳ እጅ የለበትም ወይ? ይሁዳን ለምን እንረግመዋለን?
እና እኔ የምለው በጎና ክፉ ተደጋግፎ የሚኖር ነው፣ ነው፡፡ ክፉን ብናወጣውና ዓለምን ፅደቅ በፅድቅ እናድርግ ብንል ፅድቅ በራሱ አይኖርም ወይስ? … አላውቅም፡፡ ጥያቄ ነው፡፡"



"ሁሉም ሰው የሚፈልገውን ነገር ቢያገኝ ደስ ይለኛል፡፡ ይኼ የማይቻል ነገር አይደለም፡፡ የአንድ ሰው ልዩ ነገሩ ምንድነው? ብለን ብንፈልግለት፣ ዓለም ላይ እሱ የሚደፍናትን ቦታ ብንደፍንለት እያንዳንዱ ሰው የማይገኝ ሰው ነው፡፡ የሁሉንም ሰው ልዩ ነገር፣ ችሎታና ፍላጎት ብናይለት ሁሉም ነገር ይገኛል፡፡"

ምንጭ:- ኢትኦጵ መጽሔት፣ ቅፅ 5፣ ቁጥር 048፣ ሰኔ 1995 ዓ.ም)

Zerraff Metsahfet Medeber
1.0K views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 20:42:22
856 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 20:28:55 የምስኪኖቹን መንደር በስካቫተር ያፈረሰው ሚሊየነር ።

በደቡባዊ ቻይና ግዛት የምትገኘው የደሳሳዋ ዦንኪንግ መንደር ነዋሪዎች ፡ ሸቀጣሸቀጥ ጭነው ከሚመጡ አሮጌ ከባድ መኪኖች ውጭ አንድም መኪና ወደመንደራቸው ዘልቆ አይተው አያውቁም ። ዛሬ ግን እጅግ ዘመናዊ ፡ መርሰዲስ መኪና መጥታ ቆማለች ።

እናም ነዋሪዎች ፡ በመኪናዋ እዚህ መገኘት በመገረም ዙሪያውን ከበው በማየት ላይ እያሉ ፡ አንድ በጠባቂዎች የታጀበ እድሜው በሀምሳዎቹ የሚገመት ሰው ከመኪናው ወጣ ። ማንም ደፍሮ ሰላም ሊለው ወይም ሊያናግረው የመጣ ሰው ግን አልነበረም ። እናም ሰውየው መንደሩን ለደቂቃዎች ከተመለከተ በኋላ ተመልሶ ወደመኪናው ገብቶ ሄደ ።

ይህ በሆነ በማግስቱ ወደዛች ደሳሳ መንደር ሌላ መኪና መጣ ። ከመጡት ሰወች ውስጥ የትናንቱ ሰውዬ አልነበረም ። በቁጥር በዛ የሚሉ መሀንዲሶች ነበሩ የመጡት ። በዚህ ጊዜ ነዋሪዎቹ ነገሩ ገባቸው ፡ የትናንቱ ሰው ባለሀብት መሆኑን በሁኔታው አውቀዋል ፡ እናም ይህን መንደር ሊያፈርስ መሀንዲሶች ልኳል ።
................
እነዚህ ነዋሪዎች ፡ ይህም ኑሮ ሆኖ ፡ ደሳሳ ጎጇቸውን የሚያፈርስ ሰው ይመጣል ብለው መቼም አስበው አያውቁም ነበር ። እና ሽማግሌዎች ቀርበው መሀንዲሶቹን አናገሯቸው ። ፍርሀታቸው ልክ ነበር ፡ ትናንት የመጣው ባለሀብት እዚህ መንደር ላይ ሪል ስቴት መገንባት ፈልጓል ፡፡ ለዚህም ከመንግስት ፍቃድ እንዳገኘ ፡ ከሰባ በላይ ለሚሆኑት ለመንደሩ ነዋሪዎችም ካሳ እና መኖሪያ ቤት የሚገነቡበት ገንዘብ እንደሚሰጣቸው እስከዛ ግን በመጠለያ መቆየት እንደሚችሉ ፡ እስከነገ ድረስም እቃቸውን አውጥተው በተዘጋጀላቸው ማረፊያ እንዲያስቀምጡ ነግረዋቸው ሄዱ ።

ከቀናት በኋላም ፡ ብዛት ያላቸው ግሪደሮች እና የህንጻ ሰራተኞች ትንሿን መንደር አጥለቀለቋት ።
....................

ያለቻቸውን አሮጌ እቃ አውጥተው ከቤታቸው አቅራቢያ በተዘጋጀላቸው መጠለያ ውስጥ የገቡት የዦንኪንግ መንደር ነዋሪዎች ፡ ቆመው እያዩ ለዘመናት የኖሩባቸው ደሳሳ ጎጆዎች በስካቫተር ፈረሰ ።
.............

ቃል የተገባላቸው ቤት መስሪያ ቦታም ሆነ ካሳ ሳይሰጣቸው ለወራት በመጠለያ እየተረዱ ቆዩ ። ከአመታት በፊት ከነሱ ብዙም በማይርቅ ቦታ የሚገኙ መንደሮች ልክ እንደነሱ በጨካኝ ባለሀብት ተፈናቅለው ፡ መሰደዳቸውን እያሰቡ ፡ እጣ ፈንታቸውን መጠባበቅ ጀመሩ ።
........
ይህ በሆነ በጥቂት ወራት ውስጥም የባለሀብቱ ዘመናዊ ቪላዎች ተገንብተው ተጠናቀቁና ፡ ነዋሪዎቹ በስነስርአቱ ላይ እንዲገኙ ፡ በፕሮግራሙም ላይ ለነሱም ቃል የተገባላቸው ካሳ እንደሚሰጥ ተነገራቸው ። ብዙዎች ነዋሪዎች ግብዣውን ተቃወሙ ።
.......

ትንሿ የዦንኪንግ መንደር ዛሬ በልዩ ሁኔታ ደምቃለች ። ከሰባ በላይ ዘመናዊ መኖሪያዎችን ለመመረቅ የተለያዩ እንግዶች ተገኝተዋል ። ያቺ የድሆች መንደር ፡ አይታ በማታውቀው ሁኔታ በዘመናዊ መኪኖችና በሀብታሞች ተጥለቅልቃለች ።

የምረቃው ፕሮግራም ተጀመረ ።

ያ ፡ በመጀመሪያ ቀን መርሰዲስ መኪና ይዞ ወደዚህ መንደር የመጣው ባለሀብት ፡ ንግግር ለማድረግ ወደ መድረኩ ወጣ ።
ክቡራንና ክቡራት የዦንኪንግ መንደር ነዋሪዎችና ፡ ክቡራን እንግዶች ዛሬ ልዩ የሆነውን ይህን የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ፕሮጀክት ለመመረቅ ስለተገኛችሁ አመሰግናለሁ ።

እኔ የማየው ዛሬ ሚሊየነር መሆኔን አይደለም ። የኔ ስብእና የኔ የሀብት ምንጭ ይሄ መንደር ነው ።. ... እኔ ..... ትንሽ ልጅ ሆኜ የምታውቁኝ Xiong Shuihua ነኝ ። በርግጥ ከዚህ መንደር ከወጣሁ ብዙ አመታት ተቆጥረዋልና ፡ አላወቃችሁኝም ። እኔ ግን ሁላችሁንም አስታውሳለሁ ።

ለኔና እጅግ ድሆች ለነበርነው ቤተሰቦቼ በየወሩ ቀለብ ይቆርጥልን የነበረው ሚስተር ዣይን ፡ ከልጆቻቸው እኩል ልብስ ይገዙልኝ የነበሩት የሚስ ታዮኒ ቤተሰቦች ፡ ሲርበን የሚያበሉን የዚህ መንደር ነዋሪዎች ሁላችሁንም አስታውሳለሁ ።

የኔ የአሁን ህይወት ላይ የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጣችሁ እናንተ ናችሁ ። ለዚህም ነው መንደሩን ለመለወጥ በተሻለ ህይወት እንድትኖሩ ለማሰብ የተገኘሁት ።
እናም እነዚህ ቤቶች የተሰሩት ለናንተ ነው ። ያለምንም ክፍያ በነዚህ ቤቶች ትኖራላችሁ ። ቤቶቹ ንብረቶቻችሁ ናችሁ ። በነጻ የተሰጧችሁ አይደሉም ፡ ከአመታት በፊት ለኔና ለቤተሰቦቼ መልካም ነገር በማድረግ ኢንቨስት አድርጋችሁበታል ።

እያለ እንባ እየተናነቀው ሲናገር የመንደሩ ሰወች በሙሉ በታላቅ ድንጋጤ ውስጥ ሆነው ይሰሙት ነበር ።
ባለሀብቱ ንግግሩን ቀጥሏል ።
እናም ከሀምሳ ሚሊየን ዶላር በላይ ወጭ ተደርጎባቸው የተሰሩት ፡ እነዚህ ቤቶች በፈረሱት ቤቶቻችሁ ቁጥር ልክ የተሰሩ ናቸው ፡ ነገ አዳዲስ የቤት እቃ የጫኑ መኪኖች ይደርሳሉ ። መብራትና ውሀም አትከፍሉም ። መስራት ለምትችሉ የስራ እድል ይዘጋጃል ፡ ለአቅመ ደካሞችና ማብሰል ለማይችሉ ደግሞ ዘመናቸውን ሙሉ የሚፈልጉትን መርጠው የሚመገቡበት መመገቢያ አዳራሽም ተገንብቷል ። የናንተ ውለታ ከዚም በላይ ነው አላቸውና ፡ ከመድረኩ ወረደ ።
............
በሌላ ሀገር ፡ አንድ ግለሰብ ለወገኖቹ ይህን ያህል ያስባል ፡ በኛ ሀገር ደግሞ ፡ የምስኪኖች ቤት ሀላፊነት ሊሰማው በሚገባ በመንግስት አካል ፈርሶ ቤተሰብ ሜዳ ላይ ይበተናል። ልዩነታችን ይህን ያህል ነው።

Wasihune Tesfaye
1.1K views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 20:28:16
1.0K views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 21:51:18
ዋሽንትም እናትም…

Rediet Assefa
red-8
82 views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 21:49:06
አስተማሪው "ወፍ"

ተማሪው "እባብ"

የትምህርት ዐይነት: "በደረት መሳብ"

(አጀብ!?!?)

Rediet Assefa
red-8
97 views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ