Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.28K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-06-10 17:43:40
1.1K views14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:05:41 አሁን ይሄንን ሁሉ ትዝ ያስባለኝ ነገር ምንድነው? የኢትዮጵያችንን የታወቀ ጥንታዊ የአማርኛ በልሃ-ልበልሃ ድንገት እፊቴ እያየሁ ነው፡፡ አስደናቂ ነው፡፡ ጥንታዊ ነው፡፡ ለልጆች ሳይቀር እንደ ተረት ጨዋታ የሚነገር ነበር፡፡ የምክንያት አቀራረቡ፡፡ ክርክሩ፡፡ አስደናቂ ነው፡፡ የራሳችንን ይህን የመሰለውን ማጥናት ትተን... የምዕራቡን የሌሎችን የምናጠናበት ምክንያት እንቆቅልሽ ይሆንብኛል፡፡ አለፍ ሲልም አፍራለሁ በራሴ፡፡

በመደርደሪያዬ ላይ ድንቅ ድንቅ የምዕራቡ ዓለም የፍልስፍና መሠረቶች ተብለው የሚጠቀሱ የምክንያታዊነት፣ የፍልስፍና፣ የሙግት፣ የአስተሳሰብ፣ የክርክር፣ የፍርድ... መዓት ድርሳኖች አሉኝ - አሁን ራሱ፡፡ የሶክራቲክ ዳያሌቲክ፣ የማርክስ ዳያሌክቲክ፣ የሄግል ዳያሌክቲክ፣ የካንቲያን ዳያሌክቲክ፣... መዓት የምዕራቡን ዓለም ምክንያታዊና ሎጂካዊ አስተሳሰብ የፈጠሩ ቀደምት አስተሳሰቦችን የያዙ ድንቅ መድብሎች አሉኝ፡፡ አንብቤ አልጠግባቸውም፡፡ ጠጣሩ እስኪላላልኝ የላላውን እየወጠርኩ ነው የማጠናቸው፡፡ ... እደነቅባቸዋለሁ፡፡ ግን የኛስ?

የኛስ የራሳችን በልሃ-ልበልሃ! የራሳችን ... ጥንታዊ.. የምክንያታዊነት ፍተሻ! የኛ ጥንታዊው ነገርን ከሥሩ... የማስረዳት አዕምሯዊ ስልት! የኛስ አባቶች... ቅድመ -ቅመ አያቶች... ያካሂዱት የነበረው እንደ ታላቅ ‹‹አርት›› ራሱን ችሎ ኪኑ የሚያስደንቅ የምክንያታዊነት ፉክክር! የኛስ የቀደመ ለሰው ልጅ ምክንያታዊነት፣ የሃሳብ ክርክር፣ በዱላ ብቻ ሳይሆን... በአስተሳሰብ፣ በአርጊዩመንት፣ በቃላትና በምክንያት መርታት እንደሚቻል የሚያሳዩ የራሳችን ቱባ በልሃ-ልበልሃዎችስ?

ይሄን የኛን ለዘመናት የቆየ የኛን ‹‹በልሃ ልበልሃ›› እየው እስቲ በሞቴ! (እና ካልተደመምክበት እኔን ውሸታም፣ ዲስኩራም በለኝ...)፡-

(ከሣሹ እያስረዳ ነው ጉዳዩን በዳኞች ፊት፣ እንዲህ ይላል ተከሳሹን፣ ፡-)

‹‹በልሃ ልበልሃ
ጊደሬ ጠፍታ ከደጋ
እኔም መጥቼ ፍለጋ
ከደጅህ ስላገኘሁ ሙዳስጋ
ትሆናለህ ባለዕዳ!››

(ተከሣሹም ደግሞ በዳኞቹ ፊት ነጠላውን ያደገድግና.. ለከሣሹ ይመልሳል፡-)

‹‹በልሃ ልበልሃ
ጊደርህ ብትጠፋ ከደጋ
አንተም ብትመጣ ለፍለጋ
ከደጄም ቢገኝ ሙዳስጋ
ከቤቴ በላይ ትልቅ ዋርካ
አሞራና አውሬ የሚያሽካካ
አሞራና አውሬ ሲጣለፉ
ሙዳ ስጋ ቢተፉ
ከደጄም ቢገኝ ያ ሙዳ
አያደርገኝም ባለዕዳ!››

እያለ ይቀጥላል በልሃ-ልበልሃው! ጉድ እኮ ነው! ጉድ! አፌን ነው የሚያስከፍተኝ! It’s all full of reasons! It’s all about argument! Logic! Critic of reason! Critic of judgment! Assumptions! Counter-assumptions! Its just an amazing exercise of the mind and an amazing piece of art – an instant poetry!! ተገርሜ አላባራም! ይህንን የመሰለ የክርክር ባህላችን! ይህንን የመሰለ በምክንያቶችና በማስረጃዎች ላይ ተደግፎ የመናገር ብቃት! የማሳመን ብቃት! ይህንን ያክል በግራ በቀኙ የሳሉ ስል አዕምሮዎች! ያስደንቀኛል የኛ ሀብት! ግን... ምንዋጋ አለው!!?

... ያኔ ዶክተሩ እንዳለው... ያኔ ልክ ልኬን እንደነገረኝ! የእኛን ነገር! የኛን የራሳችን ውርስ የሆነውን ስንቱን ውድ ነገራችንን! የኛን ማን ያጥናልን? ማን ያጥናልንና አንድ ባለቤት ሰጥቶ... የካንት ፍልስፍና... ክሪቲክ ኦፍ ጀጅመንት... ምናምን እያለ መጽሐፍ ያሳትምልን? ማን ለራሳችን ትውልድ ይንገርልን የራሳችንን ዘረያዕቆቦች... የራሳችንን ባለቅኔዎች... የራሳችንን የሪዝን.. የምክንያትና የነገር ፍልስፍና ማን አጥንቶ ዓለምን ያስደምምልን? ማን ትውልዳችን ከራሱ መሠረት ላይ እንዲነሳ ይምራልን? አላውቅም! ግን አዝናለሁ! በሁላችንም! በራሳችን ነገር!

የእኛ ነገር በብዙ አላስፈላጊና አፍራሽ ነገሮች ተጠምደን... ያንኑ መልሰን መላልሰን ስናቦካ.. ስንጋግር... አንዳንዱ ነቄ ዓለም የራሱን አስተሳሰብ ቀርፆ... ከራሱ አልፎ.. ዓለምን በራሱ አምሳል ዓለሙን.. የዓለሙን ህዝብ ሁሉ ጠፍጥፎ እየቀረፀው ነው፡፡ መቼ ነው የምንነቃው! ነቄ የምንሆነው? ነቄ ትውልድ የምንፈጥረው! መቼ ነው? - ይናፍቀኛል! ሁላችንም ጣት ሳንጠቋቆም የየራሳችንን ሀገራዊ የቤት ሥራ የምንሠራበትን... ራስን የመውደድ ዘመን... ራስን የማክበር... ለራስ የማወቅን ብሩህ ዘመን እናፍቃለሁ!

ፈጣሪ ድንቅ እናትሀገራችንን በፍቅር ይባርክ!

አበቃሁ!

Assaf Hailu
2.5K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:05:41 የሰው ወርቅ አያደምቅ!

(የማይደበዝዙ ምክንያታዊ ሂሶች)

ከዓመታት በፊት በአንድ ኮሌጅ የምሽት ፕሮግራም አንድ የዓለማቀፍ ህግ ኮርስ እሰጥ ነበር፡፡ ከተማሪዎቹ መሐል ህግን የማወቅ ፍላጎት ያደረባቸው በተለያዩ ፕሮፌሽኖች ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ይገኙ ነበር፡፡ እና ይህ በሌላ ሙያ ፒኤችዲ ያለው ዶክተር.. እኔ ክፍል እየገባ ይማራል፡፡

ዶክተሩ ተማሪ በጣም ደስ የሚሉ የመጠቁ ሃሳቦችንና አስተያየቶችን በነጻነት ይሰጣል፡፡ ያልገባውን ማንኛውንም ነገር አያልፍም፡፡ ያልተስመማባቸው ነገሮች ካሉም አያሳልፍም፡፡ በጣም እወደዋለሁ፡፡

.. በየሙያችን የያዝነውን ይዘን ወደሌላ የትምህርት መስክ ስንቀላቀል.. ሰፋ ያለ አድማስ ይዘን ነው የምንቀላቀለው፡፡ ብዙ insight እና አቅም ይሰጣል፡፡ አንዳንዴ በምዕራቡ የአንግሎ-ሳክሰኑ ዓለም ህግ ለመማር መጀመሪያ በሌላ ሙያ ዲግሪህን መያዝ ለምን እንደቅድመ ሁኔታ እንደተቀመጠ... ሳስብ.. ይሄ ሰው ትዝ ይለኛል፡፡ በእርግጥም ያ ልማድ ከፍ ያለ ጠቀሜታ እንዳለው እንደዚህ ሰው ያሉ ጥቂት የማይባሉ ክሪቲካል ሰዎችን እያየሁ በቂ ምስክር ሆነውኛል፡፡

ታዲያ የተለያዩ ሙያዎችንና ልምዶችን ይዘው ወደመጡ ተማሪዎች ስገባ... (በተለይ በምሽት ፕሮግራሞች ላይ) ተማሪዎችን ለማሳወቅ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ተማሪም ሆኜ ነው፡፡ እና ጓደኞቹን እንደሚያገኝም ሰው ሆኜ፡፡ ብዙ ነገር ለራሴም ይዤ ለመውጣት ነው የምገባው፡፡

አሁን የወጣለት ፖለቲከኛ የሆነው የቀድሞው የሎውስኩል ሲኒየሬ ፀጋዬ ረጋሳ (አሁን ዶ/ር ፀጋዬ አራርሳ)፣ በአንድ ወቅት በህግ ት/ቤት የተማሪዎች መፅሔት ላይ ያሳተማት ደስ የምትል አርቲክል ትዝ ትለኛለች፡- ‹‹ዴሲዶ ዴሰመስ - እየተማሩ ማስተማር›› የምትል ነበረች፡፡ በመምህርነት ባሳለፈው ልምዱ ካስተማረው እኩል ከተማሪዎቹ ብዙ ነገሮችን እንደተማረ በማስመልከት የጻፈው ነው፡፡ ከጥንት ላቲን ጀምሮ የነበረ ልማድ፡፡ ‹‹ዴሲዶ ዴሲመስ››፡፡ እያስተማሩ መማር፡፡ ጥሩ አድርጎ ነበር የፃፈው፡፡

ታዲያ እኔም ‹‹ዴሲሞ ዴሲመስ›› ሆነና... ስለ ዓለማቀፍ ህግ ምንጮች.. (ከየት ከየት ተለቅሞ ነው የመጣው የዓለም ህግ?)... የሚለውን እንደወትሮዬ በተቻለኝ መጠን መሳጭና ሰፋ ያለ አድርጌ ለተማሪዎች አቀረብኩ፡፡ ሶስት አካባቢ ክላሶች የፈጀብኝ ይመስለኛል፡፡ ይሄ ዶክተር ተማሪ ያለወትሮው ያለምንም ጥያቄና አስተያየት ሁሉንም እስክጨርስ ኖት እየያዘ ሲያዳምጥ ቆየና በመጨረሻ ግን ‹‹አሁን ወደሌላ ርዕሰጉዳይ እንሸጋገራለን›› ስል... ንዴቱን መቆጣጠር አቃተው! እና እንዲህ አለኝ... በጣም በንዴት ተሞልቶ

‹‹ቆይ እናንተ የዚች ሀገር ምሁሮች... ምንድነው የነካችሁ ነገር?
በጣም ነው የሚገርመኝ! አሁን አንተ የዓለም ሀገሮችና ታሪኮች
ሁሉ እንዴት አሁን ላለው የዓለማቀፍ ህግ ሥርዓት ምን
እንዳበረከቱ... እንዲህ ደስ በሚል ሁኔታ እየተነተንክ
ስታስረዳ ቆይተህ... እንዴት የራስህ ሀገር ኢትዮጵያ
ለዓለማቀፍ ህጉ ያበረከተችውን... አንዲት እንኳ አስተዋፅዖ
ሳትናገር... ሳታጠና.. ሳትፈልግ... ሳታዘጋጅ... አበቃሁ ትላለህ?

‹‹በቃ አለቀ? ኢትዮጵያ አንድም አበርክቶት የላትም
ለዓለምዓቀፍ ህግ? ... ለምን የሌሎችን ከምታነበንቡ
(ከይቅርታ ጋር - እያለኝ እኮ ነው ልክ ልኬን የሚነግረኝ)..
ለምን ጊዜ ወስዳችሁ...
የራሳችንን አጥንታችሁ አታስተምሩንም?!

‹‹ሌሎች ፈረንጆቹ.. ሁሉም.. የራሳቸውን አስተዋፅዖ በመፅሐፍ
አሳትመው እናንተን አስተማሩ... እናንተ ደግሞ የኛን አስተዋፅዖ
አጥንታችሁ ልታስተምሩን ሲገባ... ያንኑ የእነሱን አምጥታችሁ
ትነግሩናላችሁ? ...

‹‹እኛ አስቀድመን ክርስትያንና ሙስሊምን አብረን ያኖርን
ሀገር አይደለንም? የሌሎችን የሐይማኖት ነፃነት የማክበር
ልምድን ለዓለም አላሳየንም እኛ? የውጭ ሀገራት ቆንሲሎችንና
መልዕክተኞችን እየተቀበሉ ጠብቀው፣ አክብረው፣
ተንከባክበው ወደመጡበት የሰደዱ ጥንታዊ ንጉሣን
አልነበሩንም እኛ? ..

‹‹ለዓለማቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ህግ ያበረከትነው ምንም
አስተዋፅዖ የለም? ሴቶች በኛ ሀገር ንግሥት ሆነው አልኖሩም?
ለሴቶች እኩልነት ዓለማቀፍ ህግና አስተሳሰብ እኛ
ያበረከትነው ምንም ነገር የለም?

‹‹በጦርነት ምርኮኞችን የመንከባከብ፣ ቁስለኞችን የማከም
ልማድ በእኛ ዘንድ የለም? የሌሎችን ድንበር የማክበር...
የራሳችንን የማስከበር... ከጥንት ጀምሮ ያቆየነው ልማድ
የለንም እኛ ኢትዮጵያውያን? ከአፍሪካ ብቸኛዋ
በሊግ ኦፍ ኔሽንስ ውስጥ አባል ሆና ያበረከተችው
አስተዋፅዖ የለም ይቺ ሀገር...?

‹‹እና በቃ ‹‹የዓለማቀፍ ህግ ምንጮች›› ብለህ... የሌሎችን
የአውሮፓዎችን የቱርኮችን የራሺያኖችን የአሜሪካኖችን.. ወዘተ
አስተዋፅዖ ብቻ እነሱ እንዳስተማሩህ ዘርዝረህ... በቃ
ጨርስክ ትምህርቱን እዚህ ላይ? የኛስ አስተዋፅዖ?

‹‹ለምን የኛን አስተዋፅዖ አጥንተህ፣ መርምረህ፣ አታስተምረንም?
አንተና አንተን የመሰሉ ሰዎች ካላጠናችሁት የኛን አበርክቶት...
ማነው የሚያጠናልን? ማን ያጥናልን? በጣም ነው የማዝነው
በኛ ነገር አሣፍ! በተለይ ካንተ ብዙ እጠብቅ ነበረ... !
በጣም ነው የማዝነው››

ብሎኝ ንዴቱ እንደፋመ አበቃ! ልክ እንደ ትልቅ ሌክቸር ነበር የቆጠርኩት በእውነት! አፈርኩ! ዓይኔን ነው የገለጠልኝ፡፡ ብዙ መጻሕፍት ነበሩኝ በዚህ ጉዳይ፡፡ ብዙ አነባለሁ፡፡ ደስ የሚለኝም ርዕሰጉዳይ ነበር፡፡ ግን ለአንድም ቀን... ያገሬስ አስተዋፅዖ ምንድነበር? እስቲ ላጥናው! ላደራጀው! አሳምሬ ልወቀው... እና እንደ አንድ የኮርስ አጋዥ ማቴሪያል... ለሌሎች ላስተምረው... የሚል ሃሳብ በጭራሽ መጥቶብኝ አያውቅ ነበር፡፡

የዶክተሩ ወቀሳ ትክክል ነበር፡፡ በከፍተኛ ተመስጦና በትዕግሥት እስኪጨርስ አዳመጥኩት፡፡ አፈርኩ! አመንኩለት፡፡ ሌሎችም ብዙ አስተያየት ሰጡ፡፡ እና አንድ ኮርስ አድርገህ ራሱ ብታስተምረን በኛ በኩል የፈለገውን እናደርጋለን፣ ለኮሌጁም ማሳወቅ እንችላለን ትብብር ከፈለግክ አሉ፡፡ ሁሉም በየራሱ የተለያየ ሃሳብ አዋጣ፡፡ የሚገርም አካዳሚክ አርበኝነት ነገሠ በዚያች ጠባብ የምድር ክፍል፡፡ እና እያስተማርኩ ተማርኩ፡፡

አሁን ብዙ ዓመቶች ተቆጠሩ፡፡ በየአጋጣሚው የዓለማቀፍ ህግን የተመለከቱ ነገሮች በሰማሁ ቁጥር ያ የዶክተሩና የክፍል ተማሪዎቹ ንግግሮች በሀሳቤ ውልብ ይላሉ፡፡ አደራቸው ጎሸም ያደርገኛል፡፡ በእርግጥ እኔ የዓለማቀፍ ህግ ምሁርም አይደለሁም፡፡ የማውቃትን ታህል ለሌሎች ለማካፈል ጥረት የማደርግ አንድ ተራ ሰው ነበርኩ፡፡

ግን በሀገራችን በዚህ ዘርፍ ብቻ ራሱን ችሎ ያጠኑ፣ የተመራመሩ፣ ብዙ ነገሮችን የዳሰሱ ጥቂት የማይባሉ የዓለማቀፍ ህግ ምሁራን እንዳሉን አውቃለሁ፡፡ በየአካዳሚክ ተቋማቱ ያሉ፡፡ ብዙ አሉን፡፡ ግን ይሄን እኔ በወቀሳ የቀረበልኝ ጥያቄ ቀርቦላቸው ያውቃል ወይ?... ይሄንን ለማድረግስ ተነሳስተው ይሆን ወይ? የተሠሩ ጥናቶችስ ይኖሩ ይሆን ወይ... ? ለዓለም የኛን አስተዋፅዖ ቆጥረው ለክተው በማስረጃ አስደግፈው የሚያስረዱልን? አላውቅም፡፡ ብዙ ርቄያለሁ፡፡ እንኳ በመጻፉ፣ በማንበቡም የለሁበት፡፡
1.9K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:05:27
1.1K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:04:13 ቆይ ቆይ.. ደቡብ አፍሪካ በአፓርታይድ የዘር እሳት ስትለበለብ.. ኢትዮጵያ የት ነበረች? ምን አደረገች? ኢትዮጵያ የዚያኔ አቢሲንያ እየተባለች ትጠራ ነበር፡፡ በዓለም መንግሥታት ድርጅት ውስጥ ብቸኛዋ የጥቁር አፍሪከ ወኪል የሆነች አባል ሀገር ነበረች፡፡ እና ታሪክ መዝግቦ ባቆየን ታላቅ የሰብዓዊነት ተግባር... በ1928 ላይ በመንግሥታቱ ምክርቤት የደቡብ አፍሪካን አፓርታይዳዊ መንግሥት በጥቁር ህዝቦቹ ላይ ስለሚፈጽመው ግፍ እርምጃ እንዲወሰድበት ክስ አቀረበች!!

ዛሬ ያች ሀገር የት ነች? ኢትዮጵያችን የት ነች? የአቢሲኒያችን ልጆች ምን እያደረጉ ነው? መልሱን እተወዋለሁ፡፡ ዛሬ ደግሞ አይርላንድ ሆናለች በኛ ምድር ላይ በተተከለው መንግሥታችን ላይ... በተባበሩት መንግሥታት ምክርቤት የኢትዮጵያ መንግሥት ሰብዓዊ መብትን እየጣሰ ነውና ይቀጣልኝ ብላ የምትከሰን! ወቸ ጉድ! አይ ታሪክ! ሲያልቅ አያምር! መሆናችን ያስቆጫል! ካላስቆጨ ግን ያስለቅሳል! ከዚህ የበለጠ ሀገራዊ ትራጀዲ ከየት ይምጣ!

እንግዲህ ወደ ደቡብ አፍሪካውያኑ መጽሐፌ ልመለስ፡፡ ሀገርምድርም ገጸባህርይ ከነበረ የዚህ መጽሐፍ.. ሰው ብቻ አይደለም የሚያለቅሰው፡፡ ብለውታል የሊትረሪ ክሪቲኮቹ፡፡ እኛ የምናውቀው.. ምናልባት ‹‹ሀገርም እንደሰው ይናፍቃል ወይ?› የሚለውን ዜማ ነው፡፡ ግን ሀገር መናፈቅ ብቻ አይደለም፡፡ ሀገር እንደ ሰው ያለቅሳል፡፡ እንባው፣ ማድያቱ በሁሉም ሥፍራ ይታያል! ሀገርም ያለቅሳል!

አልቅሺ የተወደድሽ እናትሀገር አልቅሺ!

በያለንበት፡፡ ለኛም፡፡ ለሁሉም፡፡ ለሰው ልጆች ሁሉ፡፡ ላገር ለምድሩ ሁሉ፡፡ እንባን የሚያብስ በተስፋው ይጎበኘን ዘንድ፣ በፍቅሩ ህመማችንን ያድነን ዘንድ ከልብ ተመኘሁ፡፡

ደራሲዎቼን አመስግኜ አበቃሁ!

ቻው !

Assaf Hailu
965 views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:04:12 ግድየለም ልጅሺ አብዝቶ በደስታ አይሳቅ ፡፡

.. የምትጠልቀው ፀሐይ ብርሃኖቿን ፈንጥቃ
መስኩን ስታለብሰውም... በእሳቷ ውብ ጮራ...
ብዙም አይንጎድ ልጅሺ በፅሞና..፣
አይማረክ በሰፈር ባድባሩ ፋና፡፡

አዕዋፎች ጥዑም ዜማቸውን ሲያበስሩ...
ግድየለም ይቆየው እርሱም..
ልቡን አይስጥ ላገርምድሩ፡፡

ልቡን አብዝቶ አይስጥ.. ላገሩ ተራራ ሸለቆ..፣
ፍርሃት ልቡን ያገኘው ዕለት፣
የሰጠውን ልቡን በብዛት፣
ጠራርጎ እንዳይወስድበት... ፡፡

አልቅሺ፣
የተወደድሽ እናትሀገር አልቅሺ..፣
አልቅሺ.. ገና ላልተወለደው ልጅሺ . . ፡፡”

ለቅሶ ለምን? ለቅሶ ለምን አስፈለገ? ራሴን ደጋግሜ ጠይቄያለሁ! ድሮ የስቲቭ ቢኮን ታሪክ ሳነብም፣ ፊልሙን ሳይም፣ አሁንም ከሁሉ የቀደመውን የአልቅሺ እናትሀገሬን የአለን ፔተንን መጽሐፍም እየገለጥኩ.. ራሴን ደጋግሜ ጠይቄያሉ..፡- ‹‹ለምን ለቅሶ?››፡፡ ብዙ አምሰልስዬዋለሁ ይሄን ጥያቄ፡፡ ሳስበው የተሸነፈ ሰው ማድረግ የሚችለው ለቅሶ ሆኖ ታየኝ፡፡

ከወደቀበት.. ከሚረገጥበት.. ከሚገብርበት መሬት ተነስቶ አያሸንፍ ነገር... አከርካሪው ተሰብሯል ተብሏል፡፡ ተልፈስፍሷል ሀሞቱ፡፡ ክንዶቹ ዝለዋል፡፡ የጀግና መንፈሱ ተሰልቧል፡፡ ልጆቹን ቀጣይ ትውልዶቹን ለጀግንነት አያነሳሳ ነገር.. የሌለውን እንዴት? ከወደየት አምጥቶ በራሱ ትውልድ ያልተገኘውን፣ የሌለውን ጀግንነት ይሰጣል ለሌላ ትውልድ? ስለዚህ የቀረው ነገር ማልቀስ ይመስለኛል!

ማልቀስ.. እና ልቡን መንፈግ! ሀገሩን እየወደደው... የማይወደው መምሰል፡፡ በሀገሩ ውበት ያልተመሰጠ መምሰል፡፡ በሀገሩ መከፋፈል ቆሽቱ ያላረረ መስሎ ማለፍ፡፡ በአበቦቹ ውበት ያልተደሰተ መስሎ መገኘት፡፡ በሳር ምድሩ ሽታ ያልተማረከ... ከመሬት ተቆፍሮ በሚወጣው ወርቅ ልቡ ያልሸፈተበት መስሎ መገኘት፡፡...

.. ሰዋዊ ስሜቶቹን ሁሉ ማበደን፡፡ በቁሙ ራሱን መግደል፡፡ በቁሙ ሀሞቱን መግደል፡፡ በቁሙ የሚወደውንና አሳልፎ መስጠት የማይፈልገውን ነገር የማይወደው መስሎ አሳልፎ መስጠት፡፡ እና ፍቅር ከልብ እንደሌለ... አንድነት በመካከል እንደሌለ.. ጀግንነት እንዳልተፈጠረ ሁሉ... እርስበርስ ተጠላልቶ በመገኘት፡፡ እርስ በርስ በመቧጨቅ፡፡ ነው ራሱን የሚደብቀው የተሸነፈ ህዝብ፡፡ ይህ የነጻነት ማጣት የሚያስከትለው... ‹‹ዲጀነሬሽን›› ወይም ‹‹ዲናያል›› አስገራሚ ጉድ ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡

ጭቆና የማያመጣው ነገር የለም፡፡ ፍርሃትና ታይቶ የማይታወቅ ማስመሰልን ብቻ አይደለም ጭቆና የሚያመጣው፡፡ ፍራንዝ ፋነን በአልጄሪያ እስርቤቶችና ፖሊስጣቢያዎች፣ በአዕምሮ ህክምና ማዕከላትና ማገገሚያዎች ውስጥ ዘልቆ ተመራምሮ ‹‹በምድር ጎስቋሎች›› (በ“Wretched of the Earth”) መጽሐፉ እንዳስቀመጠው... በፍጹም ጭቆና ሰብዓዊ ስሜቶቹን የተነፈገ ሕዝብ... ታይቶ የማይታወቅና... ከማንም ሰብዓዊ ፍጡር የማይጠበቅ የጋራና የግል የጭካኔ ጠባይም ሊያመጣ ይችላል፡፡

አንድ ሰው ሲታወክ የሚቃወሰው የአንድ ሰው ህሊና ይሆናል... ብዙ ሰው.. ያገሩ ህዝብ እንዳለ ሲታወክ.. ሲገረፍ.. ሲወረፍ.. ሲዘረፍ... ሲጨቆን ግን... ያገሩ ህዝብ ሁሉ የሆነ የጋራ ተዛማች የጭካኔ ‹‹ማኒያ›› ውስጥ ይገባል፡፡ ይል እንደነበረው ነው ፍራንዝ ፋነን፡፡ በአፋኝ ሥርዓት ውስጥ የተንበረከከ ህዝብ አንድም እርስበርሱ ባለ በሌለ ጭካኔ ይበላላል! ሁለትም ደግሞ ሆ ብሎ የተነሳ(በት) ቀን... ገዢዎቹን.. ጨቋኞቹን ከሰብዓዊ ስሜት በራቀ አውሬያዊነት ዘነጣጥሎ ቆዳቸውን ገፍፎ ይበላቸዋል!!

ስቲቭ ቢኮም ዶክተር ነው፡፡ ፍራንዝ ፋነንም ዶክተር ነው፡፡ ህዝባቸውን የመሩትና የተነተኑት የህዝባቸውን ስነልቦና አኝከው አብላልተው በሚገባ አውቀውት ነው፡፡ አለን ፔተንም የሚለው ይሄንኑ መሰለኝ፡፡ በጭቆና ውስጥ ያለ የተሸነፈ ማህበረሰብ ጥቂት ይነፋረቃል፡፡ ጥቂት ጥቂት ይፈራገጣል፡፡

ከዚያ ራሱን ይክዳል፡፡ ስሜቱን ይክዳል፡፡ ሀገሩን ይክዳል፡፡ ፍቅሩን ይክዳል፡፡ ፍራቱንም ይክዳል፡፡ ፈራሁ ላለማለት.. ፈርቼ አስወሰድኩት ላለማለት.. ቀድሞውኑ አልፈለግኩትም ነበር.. የሚል ወኔ-ቢስነቱን የሚያረሳሳ ማካካሻ ስነልቡና ይፈጥራል ለራሱ! ወይም ይፈጠርበታል! ወይም ከዚህ በቀር አማራጭ የለውም! ...

ከዚያ የሚያፈራውም እሱኑ የመሰለ ትውልድ ይሆናል! የጎባጣ አሽከር ጎባጣ እንዲሉ!! በመጎናበስ የጎበጠ ትውልድ የሚተካው እንደራሱ የጎበጠ፣ የፈራ፣ የተጎናበሰ ትውልድን ነው፡፡ አሁን በአንዳንድ ያለም ክፍሎች ላይ የምናያቸው ቅስማቸው የተሰበሩ የቀደሙ ተሸናፊ ህዝቦች ተራፊዎች የዚህ እውነት ትክክለኛ ማሳያዎች ይመስሉኛል፡፡ የሚያሳዝን እውነት ነው፡፡

ደቡብ አፍሪካዎች ከዚህ አፓርታይዳዊ የዘር ልዩነትና አፈና ሥርዓት ከወለደው የከረመ የፍርሃት ቆፈን ወጥተው መብታቸውን ባደባባይ በእጃቸው ጨብጠው ማስከበር ሲጀምሩ... በ1990 ማንዴላ ከእስር ተፈታላቸው፡፡ የዚህ መፅሐፍ ደራሲ አለን ፔተን የማንዴላን ከእስር መፈታት አይቶ በ1992 ነው የሞተው፡፡

ከሁለት ዓመት በኋላ ማንዴላ የመጀመሪያው ጥቁር ፕሬዚደንት ሆኖ ሲመረጥ ግን ለማየት አልታደለም ደራሲው፡፡ የሚወደውንና በእንባም በእግዜር ቃልም በጀግና ቃልም የጮኸለትን ያገሩን አፈር ለብሶ አሸልቧል፡፡

ሞት አይቀርም፡፡ አንዳንዶች አፈንድደው ተጎናብሰው እያለቀሱ ይሞታሉ፡፡ አንዳንዶች የታያቸውን ከመጎናበሱ ባሻገር ያለውን ቀን ለዓለም አሳይተው ያልፋሉ፡፡ አንዳንዶች እና ከፍ ሲልም እልፎች ደግሞ... ያንን ሌሎች የታያቸውን ነጻነት ተጎናፅፈው ቀና ብለው ይሞታሉ፡፡ ሞት ካልቀረ ጀግና ተሆኖ ቢሞት! ፈክሮ ቢሞት! ሰው ሆኖ ቢሞት! እና ቢቻል አፍቅሮ፣ ተፈቅሮ፣ በፍቅር ሙክክ ተብሎ ቢሞት!

በፍቅር የሚሞቱት ደግሞ የሰዉንም የእግዜሩንም ፀጋ ተላብሰው ነው የሚሞቱት! በሰው ልጅ ታሪክ ሰውን ከሰው እያበላለጥን ስንመዘግብ... ፈሪ ሆነው የሚሞቱት ከሰውነት ፀጋ የጎደለባቸው አለ፡፡ ጀግና ሆነው የሚሞቱ የታደሉ ብፁዓን ናቸው! በፍቅር ጀግነው የሚሞቱ ግን ከሁሉም የበለጡ ሆሞዲየሶች... ከፍ ያሉ ሰብዓዊ የአምላክ ምርጦች! በአክሊል የተንቦገቡጉ ብፁዓን ናቸው!

አልቅሺ የተወደድሽው ውድ እናትሀገሬ! አልቅሺ! - የዚህ መጽሐፍ ዘመናዊ ክሪቲኮች (አርታኢዎች) ይህን መጽሐፍ ሲያንቆለጳጵሱ ምን ይሉታል... ? አለን ፔተን እኮ... በዚህ መጽሐፉ ዋና ገፀባህርያ ያደረገው ሰውን ይመስላል እንጂ... መሬቱ ራሱ ነው ገፀባህርይው! ያገሩ አፈር! መሬቱ ሳርቅጠሉ! እሱ ነው ሳናየው የሚያለቅሰው ዋና ገፀባህርዩ! ይሉታል! መታደል ነው!

ኒችም የሆነን ፒራሚድ እያሰበ ነበር የዛራቱስትራን ገፀባህርይ ፅፎ የሰጠን፡፡ ናዚዎች ዶችላንድን.. አባትሀገራችንን እያሰበ ነው ይሉታል፡፡ እኛ ደግሞ ያገርፍቅር ያንቀጠቀጣቸው ደራሲዎቻችንን... እንደ ራሺያኖች እናትምድር ብሎ እንደሚፅፍላቸው እንደ ጎርኪ ያሉ... እንደ አባ ጋሼ ሃዲስ ያሉ.. ቱባ ደራሲዎቻችንን ያብዛልን... ያክብርልን ብለን... ብናበቃስ!
946 views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:04:12 የተወደድሽ እናትሀገር.. አልቅሺ..!!
(“Cry, the Beloved Country”, Alan Paton (1948, 1987)

የአፓርታይድ የዘር ልዩነትና መድልዎ ፖሊሲ በደቡብ አፍሪካ ሲተከል ብዙ መሰረቶች ነበሩት፡፡ እንግሊዞች ብቻ አይደሉም ተጠያቂዎቹ፡፡ ምናልባት ከእነርሱም በባሰ መልኩ፣ በእንግሊዞቹ ‹‹በቦርስ›› ጦርነት የተሸነፉት... እና የመጀመሪያዎቹ የደቡብ አፍሪካ አውሮፓዊ ገዢ ለመሆን የበቁት.. የኔዘርላንድ ተወላጆች ተጠያቂዎች ናቸው፡፡

አፍሪካነሮቹ በእንግሊዞቹ ከጆሃንስበርግና ኬፕታውን.. ከሌሎቹም አካባቢዎች ሶስት ዓመት በተዋጓት እንግሊዝ ድባቅ ተመትተው ሲሸነፉ... የፈጠሩት ‹‹አፍሪካነር›› የሚባል የድቅል ቋንቋና ማንነት የተላበሰ አካል በደቡብ አፍሪካ የኦሬንጅና ፍሪናታል ግዛቶች የነበሩትን ከሀገሬው ከዙሉዎችና ከዞሳዎች ላይ በጉልበት ነጥቆ.. ያገሬውን ጥቁር ህዝብ አስገብሮ አፓርታይዳዊ እግሩን በግማሽ ደቡብ አፍሪካ ላይ መትከል ቻለ፡፡

አዲስ ከለራቸው የነጣ ገዢ መደብ ሆነው በደቡብ አፍሪካ ብቅ ያሉት እነዚህ እንግሊዞችና አፍሪካነሮችም ብቻ አይደሉም፡፡ በአብዛኛው በናታል አካባቢ ኑሯቸውን የመሠረቱ ከፍ ያለ ቁጥር ያላቸው (በወቅቱ ሩብ ሚሊየን የሚደርሱ) ህንዶችም ነበሩ፡፡ እንግሊዞቹ እያጓጓዙ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ሆነው እንዲያገለግሏቸው.. እንዲነግዱላቸው ያመጧቸው ዘሮች ናቸው፡፡ አሁንም ድረስ አሉ እዚያው፡፡ በዝተው፡፡ ሁሉም፡፡

ይሄ “Cry, the Beloved Country” መጽሐፍ ያኔ የአፓርታይድን ፖሊሲ በደቡብ አፍሪካ ሽንጧን ገትራ በደገፈችው በአሜሪካ ምድር የታተመ መጽሐፍ መሆኑ ሳይደንቅ አይቀርም፡፡

ደራሲው አለን ፔተን.. በጊዜው ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ባሉ እስርቤቶች... በኃላፊነት ይሠራ የነበረ ተቀጣሪ የፖሊስ ሱፐርኢንቴንደንት ነበረ፡፡ እና ልምድ እንዲያገኝ ተብሎ... በሰሜን አሜሪካ.. በካናዳ.. በዩኤስ አሜሪካ.. በእንግሊዝ... በአውስትራሊያ... በጀርመን.. ፈረንሳይ.. ቤልጂየም ወዘተ በሚገኙ እስርቤቶች ሁሉ እየዞረ የከርቸሌ ልምድ በመቅሰም ላይ የነበረ አፍሪካነር የሆነ የከርቸሌ ዘብ ነበር፡፡

እና በተለይ ሌላውን ዓለም ሲመለከት... ባገሩ በደቡብ አፍሪካ ያለው.. የሚሠራው ግፍ እረፍት ነሳው፡፡ ከውጭ ሆኖ ወዳገሩ በየመሐሉ እየተመላለሰ ብዙ ነገሮችን ሲቀዳና ሲያጠና ከቆየ በኋላ በመጨረሻ ከአሜሪካ ሆነው በፈቃዳቸው ባሳተሙለት በጎአድራጊ ሰዎች አማካይነት ለህትመት አበቃው፡፡ እና አብቅቶት ወዳገሩ ተመለሰ፡፡ በሠላም፡፡

የመጽሐፉ ዋና ገፀባህርይ የሆነው .. በእነዚያ ክፉ የአፓርታይድ ክፉ አፈና በጠነከረበትና በዚያው መጠን የፀረ-አፓርታይድ ትግል እንቅስቃሴው ሥር መያዝ በጀመረበት ቀውጢ ዘመን መካከል የኖረ አንድ ፅኑ የዙሉ ተወላጅ የሆነ ስቴፈን ኩማሎ ስለተባለ ካህን ነው፡፡ ስለዚያ ሰባኪና ስለልጁ አብሰሎም ታሪክ የሚያወራ.. በልቦለድ መልክ የተጻፈ የእውነተኛ ታሪክ መጽሐፍ ነው፡፡

ይሄ የአለን ፔተን እጅግ ታዋቂ መጽሐፍ ሲታተም... በብዙዎች ዓይንና ልብ ተቃውሞ እየተነሳበት የመጣውን የአፓርታይድ በዘር ላይ የተመሠረተ ሀገራዊ የአስተዳደር ፖሊሲ... በዓለም አደባባይ ደህና አድርጎ ከሰው ልብ ውስጥ ነቅሎ ሊጥለው ተፍገመገመ!! ብዙዎች ስለ አፓርታይድ ምንነት የማያውቁ ሥርዓቱን ባሉበት የዓለም ጥግ ሆነው ውጉዝ እንዲሉት የበኩሉን አስተዋፅኦ ያደረገ እጅግ ታዋቂ መጽሐፍ ነው፡፡ ዛሬ ይህ መጽሐፍ በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የሊትሬቸርና የፖለቲካ ታሪክ ማስተማሪያ ነው፡፡

ታላቁ የሳውዝአፍሪካ የነፃነት ታጋይ Stephen Bantu Biko (ወይም Steve Biko) ስሙ ከዚህ መጽሐፍ ዋነኛ ገፀባህርይ ጋር መመሳሰሉ ራሱ አንድ ገራሚ ጉዳይ ሆኖ... የስቲቭ ቢኮ ነፍስ በአፓርታይዳውያኑ እጅ በእስርቤት ካለፈ በኋላ... በስቴፈን ቢኮ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥነውና በቀድሞ ጓደኛውና የሙያ አጋሩ በዶናልድ ውድስ የተጻፈው “Cry Freedom” (“ነፃነት አልቅሺ.. /ይለቀስልሽ/” የሚል መጽሐፍ በድብቅ ከደቡብ አፍሪካ ወጥቶ ለዓለም ታተመ፡፡

ያ ርዕስ ከአየር ላይ የተገኘ ሳይሆን... ከዚህ የአለን ፔተን የቀደመ መጽሐፍ የተገኘ ነበር፡፡ አልቅሺ ውድ እናት ሀገር ይላል ፔተን፡፡ ዶናልድ ውድስ ደግሞ የስቲቭ ቢኮን ታሪክ አልቅሺ ነጻነት ብሎ ጻፈው፡፡ እና ለቅሶው በመጽሐፍት ብቻም አላቆመም፡፡ .. በ1987 በጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ደግሞ... “Cry Freedom” የተሰኘው መጽሐፍ ወደ ፊልም ተቀይሮ (እና ዴንዘልም ስቲቭ ቢኮን ሆኖ ተውኖበት) በድጋሚ በዓለም ፊት አንድ ሐሙስ የቀረውን አፓርታይድን በሃሳብ እየነረተ አንገዳገደው፡፡

በ1987 “Cry Freedom” ፊልም ሲለቀቅ.. ታዲያ ቀደም ብሎ በ1948 ታትሞ የነበረው ይሄ “Cry, the Beloved Country” የሚል መጽሐፍም.. በደራሲው አለን ፔተን አዲስ መግቢያ ተጽፎለትና አንዳንድ ነገሮች ታክለው ተከልሰው ዳግመኛ እንዲታተም ተደርጓል፡፡
ኋላ ለመጽሐፉ (እና ብሎም ለፊልሙም በተቀራራቢ መልኩ.. ) ርዕስ ሊሆን የበቃው ‹‹አልቅሺ እናት ሀገር›› ደራሲ አለን ፔተን.. በመጽሐፉ አፓርታይዲቱን ሀገሩን ደቡብ አፍሪካን አልቅሺ እያለ... አልቅሶ አንባቢውን እያስለቀሰ ከጻፈባቸው ሶስት ሥፍራዎች መሐል... ይሄኛው ከዚህ በታች የቀረበው አንቀፅ አንዱ ነው፡፡

አባባሉ.. እጅግ ልብን ይነካል፡፡ በቃ የወደድነው ነገር ሁሉ ስለሚወሰድብን... ምንምን ነገር አንውደድ፡፡ ውዱን ነገር ሁሉ እንጥላው፡፡ ይቅርብን፡፡ ፍርሃት ልባችን ስለገባ የምንወደውን ነገር ሁሉ ተጠራርጎ ይወሰድብናልና... ይቅርብን አንውደድ፣ ልባችንን አንስጥ.. እያለ ያነባል ደራሲው፡-

“Cry, the beloved country, for the unborn child that is the inheritor of our fear. Let him not love the earth too deeply. Let him not laugh too gladly when the water runs through his fingers, nor stand too silent when the setting sun makes red the veld with fire. Let him not be too moved when the birds of his land are singing, nor give too much of his heart to a mountain or a valley. For fear will rob him of all if he gives too much.”

በተቀራራቢ ትርጉም እንዲህ ብዬ ወደ ስንኝ ልመልሰው ተጣጥሬያለሁ (በበኩሌ)፡፡ ለግጥም ብዙም ነኝ፡፡ ምን ያህል እንደተሳካልኝ አላውቅም፡፡ ሀሳቡን ግን የያዝኩት ይመስለኛል፡፡ እንዲህ ይላል በዚህ መጽሐፍ ‹‹አልቅሺ የተወደድሽ እናት ሀገር›› በሚልበት ሥፍራ ላይ፡-

“አልቅሺ፣
የተወደድሽው እናትሀገር አልቅሺ..፣
አልቅሺ.. ገና ላልተወለደው ልጅሺ . . ፡፡

በጣቶቹ መሐል ውሃዎችን ሲያንቦራጭቅ፣
1.1K views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 16:03:48
1.1K views13:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 19:32:31 2. ሁለተኛው ፍልስፍናዊ ጥረት የሄግል ፍልስፍና ነው። ሄግል ይሄ ካንት ያመጣው አዋቂ ንቃተ-ህሊና (subject) እና የሚታወቅ ተቀዋሚ ነገር (object) በሚባል የመነጣጠል ጭብጥ ፈፅሞ ሊረካ አልቻለም። ስለዚህ ይሄን ከስነ-እውቀት አንፃር (epistemologically) በአመክንዮአዊ-አእምሮ ድልድይነት ሊደፈን አይችልም የተባለውን ሸለቆ <<አዋቂ ህሊና (subject) ብቻ ነው እንጂ ህላዌ ያለው አዋቂ እና የሚታወቅ ተቀዋሚ ዓለም የሚባል ክፍፍል የለም>> በማለት የሜታፊዚክስ መፍትሔ ይዞ ተነሳ።

3. ሦስተኛው ፍልስፍናዊ ጥረት ደግሞ ካንት የፈጠረውን ሸለቆ በአመክንዮአዊ መንገድ መድፈን የማይቻል ከሆነ፤ ኢምክኑያዊ (irrational) በሆነ መንገድ ነው መፈታት ያለበት የሚል ሐሳብ ይዞ የተነሳ ነው። ይህ የፍልስፍና አካሄድ ሁለት ዓይነት ወኪሎች አሉት። ጭፍን-እምነት (Faith) ላይ የሚመረኮዝ በኪርከጋርድ (Kierkegaard) የሚወከለው ሃይማኖታዊ የኢምክኑያዊነት ፍልስፍና እና ፈቃድ (Will) ላይ የሚመረኮዝ በኒቼ (Nietzsche) የሚወከለው ሴኩላር የኢምክኑያውነት ፍልስፍና ናቸው።

አሁን ድህረ-ካንት ፍልስፍና እና ድህረ-ዘመናዊነት ያላቸውን ትስስር ለመረዳት ከላይ ከተጠቀሱት የፍልስፍና መንገዶች በተለይም ደግሞ ሄግል እና ኢምክኑያውያኑ ለ20ኛው ክዘ የድህረ-ዘመናዊነት ንቅናቄ እንዲፈጠር ጥርግያ መንገድ በመክፈት ያበረከቱትን አስተዋፅኦ እንመለከታለን። አሁንም Stephen Hicks አበርክቶአቸውን እንደሚከተለው ቅልብጭ አድርጎ አስቀምጦታል።

የሄግል አበርክቶ:-

1. እውንነት (Reality) የአዋቂ ህሊና ፍጥረት (subjective creation) ነው።

2. ተቃርኖዎች (contradictions) ከአመክንዮአዊ-አእምሮ እና ከእውንነት ተፈጥሮ ጋር አብረው ያሉ ናቸው።

3. እውንነት በየተቃርኖ ዝግመተ-ለውጥ ሂደት ውስጥ ስለሆነ እውነት ከቦታ እና ከጊዜ አኳያ የሚታይ አንፃራዊ ነው ።

4. በማህበረ ፖለቲካ መስተጋብር ውስጥ ግለሰቡ (The Individual) ሳይሆን ጋርዮሻዊ ስብስቡ (The Collective) ነው አንቀሳቃሽ ኃይል (operative unit)

ኢምክኑያውያኑ ከካንት እና ሄግል ወርሰው ለ20ኛው ክዘ ያቀበሉት አበርክቶ ደግሞ:-

1. አመክንዮአዊ-አእምሮ እውንነትን የማወቅ ብቃት እንደሌለው ከካንት ጋር ያላቸውን ስምምነት፤

2. እውንነት በጣም በቅራኔ የተሞላ እና ወለፈንድ መሆኑን ከሄግል ጋር ያላቸውን ስምምነት፤

3. ስለዚህ አመክንዮአዊ-አእምሮ ተሸንፎ በስሜት (feeling)፣ ወይም በደመ-ነፍስ (instinct)፣ ወይም በእምነት ዝላይ (leap of faith) ላይ ለሚመሰረቱ ሐሳቦች ቦታ መልቀቅ አለበት የሚል ድምዳሜ፤ በዚህም

4. ምክኑያዊ ያልሆነው ነገር (the non-rational) እና ኢምክኑያዊ የሆነው ነገር (the irrational) ናቸው ስለ እውንነት ጥልቅ እውነት ሊገልጡልን የሚችሉት የሚሉ ናቸው።

የ19ኛው ክዘ የጀርመን ፍልስፍና ሁለት የሐሳብ መንገዶችን አዳብሯል። የአግምሮተ-ሐሳባዊ ሜታፊዚካል (speculative metaphysical) እና የኢምክኑያዊ ስነ-እውቀታዊ (irrationalist epistemological) መንገዶች። ጥያቄ ሆኖ የቆየው ደግሞ እነዚህን ሁለት የሐሳብ ገመዶች አንድ ላይ አስተፃምሮ ወደ ቀጣዩ ዘመን ማሻገሪያ መንገድ ፍለጋ ነበር። ይሄንን ፕሮጀክት Martin Heidegger አጠናቅቆ ለድህረ-ዘመናውያን ጥርጊያውን አመቻችቶአል።

እናስ የድህረ-ዘመናዊነት ንቅናቄ ዕዳ ነው ይዞብን ነው የመጣው ወይስ ቡራኬ ነው ይዞልን የመጣው?

የመደምደሚያውን ሐሳብ በክፍል ስድስት-ለ አቀርባለሁ።

ይቀጥላል...

Yonas Tadesse Berhe
1.5K views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 19:32:31 በምስለ-አካልነት (perception) መልክ የሚያቀርብልን አስገዳጅ ሁኔታ (necessity) የለም በማለቱ፤ ዴካር ደግሞ ምስለ-አካላት በውጫዊው ዓለም ቆስቋሽነት ሳይሆን በአእምሮአችን ውስጥ አብረውን ያሉ (innately) ናቸው በማለቱ ነው ከውጫዊ ዓለም ጋር ልናመሳክረው የምንችለው እውቀት የለንም ያስባላቸው። ካንት ደግሞ ህዩምን (ኢምፕሪስስቶችን) አእምሮአችን በስሜት ህዋሳቶቻችን በኩል የምናገኛቸውን ህወስታዊ ቅንጣቶችን (sensory atoms) አደራጅቶና አቀናጅቶ በምስለ-አካልነት (perception) መልክ በአስገዳጅነት የሚያቀርብበት ማሽነሪዎች (categories) አሉት በሚል ይሞግተውና፤ ዴካርን (ራሽናሊስቶችን) ደግሞ የአእምሮ ማሽነሪዎቻችን እውንነትን አቀነባብረው የሚያቀርቡልን ምስሎች እንጂ "አብረውን ያሉ (innate ideas)" የሚባሉ ምስሎች የሉንም በማለት ይሞግተዋል። የእውቀት እውነትነትን ከእውንነት (reality/noumena) ጋር በማመሳከር ለማግኘት የሚያደርጉትን የዘመናት ጥረት ግን ፍፁም የማይሳካ ጥረት መሆኑን ሁለቱንም አንድ ላይ ያረዳቸዋል። ምክንያቱም የአእምሮአችን ተፈጥሮአዊ ስሪት (constitution ይለዋል ካንት) እውንነትን በራሳቸው መንገድ በሚያቀነባብሩ (ወይም በሚያጣምሙ) ማሽነሪዎች የታነፀ ነውና።

3.2 ለኢምፕሪስስቶች እና ለራሽናሊስቶች የተሰጠ የካንት ምላሽ የድህረ-ዘመናዊነት ጥንስስ ስለ መሆኑ

ለኢምፕሪስስቶች እና ለራሽናሊስቶች የተሰጠው የካንት ምላሽ የድህረ-ዘመናዊነት ጥንስስ መሆኑን ለማየት ካንት ከእርሱ በኋላ ለመጡት ፈላስፎች ትቶት ያለፈው ውርስ (legacy) ምንድን ነው? ብለን መጠየቅ ይኖርብናል። በዋናነት ሁለት አይነት ውርሶችን ነው ትቶ ያለፈው:-

ሀ. የሜታፊዚክስ ጥናት ሞት (The Death of the Study of Metaphysics)

ከካንት በፊት ራሽናሊስቶችም ሆኑ ኢምፕሪስስቶች ከሚከተሉት በውከላዊነት (representationalism) ላይ የተመሰረተ የስነ-እውቀት ዘዴ የተነሳ የውጫዊው ዓለም ህላዌ (existence of reality) አስቸጋሪ (problematic) ቢሆንባቸውም ቅሉ፤ ይሄ ውጫዊው ዓለም ምን ዓይነት ምስል ወይም መልክ የያዘ እንደሆነ በሚመለከት ግን ሳይንስ በሚሰጠው ማብራሪያ ላይ አንዳቸውም ጥርጣሬ ኖሯቸው አያውቅም። ራሽናሊስቶቹ እንኳ ቢሆኑ ንቃተ-ህሊና በቀጥታ የሚገነዘባቸው ነገሮች በአእምሮ ውስጥ ያሉ ምስለ-አካላት/ሐሳቦች (percepts/ideas) ናቸው ቢሉም፤ ይህ በአእምሮ ውስጥ ያለውን ዓለም የሚመስል ውጫዊ ዓለም እንዳለ ለማሳየት ነበር ጥረታቸው።

ካንት ግን ከንቃተ-ህሊና ውጪ ያለው የኖሚና ዓለም ስሜት ህዋሳቶችንን የመቆሰቆስ (triggering) ሚና የሚጫወት ቢሆንም የምስለ-አካላዊ ፋክልቲው (perceptual faculty) የሚሰጠው ምላሽ ይዘትን ግን መወሰን አይችልም ይላል። ስለዚህ ይሄ በዙሪያችን የምናስተውለው በጊዜ እና በቦታ የተወሰነው ዓለም መስሎ የሚታየን (appearance) ወይም በአእምሮአችን ውስጥ ብቻ ያለ ዓለም ነው ማለት ነው። የስሜት ህዋሳቶቻችንን የሚቆሰቁሰው ትክክለኛው እውንነትን (things-in-themselves/noumenan) ግን በፍፁም ልናውቀው አንችልም። እዚህ ላይ ልብ ብለን ማስተዋል ያለብን ነገር ካንት <<ኖሚናን ማወቅ ከባድ ነው ወይም የኖሚናን እውቀት ማረጋገጥ (ፕሩቭ ማድረግ) ከባድ ነው>> አይደለም እያለ ያለው። አእምሮአችን በተለይም ደግሞ አመክንዮአዊ-አእምሮአችን ኖሚናን የሚያውቅበት መንገድ እስከወድያኛው ዝግ ነው ማለቱ እንጂ። በዚህም ፍልስፍናም ልክ እንደ ሳይንስ (በክፍል አምስት እንደተመለከትነው) ፊዚክስን/ፊኖሚናን እንጂ ከፊዚክስ/ፊኖሚና ባሻገር ያለውን ሜታፊዚክስን/ኖሚናን ማጥናት አይቻላትም ሲል የሜታፊዚክስ ጥናትን ከጥቅም ውጭ አድርጎታል። ከካንት በኋላ የመጡ ፈላስፎች ይሄን ጉዳይ ሲገልፁት የሜታፊዚክስ ሞት (the death of metaphysics) ብለውታል። አንዱ የድህረ-ዘመናዊነት ጥንስስም ይኼው ነው።

ለ. የእውነት ተጨባጭነት ሞት (The Death of the Objectivity of Truth)

በክፍል 4 እና በክፍል 5 እንደተመለከትነው መነሻው ደግሞ ከላይ በተብራሩት የጥሬ እውንነት እና የውከላዊነት እይታዎች ምክንያት እስከ ካንት ድረስ ባለው የፍልስፍና ታሪክ ውስጥ እውነት ማለት ሐሳቦቻችን ከእውንነት ህግጋት ጋር ተመሳክረው ስምምነት ያላቸው ሆነው ሲገኙ ማለት ነው የነበረው—በፍልስፍና የሙያ ቋንቋ (technically) correspondence theory of truth በመባል ይታወቃል። ይኼውም የእውነት ብያኔ ከንቃተ-ህሊና ውጭ በአለው ዓለም/ህላዌ ተቀዳሚነት (primacy of existence) የተቃኘ ነው የነበረው—የእውነት ተጨባጭነት (objectivity of truth) ትርጉምም ይህ ነው። ከላይ ከፍ ብለን እንደተመለከትነው ግን በካንት ፍልስፍና መሰረት ንቃተ-ህሊና እውንነትን ማወቅ ስለማይቻለው የእውነት ትርጉም በህላዌ ተቀዳሚነት ሳይሆን በንቃተ-ህሊና ተቀዳሚነት (primacy of consciousness) የሚቃኝ እንዲሆን አድርጎታል። ማለትም እውነት ማለት በአእምሮአችን ውስጥ ያሉትን ሐሳቦች ከውጫዊው ዓለም ህግጋት ጋር በማመሳከር የምናገኘው ሳይሆን፤ አእምሮአችን ውስጥ ያሉት ሐሳቦች እርስ በራሳቸው የተቀናጀ ስምምነት ሲኖራቸው ማለት ሆነ—በፍልስፍና የሙያ ቋንቋ coherence theory of truth በመባል ይታወቃል። በዚህም እውነት በአእምሮአችን ውስጥ የምንፈጥረው ግለ-ስሜታዊ (subjective) ነው ሲል የእውነት ተጨባጭነትን ከጥቅም ውጭ አድርጎታል። ከካንት በኋላ የተነሱ ፈላስፎች ደግሞ <<እውነት ማለት በእያንዳንዳችን ጭንቅላት ውስጥ የምንፈጥረው ግለ-ስሜታዊ (subjective) ነገር ከሆነ እውነት አንፃራዊ (relative) ነው>> አሉ። ይሄም ሌላኛው የድህረ-ዘመናዊነት ጥንስስ ነው። እንድያውም ከመቶ ሰባ ዓመታት ገደማ በኋላ የተነሱት ድህረ-ዘመናውያን እውነት የሚባል የለም ሙቶአል ሲሉ "ድህረ-እውነት/post truth" የሚል ፈሊጥ ይዘው መጥተዋል።

3.3 ድህረ-ካንት እና ድህረ-ዘመናዊነት

ከካንት በኋላ የፍልስፍና ማጠንጠኛ ሆኖ ጎልቶ የወጣው ጥያቄ <<ይሄ ካንት በአመክንዮአዊ-አእምሮ ድልድይነት ልንሻገረው አይቻለንም ያለው በንቃተ-ህሊና (subject) እና በውጫዊው ዓለም (object) መካከል ስላለው ሸለቆ ምን እናድርግ?>> የሚል ጥያቄ ነው ይለናል Stephen Hicks። ይሄን ጥያቄ ለመመለስም ሦስት ሰፋፊ ፍልስፍናዊ ጥረቶች ተካሂደዋል ይላል:-

1. የካንት የቅርብ ተከታዮቹ የነበሩት ሸለቆውን እንዲሁ ተቀብለው ለመጓዝ ነበር የወሰኑት። ኒዮ-ካንቲያኒዝም የሚባል በ19ኛው ክዘ ተወልዶ፤ አድጎ አድጎ በ20ኛው ክዘ ላይ ሁለት ዓይነት ቅርፆችን ይዞ ብቅ አለ። አንደኛው በ Ferdinand de Saussure ፊታውራሪነት የሚቀነቀን Structuralism ሲሆን በዋናነት ከካንት ፍልስፍና ራሽናሊስት ክንፍን የሚወክል ነው። ሁለተኛው ደግሞ በ Edmund Husserl ፊታውራሪነት የሚቀነቀነው Phenomenology ሲሆን በዋናነት ከካንት ፍልስፍና ኢምፕሪስስት ክንፉን የሚወክል ነው።
1.3K views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ