Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.28K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-05-20 20:42:46 ያበጁትን ቀደምት ፈላስፎችን ግን የአእምሮ ስንፍና ኖሯቸው ሳይሆን ጥልቅ የሆነ ፍልስፍናዊ ፕሮብሌም ገጥሞአቸው እሱን ለመፍታት በተከተሉት መንገድ ምክንያት በአመክንዮአዊ-አእምሮ እና አጠቃላይ በየዘመናዊው (modernity) የእውነት ፅንሰሐሳብ ላይ ሊያምፁ እንደቻሉ እረዳለሁ እገነዘባለሁም።

ለመሆኑ ይሄ ለድህረ-ዘመናዊነት (በዘመናዊነት ላይ አምፆ እንዲነሳ) ጥንስስ ምክንያት የሆነው ፍልስፍናዊ ፕሮብሌም ምንድን ነው?

ይቀጥላል...

Yonas Tadesse Berhe
479 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 20:42:46 ድህረ-ዘመናዊነት (Postmodernism): ማህበረሰባዊ ዕዳ ወይስ ቡራኬ?

(ዮናስ ታደስ)

ክፍል ሦስት

2. ድህረ-ዘመናዊነት ለዘመናዊነት ግብረ-መልስ ሆኖ የተነሳበት ፍልስፍናዊ የታሪክ ዳራ

ባለፉት ሁለት ክፍሎች ለማሳየት እንደሞከርኩት ድህረ-ዘመናዊነት በዋናነት፣ <<ሰው ስለ ራሱ እና ስለ ዓለም በተጨባጭነት ሊያረጋግጠው በሚችለው መልኩ እውነትን ማወቅ ይችላል>> የሚልን የዘመናዊነት (modernity) አንዱ ምሰሶ ሊባል የሚችለውን መርህ በመፃረር ነው የተነሳው። እንዲያውም ድህረ-ዘመናውያን "ተጨባጭ"፣ "እውነት"፣... ወዘተ የሚሉ ዘመናዊ የሚሏቸውን ፅንሰሐሳቦች እንደማይቀበሏቸው ለማሳየት በትእምርተ-ጥቅስ ውስጥ ነው የሚፅፏቸው።

ይሄን ቅራኔ በትክክል ለመረዳት የሚያግዘንን ፍልስፍናዊው የታሪክ ዳራ ከመመልከታችን በፊት ግን፤ ዘመናዊው እውነት እና ድህረዘመናዊው "እውነት" የት ቦታ ወይም ደግሞ ምን ላይ ነው እየተቃረኑ ያሉት የሚለውን ትንሽ ገለጥ አድርጎ ማየት የቅራኔውን ታሪካዊ ዳራ ለመረዳት አስፈላጊነት አለው።

በአንድ ወቅት ፋሲል መርዓዊ (PhD) በዘርዓ ያዕቆብ የፍልስፍና ትምህርት ቤት ስለ ድህረ-ዘመናዊነት እያስተማረ እያለ የተማሪ ጥያቄ ሲመልስ (ቃል በቃል አይደለም)፣ <<ከሳይንስ እና ከሃይማኖት ወይም ከሳይንስ እና ከጥንቁልና መንገዶች ውስጥ ሳይንስን በተለየ መልኩ ከፍ አድርገን ልንመለከተው የሚያደርገን ሚዛን የለንም>> የሚል ሐሳብ ያነሳል። ከዚህ ሐሳብ በኋላ ታድያ ክፍሉ በሃይለኛ ክርክር ተናጠ ( የሐሳቡ እና የክርክሩ ጭብጥ የፍልስፍና ትምህርት ቅፅ-፩ ላይ ሰፍሮአል)። በተለይ ከተፈጥሮ ሳይንስ የጥናት መስክ ለመጡ ተማሪዎች እንዴት ከአንድ የፍልስፍና አስተማሪ እንደዚህ አይነት "የወረደ" ሐሳብ ሊወጣ ይችላል በሚል በስሜት ነበር የሚከራከሩት። ሐሳቡ ራሱ የአስተማሪው የራሱ እንጂ ታላላቅ ስም ያላቸው ፈላስፎች እንዲህ ሊሉ እንደሚችሉም የተገነዘቡ አይመስሉም። ነገር ግን ተማሪዎቹ ልብ ብለው ስላላስተዋሉት እንጂ ፋሲል የእነ ፉኮን፣ የእነ ደሪዳን፣ እና የእነ ሊዮታርድን ሐሳብ ሲያብራራ፤ እነዚህ ድህረ-ዘመናውያን ስለ የተለያየ ርእሰ-ጉዳይ የሚያወሩ ቢሆንም ቅሉ ሁሉንም በጋራ የሚያስማማቸው ጉዳይ ቢኖር <<እውነት አንፃራዊ ነው፣ በአመክንዮአዊ-አእምሮ እና በሎጂክ መንገድ ብቻ የሚታወቅ እውነት የሚባል የለም>> የሚል ሐሳብ እንደሆነ ሲገልፅ፤ ያ ከላይ የተጠቀሰው የጦፈ ክርክር የጫረ ሐሳብ አስተማሪው ራሱ የፈጠረው ሳይሆን ከዚህ መነሻ የመነጨ መሆኑ ይገነዘቡ ነበር።

ያም ሆኖ ግን <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚለው ነጠላ-ሐሳብ (proposition) ሁሉንም ዓይነት እውነት የሚያካትት ከሆነ፤ ከሎጂክ አንፃር በእርግጥም የሆነ የሚጎረብጥ (የሳይንስ ተማሪዎቹ እንደጎረበጣቸው) ህፀፅ አለው። ምክንያቱም <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚለው ነጠላ-ሐሳብ እንደ ፍፁም እውነት አድርገን ከተቀበልነው፣ ብያንስ አንድ አንፃራዊ ያልሆነ እውነት ማለትም <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚል እውነት አገኘን ማለት ነው። ግን ደግሞ <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚለው ሐሳብ ሁሉንም "እውነት ነው" ተብሎ የሚነገርን ሐሳብ ስለሚመለከት፤ እራሱን <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚለውን ነጠላ-ሐሳብንም ጭምር ይመለከታል ማለት ነው። በዚህም <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚል ሐሳብ እንደ "አንፃራዊ እውነት" እንጂ እንደ የተረጋገጠ እውነት መውሰድ አንችልም ማለት ነው። "ፍፁም እውነት" ብለን ተነስተን ተመልሶ "አንፃራዊ" ይሆንብናል። ይህ የሚያሳየን <<እውነት አንፃራዊ ነው>> የሚል ነጠላ-ሐሳብ (proposition) ራሱን በራሱ የሚጋጭ (self-contradictory) ትርጉም አልባ ሐሳብ ነው ማለት ነው። እዚህ ላይ ልብ ብለን ማስተዋል ያለብን ነጠላ-ሐሳቡ <<ብዙ/የተወሰኑ እውነቶች አንፃራዊ ናቸው>> የሚል ቢሆን ኖሮ ራሱን በራሱ የሚጋጭ ሐሳብ አይሆንም ነበር። እንዲሁ በአጠቃላይ አንድም እውነት የሚባል ነገር የለም፤ ሁሉም አንፃራዊ ነው ለማለት ከሆነ፣ "እውነት አንፃራዊ ነው" የምንለው ግን ከሎጂክ አንፃር ራሱን በራሱ የሚቃረን ሐሳብ ነውና እያወራን ያለነው ፋላሲ ወይም ህፀፅ ነው የሚሆነው።

(በነገራችን ላይ እንደዚህ አይነት ነጠላ-ሐሳቦች/ሐሳቦች በሎጂክ እና በማተማቲክስ ራስ-ጠቀስ ነጠላ-ሐሳቦች/ሐሳቦች (self-referencing propositions/ideas) ተብለው ይታወቃሉ። ራስ-ጠቀስነታቸው ለራሱ ለአረፍተ-ነገሩ ወይም አረፍተ-ነገሩን ለሚሰራው ወይም ለሚናገረው ሰው ሊሆን ይችላል። እጅግ በጣም ብዙ ራስ-ጠቀስ ሐሳቦች አሉ። ለምሳሌ <<እኔ እየዋሸሁ ነው>>፣ <<ይህ አረፍተ-ነገር ውሸት ነው>>፣ <<እኔ እየተናገርኩ ልሁን አልሁን አላውቅም>> ፣ <<በህልሜ ቢሆንስ እየኖርኩ ያለሁት>> ...። ብዙዎቹ ራስ-ጠቀስ ነጠላ-ሐሳቦች ሕፀፅ ያላቸው ቢሆኑም ሁሉም ራስ-ጠቀስ ነጠላ-ሐሳቦች ህፀፅ ያላቸው ናቸው ማለት ግን አይደለም። ራስ-ጠቀስ ሐሳቦች በተለይ በማተማቲክስ በብዛት ነው የሚፈለፈሉት። ኩርት ጎዴል (Kurt Gödel) Incompleteness Theorem ተብሎ የሚታወቀውን ግኝቱ ፕሩቭ ማድረግ የቻለው ህፀፅ የሌለው ራስ-ጠቀስ ነጠላ-ሐሳብ በማተማቲክስ ቋንቋ ማግኘት ስለቻለ ነው። በዚሁ አጋጣሚ ስለ ራስ-ጠቀስ ነጥላ ሐሳቦች በስፋት ማወቅ የሚፈልግ ሰው ወደ ዘርዓያዕቆብ የፍልስፍና ትምህርት ቤታችን የክረምት ኮርስ በመቀላቀል የኮምፒዩተር ሳይንስ ፍልስፍና ኮርስን መከታተል ይችላል። ስለ ራስ-ጠቀስ ነጠላ-ሐሳቦች ግንዛቤ የሌለው ሰው Advanced Mathematics፣ Computer Science፣ Philosophy Proper ገብቶታል ወይም ያውቃል ማለት አይቻልም።)

እንግዲህ ድህረ-ዘመናውያን እንደሚሉት ወይም እንደሚያደርጉት <<ሎጂክ እና አመክንዮአዊ-አእምሮ ልክ የሆነውን ከስህተት፣ የተጣረሰውን ካልተጣረሰው ሐሳብ የምንለይባቸው መሳሪያዎች ሳይሆኑ፤ ምእራባዊው ስልጣኔ "እውነት" ናቸው የሚላቸውን ነገሮች በሌሎች ላይ ለመጫን የሚጠቀምባቸው የጭቆና መሣሪያው ናቸው>> ብለን በመውሰድ <<እውነት አንፃራዊ ነው>> በሚል አቋም (ሐሳብ አላልኩም) እምመራለሁ ካልን ደግሞ ፤ ሌሎች <<የተረጋገጡ እውነት ናቸው>> ተብለው የሚነገሩ ሐሳቦችን፤ ለምሳሌ ሳይንስ አስገኘኋቸው ከሚላቸውን እውነቶች ጋር ስንጋፈጥ፣ <<እውነት አንፃራዊ መሆኑን በእርግጠኛነት ስለማውቅ ሳይንሳዊ እውነትን አንፃራዊ እንጂ የተረጋገጠ ልንለው አንችልም>> የሚል መከራከሪያ ማቅረብ ከአቋም መግለጫ የዘለለ ትርጉም ወይም ቁም ነገር ሊኖረው አይችልም ማለት ነው።

እዚህ ላይ <<ታድያ ድህረ-ዘመናውያን የምር ሰነፎች እና ምንም የማይገባቸው ደደቦች ሆነው ነው በክፍል ሁለት እንደተመለከትነው በአመክንዮአዊ-አእምሮ እና በሎጂክ ላይ ያመፁት ወይም የሚያምፁት?>> የሚል ጥያቄ ማንሳት ተገቢ ነው።

በእኔ ምልከታ ምንም እንኳ አሁን አሁን በየአደባባዩ (በዩኒቨርስቲ፣ በሚድያ፣ በአርት፣ በፖለቲካ፣ በአክቲቪስትነት..ወዘተ) የሚታዩትን አብዛኞቹ ድህረ ዘመናውያንን፤ የአእምሮ ጥረት የሚጠይቀውን ሳይንሳዊ መንገድ ለመከተል ሰነፎች ከመሆናቸው በመነጨ አመክንዮአዊውን አካሄድ በቅጡ መረዳት ስለማይችሉ፤ የድህረ-ዘመናዊነት በአመክንዮአዊ-አእምሮ ላይ ማመፅን እንደ ማምለጫ እና የስንፍና መደበቂያቸው ጥሩ ዋሻ አድርገው የሚወስዱ አድርጌ የምመለከታቸው ቢሆንም፤ የድህረ-ዘመናዊነትን እርሾ የተከሉት ወይም ደግሞ የድህረ-ዘመናዊነት ጥንስስን
490 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 20:42:09 ይሄን የሐይል ሚዛን አለመመጣጥንን ለመፍታት ደግሞ <<እንዲህ ያለ ነገር ልክ ነው እንዲያ ያለ ነገር ደግሞ ስህተት ነው>> ለማለት የሚያስችለን ተጨባጭ መለኪያ (objective standard) እንዳለን አድርገን የምናስበው ነገር ማስወገድ እንዳለብን እና ሁሉም ነገር በግለ-ስሜታዊነት (subjectivism) የሚከናወን መሆኑን ወይም መከናወን እንዳለበት ነው መፍትሔ ብለው የሚያስቀምጡት። (Stephen Hicks, Explaining Postmodernism)

ዛሬ ላይ ድህረ-ዘመናዊነት እጅግ በስፋት የተቆጣጠረው ዘርፍ ቢኖር አርት/ኪነ-ጥበብ ነው። ከኪነ-ጥበብ ውስጥም ስነ-ፅሑፍን እና ስነ-ስዕልን በስፋት አሻራውን ያሳረፈባቸው ቦታዎች ናቸው።

ስነ-ፅሑፍን በሚመለከት በተለይ በልበ-ወለዱ አለም፤ የልብ-ወለድ መሰረታዊ አለባውያን ተብለው የሚታወቁ ከነበሩት እንደ ጭብጥ (theme)፣ ሴራ (plot)፣ ጡዘት (climax) ዓይነት ነገሮች በድህረ-ዘመናዊነት ምንም ቦታ የላቸውም። ለሰዋስው እንኳ ሳትጨነቅ የአእምሮ ዥረት (stream of consciousness) ያመጣልህን መፃፍ ሆኗል። (Ayn Rand, The Romantic Manifesto)

በመጨረሻም ድህረ-ዘመናዊነት አርት ላይ ያሳረፈውን ተፅዕኖ የሚያሳይ አንድ ክስተት እንመልከት። Explaining Postmodernism ላይ ትንሽ ሰፋ ብሎ ተተንትኖአል። በአጭሩ ጨምቄ እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ።

ኒውዮርክ ውስጥ ያለ አንድ Society of Independent Artists የሚባል ማህበር ማኽሴ ደሾ (Marcel Duchamp) ለተባለ አርቲስት የሆነ የአርት ስራውን እንዲያቀርብ ይጠይቀዋል። ደሾ ሆየ የሽንት መሽኛ ፖፖ መሳይ እቃ ላከላቸዋ።

በ20ኛው ክዘ ጭራቆች እና ቆሻሻ ነገሮች በአርቱ አለም መሐል ስፍራ የያዙ ጭብጦች እንደነበሩ እና በደሾ ስራ ግን የአርቱ አለም የአካዳሚኩ አለምን ቀድሞ ድህረ-ዘመናዊነትን እንደተቀላቀለ የሚያሳይ ስራ ነው ይለዋል Stephen Hicks።

ደሾ ሊያስተላልፈው የፈለገው መልእክት ግልፅ ነው። አርቲስት ማለት ታላቅ ባለ-ፈጠራ (great creator) ማለት አይደለም። አመክንዮአዊ-አእምሮ (reason)፣ ሎጂክ፣ እና ኤስቴቲክስ (aesthetics) የምእራባዊው ካፒታሊስት ማህበረሰብ የጭቆና መሳሪያዎች ናቸው። የአርት ስራ ስሜትን፣ አእምሮን፣ እና ነፍስን በአጠቃላይ የሚያነቃቃ የተለየ ነገር የለውም፤ በገፍ በፋብሪካ ውስጥ ሊመረት የሚችል ነገር ነው ለማለት ነው። ይሄም ሆኖ ደሾ የአርት ስራ ብሎ ከሌሎች በፋብሪካ ሊመረቱ ከሚችሉ እቃዎች ለይቶ የሽንት መሽኛ ፖፖ መምረጡ፣ <<አርት ሽንታችንን የምንሸናበት ነገር ነው>> የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ነው ይለናል ስቲቨን ሂክስ። ዳዳኢዝም የሚባል የትርጉም አልባነት (nihilism) ንቅናቄ ነበረ። አርት እርባና ቢስ ነው—Art is Shit—የሚል ሞቶ የዚህን ንቅናቄ ምንነት ይገልፃል፤ ድህረ-ዘመናዊነት ያደረገው ነገር ቢኖር ይሄን ሞቶ ሁሉም ነገር እርባና ቢስ ነው—Everything is shit ወደሚል ከፍ ማድረጉ ነው ይለናል ሂክስ።

ደሾ እንደዚህ ዓይነት ስራ ካቀረበ ከመቶ አመት ገደማ በኋላ መሆኑ ነው Maurizio Cattelan የተባለ ጣልያናዊ አርቲስት እኤአ በ2019 በ Miami's Art Basel በማስትሽ ግድግዳ ላይ የተለጠፈ ሙዝ የአርት ስራ ብሎ አቅርቦ በመቶ ሃያ ሺ ዶላር እንደተሸጠለት CNN እና BBCን ጨምሮ ታላላቅ ሚዲያዎች ሲዘግቡት የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።

ስለ የድህረ-ዘመናዊነት መገላጫዎች ብዙ ማለት የሚቻል ቢሆንም ከተነሳንበት ጭብጥ አንፃር ግን በወፍ በረር ይሄን ያክል ከቃኘን ይበቃል።

ለመሆኑ ድህረ-ዘመናዊነት ለዘመናዊነት ንቅናቄ የተሰጠ ግብረ-መልስ ሆኖ ሊነሳ የቻለበት ፍልስፍናዊ ምክንያት ምንድን ነው?

ይቀጥላል...

Yonas Tadesse Berhe
450 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 20:42:09 ድህረ-ዘመናዊነት (Postmodernism): ማህበረሰባዊ ዕዳ ወይስ ቡራኬ?

(ዮናስ ታደሰ)

ክፍል ሁለት

1.1 የድህረ-ዘመናዊነት መገለጫዎች በሳይንሱ ዓለም

Paul Boghossian, The Fear of Knowledge በሚለው መፅሐፉ ላይ ድህረ-ዘመናዊነት በሳይንሱ አለም ሊፈጥረው እየሞከረ ያለውን ውዥንብር የሚያሳይልኝ ነገር አስፍሮአል። ሁኔታውን በአጭሩ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ።

እኤአ ጥቅምት 22, 1996 The New York Times ጋዜጣ <<በፈጣሪ የሚያምኑ ህንዳውያን ጎሳዎች አርኪኦሎጅስቶችን አሰናከሉ>> በሚል ርእስ አንድ ያልተለመደ ዘገባ ያወጣል። በዘገባውም <<አሜሪካውያን ከየት ነው የመጡት?>> በሚል ጥያቄ ላይ በሁለት የተለያዩ እይታዎች መካከል ቅራኔ እንደተፈጠረ ይገልፃል። አንደኛው ከአርኪኦሎጂ ጥናት አኳያ በስፋት የሚታወቀው እና እንደ ትክክለኛ ማብራርያ የሚወሰደው፤ ከአስር ሺ አመታት በፊት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ከኤዥያ Bering Strait ወንዝን አቋርጠው አሜሪካ እንደገቡ ነው። የዚህ ተቃራኒ የሆነው እና ቀደምት የአሜሪካ ኗሪዎች የሚያምኑት ተረታዊ የፍጥረት አመጣጥ ደግሞ፤ ቀደምት አሜሪካውያን ቅድመ አያቶቻቸው ከመሬት በታች ባለው ዓለም ውስጥ ካሉ መናፍስቶች ወደ አሜሪካ ምድር ከወጡ በኋላ ነው።

እንግዲህ እንደ ኒውዮርክ ታይምስ ዘገባ ከሆነ በነዚህ ሁለት እይታዎች መሐል ባለው ቅራኔ ምክንያት ብዙ አርኪኦሎጂስቶች ለሳይንሳዊ ዘዴ ባላቸው ቁርጠኝነት እና ለአገር-በቀል ባህል ባላቸው አድናቆት መሐል ተወጥረው ወደ የድህረ-ዘመናዊነቱን "የእውነት አንፃራዊነት" ሐሳብ የተጠጋ አስተያየት ሊሰጡ እንደቻሉ ነው። ዙኒ (Zuni) ከሚባሉት ቀደምት አሜሪካውያን ጎሳዎች ጋር አብሮ የሰራ Roger Anyon የተባለ ብሪጣንያዊ አርኪኦሎጅስት እንዲህ ሲል ተደምጦአል፣ <<ሳይንስ ዓለምን ልናውቅባቸው ከምንችላቸው ብዙ መንገዶች ውስጥ አንዱ ነው፤ የዙኒዎች እይታ ደግሞ አርኪኦሎጂ ስለ ቅድመ-ታሪክ (prehistory) ምንነት ያለውን እይታ "ልክ ነው" ተብሎ በሚወሰድበት ደረጃ እኩል ትክክለኛነት ያለው ነው።>>

ሌላ Dr Larry Zimmerman የተባለ የIowa ዩኒቨርሲቲ መምህር ደግሞ እንዲህ ብሎአል፣<<እኔ በበኩሌ ይሄ ዓለምን የምንመለከትበት የበላይነት ያለው መንገድ ሳይንስ ብቻ ነው የሚለውን ሐሳብ አልቀበልም።>>

ይሄ ሳይንስ በእውቀት ላይ ያለውን የበላይነት የመቃወም ወይም ያለመቀበል አይነት እሳቤ ምን ያህል ስር እየሰደደ እንደመጣ ለማሳየት ሌላ ማሳያ እንጨምር።

ድህረ-ዘመናውያን ሳይንስን እና አመክንዮአዊ-አእምሮን:-

<<ወደ አንድ እውነት የሚወስድ መንገድ አለን የሚሉበት መሰረት የላቸውም፤ እንዲሁ ግን አመክንዮአዊ-አእምሮ እና ስልጣን (power) አንድና አንድ ስለሆኑ በእውነት ላይ ስልጣን ያላቸው ኢምፐሪያሊስት ሊሆኑብን ይሞክራሉ>> ብለው ይገልፁዋቿል። (Andrew Colgan, Pocket Guide to Postmodernism)

ኣብዛኞቹ በየዩኒቨርሲቲው ያሉት የህዩማኒቲስ እና ማሕበራዊ ሳይንስ የጥናት መስኮች አብርሆታዊውን የምክኑያዊነት ባህልን በግላጭ በማጥቃት ወይም ባለመቀበል፤ ሳይንስን እንደ ማንኛውም ማህበረሰብ የሚፈጥራቸው ወይም የሚያዳብራቸው ትርክቶች እና ተረቶች ፈጠራ አድርጎ የሚወስደውን የድህረ-ዘመናዊነት እሳቤ እየተከተሉት ነው።

በአንድ ወቅት ታድያ ይሄን አካሄድ ያልተመቸው አንድ Alan Sokal የተባለ ፊዚስስት በግጭት የተሞላ እና እርስ በርሳቸው በሚጣረሱ ወለፈንድ ሓሳቦች የታጨቀ ወረቀት ፅፎ ያትሙት እንደሆነ ለማየት በወቅቱ በዝነኝነት የድህረ-ዘመናዊነት ሐሳቦች ይቀነቀንበት ወደ ነበረ Social Text የሚባል አካዳሚክ ጆርናል ይልከዋል። ወረቀቱን እንዲቀበሉት ግን የሳይንስን ግኝቶች በተለየ መልኩ ክብደት ሊሰጣቸው እንደማይገባ የሚገልፁ እንደ፣ <<ሳይንስ አስገኘኋቸው የሚላቸውው ቁሳዊ "እውነታ" ልክ እንደ ማህበራዊ "እውነታ" ማህበረሰባዊ ትብብር እና የቋንቋ ችሎታ የፈጠራቸው (social constructs) ናቸው>> የሚል የእውነት አንፃራዊነትን የሚያንፀባርቁ የድህረ-ዘመናዊነት ሓሳቦችን ኣካትቶበታል። የአርቲክሉ አርእስትም የድህረ-ዘመናውያንን ልብ የሚያሞቅ፣ <> የሚል ነበር።

በሚገርም ሁኔታ Social Text ፣<<ሳይንስን እና አመክንዮን የሚበቀልልኝ አሁን ገና ነው የተገኘው>> በሚል ስሜት በሚመስል ሁኔታ ወረቀቱን አተመው። ወረቀቱ ከታተመ ከ 3 ሳምንት በኋላ ደግሞ Sokal አርቲክሉ ማላገጫ (Hoax) እንደነበረ Lingua Franca በተባለ መፅሔት አጋለጠ። በዚህ ምክንያትም ኤዲተሮቹ እውቅ ፕሮፌሰሮች ናቸው የሚባልለት Social Text መሳቂያና መሳለቂያ ለመሆን በቃ። በዚሁ አጋጣሚ ይህን ኩነት ተከትሎ <<እንዲህ አይነት ሙከራ ትክክል ነው ወይ?>> በሚል በSokal ደጋፊዎች እና በSocial Text ደጋፊዎች መካከል ለረጅም አመታት የቆየ Sokal Hoax በሚል ጥላ ስር የሚካሄድ ክርክር እንደነበረ መጥቀስ ሁኔታውን በደንብ ለመገንዘብ ይረዳል።

በኋላ ላይ ሳይንስን በተመለከተ አጠቃላይ የድህረ-ዘመናውያን (ታላቅ ስም ያላቸው የንቅናቄው አባላት ጭምር) ኣካሄድ በትርጉም አልባ ሐሳቦች እና ዝባዝንኬዎች የተሞላ እንደሆነ ለማሳየት Sokal, Fashionable Nonsense: Postmodern Abuse of Science የሚል መፅሐፍ ከየሒሳብ ሊቅ ጓደኛው Jean Bricmont በመሆን አሳትመዋል።

እንግዲህ እነ Alan Sokal ን ጨምሮ እንደ Richard Feynman, Carl Sagan, Richard Dowkins... ወዘተ ዓይነት ከየዘመናዊነት መለያ ባህርያት ከሆኑት ሳይንስ እና አመክንዮ/ሎጂክ ያልተጣሉ ሳይንቲስቶች ከላይ ያየናቸውን ድህረ-ዘመናውያን አይነት አስተያየት ሊሰነዝሩ ባይችሉም፤ አሁን አሁን በስፋት የምንሰማው <<መፅሐፍ ቅዱስ ወይም ቁርአን ወይም... ትክክል ነው ብለው የሚያምኑ ሳይንቲስቶች እኮ አሉ>> የሚል ክርክር የድህረ-ዘመናዊነት መስፋፋት ተፅእኖ መሆኑ ግልፅ መሆን ይገባዋል።

1.2 የድህረ-ዘመናዊነት መገለጫዎች በባህል እና በአርቱ አለም

ድህረ-ዘመናዊነት የፈጠረው ወይም ሊፈጥረው እየሞከረ ያለው ማህበረሰባዊ ባህል በፅሑፉ ሦስተኛው ክፍል በስፋት እመለስበታለሁ። እዚህ ላይ የባህል መገለጫዎቹን በአጭሩ ላስቀምጥ። ድህረ-ዘመናዊነት በዋናነት ሊያስፋፋ የሚፈልገው ባህል ፀረ-አብርሆት (anti-enlightenment) ነው። ይሄ የኔ ትንታኔ አይደለም። የድህረ-ዘመናዊነት ንቅናቄ አባቶች ተብለው የሚታወቁት እንደነ ዣክ ደሪዳ (Jacques Derrida) እና ሚሸል ፉኮ (Michel Foucault) በግላጭ የሚሉት ነው። በነ ፉኮ አመለካከት ይሄ ዓለም ሓይለኞች የባህል እሴቶቻቸውን አስተሳሰባቸውንም ጭምር ከማህበረ-ፖለቲካዊ መስተጋብሩ ባገለሏቸው ሰለባዎቻቸው (The disenfranchised) ላይ የሚጭኑበት፤ ሁሉም ደግሞ ለማህበራዊ የክብር ቦታ (status)፣ ለስልጣን (power) እና ለሃይል የበላይነት (domination) የሚሯሯጡበት መድረክ ነው። ድህረ-ዘመናውያኑ ማንኛውንም ችግር የሚመለከቱት እንግዲህ በዚህ ለስልጣን ወይም ለየበላይነት ፉክክር በሚደረግ ትግል እና በውጤቱ በሚፈጠረው የሐይል ሚዛን አለመመጣጠን መነፅር አጮልቀው እያዩ ነው።
509 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 20:41:28 ድህረ-ዘመናዊነት (Postmodernism): ማህበረሰባዊ ዕዳ ወይስ ቡራኬ?

(ዮናስ ታደሰ)

እንደ መግቢያ

ድህረ-ዘመናዊነት እንደ መወያያ ርእሰ ጉዳይ ሆኖ በሚቀርብበት የፍልስፍናዊ ውይይት መድረኮች ላይ፣ "ድህረ-ዘመናዊነት ከሰው ልጅ የሐሳብ ታሪክ ሂደት አንፃር ሲታይ እንደ እድገት ነው የሚወሰደው ወይስ እንደ ውድቀት?" የሚል ጥያቄ ሁሌም የጦፈ ክርክር እንዳስነሳ ነው። "ድህረ-ዘመናዊነትማ ቡራኬ ነው" ብለው ከሚከራከሩት ወገን (በአብዛኞቹ የውይይት መድረኮች ላይ ያስተዋልኩት፣ የሚበዛው የውይይቱ ተሳታፊ ቡራኬ ነው የሚል ነው) የሚነሳ አንድ የመከራከሪያ ሐሳብ ታድያ ግርምትን የሚያጭርብኝ ነው። የመከራከርያ ሐሳቡ ጭብጥ ይዘት ሲጨመቅ እንዲህ የሚል ነው:-

ልክ የሰው ልጅ ግብርና ዘመንን ተሻግሮ የኢንዱስትሪ ዘመን ሲገባ፤ ወይም የኢንዱስትሪ ዘመንን ተሻግሮ የኢንፎርሜሽን ዘመን ሲቀላቀል እድገት ነው እንደምንለው ሁሉ ድህረ-ዘመናዊነትም ዘመናዊነትን ተሻግረን የምንቀላቀለው ዘመን ስለሆነ እንደ እድገት ነው መወሰድ ያለበት።

የዚህ ዓይነቱ መከራከሪያ ሐሳብ ህፀፅ እንግዲህ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ታሪክ እና የፍልስፍና ታሪክ አካሄድ አንድ ዓይነት አድርጎ መፈረጁ ነው። ማለትም ልክ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ታሪክ ላይ በጊዜ ሂደት የታየው ነገር የሐሳብ እድገት ዝግመተ-ለውጥ (በተለይ ያለፉትን ሁለት ወይም ሦስት መቶ ዓመታትን ስንመለከት ፈጣን የሚባል) ስለሆነ እና፤ የዚህን የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ እድገት ተከትሎ የሚመጣው ውጤት ደግሞ ማህበረሰባዊ እድገት እና ስልጣኔ ተደርጎ እንደሚወሰደው ሁሉ፤ በፍልስፍና ታሪክ ላይም በጊዜ ሂደት የሚታየው ነገር የሐሳብ እድገት ዝግመተ-ለውጥ መሆን አለበት፤ ከዚህ የተነሳም የሐሳብ ዝግመተ-ለውጡን ተከትለው የሚፈጠሩ ዘመኑን የሚበይኑ ንቅናቄዎችም ማህበረሰባዊ እድገት ተደርገው ነው መወሰድ ያለባቸው የሚል አንድምታ አለው። ይሄ ግን ስለ ፍልስፍናዊ ንቅናቄዎች (ወይም ስለ ፍልስፍናዊ የዘመን ብያኔዎች) ያለውን የግንዛቤ እጥረት አጉልቶ የሚያሳይ እንጂ ምንም ውሃ የማይቋጥር መከራከርያ መሆኑን በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ የግሪክ እና የሮማ (አንዳንዴ ግሪኮ-ሮማ በመባል የሚታወቀው ዘመን) ስልጣኔዎች ከነበሩበት ዘመን በኋላ ቀጥሎ የመጣውን እና ለ 10 ክፍለ ዘመናት የዘለቀውን የጨለማው ዘመን (The Dark Age) የሚባለውን ማስታወስ በቂ ነው።

የዚህ ፅሑፍ ዓላማ ግን ይሄን ስሑት የመከራከርያ ሐሳብ መተቸት ሳይሆን፤ እንደው ለመሆኑ በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ የሚታወቁትን የዘመን ብያኔዎች ወይም ደግሞ በየጊዚያቱ ለሚከሰቱ ፍልስፍናዊ ንቅናቄዎች በአወንታዊ (ቡራኬ) ወይም በአሉታዊ (ዕዳ/እርግማን) መንገድ እንዲፈረጁ የሆኑበትን ምክንያት በአጭሩ በመዳሰስ፤ በዚሁ መነፅርም ድህረ-ዘመናዊነትስ የትኛው ምድብ ላይ—ዕዳ/እርግማን ወይስ ቡራኬ— እንደሚመደብ ወይም ሊመደብ እንደሚገባ ለማሳየት ነው።

ስለዚህ የፅሑፉ አካሄድ የሚሆነው በመጀመርያው የፅሑፉ ክፍል (section) ዘመናዊነት ምንድን ነው? ለሚል ጥያቄ አጭር ብያኔ በማስቀመጥ በዚሁ ብያኔ መሰረት ድህረ-ዘመናዊነት ዘመን ላይ ነው ያለነው ሊያስብሉ የሚችሉ መገለጫዎችን ከተለያዩ ኣቅጣጫዎች በተለይም ከሳይንስ፣ ከባህል፣ እና ከአርት አንፃር ማሳያ ሊሆኑ የሚችሉ ክስተቶችን ወይም ኩነቶችን እያጣቀስን እንመለከታለን። በሁለተኛው የፅሑፉ ክፍል ደግሞ ለድህረ-ዘመናዊነት መነሳት ዋና መግፍኤ ምክንያት የሆነውን ነገር ለማንፀር እንዲረዳን አሁንም አጭር የፍልስፍና ታሪካዊ ዳራ በማስቀመጥ፤ በዚሁ የፍልስፍና ታሪክ ማእቀፍ ውስጥ ተለይተው በስፋት የሚታወቁትን የዘመን ብያኔዎች ወይም ደግሞ ፍልስፍናዊ ንቅናቄዎችን በአዎንታ ወይም በአሉታ የሚወሱበትን ምክንያትም እንመለከታለን። ከዚህ በመነሳትም በሦስተኛው እና የፅሑፉ መደምደሚያ በሚሆነው ክፍል "ድህረ-ዘመናዊነት ዕዳ ወይስ ቡራኬ?" ለሚለው ጥያቄ ተገቢው መልስ መሆን ያለበትን በማስቀመጥ እንቋጫለን።

1. ድህረ-ዘመናውነት ምንድን ነው? መገለጫዎቹስ?

በመጀመርያ ደረጃ ሊታወቅ የሚገባው ነገር ቢኖር ድህረ-ዘመናዊነት ለ የዘመናዊነት (modernity) ንቅናቄ ግብረ-መልስ ሆኖ በ1970ዎቹ አካባቢ የተነሳ ንቅናቄ እንጂ አንድ ወጥ የሆነ በስርዓት የተዋቀረ ፍልስፍና ወይም ዶክትሪን አይደለም። ድህረ-ዘመናዊነት ማለት:-

ሰዎችን ሁሉ እኩል በሆነ መንገድ የሚያስማማ ሁለንታዊ እውነት (universal truth) የሌለበት፤ እውነት እና ሞራሊቲ አንፃራዊ የሆኑበት፤ ሁሉም ባህሎችና ሃይማኖቶች ትክክል የሚሆኑበት ("ጎጂ ባሕል" የሚባል ነገር የሌለበት)፤ ሰዎች እውነትን ከገሃዱ ዓለም ጋር አመሳክረው የሚፈልጉበት ሳይሆን በዲስኩር፣ በቋንቋና በፖለቲካ ላይ ተመርኩዘው የ"እውነትን" ተፈጥሮ የሚረዱበት አዲስ ዓለም ነው። (ፋሲል መርዓዊ፣ የፍልስፍና ትምህርት ቅፅ-፩)

ድህረ-ዘመናውያን "እውነትን ኣንፃራዊ" ከማድረጋቸው ወይም ደግሞ አሁን አሁን በ"ድህረ-እውነት/post-truth" አቋማቸው "እውነት የሚባል የለም" ከማለታቸው የተነሳ፤ ከባህል፣ ከሞራሊቲ፣ ከፖለቲካ፣ ከቋንቋ ወዘተ ኣንፃር እጅግ የተለያዩ እና ኣብዛኛውን ጊዜም እርስ በራሳቸው እየተጣረሱ በሚያቀርቡት ሐሳብ ምክንያት ድህረ-ዘመናዊነትን በተመለከት አንድ ወጥ የሆነ ብያኔ ለማስቀመጥ አስቸጋሪ ቢያስመስለውም፤ ከስነ-እውቀት አኳያ ግን ሁሉንም ኣስተሳስሮ የሚይዝ መሰረተ-ሐሳብ (premise) አለ:-

ብዙ ከስረ-መሰረታቸው የሚለያዩ ግን ደግሞ "በእኩልነት ተገቢ" የሚባሉ ዓለምን የምናውቅባቸው መንገዶች አሉ፤ ሳይንሳዊው የእውቀት መንገድም ከነዚህ የእውቀት መንገዶች አንዱ እንጂ ብቸኛው የእውቀት መንገድ አይደለም። (Paul Boghossian, The Fear of Knowledge)

ስለ ድህረ-ዘመናዊነት ብያኔ ይሄን ያክል ካልን ይበቃናል። እስቲ አሁን ደግሞ ድህረ-ዘመናዊነት ዘመን ላይ ነን ሊያስብሉ ከሚችሉ መገለጫዎች ውስጥ ጎልተው የሚታዩትን በጥቂቱ እንመልከት።

ይቀጥላል...

Yonas Tadesse Berhe
822 views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 20:39:49
857 views17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 21:42:29 ኢትዮጵያ ኑዛዜን የነፈገችው ታላቁ ሰዓሊ!
============================

(ይትባረክ ዋለልኝ)

በ19 50ዎቹ ዘመን የተነሱ የኪነጥበብ ባለሙያዎች በስራዎቻቸው ከሐገራቸው አልፈው በአለም ተወዳደሪ መሆናቸው ስራዎቻቸው ህያው ምስክሮች ናቸው:: የዚህ ዘመን የጥበብ ሰዎች በሐገሩ ፍቅር የተቃጠሉ ለተበደለውና ለተገፋው የሚቆረቆሩ: በስራቸው ለተገፉት ድምፅ የሆኑ ነበር:: ዛሬ ከነዚሁ የጥበብ ባለሙያዎች መካከል ስለ ሰዓሊ ገ/ክርስቶስ ደስታ አንዱ ነው:: ዛሬ ገ/ክርስቶስ ለምን ከሐገሩ ተሰደደ ? ስል እጠይቃለሁ::

ሰዓሊና ገጣሚ ገ/ክርስቶስ ደስታ አገሩን አጥብቆ የሚወድ ታላቅ የስነጥበብ ሰው ነበር:: ገ/ክርስቶስ ለአገሩ የነበረውን ፍቅር “ኢትዮጵያ እናቴ“ ሲል በሰጣት ቦታ የአገሩን ናፍቆት “አገሬ“ “እንደገና“
በተሰኙ ግጥሞቹ እንደዚሁም የአገር ቁጭቱን “የጾም ቀን“ እና “በባእድ አገር“ በተሰኙት ግጥሞቹ በሚገባ ገልጾታል፡፡ በተለይ አገሬ የተሰኘው ግጥሙ አንጀት ይበላል፡፡ ምን ይደረግ ይህ ታላቅ ሰው በስደት እንደማሰነ ሃገሩ ኑዛዜን ነፍጋው የአገሩን አፈር ለመቅመስ አለመታደሉ ያስቆጫል፡፡ ለነገሩ ይህች ሃገር ኑዛዜን የነፈገቻቸው ስንት ታላላቅ ኢትዮጵያውያን እንዳሉ ሁላችንም የምናውቀው ነው:: ዛሬ ግን ገ/ክርስቶስ ደስታ እንዲህ ሐገሩን እየወደደ ለምን ስደት?

ከዚህ በታች ሰዓሊው በደርግ የስልጣን ዘመን በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የስዕል ዓውድ ርዕይ አዘጋጅቶ ነበር :: ዓውዱ ርዕዩን በማስመልከት ቁምነገር ከተሰኝ መፅሔትን ጋር ቃለመጠይቅ አድርጎ ነበር:: እኔም መፅሔቱን አግኝቼ ገብሬ የደረገውን ቃለ መጠይቅ አነበብኩኝ:: ለገብሬ የቀረቡትን ጥያቄዎችና የእርሱን መልስ ሳነብ በጣም አመመኝ:: ጥያቄዎቹ አቋምያላቸው እና ይህን የጥበብ ሰው ከስርዓቱ ጋር ሆን ብለው አጋጭተው አንድ ነገር ለማስደረግ እንደሆነ ጥያቄዎቹ በሚገባ የሚያሳዩ ናቸው:: እኔም የገብረክርስቶስን መልስ ትቼ የተወሰኑትን ጥያቄዎች ብቻ ላካፍላችሁ::ሙሉ ጥያቄና መልሶቹን በፎቶ አስደግፌዋለሁ!!

ለሰዓሊ ገ/ክርስቶስ የቀረቡ ጥያቄዎች
==========================

ጥያቄ:- እንግዲህ በአንዲት በተፋፋመ አብዮት ውስጥ በምትገኝ ሐገር የእርስዎ አጠቃላይ የሥዕል ኢግዚቢሽን ቀርቧል:: እነዚህ ስራዎች አብዮታዊ የሆነ ኪነታዊ ይዘትና ቅርፃቸውን ከትግሉ አንፃር አሟልተው ቀርበዋል ብለው ያምናሉ?

ጥያቄ:-የወደቀውን የኃይለስላሴን የፊውዳል ቡርዧ መንግስት ለመጣል በየቦታው የመረረ ትግል ይካሄድ ነበር::መቼም ይህን ትግል ለነፃነትና ለተሻለ ስርዓት የሚደረግ መሆኑ ትክክለኛነቱ አያጠራጥርም:: ታዲያ በዚያን ጊዜ ለትግሉ በአለዎት ሙያ ያህል ተሳትፎ አድርገዋል?

ጥያቄ:-በተለይ በአሁኑ የመደብ ትግል በተፋፋመበት ጊዜ ሥዕል ለኅብረተሰቡ የሚሰጠው አገልግሎት ምንድን ነው?

ጥያቄ :-በኅብረተሰቡ ውስጥ በሚደረገው የመደብ ትንቅንቅ ሥዕል የመደብ ፀባይን ያንፀባርቃል?

ጥያቄ:- ከየካቲት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በፊት በሰሯቸው ሥዕሎችና ከዚያ ወዲህ በሳሏቸው ሥዕሎች መካከል ልዩነት አለ? ከአብዮቱስ ምን ተምረዋል?

ጥያቄ:-በኢትዮጵያ ውስጥ የስዕል እድገት ከአብዮቱ ወዲህ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

ጥያቄ:- ከስራዎችዎ መካከል "የወዛደሩ መልክ" ብለው ያቀረቡት ስዕል በርግጥ ወዛደሩን ይወክላል?በኃሳብዎ ነው የሳሉት? ወይስ ተመልክተው የወዛደሩን ሕይወት በርግጥ ያንፀባርቃል ብለው ያምናሉ?

ጥያቄ:- .....በአብስትራክት የአሳሳል ዘዴ በአሁኑ ጊዜ በተለይ ትግል በተፋፋመበት ወቅት ትግሉን ለማጉላት ለሕዝቡ ለማቅረብ ምን መልዕክት አለው ይላሉ? ለመጥቀስም "ሰማያዊ ድርሰት "ብለው የሰየሙትን የእብስትራክት ስዕል .....

ጥያቄ:- የሥዕል ተቀዳሚ አላማው ለንግድ ህዝብን የመቀስቀሻና የማስተማሪያ መንገድ ነው::ስለዚህም ስለ መደብ ትግሉ ለማስተማርና ቅስቀሳ ለማድረግ ወደ ሰፊው ህዝብ ጠልቆ መግባት ያስፈልጋል::በዚህ አንፃር እርስዎ በሙያዎ አማካኝነት ከዚህ በፊት ምን አድርገዋል? ወደፊትስ ምን ውጥን አለዎት?

ጥያቄ :-የዕርስዎ የስዕል ትርኢት ተከፍቶ በመታየት ላይ ሳለ አንዲት 12 ገጽ ያላት የሥዕሎችን ስምና አንዳንድ ጋዜጦች የሰጡበትን ፅሑፍ የያዘች ትንሽ መፅሔት በአንድ ብር ሂሳብ በመሸጥ ለንግድ ውላለች ለምንድን ነው ልትሸጥ የቻለችው?

ለዚህም ይመስላል ገብረክርስቶስ ደስታ ይህንን ግጥም መፃፉ!

ከባዕድ ሰማይ ስር
============
ጉም እንደጨለፈ፣
የነሌኒን ምርኮ፣ ያ ትውልድ አለፈ፡፡
አወይ ምስኪን ቧጋች፣ ሕልሙን የተቀማ
ራዕይ መሣይ ቅዠት ደጋግሞ እየሰማ፡፡
መልስ አልባ ጥያቄ ከንቱ እንደጠየቀ
ይኼኛውም ያልፋል ከራሱ እንደራቀ።

የገብረክርስቶስ ግጥም ጩኸቱ ይሄ ነው::

በሌላ ጊዜ ገብረ ክርስቶስ ደስታ በስደት በነበረበት ዘመን የፃፈውን ልብ የሚነካ ደብዳቤ አካፍላችኃለው::

Yetebarek Walelegn
1.8K views18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 21:39:21
1.5K views18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 15:21:27 9/ ብ/ጀ ከበደ ወ/ጻዲቅ = የ 606ኛ ኮር ዋና ም/አዛዥ
10/ ብ/ጀ ሰለሞን ደሳለኝ = የ 102ኛ አየር ወለድ ክ/ጦር ዋና አዛዥ
11/ ዶ/ር ኮሎኔል ጌታቸው አወቀ = የሁአሰ ሆስፒታል ሜዲካል ዳሬክተር
12/ ኮሎኔል መስፍን አሰፋ = የ2ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር አዛዥ
13/ ኮሎኔል ፈቃደ እንግዳ = የሁአሰ ዘመቻ መምሪያ ረ/ኃላፊ
14/ ሌ/ኮ ዘርአይ እቁባአብ = የሁአሰ ቀዳሚ መምሪያ ፖለቲካ ኃላፊ
15/ ሌ/ኮ ዮሀንስ ገብረማሪያም = የመከላከያ ቀዳሚ መምሪያ ወታደራዊ መረጃ ኃላፊ
16/ ሻለቃ ካሳ ፈረደ = የሁአሰ መሀንዲስ መምሪያ ኃላፊ
17/ ሻለቃ ሚካኤል ማርቦ = የ 2ኛ ታንከኛ ብርጌድ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ
18/ ሻምበል ጌታሁን ግርማ = የሁአሰ ዋና አዛዥ ልዩ ረዳት መምሪያ ኃላፊ

ይህ ሁሉ የጦር ጠበብቶች እልቂትም እንዲህም በመቶዎች የሚቆጠሩ መኮንኖች የጅምላ እስር ግዙፋን ሰራዊት ያለ እውነተኛ እና ልምድ ያለው መሪ በማስቀረት በአጭር ጌዜ ውስጥ ሰራዊቱን ሙሉ ለሙሉ ለአስከፊ ውድቀት ዳርጎታል ።

ፈጣሪ የማች መኮንኖችን ነፍስ ይማር

Dechasa Angecha Tadesse
2.0K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 15:21:27 የአብዮታዊው ሰራዊት ጥቁር ቀን

ዝክረ ግንቦት 8 1981 ዓ.ም ያልተሳካና ደም አፋሳሽ የነበረው መፈንቅለ መንግስት ሙከራ

ልክ በዛሬዋ ቀን ከ34 ዓመት በፊት ግንቦት 8 1981 ዓ.ም በከፍተኛ ጀነራል መኮንኖች በፕሬዚደንት ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማርያም ላይ በአዲስ አበባና በአስመራ ላይ ደም አፋሳሽ ሆኖ የተጠናቀቀው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ የተደረገበት ዕለት ነው ።

ይህች ቀን በተለይም በአዲስ አበባ እና በአስመራ የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች እቅዳቸውን ለማስፈፀም የኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን ለጉብኝት ከሀገር መውጣት ተከትሎ እንቅስቃሴ የጀመሩበት እለት ነበረች ።
የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች በግንቦት 8 ቀን ረፋድ ላይ አዲስ አበባ አምባሳደር ቲያትር አካባቢ በሚገኘው የመከላከያ ሚኒስቴር ህንፃ ውስጥ በኢታማጆር ሹሙ ሜጀር ጀነራል መርዕድ ንጉሴ መሪነት የዕቅዱ አተገባበር ላይ ውይይት ይዘዋል ።

ሌ/ኮ መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ምስራቅ ጀርመን / GDR ለጉብኝት ለመጓዝ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ውስጥ ገብተዋል ። የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች የኮ/ል መንግስቱን አገዛዝ ለማስወገድ መከላከያ ሚኒስቴር ህንፃ ውስጥ የዕቅድ አፈፃፀም ውይይት ላይ ነበሩ ።

ጀነራሎቹ "ኮሎኔሉን በአየር ላይ እንዳሉ በአየር ኃይል ጀቶች ይመቱ አሊያም በአየር ኃይል ጀቶች ተገደው አስመራ አርፈው በቁጥጥር ስር ይዋሉ " በሚለው ቁልፍ የመፈንቅለ መንግስቱ ጉዳይ ላይ መስማማት ላይ ሳይደርሱ ፕሬዚደንቱን የያዘቸው አውሮፕላን የኢትዮጵያን የአየር ክልል ለቃ ወጣች ።

አዲስ አበባ ያሉት የጦር መሪዎች እርምጃ ሳይጀምሩ ቀደም ብሎ በታሰበው የአፈፃፀም እቅድ መሰረት አስመራ የነበረው በሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ደምሴ ቡልቶ የተመራው ኃይል ከአዲስ አበባ በተላከለት መልእክት መሠረት አድርጎ ኮ/ል መንግስቱ እንደተወገዱ ስለተነገረው እሱ መረጃ ይዞ ወደ ማስፈፀሙ ገብቶ መንግስቱ ኃይለማርያም ከስልጣን መውረዱን በአስመራ ራዲዮ አስነገረ ።

አዲስ አበባ ያለውንም እንቅስቃሴ ለመርዳት እና ቁልፍ የተባሉ መንግስታዊ ተቋማትን የራዲዮና ቴሌቭዥን ጣቢያ ፣ አየር ማረፊያ ፣ ቴሌኮሚኒኬሽን፣ የጦር ክፍሎች ፣... ለመቆጣጠር እንዲቻል መቺ ኃይል የሆነውን ኤርትራ የነበረውን 102ኛ አየር ወለዱን በሁአሠ ም/አዛዥ በነበሩት ሜ/ጀ ቁምላቸው ደጀኔ መሪነት ከአስመራ ወደ አዲስ አበባ ላከ ።

ይሁን እንጂ በኋላ የነገሩን መበላሸት አይቶ የሀይል አሰላለፉን አስተካከለ በተባለለው የደህንነት ሚንስትሩ ኮሎኔል ተስፋዬ ወልደስላሴና በሻንበል መንግስቱ ገመቹ በሚመራው የልዩ ጥበቃ ብርጌድ አማካኝነት የአዲስ አበባው መፈንቅለ መንግስት ሙከራው አመሻሽ ላይ ከሸፈ ። ኮሎኔል መንግስቱም ከምስራቅ ጀርመን ወደ አዲስ አበባ በፍጥነት ተመለሱ ።

የአዲስ አበባው መፈንቅለ መንግስቱ በተለያዩ ምክንያቶች ከጥቂት ሰአታት በኃላ ሲከሽፍ ኢታማጆር ሹሙ ሜ/ጀ መርዕድ ንጉሴ እና የአየር ኃይል አዛዡ ሜ/ጀ አመኃ ደስታ መከላከያ ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ራሳቸውን በታጠቁት መሣሪያ አጠፉ ። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የነበሩት ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይ ከሙከራው በኋላ ተሰውረው በፀጥታ ሃይሎች ሲፈለጉ ቆይተው ከሙከራው አራት ቀን በኋላ መከላከያ ሚኒስቴር ግቢ ውስጥ ተሸሽገው ተገኙ ። ጄኔራል ፋንታ ከተያዙ ከቀናት በኋላ እዚያው የታሰሩበት ማዕከላዊ ምርመራ ግቢ ውስጥ ባልታወቀ ምክንያት ተገደሉ ።

ሌላው የመፈንቅለ መንግስቱ ዋና ጠንሳሽ የዘመቻ መምርያ ኃላፊ የነበሩት ሜ/ጀነራል አበራ አበበ ጠንሳሾቹን ለማነጋገር የመጡትን የወቅቱን የመከላከያ ሚኒስቴር የነበሩትን ሜ/ጀነራል ኃ/ጊዮርጊስ ሀ/ማርያምን በሽጉጥ ክፋኛ አቁስለው ከጊቢው በአጥር ተንጠላጥለው አመለጡ ።

1/ ሜ/ጀ ኃይሉ ገ/ሚካኤል - የምድር ጦር ዋና አዛዥ
2/ ሜ/ጀ ወርቁ ዘውዴ - የፖሊስ ሰራዊት ጠቅላይ አዛዥ
3/ ሜ/ጀ ዓለማየሁ ደስታ - የምድር ጦር ምክትል አዛዥ
4/ ሜ/ጀ ዘውዴ ገብረየስ - የ603ኛ ኮር ዋና አዛዥ
5/ ብ/ጀ ደሣለኝ አበበ - የጦር ኃይሎች አካዳሚ ዋና አዛዥ 6/ ብ/ጀ ሰለሞን በጋሻው - የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ
7/ ብ/ጀ ተስፋ ደስታ - የአየር ኃይል ዘመቻ መኮንን
8 ብ/ጀ እንግዳ ወ/አምላክ - የ606ኛ ኮር ዋና አዛዥ /ሁአሰ 9/ ብ/ጀ እርቅይሁን ባይሣ - የ607ኛ ኮር ዋና አዛዥ /ሁአሰ 10/ ብ/ጀ ነጋሽ ወልደየስ - የ 608ኛ ኮር ዋና አዛዥ /ሁአሰ
11/ ብ/ጀ ገናናው መንግሥቴ - የ6ኛው አየር ምድር ዋና አዛዥ /ሁአሰ
12 ብ/ጀ ተስፋዬ ትርፌ - በአገር መከላከያ ሚኒስቴር ዘመቻ መኮንን

መፈንቅለ መንግስቱን ለማክሸፍ በተንቀሳቀሰው በሻንበል መንግስቱ ገመቹ በተመራው የልዩ ጥበቃ ብርጌድ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ ። በመጨረሻም ከአንድ አመት የጦር ፍ/ቤት ሂደት በኃላ ግንቦት 13/1982 ዓ.ም በፖለቲካዊ ውሳኔ ተረሸኑ ።

የሁአሠ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ደምሴ ቡልቶ የመሩት የአስመራው የመፈንቅለ መንግስቱን የሶስት ቀናት እድሜ አስቆጥሮ ነበር ። ሙከራው መክሸፋ ተከትሎ የ102 ኛ አየር ወለድ ወታደሮች ጀነራል ደምሴን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ መኮንኖችን በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት እየደበደበና በጭካኔ እናነቀ በዘፈቀደ ፈጃቸው ።

የዘመቻ መምሪያ ዋና ኃላፊ የነበሩት ሜ/ጀ አበራ አበበ መፈንቅለ መንግስቱ ከተካሄደበት መከላከያ ሚኒስቴር ግቢ አጥር ዘሎ አምልጠው ለወራት ሲፈለጉ ከቆየ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኝ የዘመዱ ቤት ውስጥ ተደብቀው ቆይተው በጥቆማ ፖሊሶች ደርሰውባቸው ቤቱ ሲከበብ ሜ/ጀ አበራ አጥር ዘሎ ለማምለጥ ሲሞክሩ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ ።

መቺ ሀይል ከአስመራ በአንቶኖቭ ጭነው አዲስ አበባ የመጡት ሜ/ጀ ቁምላቸው ደጀኔ የነገሮች መበላሸትና የግንኙነት መስመር ስለተቋረጠባቸው ተሠውረው በመቆየት ከሀገር በሙውጣት በመጨረሻ አሜሪካን ገቡ ። ዋና ተዋናይ ሆነው ብቸኛ በህይወት የተረፋ ጀነራልም መኮንንም እሳቸው ብቻ ናቸው ።

ከሁለተኛው አብዮታዊው ሰራዊት ዋና አዛዥ ሜ/ጀ ደምሴ ቡልቶ ጋር በአስመራ ከተማ በ102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ህይወታቸው በአሰቃቂ ና በዘፈቀደ ሁኔታ ህይወታቸውን ያጡት ስመጥር ጀነራሎች እና ሌሎች መኮንኖች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

1/ ብ/ጀ አፈወርቅ ወ/ሚካኤል = የኤርትራ ክ/ሃገር የአስቸኳይ ጊዜ ዋና አስተዳዳሪ
2/ ብ/ጀ ታዬ ባላኪር = የኤርትራ ክ/ሃገር አቢዮታዊ ፖሊስ ዋና አዛዥ
3/ ብ/ጀ ታደሰ ተሰማ = የሁአሰ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
4/ ብ/ጀ ወርቁ ቸርነት = የሁአሰ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ
5/ ብ/ጀ ንጉሴ ዘርጋው = የአስመራ አየር ኃይል ዋና አዛዥ
6/ ብ/ጀ ከበደ መሀሪ = የሁአሰ ድርጅት መምሪያ ኃላፊ
7/ብ/ጀ ተገኔ በቀለ = የኤርትራ ክ/ሃገር የአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር ዘመቻ መኮንን
8/ ብ/ጀ ከተማ አይተንፍሱ = የ 606ኛ ኮር ዋና አዛዥ
1.6K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ