Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.28K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-07-02 22:35:46 በእውቀቱ ስዩም

—የታሪክ እውቀቱ ያስደንቀኛል። ሰፊ እና ዝርዝር የታሪክ እውቀት አለው። የነገስታት ታሪክ፣ የቤተክህነት ታሪክ፣ የጦርነት ታሪክ ወዘተ ወዘተ

—ታሪክ በመሰረቱ አሰልቺ ነው። በዚህን ግዜ እንዲህ ሆነ እንዲህ ተከሰተ ወዘተ ወዘተ ይህንን እውቀቱን ሳይቸክ በለዛ አስውቦ፣ በጥበብ ይተርካል። ያነበበውን ታሪክ እንደወረደ ሳይሆን አመንዥኮ፣ ከራሱ ጋር አዋህዶ፣ የራሱን ቀለም ጨምሮ እንካችሁ ይላል። ደግሞም ታሪክ አውቃለሁ ብሎ አይዘላብድም። የታሪክ እውቀቱን በትክክለኛ አውድ ነው የሚጠቀመው። ለሁሉም አውድ የሚሆን የታሪክ እውቀት ከየት አመጣ?! ምን ያህል ቢያነብ ነው?! 'ገርሞኝም አያባራ' አለ ጋሽ ስብሐት።

—በግሌ ለግጥም እምብዛም ነኝ። መንፈሴ ብዙም ለግጥም አይደነግጥም። የበእውቄን ግጥም ግን እያሳደድኩ አነባለሁ። ቃላቶቹ ፍጹም ሆነው ሲሰካኩለት ሚሊየን ግዜ ተመልክቼ ተደንቄያለሁ። በሚያነሳው ሃሳብ እና ቁምነገር፣ በተመረጡ ቃላቶቹ፤ ስሜትን ቆንጥጦ በመያዙ ዘወትር እንደተደመምኩ ነው።

—ሌላው የበውቄ ታላቅ ችሎታ ቧልቱ ነው። በዚህ እንደ ማርክ ትዌይን ካሉ ታላላቅ ቧልተኞች ጋር ይመደባል። ቧልት የነጠረ የጥበብ ዘዬ ነው። ቧልት አለቅጥ የተነፋ ፊኛን የሚያስተነፍስ የተወጠረ ስሜትን የሚያረግብ ረቂቅ መሳሪያ ነው። በእውቄ በቧልቱ ትልልቅ ጉዳዮችን በምጸት ይተቻል። ከማንኛውም አናዳጅ ሁኔታ ውስጥ ፈገግታ ይፈጥራል፤ ሳቅ ያመርታል።

—በእውቄ ብልጥ ነው። ይህ ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ከንባብ እንደተጣላ፣ ብዙም እንደማያነብ ስላወቀ ወጎቹን በሲዲ አሳትሞ መጣ። እንዲያውም ብዙ ኢትዮጵያዊ መጽሀፍ ስለማይገልጥ፣ 'በእውቀቱ ስዩም ማነው?' ብለህ ብትጠይቅ 'እ! ኮሜዲያኑ!' የሚል መልስ ታገኛለህ።

ሁሉም ዘመን የራሱ ደራሲዎች፣ ገጣሚዎች፣ ፈላስፋዎች፣ ጸሀፊ ተውኔቶች አሉት። በእናንተ ዘመን ማነበር ተብዬ ብጠየቅ ሳላመነታ፦

በእውቀቱ ስዩም
አዳም ረታ
አለማየሁ ገላጋይ
እንዳለጌታ ከበደ እላለሁ።

Tewodros Shewangizaw
1.7K views19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 22:35:38
1.5K views19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 14:02:48
የበጎ አድራጎት ዘመን … የክፉ አድራጎት ዘመን … የብልኽነት ዘመን … የሞኝነት ዘመን … የጽኑ ዕምነት ዘመን … የጥርጣሬ ዘመን … የብርሐን ዘመን … የጭለማ ዘመን … ተስፋ የሚጣልበት ዘመን … ተስፋ የማይጣልበት ዘመን … ሁሉም ነገር የተሟላበት ዘመን … አንዳችም ነገር ያልተሟላበት ዘመን … የደስታ ዘመን የኀዘን ዘመን። ባጭሩ ዘመኑ ተቃራኒ ኹኔታዎች የነገሡበት ዘመን ነው።

It was the best of times, it was the worst of times, it was the age of wisdom, it was the age of foolishness, it was the epoch of belief, it was the epoch of incredulity, it was the season of Light, it was the season of Darkness, it was the spring of hope, it was the winter of despair, we had everything before us, we had nothing before us, we were all going direct to Heaven, we were all going direct the other way.



… ቀን በንግድ ሥራ ተሰማርተው የሚውሉ ነጋዴዎች ሌሊት ጭለማ ለብሰው የውንብድና ሥራ ይፈጽሙ ነበር። ተራ ወንበዴዎች በቀን ብርሐን የሠላማዊ ዜጎችን ንብረት ይዘርፉ ነበር። በኧርስ በርሳቸውም መሣሪያ ተታኩሰው ይገዳደሉ ነበር።



ዘመኑ ሽፍቶች የገነኑበት ዘመን ነው።



"የሁለት ከተሞች ወግ" በቻርለስ ዲክንስ፣ ሣህለብርሐነ ማርያም አስጥረው እንደመለሱት

@Bookshelf13 @Bookshelf13
@Bookshelf13 @Bookshelf13
1.7K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 20:22:12 ሃያስያን ልብወለዶችን በሁለት ትላልቅ ክፍሎች ይመድባሉ፦ ሴራ መር እና ገጸባህሪይ መር ብለው። ስሞቹ በራሳቸው ገላጭ በመሆናቸው አላብራራም።

ጥሩ መጽሀፍ ሳነብ ከሁሉም ነገር በላይ የሚመስጡኝ ገጸባህሪያቱ ናቸው። ሴራው አይደለም፤ ታሪኩ አይደለም። በአሜሪካ ስነጽሑፍ ጎልተው ከወጡ ልብወለዶች አንዱ Gone with the Wind ነው። የዚህ ልብወለድ ዋና ገጸባህሪይ ደግሞ እስካርሌት ኦ'ሃራ ናት። በጣም ሊጠኑ፣ ሊመረመሩ ከሚገቡ ትላልቅ ገጸባህሪይ መሀል እስካርሌት አንዷ ናት።

እስካርሌት ደፋር ናት፤ ሁልግዜ የፈለገችውን ታገኛለች።
መጽሀፉ እንዲህ ይላል፦ "እስካርሌት ጠይቃ የተከለከለችው አሽሌን ብቻ ነው"። እስካርሌት controlling ናት፤ ለራሷ የተጋነነ አመለካከት አላት፤ ቀበጥ ናት፤ በወንዶች ስሜት መጫወት ትወዳለች።

በእርግጥ እስካርሌት ብዙ ጉድለት አለባት። ግን ሃይለኛነቷ፣ በወንዶች አለም ወንዶችን በልጣ መገኘቷ ጠንካራ ጎኗ ነው። ከእስካርሌት ባህሪ ሁሌ የሚገርመኝ she takes the driver's seat። ከማንም ጋር ማንም ቦታ ብትሆን የራሷን ፍላጎት ታስቀድማለች። ሰዎችን እንደ እቃ ትጠቀምባቸዋለች።

ሌላው ደግሞ ውስጧን የምታዳምጥ አይመስለኝም። አለሟ ከውጪ ነው። ጭር ሲል አትወድም። መታየት ትፈልጋለች።

በብዙ የአለም ባህል አንድ ወንድና ሴት ቢዋደዱ ቀድሞ የፍቅር ጥያቄ የሚያቀርበው ወንዱ ነው። ሴቷ ብትወድም፣ ፍላጎቱ ቢኖራትም አፍ አውጥታ አትጠይቅም፤ ፍንጭ ልትሰጥ ትችላለች። የፈለገው ቢሆን ከዛ አታልፍም። እስካርሌት ግን ሴት አይደለችም። አፍ አውጥታ አሽሌይን 'እወድሃለሁ' አለችው። የፍቅር ጥያቄዋን አልቀበል ሲላት በጥፊ ታጮለዋለች።

የታባቱ!!

ሬት በትለርም የወደዳት ይሄንን አይቶ ነው። እስካርሌት እንደ ሌሎቹ የደቡብ ሴቶች አይደለችም። በዘወርዋራ መንገድ አትሄድም፤ አንድ ነገር ከፈለገች ቀጥታ ሄዳ ታገኘዋለች።

አባቷ በጣም ይወዳታል፤የጠየቀችውን ነገር ሁሉ እየሰጠ ነው ያሳደጋት። ሴት ብትሆንም የመጀመሪያ ልጅ ስለሆነች በነጻነት ነው ያደገችው—እንደ ሴት ቁጥጥር ሳይበዛባት። ስለዚህ ሁሉም ጥሩ ነገሮች እንደሚገቧት እያሰበች ነው ያደገችው

የእስካርሌት ችግር ከአስተዳደጓ ይመስለኛል። ለልጅ ሁሉም ሊሰጠው፣ ሁሉም ሊከለከል አይገባም። እስካርሌት ሁሉም እየተሰጣት ነው ያደገችው። አሽሌይን ፈለገች፤ እቅድ አወጣች፤ እቅዷ አልሰራም፤ ይሄኔ ተናደደች፤ የማታውቀው ነገር ሆነ፤ እኔኮ እስካርሌት ነኝ!
የፈለግኩትን ሁሉ አገኛለሁ።

መጽሀፉ እንዱህና እንዲህ እየጦዘ ታሪኩ ይቀጥላል!

Tewodros Shewangizaw
1.6K views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 20:21:50
1.3K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 20:17:00 ግዜው 1860 ነው። ሬት በትለር 35 አመት ሞልቶታል። የእርስ በእርስ ጦርነቱ ሊጀምር ነው። ሁለቱም ወገኖች የጦርነት ድቤ እየደለቁ ነው። ደቡባውያኑ ሰፋፊ የጥጥ እርሻ ያላቸው ሃብታሞች ናቸው። እርሻው የሚለማው በባሮች ጉልበት ነው። ሰሜናውያኑ በበኩላቸው ባርነትን አጥፍተው ህገወጥ አድርገውታል። በምትኩ ትላልቅ ኢንደስትሪዎችን ተክለዋል።

አብርሃም ሊንከን ለፕሬዚዳንት ሲወዳደር ከተመረጠ ባርነትን ከመላው አሜሪካ እንደሚያጠፋ ቃል ገባ። ምርጫውን ሲያሸንፍ የገባውን ቃልኪዳን ለመጠበቅ ስራውን ጀመረ። አንድ ሃገር በሁለት የተለያየ ስርአት መተዳደር እንደሌለባቸው አወጀ። ይኼኔ ሁለቱም ወገኖች ተቆጡ።

ደቡባውያኑ ያላቸው አንድ ነገር ሰፋፊ እርሻ ነው። ባርነት ከተወገደ እርሻቸውን ማን ያለማላቸዋል? በባሮች ትከሻ ቀለል ያለ ኑሮ የሚኖሩ ህዝቦች ነበሩ። የባርነት ስርአትን ማፍረስ ያንን የተንደላቀቀ ህይወት መሰናበት ነው።

ሬት በትለር ግን እንደ ሌሎቹ ደቡባዊውን አይደለም። የኮንፌዴሬሲው ባንዲራ ሲውለበለብ ሰውነቱን አይወረውም። ብሔራዊ መዝሙር ሲዘመር አይነሽጠውም። እንዲያውም ሬት እንዲህ ይላል፦

"ሃገር ስትበለጽግ አብሮ ሃብታም መሆን ይቻላል። በተቃራኒው አለም ወደ ውድቀት ስትንደረደር የበለጠ እጥፍ ሃብታም መሆን ይቻላል።"

በዚህ ፍልስፍና እየተመራ ሬት በሙሉ ሃይሉ ወደ ኮንትሮባንድ ንግድ ውስጥ ይገባል። ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ የማይሸጠው ቁሳቁስ አልነበረም—ከሽቶ እስከ መሀረብ፣ ከመጠጥ እስከ ልብስ። ሬት በትለር መላው ሃገር ወደ አመድነት ቢቀየር ግድ የሚሰጠው ሰው አይደለም። ለሱ ዋጋ ያላቸው ነገሮች የንግድ ስራውና ትርፉ ብቻ ናቸው።

ጦርነቱ ሲገባደድ ሬት ሚሊየነር ሆኗል። ይህ ሃብት በብዙሃን ደም የተገኘ ነው። ሬት በተደጋጋሚ የሚጠቀማት አንድ ሃረግ አለች፦

"እንደ እውነቱ ከሆነ ውዴ ምንም ግድ አይሰጠኝም።"

አዎ ሬት ግድ አይሰጠውም። ሃገሪቷ በእሳት ብትነድ ግድ አይሰጠውም፤ ሚሊየኖች ቢሞቱ ግድ አይሰጠውም፤ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ ቀውስ ቢሰፍን ግድ አይሰጠውም። ለሬት ግድ የሚሰጠው አንድ ነገር ብቻ ነው—ገንዘብ፣ እጅግ ብዙ ገንዘብ። ገንዘብ የሚያስገኝለት ከሆነ ለመስዋዕትነት የማያቀርበው ነገር የለም። አለማችን ወደ ሲኦል የምትንደረደረው በነዚህ አይነት ሰዎች ምክንያት ነው።

¤¤¤

ነገም ሌላ ቀን ነው ውስጥ በጣም የምወዳት ገጸባህሪይ ሜላኒ ሃሚልተን ነች። ልቧ ትልቅ ነው— ያለ ምንም ተቀጥላ ምክንያት ሁሉንም እኩል ትወዳለች። አምስት ደቂቃ አብሯት ያሳለፈ ሁሉ ይወዳታል። ነፍሷ ምትሃታዊ ባህሪ አለው። ሰዎች ለራሳቸው እንኳን የማይታያቸውን ጥሩነት በማየት ዘወትር ታስደንቀኛለች።

ሰዎች ላይ አትፈርድም። ሁሉንም እንዳሉ ትቀበላቸዋለች ጨካኝና መጥፎ እንኳን ቢሆኑ። ልቧ ግዙፍ ስለሆነ ለሁሉም የሚበቃ ቦታ አላት።

ደቃቃ ብትሆንም ደፋር ናት—ፍርሃት የሚባል ነገር አልፈጠረባትም። ትልቅ ነፍሷ ትንሹ ሰውነቷን ሸፍኖታል። በአስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ሆና እንኳን አትፈራም። እንደዚያ አምርራ የምትጠላት ስካርሌት እንኳን በሃቀኛነቷ ታከብራታለች። በአረብኛ እንዲህ የሚል አባባል አለ፦

"ለልበ ንጹህ፣ ሁሉም ንጹህ ነው"
.
እኔ ደግሞ በልብወለድም ይሁን በእውነታ ከሜላኒ የበለጠ ንጹህ አልገጠመኝም።

¤¤¤

እስካርሌት ከአሽሌይ ድብን ያለ ፍቅር ይዟታል። ከሱ ጋር ለመሆን የማትፈነቅለው ድንጋይ፣ የማታደርገው ነገር የለም። እሱ ግን እስካርሌትን ትቶ የምትመስለውን፣ የሚመስላትን ሜላኒን አገባ። ይኼኔ እስካርሌት አረረች ፤ ቆሽቷ ደበነ።

እስካርሌት ለሶስት ግዜ ያህል አግብታለች—ግን አንዱም ለፍቅር አልነበረም። ሌላ ድብቅ አላማ ነበራት—ቁሳዊም ሆነ ሌላ።

በመጨረሻ ሜላኒ በወሊድ ሞተች። አሁን ህይወቷን ሙሉ ስታሳድደው የኖረችው አሽሌይ ነጻ ሆነ። ነገር ግን ለሱ የነበራት ስሜት ሁሉ ተኖ ማለቁ ገረማት።

አሁን የሚወዳትን ሬት መውደድ ጀመረች። ነገር ግን ረፍዶ ነበር። እሷ ለአሽሌይ የነበራት ስሜት እንደሞተ ሁሉ፤ ሬት ለሷ የነበረው ስሜት ሞቷል። የምትወደውን አሽሌይን ስታሳድድ የሚወዳትን ሬትን አጣች። እስካርሌት ግራ የሚያጋባ የህይወት እንቆቅልሽ ሲገጥማት ዘወትር እንደዚህ ትላለች፦

"ይሄን ዛሬ አላስበውም። ነገም ሌላ ቀን ነው!"

¤¤¤

በማያልቅ የእርስበርስ ጦርነት ውስጥ ለምንኖረው እኛ ይሄ መጽሐፍ ትልቅ መልእክት አለው። ከታሪክ የምንማረው ከታሪክ አለመማራችንን ነው ይባላል። እንኳን ከአሜሪካ የእርስ በእርስ ጦርነት፣ ከራሳችንም ታሪክ አልተማርንም። በናፍቆት የሚጠበቅ የኦሎምፒክ ውድድር ይመሰል በየ10 አመቱ ጦርነት እንገጥማለን።

Tewodros Shewangizaw
1.3K views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 20:16:51
1.1K views17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 19:41:36 ይህን ያውቃሉ "የጠፉ መጻሕፍት አውደ ርዕይ" ነገ የመጨረሻ መጨረሽታ መሆኑን? በርካታ ከህትመት ርቀው፣ ከገበያ ጠፍተው የቆዩ መጻሕፍቶች ብርሐናዊ ሠልፍ ሲያካሂዱ ዛሬ (ቅዳሜ) ውለዋል። ካስተዋልኳቸው ከተወሰኑ መጻሕፍት በስተቀር አሁን ባለው የሕህትመት ግሽበትና የወረቀት መናር ንፅፅር የመጻሕፍቶቹ ዋጋ ያልተጋነኑ ተቀማሽ (ምክንያታዊ) ናቸው። Mexico Book Corner ፀጉሩን ጎንጉኖ፣ ሲሊፐሩን አጥልቆ ለፍፃሜው፣ ለማክተሚያው ዝግጅት ነገ (እሁድ) ይጠብቃችኋል። ሰው ወገቡን ታጥቆ ጠብ፣ እርግፍ ብሎ የደገሰውን ሲታደሙለት፣ ሲቀምሱለት ደስ ይለዋልና ነገ በእጅብ ከመጻሕፍት ቡፌው ተቃመሱ። አድራሻ መስቀል አደባባይ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ባለው የከተማ ማዕከል ውስጥ ነው።

@Bookshelf13 @Bookshelf13
@Bookshelf13 @Bookshelf13
1.2K views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 17:44:35 ለአመክንዮአዊ-አእምሮ ይግባኝ ማለት በማይቻልበት ሁኔታ ደግሞ የቡድን መበታተን (group balkanization) እና ግጭት ግዴታ የሚያጋጥሙ ውጤቶች ናቸው።

እንግዲህ <<እውንነትን (reality) እና አመክንዮአዊ-አእምሮን (reason) ወደ ጎን ገሸሽ ካደረግናቸው በኋላ ምን ይዘን ነው የምንጓዘው?>> ለሚለው ጥያቄአችን ቁጣ (rage)፣ የስልጣን ጥማት (power lust)፣ ፀፀት (guilt)፣ እና ፍርሐት (fear) የሚባሉ የድህረ-ዘመናዊው ዓለምን በማዕከላዊነት የሚያቁሙ የስሜት ዓምዶችን ይዘን ነው የምንጓዘው የሚል መልስ ነው የምናገኘው። ለምሳሌ አሁን ባለንበት የድህረ-ዘመናዊነት ባህል ተፈጥሮአዊ ከባቢያችንን በቅጡ አውቀን እና ተረድተን ልንወስደው የሚገባን እርምጃም ሆነ ጥንቃቄ እንድንረዳ ሳይሆን "ዓለማችን ልትጠፋ ነው" በሚል ፍርሐት ወይም "ተፈጥሮን እየጎዳናት ነው" በሚል ፀፀት ውስጥ እንድንገባ ነው ዋና ትኩረት የሚሰጠው።

በሌላ በኩል ድህረ-ዘመናዊነት በተንሰራፋበት ቦታ ሁሉ መጥፎ የሆነ የፖለቲካዊ ይሉኝታ (political correctness) ባህል እየተመለከትን ያለነው ለዚህ ነው። ምክንያቱም:-

- አመክንዮአዊ-አእምሮን አያስፈልግም ብለን አሽቀንጥረን ከጣልን በኋላ እኛ ራሳችንም ሆነ ሌሎች አመክንዮአዊ ባህሪ እንዲያሳዩ ልንጠብቅ አንችልም።

- ለስሜቶቻችን ቀዳሚ ስፍራ ከሰጠን በኋላ እንቅስቃሴያችን እና ለሁኔታዎች የምንሰጠው ግብረ-መልስ ሁሉ እንጭጭ እና በጊዜያዊ ነገር ላይ የታጠረ ነው የሚሆነው።

- ራሳችንን እንደ ግለሰቦች የመቁጠር ስሜቱ ከጠፋብን በኋላ ማንነታችንን ከየቡድናችን ወደ መፈለግ ነው የምንገባው። ከተለያዩ ቡድኖች ጋርም የጋራ የሚባል ነገር ስለማይኖረን ሌሎች ቡድኖችን እንደ ተገዳዳሪ ጠላት እንመለከታቸዋለን።

- ምክኑያዊ እና ገለልተኛ የሆነ መለኪያ ሚዛንን (standard) አሽቀንጥረን ከጣልን በኋላ የጉልበት ፉክክር መሬት ላይ መትተግበር ያለበት አማራጭ አድርገን እንቀበላለን። ቅራኔን በሰላማዊ መንገድ መፍታትን አሽቀንጥረን ከጣልን በኋላ ደግሞ እጅግ ምህረት የለሹ አካል ብቻ ህልውናውን እንደሚያስጠብቅ በቃላት ልንገልፀው ባንችል እንኳ ልቦናችን የሚነግረን ሐቅ ነው።

ድህረ-ዘመናዊነት በተንሰራፋበት ቦታ ሁሉ እንደ ፍልስፍና እና እንደ ንቅናቄ ጠንካራ የሆነ ተጠራጣሪነት እና ግለ-ስሜታዊነት ዋና መገለጫዎች ሆነው የሚወጡ ሲሆን፤ ከዚህ በመነጨ ደግሞ ሞራሊቲን በሚመለከት ስነ-ምግባራዊ አንፃራዊነት (ethical relativism) ጎልቶ ይወጣል። በማህበረ ፖለቲካዊ ፍልስፍና ደግሞ ጋርዮሻዊ ስብስብን (collectivism) በዜሮ ድምር ላይ ከተመሰረተ የእርስ በርስ ግንኙነት ጎልቶ ይወጣል። ይህ ሲባል በጋርዮሻዊ እይታው ማንነቶቻችንን ከዘራችን ወይም ከፆታችን ወይም ከመደባችን የሚገነቡ ናቸው ማለት ነው—ማለትም እንደ የአንድ ጋርዮሻዊ ቡድን አካል ሆነን ብቻ ነው ህልውና የሚኖረን እንጂ እንደ ግለሰብ ከቡድናችን ከተነጠልን ከባህር እንደወጣ ዓሣ ነን የሚል እይታ የበላይነት ያገኛል ። የዜሮ ድምር እይታው የሚመነጨው ደግሞ እነዚህ ቡድኖች እርስ በርሳቸው በሞት ሽረት ግጭት ላይ ያሉ ናቸው ብሎ ስለሚቀበል ነው። ስለዚህ እንደ የድህረ-ዘመናዊነት ምልከታ ከሆነ ማህበረሰብ ምንጊዜም ቢሆን በቡድኖች መሐል በሚኖር ቅራኔ ዙርያ የተዋቀረ ነው—የጥቁሮች እና የነጮች፣ የወንዶች እና የሴቶች፣ የሀብታሞች እና የድሆች፣ አውሮፓ ማዕከሉ ያደረገ (Eurocentric) እና አፍሪካ ማዕከሉ ያደረገ (Afrocentric)...ወዘተ።

ከዚህ የተነሳ ነው እንግዲህ ድህረ-ዘመናዊነት በተንሰራፋበት ቦታ በተለይም በአሜሪካ እና በአውሮፓ <<ባዮሎጂካል ፆታዬን ማንም አይወስንልኝም፣ ወንድነት እና ሴትነት ምርጫ ነው፣ እንዲያውም ባዮሎጂካል የሚባል ፆታ ሁሉ የለም፤ ከሁለቱም ውጪ ሁሉ ልሆን እችላለሁ >> በሚል ቅጥአንባሩ በጠፋበት የፆታ ዘውግ (gender) እና ሴታዊትነት (feminism) ንቅናቄዎች ዘንድ ፈቃድ ሳያገኙ አንተ/አንቺ እያሉ መጥራት ሁሉ በህግ በወንጀል ባያስቀጣም ከማህበራዊ መስተጋብር ግን የሚያግልል ሲሆን እየተመለከትን ያለነው።

ከዚህ የተነሳ ነው እንግዲህ ድህረ-ዘመናዊነት በተንሰራፋበት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥም ካሪክለሞች ሳይንሳዊ መንገድን ተከትለው ሳይሆን ቡድናዊ ተዋፅኦ ለማመጣጠን በሚል የጥቁሮች፣ የፈሚንስቶች፣ የአውሮፓውያን (Eurocentric)፣ የአፍሪካውያን (Afrocentric)፣ ...ወዘተ የሚባሉ የጥናት መስኮች ሲከፈቱ የምናስተውለው። (Paul Hollander, Discontents: Postmodern & Postcommunist)

ድህረ-ዘመናዊናት ከብሔርተኝነት እና ከማርክሲስታዊ ሶሻሊዝም አኳያስ ምንድን ነው ያበረከተው የሚለውን ራሱን አስችዬ በሌላ ርእስ እመለስበታለሁ። አሁን እንደማጠቃለያ
በአንድ ወቅት በፍልስፍና ት\ቤታችን የክረምቱ ኮርስ ላይ ድህረ-ዘመናዊነት በፍልስፍና ያስከተለው ዕዳ ብዬ በገለፅኩት ፅሑፌን እቋጨዋለሁ:-

<<እንደነ Stephen Hawking ዓይነት ሳይንቲስቶች በፍልስፍና ተስፋ ቆርጠው "ፍልስፍና ሙቷል" ብለው የፍልስፍና እና የፈላስፎች ሚና መሆን የነበረበትን በድፍረት ቀምተው <> እንዲሉ ያደረገ፤ በግለሰባዊነት መርህ ዙሪያ ሲቀነቀን የነበረውን የዘመናዊነት (modernity) አንዱ ምሰሶ ብዝሐነትን (pluralism) አጥፍቶ የዘረኝነት አምድ በሆነው ጋርዮሻዊው multiculturalism ሊተካ የሚተጋ፤ እውነተኛና ጥልቅ ፍልስፍናዊ ተዋስኦዎችን አጥፍቶ በ "ድህረ-እውነት ዘመን ነው ያለነው" ሰበብ ሁሉም የየራሱን ጋርዮሻዊ ዘውግ ይዞ የወረደ (mediocre) አስተሳሰብ ይዞም ቢሆን በኩራት እንዲኮፈስ ያስቻለ፤ በአጠቃላይ በምእራብ ፍልስፍና ታሪክ የጨለማው ዘመንን (dark age) በሚያስንቅ መልኩ ፍልስፍናን የገደለ ንቅናቄ ነው።>>

ለእናንተስ የድህረ-ዘመናዊነት ንቅናቄ ዕዳ ነው ወይስ ቡራኬ? እንወያይበት እንከራከርበት።

ተፈፀመ።

ማስታወሻ:
* ዲኮንስትራክሽን (deconstruction) ደሪዳ ያመጣው የትችት ህልዮት (theory of criticism) ሲሆን፤ በጥቅሉ አንድን ህልዮት ወይም ተዋስኦ (discourse) ወደተለያዩ ክፍሎች በመስነጣጠቅ በውስጡ ያሉትን ድብቅ ቅራኔዎችን ለመግለጥ እና የህልዮቱ ባለቤቶች ወይም አቀንቃኞች በተዋስኦዎቻቸው ውስጥ በግላጭ ከስተላለፏቸው ጭብጦች በስተጀርባ ያሉትን "ድብቅ ዓላማዎች" ፈልቅቆ ለማውጣት የሚያስችል ዘዴ ነው ማለት ይቻላል።

Yonas Tadesse Berhe
1.4K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 17:44:35 ድህረ-ዘመናዊነት (postmodernism): ማህበረሰባዊ ዕዳ ወይስ ቡራኬ?

(ዮናስ ታደሰ)

ክፍል ስድስት-ለ (የመጨረሻው ክፍል)

3.2 የድህረ-ዘመናዊነት ንቅናናቄ ፍሬዎች

ለድህረ-ዘመናዊነት መነሳት ዋና መግፍኤ ምክንያት የሆነውን ፍልስፍናዊ ታሪካዊ ዳራ በስፋት ተመልክተናል። አሁን ደግሞ "ከፍሬዎቻቸው ታውቋቸዋላችሁ" እንዲል መፅሐፍ፤ የድህረ-ዘመናዊነት ንቅናቄ ፍሬዎችን በማየት ዕዳ ወይስ ቡራኬ የሚል ዳኝነት እንሰጣለን።

ምንም እንኳ በአብዛኛው ሊትርቸር ድህረ-ዘመናዊነት ለዘመናዊነት የተሰጠ ግብረ-መልስ ሆኖ የተነሳ ንቅናቄ ተደርጎ የሚሳል ቢሆንም ቅሉ፤ በዋናነት በክፍል አምስት እና በክፍል ስድስት እንደተመለከትነው በመሐል ፀረ-አብርሆትን እንደ መሸጋገሪያ ተጠቅሞ የተነሳ ንቅናቄ መሆኑን ግልፅ ነው። ለዚህም ነው <<ድህረ-ዘመናዊነት በካንት ስነ-እውቀት የተጀመረውን የፀረ-አብርሆት ንቅናቄ የመጨረሻው ውጤት ነው>> የሚለው የStephen Hicks መደምደሚያ ትክክለኛ ድምዳሜ የሚሆነው። ከሂክስ መደምደምያዎች እያጣቀስን እንቀጥላለን።

ከ17ኛው ክዘ አጋማሽ በኋላ ዘመናዊው ዓለም በአመክንዮአዊ-አእምሮ አጠቃላይ ሐይል እና አመክንዮአዊ-አእምሮ ሳይንሳዊ እውቀት ለማግኘት በአለው እምቅ-አቅም (potential) ላይ የነበረው ብሩህ ተስፋ እጅግ ብርቱ ነው የነበረው። በተለይ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ አንፃር ይህ ብሩህ ተስፋ እስከ አሁን ድረስ ጎልቶ የሚታይ ሲሆን፤ ከአመክንዮአዊ-አእምሮ አንፃር ግን ደብዛው ጨርሶ አልጠፋም ነው ልንል የምንችለው። ከ18ኛው ክዘ አጋማሽ ጀምሮ ከተጠራጣሪ ፈላስፎች እና ከአንፃራውያን ፈላስፎች የሚሰነዘረውን የስነ-እውቀት ተግዳሮትን ግን ዘመናውያን ፈላስፎቹ የሚቋቋሙት አልነበረም። ከስነ-እውቀት አኳያ ቁልፍ ሚና የተጫወቱትን በዋናነት ህዩምን እና ካንትን አነሳን እንጂ ሩሶም (Rousseau) በፀረ-እብርሆት እንቅስቃሴው ላይ የተጫወተው ሚና ቀላል አይደለም።

ይሄ የፀረ-አብርሆት እንቅስቃሴ ሄዶ ሄዶ በ20ኛው ክዘ አጋማሽ ላይ ሲደርስ በተለይ በአከዳሚክሱ አለም ተጨባጫዊነትን የሚከላከል ፈላስፋ የጠፋበት ደረጃ ነው የደረሰው። በዚህም ቁልፍ የሆኑ የድህረ-ዘመናዊነት የመሰረተ-ሐሳብ ግብአቶች በ20ኛው ክዘ የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ በነበሩት ፈላስፎች ተሰርተው ተጠናቅቀዋል። በዚህ ወቅት የነበሩት የአመክንዮአዊ-አእምሮ እና የሳይንስ ደጋፊዎች ደግሞ ድህረ-ዘመናውያኑ ለሚጠቀሟቸው ጥርጣርያዊ (skeptical) እና አንፃራዊ (relativistic) መከራከሪያዎች ይሄ ነው የሚባል ምላሽ መስጠት ሳይችሉ ቀርተው መንፈሳቸው ተዳክሞ አቅጣጫ-አልባነት ስሜት ውስጥ የገቡበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው። (የአይን ራንድ ኦብጀክቲቪዝም ፍልስፍና ከአከደሚክሱ አለም ውጪ ሆኖ ገና እያቆጠቆጠ የነበረ ስለሆነ የፀረ-አብርሆቱን እንቅስቃሴ ሲመክት የነበረው በአደባባይ እንጂ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ አልነበረም።)

ከዚህ የተነሳ አብዛኛው የ20ኛው ክዘ ፍልስፍና እዚያም እዚህም በትንሽ በትንሹ የሚፈልቅ በስርዓት ያልተቀነባበረ ነው የነበረው። ዓበይት ከሚባሉት የፍልስፍና አካሄዶች መጥራት የሚቻለው በዋናነት logical positivism እና continental philosophy ናቸው። የድህረ-ዘመናዊናት ፍልስፍናም እንግዲህ በዋናነት ከእነዚህ ሁለት የፍልስፍና አካሄዶች ስነ-እውቀታዊ (epistemological) አንድምታዎቻቸውን በማስተፃመር ነው ሊያቆጠቁጥ የቻለው ። በዚህ ወቅትም ነው እንግዲህ ዲበ-አካላዊ ፀረ-እውንነትን (metaphysical antirealism)፣ ስነ-እውቀታዊ ግለ-ስሜተኝነትን (epistemological subjectivity)፣ የሁሉም የእሴት ጉዳዮች ስረ-መሰረት ስሜት እንደሆነ አድርጎ ማስቀመጥን ፣ ከዚህ በመነጨም የእውቀት እና የእሴት አንፃራዊነትን፣ እና ሳይንሳዊ መንገድን ዋጋ የማሳጣት ወይም ዋጋ የሌለው አድርጎ የመውሰድ እሳቤም ሲያቆጠቁጥ የምናገኘው።

ምንም እንኳ ድህረ-ዘመናውያን ራሳቸውን ፀረ-ሜታፊዚክስ እና ፀረ-ኤፒስተሞሎጂ አድርገው ቢገልፁም ፅሑፎቻቸውን ስንመለከት ግን እንድያውም በነዚህ ጭብጦች ላይ በልዩ ሁኔታ የሚያተኩሩ ሆነው ነው የምናገኛቸው። ድህረ-ዘመናውያኑ በመስራች አባትነት የሚጠቅሱት ሃይደገር (Heidegger) ለስሜት (emotion) ቦታ ለመተው ሲል አመክንዮአዊ-አእምሮን ያጠቃል፤ ፉኮ (Foucault) እውቀትን ወደ የማህበረሰባዊ ስልጣን (power) መገለጫነት ያወርደዋል፤ ደሪዳ (Derrida) ቋንቋን ዲኮንስትራክት (deconstruct) [* ከስር ያለውን ማስታወሻ ይመልከቱ] አድርጎ ወደ የስነ-ውበታዊ ጨዋታ መሳሪያነት ይቀይረዋል፤ ሮርቲ (Rorty) ደግሞ እውናዊው (realist) እና ተጨባጫዊው (objectivist) የፍልስፍና አካሄድ ለይቶ ውድቀቶቻቸውን የሚተነትነው በዋናነት ዲበ-አካላዊና ስነ-እውቀታዊ በሆነ ቋንቋ ነው።

ይሄን የድህረ-ዘመናዊነት ፀረ-እውንነት የሆነ ሜታፊዚክስ እና ፀረ-አመክንዮአዊ-አእምሮ የሆነ ኤፒስተሞሎጂ ተከትለው ነው እንግዲህ በቀጥታ በሚባል ደረጃ የድህረ-ዘመናዊነት ማህበራዊ ውጤቶች/ፍሬዎች የሚከተሉት።

በመሰረታዊነት የሚነሳው ጥያቄ <<እውንነትን (reality) እና አመክንዮአዊ-አእምሮን (reason) ወደ ጎን ገሸሽ ካደረግናቸው በኋላ ምን ይዘን ነው የምንጓዘው?>> የሚል ጥያቄ ነው የሚሆነው። ድህረ-ዘመናዊነት በደንብ እየተንሰራፋ በመጣበት ወቅት ሁለት አማራጮች ነው ያሉት። ፊታችንን የወግ-አጥባቂዎች (conservatives) ምርጫ ወደ ሆነው ትውፊትታዊ እምነት እና ባህል ማዞር እና ትውፊታዊውን አካሄድ መከተል፤ ወይም ደግሞ ፊታችንን የድህረ-ዘመናውያኑ ምርጫ ወደ ሆነው አንኳር ስሜቶቻችንን በማዳመጥ ስሜቶቻችን የሚነግሩንን ወደ መከተል ማዞር። አሸናፊ ሆኖ ጎልቶ የወጣው ሁለተኛው አማራጭ ነው።

<<ለመሆኑ አንኳር የሚባሉ ስሜቶቻችንስ ምንድን ናቸው?>> ብለን ስንጠይቅ ደግሞ በ19ኛው ክዘ ስለ ሰው ተፈጥሮአዊ ምንነት በበላይነት ሲቀነቀኑ ከነበሩት ህልዮቶች እና የነሱ ተቀጥላዎች ሆነው ወደ 20ኛው ክዘ ከተሻገሩት ጋር ነው የምንጋፈጠው። ከኪርከጋርድ እና ከሃይደገር የስሜቶቻችን አንኳር ማለት ጥልቅ የሆነ የፍርሐት እና የፀፀት ስሜት መሆኑን እንማራለን። ከማርክስ የስሜቶቻችን አንኳር ማለት የመነጠል (alienation)፣ ሰለባ የመሆን (victimization)፣ እና የቁጣ ስሜት (rage) መሆኑን እንማራለን። ከፍሮይድ የስሜቶቻችን አንኳር ማለት ስውር እና ዓመፀኛ የሆኑ ፆታዊ ግፊቶቻችን (dark and aggressive sexual urge) እንደሆኑ ይገለጡልናል።

እነዚህ አንኳር ስሜቶቻችን <<በባዮሎጂያችን ነው የሚወሰኑት ወይስ በማህበረሰብ>> በሚል ጥያቄ ላይ በድህረ-ዘመናውያን መካከል ልዩነት አለ። በእርግጥ ግን ጠንካራ ድጋፍ ያለው "ማህበረሰባዊ" የሚለው ነው። ግለሰቦች የስሜቶቻቸው የበላይ ተቆጣጣሪ አይደሉም በሚል ሐሳብ ላይ ግን ሁለቱም ወገን ይስማማሉ። ማለትም ማንነታቸው አባል በሆኑበት ቡድን (ተዋልዶአዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፆታዊ...) የሚወሰን ነው ማለት ነው። እነዚህ ማንነትን የሚቀርፁት ኢኮኖሚያዊ፣ ፆታዊ፣ ተዋልዶአዊ ተሞክሮዎች ወይም እድገቶች ደግሞ ከቡድን ቡድን የሚለያዩ ስለሆኑ፤ የተለያዩ ቡድኖች የጋራ የሆነ ማዕቀፍ የላቸውም ወይም አይኖራቸውም። የተለያዩ አመለካከቶቻቸውን እና ስሜቶቻቸውን የሚያስታርቁበት ተጨባጭ የሆነ መለኪያ ሚዛን (standard) በሌለበት እና
1.3K views14:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ