2023-04-30 20:21:31
ካርል ማርክስ የብዙ ታላላቅ ስራዎች ባለቤት ነው፡፡ ከስራዎቹ ሁሉ እጅግ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ግን “Das Kapital” ነው፡፡ ማርክስ ይህንን መጽሐፍ ያዘጋጀው በሶስት ቅጾች ቢሆንም እርሱ በህይወት እያለ ለኅትመት የበቃው የመጀመሪያው ቅጽ ብቻ ነው፡፡ ሁለቱ ቅጾች ከእርሱ እልፈት በኋላ የምንጊዜም ታማኝ ጓደኛው በነበረው ፍሬድሬክ ኤንግልስ ነው የታተሙት፡፡ ይህ መጽሐፍ በተለያዩ ቋንቋዎች የተተረጎመ ሲሆን በሀገራችንም የመጀመሪያዎቹ ሁለት ቅጾች በአማርኛ ተተርጉመዋል፡፡
የማርክስ ታላቅ ስራ የሆነው “ዳስ ካፒታል” በውስጠ ይዘቱ ምን ይመስላል? በዚህ ጽሑፍ አቅም ለመመለስ አይቻልም፡፡ ሆኖም ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ በዚህ ዙሪያ ከጻፈው ትንሽ ቀንጨብ ብናደርግ ስለመጽሐፉ በመጠኑ ሊያስረዳ ይችላል፡፡
“Marx's masterpiece, Das Kapital, the “Bible of the working class,” as it was officially described in a resolution of the International Working Men's Association, was published in 1867 in Berlin and received a second edition in 1873. Only the first volume was completed and published in Marx's lifetime. The second and third volumes, unfinished by Marx, were edited by Engels and published in 1885 and 1894. The economic categories he employed were those of the classical British economics of David Ricardo; but Marx used them in accordance with his dialectical method to argue that bourgeois society, like every social organism, must follow its inevitable path of development. Through the working of such immanent tendencies as the declining rate of profit, capitalism would die and be replaced by another, higher, society. The most memorable pages in Das Kapital are the descriptive passages, culled from Parliamentary Blue Books, on the misery of the English working class. Marx believed that this misery would increase, while at the same time the monopoly of capital would become a fetter upon production until finally “the knell of capitalist private property sounds. The expropriators are expropriated.”
ከማርክስ ስራዎች መካከል በዓለም ዙሪያ በስፋት የተሰራጨው ደግሞ “የኮሚኒስት ፓርቲ ማኒፌስቶ” የተሰኘው ጥራዝ ነው፡፡ ማርክስ ይህንን ስራ ያዘጋጀው ከኤንግልስ ጋራ በመተባበር ሲሆን በጊዜው በመቋቋም ሂደት ላይ የነበረ Communist League የተሰኘ ህቡእ ማህበር ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ነው የተጻፈው፡፡ “የሁሉም ሀገር ሰራተኞች ተባበሩ” የሚለው ዝነኛ የኮሚኒስቶች መፈክር የተወሰደው ከዚህ ታዋቂ ጥራዝ የመጨረሻ ዐረፍተ ነገር ነው፡፡
=== ሜይ ዴይ==
May 1 (ሚያዚያ 23) የሰራተኞች ቀን ሆኖ መከበር የጀመረው እ.ኤ.አ በ1889 ነው፡፡ ይህም ካርል ማርክስ ከሞተ ከስድስት ዓመታት በኋላ መሆኑ ነው (ማርክስ የኖረው ከ1818 እስከ 1883 ነው)፡፡ ይሁንና ለዕለቱ መከበር ዐቢይ መነሻ የሆነው ማርክስ ከታገላለቸው ግንባር ቀደም የሰራተኛው መደብ ጥያቄዎች አንዱ የሆነው የስምንት ሰዓት የስራ ጊዜ ነው፡፡ ይህ ዕለት ከሌሎች የዓመቱ ቀናት ተመራጭ የሆነው ደግሞ በሰራተኛው መደብ ትግል ውስጥ የማይረሳ አጋጣሚ የተፈጠረበት በመሆኑ ነው፡፡ ታሪኩ እንደሚከተለው ነው፡፡
የ19ኛው ክፍለ ዘመን ሶሻሊስቶች ሲያነሱት የነበረው የስምንት ሰዓት የስራ ጊዜ በበርካታ የአውሮጳ ሀገራትና በአሜሪካ ግዛቶች ተከታታይ የስራ ማቆም አድማዎች እንዲጠሩ ምክንያት ሆኖ ነበር፡፡ የየሀገራቱ መንግሥታት ጥያቄውን ለረጅም ጊዜ ሲገፉት ቆይተዋል፡፡ በሜይ 1 ቀን 1867 ግን የአሜሪካዋ አሊኖይ ግዛት መንግሥት ለጥያቄው ህጋዊ እውቅና ሰጠ፡፡ ሆኖም ይህ መብት ለሃያ ዓመታት ያህል ተፈጻሚ ሊሆን አልቻለም፡፡ የዚህም ምክንያት የዘመኑ የኢንዱስትሪ ከበርቴዎች መብቱ ተፈጻሚ እንዲሆን የሚጠይቁ ሰራተኞችን ከስራ የሚያባርሩ መሆናቸው ነው፡፡ በመሆኑም ሰራተኛው የስራ ዋስትና ላለማጣት ሲል ለረጅም የስራ ሰዓታት በፋብሪካዎች መስራቱን ቀጥሏል፡፡
በሜይ ወር 1886 ግን ታሪካዊ ድርጊት ተፈጸመ፡፡ በዚህ ዕለት በቺካጎ ከተማ የሚገኘው የማኮርሚክ የእርሻ ማሽነሪዎች ፋብሪካ ሰራተኞች የስራ ጊዜን በስምንት ሰዓት የሚገድበው መብት ተፈጻሚ እንዲሆን ለመጠየቅ ከሜይ 1-4/1886 የሚቆይ የስራ ማቆም አድማ ጠሩ፡፡ ብዙሃኑ ሰራተኞችም የአድማው ተሳታፊ ሆኑ፡፡ በሶስተኛው ቀን (ሜይ 3/1886 ) ግን ከሰራተኞቹ መካከል አድማውን የሚቃወም ቡድን ተፈጠረ፡፡ የቺካጎ ፖሊስ የአድማውን ተቃዋሚዎች ከብዙሃኑ ሰራተኞች ለመከላከል በሚል ባደረገው ጣልቃ ገብነት የስድስት ሰራተኞች ህይወት ጠፋ፡፡ ይህም ብዙሃኑን ሰራተኞችና የሰራተኛው መደብ ደጋፊዎችን አበሳጫቸው፡፡
ሰራተኞችና ግራ ዘመም ደጋፊዎቻቸው በተከታዩ ቀን (May 4/1886) የፖሊስን የጭካኔ እርምጃ የሚቃወም ሰልፍ ጠሩ፡፡ ሰልፉም በከተማዋ እምብርት ላይ በሚገኘው የሄይማርኬት አደባባይ (Haymarket Square) መካሄድ ጀመረ፡፡ በርካታ የሰራተኛ መደብ መሪዎች ሲደርስባቸው የነበረውን የጉልበት ብዝበዛ እየተነተኑ ተናገሩ፡፡ በፖሊስ የተወሰደውንም ጥቃት አወገዙ፡፡ ሰራተኞችም የመሪዎቻቸውን ቁጭት በጭብጨባና በመፈክሮች እያጀቡ አስተጋቡት፡፡ ሰልፉ ሰላማዊ ሆኖ መካሄዱን ቀጠለ፡፡ ከሰዓት በኋላ ግን ያልታወቀ ሰው በሰልፈኞቹ ዙሪያ በነበሩት ፖሊሶች ላይ ቦምብ በመወርወር ሰባት ፖሊሶችን ገደለ፡፡
በዚህ እርምጃ የከበርቴው ወገንና ደጋፊዎቻቸው በጣም ተቆጡ፡፡ የአሜሪካ ጋዜጦች ወሬውን እየተቀባበሉ የሰራተኛ መብት ታጋዮችን አብጠለጠሏቸው፡፡ “ከአውሮጳ (በተለይም ከጀርመን) የመጡ ሶሻሊስቶች ሀገራችንን ሊበጠብጧት ነው” እያሉ ነገሩን አሟሟቁት፡፡ ቀኝ ዘመም ፖለቲከኞች “የአሜሪካን አንድነት ለመናድ በሚፈልጉት ሶሻሊስቶች ላይ አፋጣኝ እርምጃ ይወሰድ” እያሉ ወተወቱ፡፡ ቦምቡን የወረወረ አካል ማንነት እስከ አሁን ድረስ ተለይቶ አልታወቀም፡፡ የታሪክ ምሁራን ግን የቺካጎ ከተማ ከበርቴዎች በላኳቸው ቅጥረኞች እንደተወረወረ ይጠረጥራሉ፡፡
1.0K views17:21