Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.28K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-29 22:26:43 ሠይጣኑን እንዴት ጠብቀኸው ነበር?

(Reframe your expectations! መነፅርህን አሁኑኑ አስተካክል!)

በናዚ ዘመን የሒትለር የቅርብ ሰዎች ከነበሩት ከፍተኛ ባለሥልጣናት መሐል ለሂትለር ጦርነቶች የሚያስፈልጉ የሎጂስቲክ አቅርቦቶችን በማስተባበርና ሒትለርን የሚያስደምሙትን ግዙፍ የምህንድስና ግንባታዎች በመንደፍ ያገለገው የሒትለር መሃንዲስ፣ አልበርት ስፒር፣ የናዚ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሞት ሲቀጡ፣ በህይወት እንዲተርፉ ከተፈቀደላቸው እጅግ ጥቂት ዕድለኞች አንዱ ነው።

(በህይወት ተርፎም ከእስር ተለቆ በሠላም በነፃነት ኖሯል። ይህን ተስተካካይ የሌለውንና እስከዛሬም በዋና ምንጭነት ተደጋግሞ ሲጠቀስ የሚኖር የቅርብ ምስክርነቱን የያዘ.. ስለናዚ መንግሥትና ስለመሪው ሒትለርና ሸሪኮቹ ሰብዕና የሚተነትን እጅግ ተደናቂና አስደማሚ መፅሐፍም ሊያሳትም በቅቷል ስፒር።)

በዚህ መፅሐፍ አልበርት ስፒር በቅርብ ስለሚያውቀው ሂትለር ሲናገር ደጋግሞ የሚገረመው በሒትለር የተግባቢነት፣ የሰው አክባሪነትና የቅለት ባህርያት ነው።

ሂትለር "ከተራው ሕዝብ" ጋር ሲሆን እጅግ ቅለት የሚሰማውና ነፃ ሆኖ የሚገኝ ትሁትና ሰው-አክባሪ ሰው እንደሆነ ይናገራል አልበርት ስፒር።

የሒትለርን ነፍስ እጅግ ዘና ብላና ነፃነትን ተቀዳጅታ የምታያት ቀሪው ዓለም በሚያውቀው የሆነ የንግግር መድረክ ላይ ሲወጣ፣ አሊያም በሆነ ቦታ በተዘጋጀለት የክብር ሥፍራ ላይ አልነበረም።

ሒትለር ወደ መድረክ ከመውጣቱ በፊት በአካባቢው ከሚያገኛቸው ሠራተኞችና ባለሙያዎች ጋር እንደ ጓደኛ ሆኖ ማውራት በጣም የሚያስደስተው ሰው ነበር ይለናል ስፒር።

ለበታቾቹ ሠራተኞች ከፍ ያለ አክብሮት ነበረው ሒትለር። ምግብ ቤት ገብቶ ስለቀረበለት ምግብ፣ ወይ ስለ አስተናጋጁ፣ወይ ስለለበሱት ልብስ፣ ወይ ስለመጡበት ሀገር ጠይቆ፣ የሆነ ሰዎቹን የሚያደንቅበትና የሚግባባበት አስተያየቱን ሳይሰጥ አይወጣም ይለናል።

አንዴ የሆነ ምግብ ቤት ገብቶ አስተናጋጁን ሲያዋራው ከኦስትሪያ ነው የመጣሁት ይለዋል። እና ሒትለር እሱም ከኦስትሪያ እንደመጣ ለአስተናጋጁ አውርቶለት፣እንዴት ባንዴ የወንድማማችነት ስሜት በመካከላቸው እንደፈጠረ ያስታውሳል አልበርት ስፒር።

ሂትለር አንዴ፣ ለአንዲት ቀን፣ ከብዙ ዓመት በፊት፣ መንገድ ላይ፣ ወይ የሆነ መሥሪያቤት ውስጥ፣ ወይ በሆነ አውቶቡስ ላይ፣ ያገኘውን ሰው ከነታሪኩ፣ ከነስሙ፣ ከናወሩት ነገር አይረሳም ይለናል ስፒር በመደነቅ።

ሂትለር ከፍተኛ የሥልጣን እርከን ላይ ከወጣ በኋላ ራሱ በሆነ አጋጣሚ እነዚያን ቀድሞ ተራ ኑሮ እየገፋ ያገኛቸውን ሰዎች ሲያገኝ፣ በፍፁም ትህትና ራሱን አቅልሎ የድሮውን ትዝታ ልቅም አድርጎ እያስታወሰ ሲደሰቱ ማየት የሚያረካው ተግባር እንደሆነ ይመሠክራል ስፒር።

ሒትለር በቢሮው የሚሠሩ ሰዎችን ሳይረሳ ስለቤተሰባቸው ጉዳይ ይጠይቃል። ሳይረሳ ስለጓደኞቻቸውና ስለታመሙ ዘመዶቻቸው ሳይቀር ይጠይቃል። ወጣት ሠራተኞቹን "እስከማጣበስ" የደረሰ የወጣትነት፣ የጓደኝነትና የቅንነት ስሜት ለበታቾቹ እንደሚያሳይ ይናገራል።

ሌላ ቀርቶ በልጅነቱ ያከመውን የጥርስ ሃኪም የነበረ ትውልደ-እስራኤላዊ ዶክተሩን አስታውሶ፣ እስራኤሎቹን ማፈስና መግደል ከመጀመሩ ጥቂት ቀደም ብሎ ከጀርመን እንዲወጣ አድርጎታል። ሊያተርፈው።

(በእርግጥ ይህ የሒትለር ችሮታ ባንድ ሰው ብቻም የተወሰነ አይመስልም። የሀርቫርዱ ብራየን ሪግ በቅርብ ዓመታት አጥንቶ በፃፈው "የሒትለር ጂዊሽ ወታደሮች" መፅሐፍም ላይ ሒትለር ብዙ የእስራኤል ደም ያላቸው ባለኒሻን ወታደሮችን እንደሙሉ የጀርመን ዜጋ እንዲቆጠሩ የፃፋቸው መመሪያዎች ተመልክተዋል።)

(በእርግጥ ሒትለር አስከፊ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ በሚዋኝበት በመጨረሻው ራሱን ሊያጠፋ በወሰነበት ቅፅበቱ ላይ ራሱ፣ ሠራተኞቹን ከፀሐፊዎች እስከ ወጥቤት ሠራተኞቹ ድረስ እየዞረ የሞቀ ሠላምታ አቅርቦና መልካሙን ተመኝቶ እንደተሰናበታቸው በብዙ የህይወት ታሪክ ዝክሮቹ ተዘግቦለት ይገኛል።)

"... he acted in a friendly way to “the little guy”. To his secretaries, to their husbands. He’d play matchmaker for his staff. Inquire about the children of friends. Allow his old Jewish childhood dentist to leave the country unharmed before the Holocaust kicked off…."

ሒትለር በፈለገው ርዕሰጉዳይ ላይ ላቅ ያሉና የበሰሉ ውይይቶችን የማድረግና በርቱዕ አንደበት የማስረዳት ብቃት ቢኖረውም፣ ብዙ ጊዜ ከተራ ሰዎች ጋር ሲሆን የሚሰማው የመንፈስ ቅለት፣ ከተከበሩና በተለይ "የትልቅሰው ዘር" ተብለው ከሚቆጠሩ (በስማቸው ላይ "ቮን" የሚል የክብር መጠሪያ ከተደረበላቸው ሰዎች) ጋር ሲሆን ግን የመዝናናት መንፈሱ በቁጥብነትና በሲሪየስ ሙድ እንደሚቀየር የታዘበውን ፅፏል ስፒር።

የሚገርመው፣ እነዚያም አንቱታ የተቸራቸው ብዙዎቹ ሰዎች የቱንም ያህል ከሒትለር ጋር ለጥቅማቸው ወይም ላገራቸውም ጥቅም አብረው ቢሰለፉ፣ ነገር ግን በግል ቀርቦ ላዋያቸው በሚስጥር ሒትለርን የሚጠሩት "ያ ጭባ ወታደር" እያሉ ነው ሲል ይመሠክራል ስፒር።

ሒትለር የቱንም ያህል በሥልጣንና በኃይል ተምዘግዝጎ ቢወጣ፣ ለእነዚህ ሰዎች ሒትለር ማለት ከሚገባውና መገኘት ከነበረበት የህይወት ሥፍራው አጓጉል አጥር ዘልሎ ባልዋለበት ያለሥፍራውና ያለደረጃው የተገኘ፣ መደዴ ሰው፣ አሊያም ይሉኝታና የጨዋ መገራት ያልጎበኘው ተራ ዓይንያወጣ ወንበዴና ሽፍታ ሆኖ ነበር የሚታያቸው። ተጀምሮ እስኪጨረስ።

ሒትለር በበኩሉ ለምን ከእነዚህ ከበርቴዎች ጋር ሲሆን ከተራው ሕዝብ ጋር ሲሆን የሚሰማውን ዓይነት ቅለትና የሚታይበትን ትህትና እንደማይላበስ ስፒር ሲያስረዳ፣ ምናልባት ሒትለር በጅምሩ ለከበርቴዎቹ ከፍ ያለ ትህትናና አክብሮት ቢኖረውም ለእርሱ የናዚ ዓላማና ለሀገር ጉዳይ ግን የፈለገውንና የጠበቀውን የገንዘብም ሆነ ሌላ እገዛ ለማድረግ ፈቃደኝች ሆነው ስላላገኛቸው፣ ነገሩ ሲደጋገም፣ ለእነዚህ "ጩቆች" ትሁት መሆን አስፈላጊ አይደለም የሚል አቋም ላይ ደርሶ ሊሆን እንደሚችል ያስረዳል።

የሆነ ሆኖ አልበርት ስፒር እጅግ ተደንቆ እኛን አንባቢዎቹንም የሚያስደንቀን በሒትለር ውስጥ ተዳብለው ስለሚገኙት እጅግ የተራራቁ ሰብዕናዎች ሲናገር ነው።

በአንድ ሥፍራ ፉህረሩን (አዶልፍ ሒትለርን) ሲገልፀው ደስ በሚል ቋንቋ እንዲህ ይለዋል፦

"Hitler is a great and enduring paradox, an enigma — boundless evil in an often surprisingly polite package. A sea of anger and hatred, brewing underneath a surface that could be deceptively charming."

"ሒትለር ራሱን የቻለ አንድ ትልቅና ሳይፈታ ብዙ የሚዘልቅ ምሥጢር ነው። መጨረሻ ሊበጅለት የሚያዳግት ከፍ ያለ እርኩስ መንፈስ፣ እጅግ ትሁት በሆነ መጠቅለያ ውስጥ ተጣምሮ የሚገኝበት ፍጡር ነው። ባህርን የሚያስንቅ ንዴትና ጥላቻን ያቆረ ሰው፣ በሚያስገርም የማደንዘዝ ኃይል፣ እጅግ ማራኪና ውብ በሆነ ተጫዋችና ሩህሩህ ሰብዕና ውስጥ ተጠልሎ ይገኛል። የሒትለር ነገረሥራ ራሱን የቻለ እንቆቅልሽ ነው...።"
1.2K views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 22:26:18
1.0K views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 20:12:48 የጊዜን ሽምጠጣ ፡

የዘመንን ፍጥነት ፡ እኔ ምናውቅና?
ቅዳሜ ልጅነት ፡ እሁድ ሽምግልና።

Rediet Aseffa
1.2K views17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 20:10:47 አለመግባባቱ የተፈጠረው ትልቋን ልጃቸውን ከወለዱ በኋላ ነው ።

እናም አብረን መኖር አንችልም ብለው ለመለያየት ወሰኑ ። ታዋቂው የሆሊውድ አክተር ቫን ዲዝል ከሜክሲኳዊት ሚስቱ Paloma Jimenez ጋር አብረው ሲኖሩ ፡ ህጋዊ የጋብቻ ውል አልፈፀሙም ። ስለሆነም በሚለያዩበት ወቅት ሀብቱን እንዲያካፍላት የሚገደድበት ህግ የለም ።

አብረው በፍቅር በቆዩበት ወቅት ይኖሩበት የነበረው እጅግ ዘመናዊ ቪላ በግሉ የተመዘገበ ነው ። ሆኖም ከሚስቱ ጋር ባለመግባባት ሲለያዩ ቤቱን ጥላለት እንድትወጣ አልጠበቀም ።
ከዚህች ሴት ጋር ይዋደዱ ነበር ፡ ቆንጂዬ ሴት ልጅም ሰጥታዋለች ። በአንድ ወቅትም የቫን ዲዝል ሚስት ተብላ ሚዲያው አውቋታል ። ስለዚህ ከዚህ ቤት ብትለቅ ፡ ካላት የገቢ ምንጭ አንጻር ፡ ተከራይታ መኖር የምትችለው አነስተኛ ቤት ነው ።

ይህንን ያሰበው ቫን ዲዝል ፡ ይህማ ፈፅሞ አይሆንም አለ ። በአንድ ወቅት የኔ ሚስት የነበረች ሴት ፡ የልጄ እናትማ ፡ ከዘመናዊ ቪላ ወጥታ ዝቅ ብላ አትኖርም በማለት ፡ አብረው ይኖሩበት የነበረውን ውድ ቪላ ከልጃቸው ጋር እንድትኖርበት ጥሎላቸው ወጣ ።
...........
በዚህ ሁኔታ ከተለያዩ በኋላ ፡ የቤቱን ወጭ ፡ የሚያስፈልገውን ማንኛውንም ነገር ፡ ያላንዳች ጠያቂ የሚሸፍነው እሱ ነው ። እንዲሁም ይህን መሳይ ዜናዎች በሚገኑበት ሀገር ሆኖ ፡ ለአንድም ሚዲያ ከሚስቱ ጋር ስለመለያየታቸው አልተናገረም ።
እንዲህ እንዲህ እያለ ፡ ለሶስት አመታት ያህል ተለያይተው ቆዩ እና በአንድ እለት የስራው አንዱ አካል በሆነ የፎቶ ፕሮግራም ላይ እያለ ፡ ስልኩ ጮኸ ።
የቀድሞ ባለቤቱ አደጋ ደርሶባት ደም ስላስፈለገ ይህንን ሊነግሩት ከሆስፒታል የተደወለ ስልክ ነበር ። ቫን ይህንን እንደሰማ ፡ ፕሮግራሙን አቋርጦ ሲከንፍ ወደሆስፒታል ሄደ ።
ባለቤቱ በሆስፒታሉ ውስጥ ተኝታለች ። ራሷን አታውቅም ። እና በአስቸኳይ ደም ያስፈልጋታል ። ቫን ዲዝል ወዲያውኑ የሚያስፈልጋትን ደም ሰጥቶ እና የህክምና ወጭ ሸፍኖ የቀድሞ ባለቤቱን ማስታመም ያዘ ።
ሜክሲኳዊቷ ሞዴሊስት Paloma Jimenez ከህመሟ ብዙም ሳትቆይ ዳነች ።

ከደረሰባት አደጋ ሙሉ ለሙሉ ድና ወደቤቷ ከተመለሰች በኋላም. . ይህ ሰውኮ ለኔ መልካም ነው ለምን ተለየሁት ስትል አሰበች ።
በተመሳሳይ እሱም ከዚህች ሴት ጋር ፡ ከማያግባቡን ነገሮች ይልቅ ፡ በፍቅር ሊያኖሩን የሚችሉ ነገሮች ይበዛሉ ፡ ለምን ተለያየን ሲል ያስብ ነበር ።
እና ያለምንም ንግግር በሀሳብ ተግባብተው ፡ ርቆ ከሚኖርበት ቦታ ሻንጣውን ይዞ መጣ ። ትዳር እንዳዲስ ተጀመረ ። ሌሎች ተጨማሪ ሁለት ልጆች ተወለዱ ።
በተለያዩበት ወቅት ለእርሷ መልካም ሰው ነበር ። ስለዚህ በልባቸው ቂም አልነበረም ። አሁን ላይ. .. ያ . በአንድ ወቅት መልካምነት ያስተሳሰረው የነቫንዲዝል ትዳር ደስተኛ ቤተሰብ አፍርቶ ዛሬም ድረስ በፍቅር ቀጥሏል ።

WASIHUNE TESFAYE
1.3K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 20:10:41
1.3K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 23:23:59 ለፈገግታ…
የሆነ ቀልድ ትዝ አለኝ

የይርዳው እናት ለይርዳው ሚስት ፈልገው መጨረሻ ላይ ተለቅ ያለች መልከ ጥፉ የምትባል አይነት ሚስት ያገኙለትና ለቤተሰቦቿ ሽማግሌ ይልካሉ። እናም የልጅቷ እናት የሚያገባት ሰው አይነ ስውር መሆኑን ሲያውቁ "ልጄንማ አይነ ስውር አያገባትም..." ማለታቸውን የይርዳው እናት ሰሙና

"እሱማ የኔም ልጅ ቢያያት አያገባትም"

Abdu Abdela Baba
1.4K views20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 21:43:38 [የዓለም መጻሕፍት ቀንን አስመልክቶ] ቆየት ካሉ አስቂኝ ርዕሶች ካሏቸው አጫጭር ልቦለዶች ውስጥ

ZERRAF METSAHFET MEDEBER
1.5K viewsedited  18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 21:41:49
1.4K views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 21:39:44 ጊዜው ደርግ ስልጣን በጨበጠበት ዘመን ነው። ወታደራዊ መንግስት "ደርግ" ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህንን እና አያልነህ ሙላቱን እስር ቤት አስገባቸው።

እስር ቤቱ በጣም ጠባብ ነው። እስረኛው ደግሞ ብዙ። ከዚህ የተነሳ መፈናፈኛ ቦታ የለም። የሰው ላብ ፣ የክፍሉ ሽታ ፣ ሌላም ሌላም ነገር ተደማምሮ ቤቱ በቅማል እና ቁንጫ ተሞልቷል።

እና የዚህ እስር ቤት አለቃ ሻምበል አባቴነህ ይባላል። አንድ እለት እስረኞችን ሊያይ መጣ።

ከታሳሪዎቹ መሃል አንድ ሰው እጁን ለጥያቄ አወጣ። ያ ሰው አያልነህ ሙላት ነበር። የሚነበብ ነገር እንዲያመጣላቸው እንዲህ ብሎ ጠየቀ።

"እዚህ የምናነበው ጋዜጣም ሆነ መፅሀፍ የለም። ስለዚህ..." ብሎ ሳይጨርስ።

"ዝጋ! አንተ አይደለህም ምን እንደሚያስፈልግ የምትነግረን። ሲያስፈልግ ወታደራዊ መንግስት ያስተምርሃል።" ብሎ አሸማቀቀው። ይህቺን ገጠመኝ ያነበብኩት አንዳርጋቸው ፅጌ የፃፈው መፅሀፍ ላይ ነው።

ነገሩ Ironic ነው። አያልነህ እኮ ቀደም ብሎ በንጉሱ ዘመን ራሺያ ሄዶ ስነፅሁፍን እስከ ሁለተኛ ዲግሪ ድረስ ያጠና ነው።

እንደውም ስለ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ጣጠኛ ትያትር ፅፎ ከሀገር እንዳይወጣና ለሶስተኛ ዲግሪ የሰራውን የጥናት ወረቀት እንዳያቀርብ ተደረገ እንጂ ይሄኔ ዶ/ር አያልነህ እያልን ነበር የምንጠራው።

ከነበረበት ሶቭየት ህብረት ፀጋዬ ነው "ና ሀገርህ ላይ ስራ" ብሎ ገፋፍቶ ወደ ሀገሩ የመለሰው።

አያልነህ ያለው የስነፅሁፍ እውቀትም አስገራሚ ነው። ለዚህ ምስክሩ ደግሞ የፃፈው የስነፅሁፍ ቅኝት የሚለው መፅሀፉ ነው። በግሌ በጣም የምወደው መፅሀፍ ነው። ስነፅሁፍን እና የስነፅሁፍ ታሪክን ለማንበብ ለሚመርጥ ሰው ተወዳጅ መፅሀፍ ነው።

አያልነህ በዚህ መፅሀፉ የአለም ስነፅሁፍን ያስቃኘናል። የእንግሊዝ፣ የራሺያ፣ የፈረንሳይ፣ የህንድ ፣ የጀርመን፣ የአሜሪካ ወዘተ የስነፅሁፍ ታሪክ ቅኝትን ከየሀገራቱ ታዋቂ ደራሲዎች ስራ ጋር እያዛመደ ብዙ ብዙ ይለናል (...)

ALTAYEH KIDANE
1.3K viewsedited  18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 21:39:06
1.2K views18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ