Get Mystery Box with random crypto!

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የቴሌግራም ቻናል አርማ bookshelf13 — ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
የሰርጥ አድራሻ: @bookshelf13
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.28K
የሰርጥ መግለጫ

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-07-06 14:51:44
902 views11:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-06 14:43:14 #አልኬሚስቱ
---
በመካከለኛው ዘመን የተነሱ ብረትን አቅልጦ (አንጥሮ) በማጣራት ወደ ወርቅ ለመቀየር ለተጉ የግኝት ባለቤቶች የተሰጠ ስያሜ ነበር፤ አልኬሚስት። ከቅዠት የተወሰደው መገለጣቸው ከመወገዝ አላዳናቸውም ነበር፤ የሚረዳቸውም አልነበረም።

አልኬሚ ብረትን ወደ ወርቅ ከመቀየር የሚልቅ ሐሳብ አለው። አልኬሚ የልውጠት (transformation) ጥበብ ነው። የነበረውን ማንነት ወደ ላቀው ምንነቱ የማሻጋገር ጥበብ ነው። ሂደቱ የነገሮችን ምንነት በመረዳትና በከፍተኛ ደረጃ በማጣራት የምንነታቸውን የላቀ ልዕልና እንዲወርሱ የማድረግ ጥበብ ነው።

ሰዎች የተሰጣቸውን ተፈጥሯዊ ዕምቅ ኃይልና ድንቅን የማድረግ ጥበብ መጎናጸፍ የሚችሉት ልቡናቸውን በማጥራት ልምምድ ውሰጥ ሲያልፉና ከተሰጣቸው ታላቅ ማንነት ጋር ሲተዋወቁ መሆኑን ካርል የንግን ጨምሮ አንጋፋዎቹ የሥነልቡና ባለሙያዎች ያትታሉ፡፡
በየዘመኑ ይህን ልምምድ ከውነው በመገለጥ ውስጥ የሚኖሩ አልኬሚስቶች በምድራችን እንደሚከሰቱ ይሰማኛል፤ ልብ ስል።

ለአለፉት ሃያ ዓመታት በምድራችን የተከሰተ አልኬሚስት ነበር፤ ኤሊያስ መልካ! ስምን «መልአክ ያወጣዋል» እንዲሉ፣ «መልክኣ ጥበብ» ብንለውስ!? እርግጥ «መልካ» በአማርኛም በኦሮምኛም (ምናልባት በጉራግኛም) ተቀራራቢ ትርጉም አለው፤ መንጋው (ብዙ እንስሳት) ውኃ የሚጠጡበትና ለመሻገርም ምቹ የሆነ የአንድ ወንዝ ወይም ጅረት አካል ነው። ኤልያስ ከአልኬሚስትነት አልፎ፣ ስሙ እንደሚነግረን፣ ብዙዎችን የጥበብ ሰዎች በጥበቡ ሲያማክል (ማዕከል ሲሆን) የጥበብ ታዳምያንንም ጥበብ ሲያስጎነጭ፣ ጥበብንም ከዘመን ወደዘመን ሲያሸጋግር የኖረ ግለሰብ ሳይሆን ጀማ (ብዙኃን ሊሰኝ የሚችል) ነበረ። ለዚህ ነው ከመልካነት መገኘትን መልአክ ነው ያዘዘው ያልነው።

በዚህ ዘመን የሚወጡ የጥበብ ሥራዎች፣ በተለይም የሙዚቃ ጥበባት አብዛኞቹ ጠዋት ተዘፍነው እረፋዱ ላይ የሚረግፉ የማለዳ ጤዛ ሆነው አስተውለናል። ዘመን ተሻግረው በጥበብ ክፍታችንን የሚሞሉ፣ ውበታችንን የሚገልጹ፣ ሰናይነታችንን የሚያንጸባርቁ፣ ዕኩይነታችንን በድፍረት የሚኮንኑ የሙዚቃ ውጤቶች ጥቂቶች ናቸው። እነዚህን ዓይነት ዘመን ተሸጋሪ የጥበብ ፍሬዎች ለማፍራት ከተለመደውና ከድግግሞሹ ማምለጥ ሊስፈልግ ይችላል፡፡

የውስጣቸውን መገለጥ አጋርተውን አዲስ መንገድ የሚሠሩልን የጥበብ ሰዎች "ለጥበብና ለሕዝብ የሚወግነውን ብቻ ልሥራ" ብለው፣ የውስጥ ስሜታቸውንና አመለካከታቸውን ለወገን በመሰዋት (social desirability) የሚጸኑት ከራሳቸው ጋር መተናነቅ ካልፈሩ (fear of knowing the self) ብቻ ነው። ለዚህ ደግሞ በተለየ መልኩ የሚያስብ ሻል ያለ የግል ምልከታ ያለው ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል።

አለበለዚያ ማኅበረሰቡ እንደሚፈልገውና እንደገበያው ሁኔታ ያተኮሩ "እጅ እጅ" የሚሉ (monotony) ሐሳቦችን ብቻ ለማመንዠክ እንገደዳለን። ይህ ብቻም አይደለም፤ ዘፋኞች ለማኅበረሰብና ለራስ ጥቅም ፍላጎት ሲገዙ፣ በውስጣቸው የማይቀበሉትን ሐሳብ የለበጣ ሲዘምሩትም ይታያል።

ከተለመደው ነገር ለመውጣትና ውስጥን አዳምጦ ውስጥን በማስዋብ (As within So without/ "እንደ ልቦናችን ደጃችን " እንዲሉ ጥንታዊ አልኬሚስቶች) ዓለምን ማስዋብ እንደሚቻል የሚያሳዩን ጥቂቶች ናቸው። የዚህ ዓይነት የላቀ ሰብእና ለመጎናጸፍ በሚደረጉ ጥረቶች መሐል ሌሎችን አብሮ የማነጽ ኢላማ የተሳካላት ድንቅ ነፍስ የኤልያስ መልካ ናት።

ለቁጥር የሚያዳግቱ ባለተሰጥኦ ነፍሶችን የላቀው ማንነታቸውን እንዲጎናጽፉ ያስቻላቸው፣ ወደ ወርቅነት ያሸጋገራቸው አልኬሚስት ኤሊያስ መልካ ነው። የተሰጠው ¹ ELIXIR OF LIFE በጸጋው ላይ ሲያርፍ ዘላለማዊነት ይናኝበታል። ይህ የዘመን ክስተት ለጆሮ ብቻ ሳይሆን፣ ለፍሳችን ንጽሕና ሲጠበብ የኖረ ጠቢብ ነው።

ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ ጎሳዬ ተስፍዬ፣ኢዮብ መኮነን፣ ዘሪቱ ከበደ፣ ሚካኤል በላይነህ፣ታደለ ሮባ፣ ትግስት በቀለ፣ አብነት አጎናፍር፣ ገረመው አሰፍ፣ ማዲንጎ አፈወርቅ፣ ይርዳው ጤናው፣ ጌቴ አንለይ፣ ጆኒ ራጋ፣ ኃይሌ ሩት፣ ጌዲዮን ዳኔል፣ እንዳለ አድምቄ፣ ቤሪና፣ ዳን አድማሱና ሌሎች በኤሊያስ መልካ የጥበብ እጆች ተገርተው ዳግም የተፈጠሩ ድምጻውያን ናቸው፡፡

ኤሌያስ በጥበብ ውስጥ ነጻነቱን አስከብሮ ከተሰለቸው ልማድ በማፈንገጥ፣ ያበረከታቸው የሙዚቃ ሥራዎች ማኅበረሰቡን የሚያንጹና ተስፋንም የሚሰንቁ እንጂ፣ ዝሙትና ውርዴ ሐሳብን የሚለፍፉ አልነበሩም፡፡ የኤሊያስ ፈጠራዎች የዚህ ዓይነት ፣ራዎችን ይጠየፋሉ። ለዚህ ዋቢ አንዲሆን፣ በኢዮብ መኮነን፣ በዘሪቱ ከበደና በጌቴ አንለይ ላይ ያሰረጸውን የግጥም ጨብጥ ልብ ይሏል፡፡

ኤሊያስ ትቶን እስኬደበት ጊዜ ድረስ፣ ሙዚቃን በክብር ሲራቀቅበት ቆይቷል፡፡ የተሰጠውን መክሊት ተጠቅሞ አሻራውን በማኖር፣ ስሙንና ሥራዎቹን ዘላለም አጽድቆ፤ ተከታዮቹን ደግሞ በልባቸው ብርሃን ፈንጥቆ ተሻግሯል፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያት አለ፡፡ ከዚህም ተተኪዎቹና አዲሱ ትውልድ ሊወርሳቸው ከተገባቸው ወርቃማ መርሖች መካከል ቀጣዮቹን (በኮመንት ሳጥኑ ውስጥ የሚገኙትን) በጥሞና እንድናጤናቸው የአልኬሚስቱ ኤሊያስ ሕይወት ሹክ የሚለን ይመስለኛል፡፡…

Surafel Ayele
822 views11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-06 14:42:47
635 views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-06 14:41:32 የአያ ሙሌ ነገር!

ሰበቡ እኔ በግል ከልዑል አስወደደኝ አልበም ውስጥ የምወደው ballad ነው።

"በመዋደዳችን ዝናቡ ዘነበ
ፍቅር አዲስ ሆነና
ቡቃያው አበበ "
ይሄ ግጥም የአዲስንና የአቤን ፍቅር ከጅምሩ ጀምሮ የሚያውቀው የአያ ሙሌ ስራ ነበር። አዲስ አቤን ለመጎብኘት የምሽት ክበብ ስራዋን ጨርሳ በጠዋት የተከራየበት ቤት ስትመጣ ፣ አያ ሙሌ ደግሞ ፍቅራቸውን እንዲያጣጥሙ በሚል ሳይከፋው ከተዳበለበት የአቤ ቤት ለብቻቸው ጥሏቸው ይወጣ ነበር። ኋላ ላይ "ሰበቡ" የተሰኘውን ግጥም እንደሰጣት ከፋሲካ ከበደ ማስታወሻ አንብበናል። ከታች የተያያዘው የአልበሙ ሽፋን ላይ ያዲያ ስሙ የለም። ሲራክ በራሱ ግሩም ባለሞያና የብዙ ድንቅ ክላሲክ ዘፈኖች ዜማ ባለቤት ጭምር ነው። የዚህኛው ውዥንብር ግራ ያጋባል።

Senedu Abebe ደግሞ ሃይልዬ ለእናቱ ሃዘን በተቀመጠበት ጊዜ አያ ሙሌ ለቅሶ ሊደርሰው ሄዶ እዛው ቁጭ እንዳለ "መጥቻለሁ" የሚለውን ስራ ፅፎ "እዝን ይሁንልኝ " በሚል ለሃይልዬ እንደሰጠው መስማቷን አጫውታን ነበር። በአልበሙ ግን የግጥም ደራሲነቱ ሳይነሳ ቀርቷል።

በሌላ ጊዜ " ዞምዬ ዞማዬ ማር ዘነቤ
እኔው በፍቅርሽ ብጀነጀን
ልክረም ባንቺው መጀን … "

እያለ የሚሄድ የወሎን ውበት ፣መልክአምድርና የሰውን አኗኗር ቤተኛ በሆነ ዘዬ የሚገልፅ ዘፈን ስመሰጥበት አይቶ የግጥሙ ደራሲ አያ ሙሌ እንደሆነ አንድ የስነፅሁፍ መምህር እየነገረኝ ነበር። በዚህም ሶሻል ሚዲያ ተነስቶ ጭቅጭቅ ፈጥሯል። ይንን ግጥም ለመፃፍ የግጥም አዋቂ ብቻ ሳይሆን ቦታውንና ህዝቡን ማወቅና አብሮ መኖር ግድ ይላል። በዚህ ብቻ የዚህን ሰው መረጃ ላምን ተገድጃለሁ። ነገር ግን" የቴዲ አይሆን ይሆን የሚል "ቀናኢ ጥያቄ ማንሳት የመለኮትን ህልውና እንደመጠርጠር የሚያስወግዝ፣ የኮመንት ቦክሱንም በስድብ ከማጨቅ የዘለለ መረጃ አያስገኝልኝም።

በርካታቶች ከእፍኙ ቆንጥረው ደምቀዋል። የደመቁበትን ክብር ደግሞ አካፍለውት አይውቁም።

ስትኮንናቸው ዝናቸውን ተጠቅመው አፈር ያለብሱሃል። ወይም ተከታዮቻቸው ከጨበጡት ማይክ ጀርባ ያሉትን ምስኪን ግ ደግሞ ጉምቱ የጥበብ እጆች ማየት ስለማይፈልጉ አያ ሙሌን መሰል ሰው በየዘመኑ እናከስማለን።

በርካቶች ሃቁን ቆርጥመው በልተዋል። በርካቶች እንደዋዛ ከአንደበቱ የፈለቁትን ጥበባት ሰብስበው ከብረውበታል።
አያ ሙሌ! ሙልጌታ ተስፋዬ!
እና እሱም ይሄን ያውቃል! ምን አለ?

" መድመቂያ ካባቸውን እስካለብሳቸው እላይ ይሰቅሉኛል። ከወሰዱ በኋላ ግን አንስተው ለመፈጥፈጥ ይፈጥናሉ።

"እንዲህ ሆነህማ አንሰጥህም፣ ብንሰጥህም አረቄ ቤት ሄደህ ነው በአንዴ የምትጨርሰው፣ ይላሉ። ብጨርሰውስ የሰራሁበትን ሃቄን አንድጄ ብሞቀውስ ምን አገባቸው? ይል ነበር።
" ያለኝኝን ለህዝብ ልስጥ ብዬ እንጂ ዘፋኝ ማለት ከምላስ ላይ ምራቅ ከ ቅንድብ ላይ ኩል የሚሰርቁ ጉዶች ናቸው።
ጎጆዬን አፍርሼ ጎጆ በቀለስኩላቸው፣ እኔ ቀምዬ እከካቸውን ባራገፍኩላቸው ፣ አድምቄያቸው ያጨለሙኝ አንሶ እንዴት እንደሚጠየፉኝ ውስጣቸውን እኔ በማየው በማይበት ጊዜ የፈጠራቸው አምላክ ይቅር ይበላቸው እላለሁ። ሰውን የሚያህል ክቡር ፍጡር እንዴት በልብስ ይመለካል? " ሲል ተናግሮ ነበር።

"እናንተጋ ያለኝን ሃቅ ለማርያም ሰጥቻለሁ ደጃችሁም አልደርስም! " በሚል ሁሉን ትቶ አልፏል።

(ሃቅ በሊታዎች ወዮላችሁ! ከግንድ የሚያላጋ ልጅ ላላት ማርያም ነው እንባውን የሰፈረላችሁ! )

Surafel Ayele
777 views11:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-06 14:40:48
773 views11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 23:37:26
ለወዳጆቼ ... ሁሉ ነገር ስህተት አይደለም። በአርክቴክቸር ሰባት መሰረታዊ እሳቤዎች አሉ። እነርሱም Emphasis, Balance, Contrast, Repetition, Proportion, Movement እና Space ናቸው።

ከእነዚህ እሳቤዎች ከታች በምስሉ የምትመለከቱት ያለማወቅ ውጤት የሚመስል ለዚያውም የምጣኔ ጋር የተያያዘ ድርጅት ማስታወቅያ ትኩረታችሁን ስቦ አይቻለሁ። ለአንዳንዶቻችሁ ጥሩ መዝናኛ ሆኗል። ነገሩ ወዲህ ነው። ተከተሉኝ።

በአርክቴክቸር መሰረታዊ ሰባት እሳቤዎች አንዱ Emphasis ነው። በግርድፉ ለሆነ ነገር አጽንኦት መስጠት ወይም አጽንኦት ማለት ነው። እንደምትመለከቱት "Planning" የሚለው ማስታወቅያ በዚህ እሳቤ ትኩረታችሁን የሳበው አጽንኦት ስለተሰጠው ነው። በአገራችን ለዚህ እሳቤ የሚሆን ምሳሌ አቢዮት አደባባይ ፊትለፊት Grove Garden Walk አካባቢ የሚገኘው ፊንፊኔ ሕንፃ Finefine የሚለው ጽሑፍ የተጻፈበትን መንገድ ማየት በቂ ነው። ምን ለማለት ነው? ሁሉ ነገር ስህተት አይደለም።

ሱለይ አደም
1.6K views20:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 22:47:42 አሜሪካኖች በየአመቱ አንድ ውድድር ያደርጋሉ—ኧርነስት ሄሚንግዌይን የመምሰል ውድድር። ሸበቶ፣ ጺማም አዛውንቶች ከመላው አሜሪካ ለዚህ ውድድር ይሰባሰባሉ። ሄሚንግዌይ የአልኮል ሱሰኛ ነበር። ውድድሩንም መለስተኛ የመጠጥ ፌስቲቫል ይመስላል። የአልኮል ዘር እንደ ጉድ ይጠጣል።

ብዙ ግዜ ጥያቄ የሚፈጥርብኝ አንድ ጉዳይ ነበር። አሜሪካኖች ትልቁ ደራሱያቸው ሄሚንግዌይ ነው ወይ? ሄርማን ሜልቪልና ማርክ ትዌይን የት ገብተው ነው? ስለ ሄሚንግዌይ በደንብ ሳውቅ ግን ነገሩ ተገለጸልኝ። ሄሚንግዌይ ደራሲ ብቻ አልነበረም። ሄሚንግዌይ icon(ምልክት) ነበር። የጻፋቸው መጽሀፍት ብቻ ሳይሆን የኖረው ኑሮ አስደናቂ ነበር። በአንደኛው የአለም ጦርነት የአምቡላንስ ሾፌር ሆኖ ተሳትፏል፤ በስፔይን የእርስ በእርስ ጦርነትን ተመልክቷል፤ የጎሽ ውድድር(bullfighting) ተካፍሏል። አደንና አሳ ማጥመድ ነፍሱ ነበር። እንደ ሰለብሪቲ የተንደላቀቀ ህይወት ኖሯል። በአንደኛ ደረጃ ትኬት አለምን ዞሯል። ብዙ ብዙ . . . በአጭሩ ሄሚንግዌይ አስደናቂ ሰው ነበር። በስሙ ውድድር ቢዘጋጅለት አይበዛበትም።

ይሄን ሃሳብ ይዤ ወደ እኛ ሃገር ልምጣ። ብዙ ድንቅ ደራሲዎች አሉን። ጋሽ ስብሐት አንዱ ነው። ስብሐት የኢትዮጵያ ስነጽሑፍ ንጉስ አይደለም። ውድድር ውስጥ መግባቱን ባልወደውም ስብሐትን የሚበልጡ ታላላቅ ደራሲዎች አሉን—ጸጋዬ ገብረመድህን፣ ሐዲስ አለማየሁ፣ ዳኛቸው ወርቁ፣ በአሉ ግርማ ወዘተ ወዘተ። ነገር ግን እንዲህ ያለ ደራሲን የመምሰል ውድድር ለማዘጋጀት ከተፈለገ ከስብሐት የበለጠ የሚመጥን የለም። አንደኛ ስብሐት እንደ ደራሲ ብቻ ሳይሆን እንደ ሰው የሚወደድ ነው—ስብእናው ግዙፍ ነው። ሌላው ደግሞ ስብሐት ከስነጽሁፍ ማእቀፍ ውጪም ታዋቂ ነው—ሰለብሪቲ ቢጤ ነው። የማያነበውም፣ መጽሀፍ ገልጦ የማያውቀውም ስብሐትን ያውቀዋል። Icon ነው። በስሙ ብዙ ቀልዶች ይነገራሉ—አብሮን እያለ ተረት ወደ መሆን ደረጃ ደርሷል። የተደበቁ፣ የማይወሩ ጉዳዮችን በመድፈር፣ አደባባይ በማውጣት የባህል አብዮት የፈጠረ ሰው ነው። ከነእንከኖቹ የሚወደድ ሰው ነበር።

ስብሐት ገብረእግዚአብሔርን የመምሰል አመታዊ ውድድር ቢዘጋጅ ለስነጽሁፍ፣ ለባህል ውለታ ዋልን ማለት ነው።

Tewodros Shewangizaw
1.4K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 22:47:26
1.2K views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 22:43:50 እውነተኛ ስሙ ዊሊያም ሲድኒይ ፖርተር ይባላል። 36 አመቱን ሲደፍን ወንጀል ሰርቶ ለ5 አመት ዘብጥያ ወረደ። ታዲያ እስር ቤት ገብቶ አርፎ አልተቀመጠም። ኦ ሄንሪ በሚል የብእር ስም ብዙ አጫጭር ልብወለዶችን ጻፈ። የብእር ስም ለመጠቀም የመረጠው ሃቀኛ አሜሪካውያን የወንጀለኛ ግለሰብ መጽሀፍ ገዝቶ ለማንበብ ፍላጎት አይኖራቸውም ብሎ ስለደመደመ ነበር። ኦ ሄንሪ በአጫጭር የልብወለድ ታሪኮቹ ውስጥ በማይጠበቁ፣ አስደናቂ አጨራረሱ ይታወቃል።

¤¤¤

ቻርልስ ቡኮውስኪ ሰካራም ነበር። የወጣለት አለሌ፣ የቁማር ሱሰኛ፣ ጋጠወጥ ወዘተ ወዘተ ነበር። ሲብስበት ደግሞ ገጣሚ ለመሆን ይሞካክራል።

ለአመታት መጽሀፍን ልናሳትም አንፈልግም የሚል የእንቢታ መልስ ሲያስተናግድ ከኖረ ከ30 አመት በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ ታተመ። ያገኘውን ጥቂት ገንዘብ ሁሉ አደንዛዥ እጽ፣ አልኮል፣ ሴተኛ አዳሪና ቁማር ላይ ያጠፋል። በመጨረሻ 6 ረዥም ልብወለዶችን፣ በመቶ የሚቆጠሩ አጫጭር ታሪኮችን አሳተመ። በአጠቃላይ ሁለት ሚሊየን የመጻህፍቱን ቅጂ ቸበቸበ።

አስገራሚው ነገር ቡኮውስኪ የተሳካለት ደራሲ ከሆነ በኋላ እንኳን የህይወት ዘይቤውን አልቀየረም ነበር። ያንኑ ቆሻሻ ህይወት መኖር ነበር የቀጠለው—ይጠጣል፤ ይጦዛል፤ ሴተኛ አዳሪ ያተራምሳል፤ ይቆምራል።

¤¤¤

ስብሐት ይባላል። ይጠጣል፣ ይቅማል፣ ብዙ ሴቶችን ይተኛል። ይህንን ሁሉ እንደሚያደርግም አይደብቅም። ይህ የመረጠው የኑሮ ዘዬ ነው—ለዚህ ደግሞ ማንንም ይቅርታ አይጠይቅም። እንዲያውም የገዛ ህይወቱን ቀባባቶ፣ አሳምሮ መጽሐፍ ያደርገዋል። የሴት መብት ተካራካሪዎች ሴቶችን የወሲብ ሸቀጥ አድርጎ ቀርጿቸዋል ብለው ይከሱታል። ስብሐት ግን በተለይ በወጣቱ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነው። ስለ ወሲብ እና የጾታ ግንኙነት አብዝቶ ይጽፋል፤ ይናገራል። ብቻ አከራካሪ ስብእና ነው።

¤¤¤

በመጨረሻ አንድ ጥያቄ፦

የደራሲ ስብእና ግድ ይሰጣችኋል ወይ? አፈንጋጭ፣ ያልተለመደ፣ ወጣ ያለ ባህሪ ያለው ደራሲ ምን አይነት ስሜት ይፈጥርባችኋል? የአንድ ደራሲ ስብእና መጽሀፉን ለማንበብ የመፈለግ ስሜታችሁ ላይ ተጽዕኖ ይፈጥርባችኋል?

Tewodrose Shewangizaw
1.3K views19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 22:43:11
1.2K views19:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ