Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 159.61K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-06-08 16:20:17 የእናቴ ልጅ
ክፍል ሃያ ስድስት

ሰውን ከልብህ ስትጠላው ድምፁንም ሆነ አይኑን ለማየት ትጠላለህ ልክ የማይስማማህን ምግብ በግዴታ ብላ እንደመባል ነው የሚሆንብህ ። በሰአቱ የተሰማኝ ነገር  ለመናገር የማይቻል አስቸጋሪ ነበር ።
ወንድሜ ነብሰ ገዳይ ቀጥሮ ሊያስገድለኝ ተደራደረ በኔ በእናቱ ልጅ ላይ ።ለምን ብቻውን ወራሽ ለመሆን ለገንዘብ ብሎ ።'ምን አይነት ጊዜነው ክፉ ዘመን 'ብለው እናቶች አንዳንዴ የሚያማርሩት ያለነገር አይደለም ለካ ።እንደዚ አይነት የበዛ እራስ ወዳድነትእና ጥቅመኝነት ስላለ ነው ። ሰው እንዴት በሌላው ላይ ተረማምዶ ሕይወት ለመመስረት ይጥራል ። ሲሆን አቅምና ጉልበቱን አይምሮውን ተጠቅሞ እራሱን መለወጥ ሲኖርበት ባለፋበት ሀብት ላይ አይኑን ጥሎ  ሰውን እስከማጥፋት መድረስ ተገቢነው።  እውነትም ከባድ ጊዜ ወንድም በወንድሙ ላይ የሚነሳበት መሰሪነት የበዛበት ።
እናቴ ሽማግሌውን በጥያቄ ማጠደፉን አላቆም አለች እሳቸውም ዝም ብለው አቤልን ማየት ሆነ  ባዩሽ እያለቀሰች በመዘፍዘፊያ ውሃ አምጥታ ደሜን በጨርቅ እያረጠበች ትጠራርጋለች  ደግነሽ እልልልታዋ ወደኡኡታ ተቀይሮባታል
"ኡኡኡኡ እኔን አፈር ልብላ እኔን አክስትህን የኔሸበላ እንዲሁ ጠርተው ከመንገድ ሊያስቀሩህ ?የስራቸውን ይስጣቸው መዳኒዓለም ። እኔማ መጀመሪያም ሰትወጣ ደስ አላለኝም ነበር"እያለች ታለቅሳለች
"እባክዎት ማነው እንዲ ያደረገው ይንገሩኝ አባቴ "አለች እናቴ  ድምጿ ፍርሐት ያዘለ ነው ።ሽማግሌው እንዲነግሯት አልፈለኩም ለነገሩ እሳቸውም ዝም ብለዋት ነበር  ።እናቴ የልጇን የመጨረሻ አውሬነት ስታውቅ ምንልትሆን ትችላለች ፡ይህንን ነው የፈራውት ።እንጂማ አቤልን አንቄ ብገድለው እንኳ አሁን ላይ ቅር አይለኝም ነበር  ። ሽማግሌው ፡ያጎነበሰ ሰውነታቸው ቀጥ ብሎ መቆሙ በራሱ ገርሞኛል እኛ ድቅቅ ያሉ ሰውዬ በሳምንቱ ውስጥ ምን አግኝተው ነው እንዲ ቆፍጠን ያሉት ከክሳታቸው በቀር ተለውጠዋሉ  ። እናቴ ውትወታዋን አላቋረጠችም ሽማግሌው ደሞ ቃላት ያጡ ይመስል አቤል ላይ እንዳረፉ ነው ።አቤል ምንም ነገር ሳይተነፍስ ቆይቶ ድንገት የባነነ ይመስል ።
"አንቺ ባዩሽ ጓደኛውን ሊያገኝ ነው የወጣው አላልሽም ነበር እንዴ "አላት ባዩሽ አቀረቀረች
"እንዴ እሱማ እሱ የነገረንን ነው የሆነሰው በስልክ ጠርቶት ነው እንደውም ያንተው ጓደኛ እንደሆነነው ናቲ የነገረን አይደልእንዴ ናቲ ? ደሞስ የሆነ ሆነና ወጥተን እንፈልገው ስልህ ይመጣል ምን ይሆናል እያልክ ያዘናጋኽን አንተ አይደለህ "አለች አክስቴ ደግነሽ ቆጣ ብላ ።
እናቴ በጥርጣሬ ወደ አቤል ዞረች አይኗን ለመሸሽ ይመስል ተንቀሳቀሰ ፡  እናቴ ወደ አቤል ተጠግታ
"አንተ አንድ ነገር አድርገሃል እንዴ?"አለች ድምጿ እየተንቀጠቀጠ
"ኧረ እማዬ እኔ እኔ መቼ አአገኘውት እዚሁ ካካንቺ ጋር አአልነበርኩም "አለ እየተንተባተበ ።
"ባትሆን ይሻላል ከሆነ መቼም ይቅር አልልህም "ከማለቷ ።የሽማግሌው ቁጣ ገንፍሎ ወጣ ፍፁም ሌላ ሰው ሆኑ በፍጥነት እናቴን ከአቤል ዞር አድርገዋት ፊትለፊት አቤልን ተጋፈጡት  ከኪሳቸው የሚያብለጨልጭ ስለት አውጥተው የአቤል አንገት ላይ ቀሰሩት ፡አቤል እንዲ አይነት ነገር ገጥሞት ስለማያውቅ በድንጋጤ ፡ የእናታችንን ስም ጠራ ሽማግሌው በቁጣ "አንተ ነህ ወንድምህን ልታስገድል የነበረው አንተ ሳታየኝ በጨለማውስጥ ከዛ ከይሲ ነብሰ ገዳይ ጋር ስትደራደር አይቼሃለው ፡እዛ የቆማችሁበት ጨለማ ውስጥ ተደብቄ ሰምቻችዋለው ።ከዛ ምን እንዳደረኩ ታውቃለህ በፍጥነት እዚ መጣው ናቲ ከቤት ወጥቶ እናንተ የጠራችሁት ቦታ እንዳይመጣ ፀልዬ ነበር ነገር ግን መጣ ስለዚ እሱ አንተ የተጎዳህ መስሎት ሲሮጥ ከመንገድ ያገኘውትን ዱላ ይዤ ተከተልኩት ግን የሱንያክል መፍጠን አልቻልኩም ። እዛ ስደርስ የመጨረሻ እስትንፋሱን ሊዘጋው ቅጥረኛህ በዚ ስለት ሊሰነዝርበት ሲል የሞት ሞቴን በዱላ አናቱን አልኩና ጣልኩት ። ለትንሽ ልጄን አጥቼው ነበር ።አንተ አቤል መባል አልነበረብህም አንተ ቃዬል ነህ "ብለው አቤልን በጥፊ አጮሉት አቤል ሶፋውላይ በቁሙ ወደቀ ። እናቴ አበደች የምትይዝ የምትጨብጠው ጠፋት ። ደግነሽ የቤቴ ጉድ ብላ ለቅሶዋን አባሰችው ።ባዩሽ አፏን በሁለት እጆቿ ይዛ በድንጋጤ ቆማለች ።እኔ የሽማግሌው ከኔም በላይ ሆነው ተበሳጭተው እንደዛ ሲሆኑ ሳይ ተገርሜአለው በዚች ጥቂት ጊዜ ምን ያክል ቢወዱኝ ነው የኔ ተቆርቋሪ የሆኑት ።
"አንተ አንተ በቃ መቼም አታርፍም ደሞአሁን ምንድነው  ያልከኝን ሁሉ አድርጌ ጉዞህን አስተካከልኩ አሁን እሺ ምንድነው ከሱ ጋር የሚያጣላህ "ብላ ቁጭ ብላ እናታችን አለቀሰች አቤል ምን ያክል እንደሚሰባብራት አውቃለው እናቴ አሳዘነችኝ እናት ናትና ።
"አንተ መቼም ወደውጪ አትሄድም መቀጣት አለብህ ባለጌ እኔ ነበርኩ አቤል ያልኩህ ስትወለድ አንተ ግን የአቤልነት ጫፍ የለህም ሴጣን "አሉ ሽማግሌው ስሜታዊ ሆነው ።እሳቸው በቁጣውስጥ ሆነው የተናገሩት ነገር አምልጦአቸው ቢወጣም ፡እኛ በቤት ውስጥ ያለነው ሰዎች ሁሉ በአንድነት ምን ብለን ድምፅ አወጣን ። በተለይእናቴ አይኗም ሳይቀር ፈጠጠ ።በዚ ጊዜ ግን እኔ የሌለኝን ብርታት ከየት እንዳመጣሁት አላውቅም ተነስቼ ከፊትለፊታቸው ቆምኩ ።
"እርሶ ማን ነዎት ለሱ ስም ያወጡለት "አልኳቸው።መናገራቸውን ያወቁ አይመስልም ደነገጡ
"ይንገሩኝ እርሶ ማን ነዎት"ጮውኩ
"እኔ ምን አልኩ እባክህ ናቲ ተው "አሉ ተጨንቀው ወደ እናቴ እያዩ
"አንዴ ተናግረዋል እኔነኝ ስም ያወጣውለት ብለዋል "አልኳቸው ።እናቴ እንደመንገዳገድ እያረጋት መጣችና ሽማግሌውን በትኩረት አየቻቸው ። ድንጋጤዋ ጨመረ የለበሱትን ቲሸርት በጎን በኩል ገለፅ አድርጋ አንድ ምልክት አየች ከዛ በዋላ "ግዛው !!!!!!"ብላ ጮሃ ወደመሬት ወረደች መሬት ከመንካቷ በፊት ሽማግሌው ፈጥነው ያዟት ..........

Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.1K viewsTsiyon Beyene, 13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 21:00:03 "የትናየት ካንቺ የምትፈልገው ይህንን ነው... ማለትም ፀብ.... ከሷ የተሻልኩ ነኝ ብለሽ ካሰብሽ እቅዷን ቀድመሽ አክሽፊባት...."

"ማለት..... እንዴት አድርጌ"

"እኔ አግዝሻለሁ..." እንስማማ አይነት እጁን ዘረጋልኝ። ሳላወላውል ጨበጥኩት.... ተገኝቶ ነው ይቺን የሰው ቆንጥር ከአጠገቤ የሚያርቅልኝ

ወደ መነሻ

አስታወሳችሁ መነሻዬን እንጂ መድረሻዬን ሳላውቅ እግሬ ወደመራኝ እየሄድኩ ነው ብያችሁ ነበር። አዎ መንገዴንቨ አላቋረጥኩም። ከእርምጃዬ እኩል ትዝታዬ በልቤ ውስጥ ይፈሳል በአይምሮዬም ውስጥ ይመላለሳል።

ከተማውን ሙሉ ለሙሉ መልቀቄን ያስተዋልኩት ከፊት ለፊቴ ያለው ሰፊ የግጦሽ ሜዳ ላይ የእረኛዎችን ድምፅ ስሰማ ነው።

ድንገት እኔን አልፎ ሲጥጥ ብሎ የቆመ መኪና ከሀሳቤ አንቅቶ አስበረገገኝ። ቅድም ሳይገጨኝ ያለፈው መኪና.... ከውስጡ አንድ ሰው ወረደና ወደኔ መጣ። በድንጋጤ ደርቄ ነው የቀረሁት

"ህያብ በዚህ መልኩ አገኝሻለሁ ብዬ አልጠበኩም ነበር" አጠገቤ መጥቶ ክንዴን ያዘኝ ልክ እንደመጀመሪያው ቀን ልዩነቱ ያኔ ከኋላ አሁን ግን ከፊት ለፊት መሆኑ ነው

"ቅድም አንተ ነበርክ"

"አዎ ግን አንቺ መሆንሽን ለመለየት ጊዜ ወሰደብኝ ህያቤ በጣም ተጎሳቁለሻል አንቺ እንደሆንሽ ያወኩት "ዞር በሉልኝ አስማሳዮች" ብለሽ ስትናገሪ በሰማውት ድምፅሽ ነው አረማመድሽ ደግሞ አረጋገጠለኝ። እናም ተከተልኩሽ.... የምትሄጅበትን መድረሻሽን ለማወቅ ተከተልኩሽ ግን እንደማየው.......

"ቢኒ እኔ...." ቃላቶቼ አፌ ላይ ተንገዋለሉ። ወደራሱ አስጠግቶ እቅፍ አደረገኝ።

"እሽሽሽሽሽሽሽ ይገባኛል ምንም አታስረጂኝ"

በህይወት መንገድ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ተገናኘን..... እኔና ቢኒ

ይቀጥላል
5.4K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 21:00:02 #ህያብ


#ክፍል_አራት


#ድርሰት_በኤርሚ

ነሀሴ መጨረሻ ላይ ውጤት መጣ ተባለና አየን ጥሩ ውጤት ነው ያመጣሁት ግን ሩቅ ሀገር ነው የመደቡኝ ጎንደር ዩንቨርስቲ በምፈልገው ዲፓርትመንት(ህክምና)

እናቴን እና ልጄን ትቼ እንዴት ችዬ ይህን ያክል እርቃለሁ.. ትምህርቴን መተው እናቴን እንደመቅበር ነው። ሁላችንም ቢከብደንም ግዴታ ሄጄ መማር አለብኝ።
.....
ስራ ቦታዋ ሄጄ ለእናቴ ስነግራት እልልታዋን አቀለጠችው። ደንበኞቿ ምን እንደተፈጠረ ሲጠይቁኝ ነገርኳቸው እንኳን ደስ ያለሽ እያሉ እናቴን አቀፏት..... ከሁኔታቸው እኔ ሳልሆን እናቴ ውጤት የመጣላት ነበር የሚመስለው....
......
ቤት ውስጥ ጎረቤቶቻችንና አንዳንድ የእናቴ ወዳጆች በተገኙበት መጠነኛ የሽኝት ዝግጅት ተደረገልኝ። ልለያት እንደሆነ ያላወቀችው ልጄም ከኔ እኩል ፍንድቅድቅ ብላለች። እንግዶች በልተው ማዕዱ ከፍ ካለ በኋላ እናቴ ወደ መሀል ወጣችና
"አንዴ ፀጥታ...." ብላ ጨብጨብ ስታደርግ ሁሉም ሰው ባንዴ ዝምምም አለ።

"በህይወቴ እንደዛሬ የተደሰትኩበት ቀን የለም ... ልጄ ዩንቨርስቲ ገባችልኝ። ይሄ ከምንም በላይ ትልቁ ህልሜ ነው። እዛ ሄዳ በስኬት እንደምትመለስ እተማመንባታለሁ። ትልቅ ነገርም ባይሆን ይሄን ስጦታ በእናንተ ፊት እሰጣታለሁ" ወደኔ መጥታ ጉንጬን አገላብጣ ከሳመችኝ በኋላ የተጠቀለለውን ስጦታ ሰጠችኝና"ክፈቺው..." አለችኝ። የተጠቀለለበትን ወረቀት ስከፍተው ሞባይል ከነ ቻርጀሩ ብቅ አለ። አላመንኩም እናቴ ለኔ የእጅ ስልክ ገዛችልኝ... በዚያን ጊዜ አብዛኛው ሰው ባለ ሞባይል እየሆነ ቢሆንም እኔ ይኖረኛል ብዬ ግን አላሰብኩም ነበር።

"አመሰግናለሁ እናቴ.... ደግሞ ቃል እገባልሻለሁ... አኮራሻለሁ"

"እተማመንብሻለሁ የኔ ጀግና.... ሳትሳቀቂ በናፈቅሺን ሰዓት መደወል ብቻ ነው...."ወደ ደረቷ ወስዳ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ። ይሄን እቅፍ እኮ ስወደው..............
ቃል ባትናገር እንኳን በእቅፏ ብቻ ብዙ መልዕክት የምታስተላልፍልኝ ይመስለኛል።
"በርቺ....
ባንቺ እተማመናለሁ....
እኔ አለሁልሽ...
እወድሻለሁ......." ብቻ ስታቅፈኝ ከዚህም በላይ ብዙ የምትለኝ ይመስለኛል።
..............

የምወዳት ልጄን እና እናቴን ተሰናብቼ ወደ አፄ ፋሲል ሀገር ጥንታዊቷ ጎንደር ተጓዝኩ ።
..........

ምዝገባ እና ሌሎች ፕሮሰሶች አልቀው ትምህርት የምንጀምርበት ቀን ደረሰ...... የመጀመሪያ ቀን እንደመሆኑ አብዛኛው ተማሪ ቀድሞ ክፍል ተገኝቷል ከነኛ መሀል አንዷ እኔ ነኝ።
.....
ከደቂቃዎች በኋላ
"ይሄ ሸበላ ብቻ እንዳይሆን የሚያስተምረን" ከኋላዬ ያለችው ልጅ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ አንሾካሾከችልኝ። ከንግግሯ እኩል ቀና ብዬ ወደ ፊት ለፊቴ አየሁ..... " ዋው ውበት ..... ዋው ቁመና.... ዋው ደረት...." ብዙ ዋው የሚያስብሉ ነገሮችን ያሟላ ሸበላ ሰው.....
......
"እሺ ዛሬ ብዙም የምንማረው ነገር አይኖረንም እርስ በርሳችን እንተዋወቅና ኮርስ አውትላይን እሰጣችኋለሁ...... እምም ከፊት ልጀምር ስምሽን አስተዋውቂን እስኪ...." ምኑ ነው ምን አለ እስከምረጋጋ እንኳን ሌላ ሰው ቢጠይቅ

"ህያብ በዛብህ እባላለሁ የመጣሁት ከአዲስ አበባ" ጣቱን ከኔ ቀጥሎ ወዳለችው ልጅ ጠቆመ

"መቅደስ ገዛህኝ..... ከሀዋሳ
ተፈሪ ይልማ...... ከደሴ
አብሳላት አበበ.... ከአዳማ
የትናዬት ዘመረ..... ከአዲስ አበባ......" ሁሉም ስማቸውን እና የመጡበትን ከተማ ተናገሩ ሁላችንንም ከሰማ በኋላ

" የኔ ስም ደግሞ ዮናታን ይባላል የ...." ከዚህ በኋላ ያለውን አልሰማሁትም .... ዮናታን.... ዮኒ ስሙ ደስ ይላል መልኩም ደስ ይላል። ሳላውቀው ስለሱ ብዙ አሰብኩ.... እጄ ላይ ያረፈ ወረቀት ከሀሳቤ አነቃኝ

"ያልኩትን ሰምተሽኛል ህያብ" ድንብርብሬ ወቶ አይን አይኑን አየው ጀመር እሱም ትንሽ ካየኝ በኋላ

" ተወካይ እስክትመርጡ ድረስ አንቺ ተወካይ ሆነሽ እነኝህን ወረቀቶች ለሁሉም አዳርሺ...." መልሴን ሳይጠብቅ ክፍሉን ለቆ ወጣ። እንዴ ቆይ ደግሞ ስሜን እንዴት ባንዴ ያዘው..... ይገርማል
........
" እና እኔንም አፈዘዘኝ እያልሽኝ ነው" አለችኝ ከፊት ለፊቴ መጥታ

"ይቅርታ እህቴ ምን......"

."ቅድም አልሰማሽኝም የትናየት.... የትናዬት ነው ስሜ"

"እሺ የትናዬት የምትይው አልገባኝም"

"ቀስ ብሎ ይገባሻል ለማንኛውም የራሴን ልውሰድ." አንዱን ወረቀት አንስታ እየተቆናጠረች ከክፍሉ ወጣች።

"ወይ አምላኬ ስንት አይነት ሰው አለ" ብዬ ስዞር ሁሉም አፍጠው የሚያዩኝ እኔን ነው።

ህይወት ልክ በምኞታችን ውስጥ እንዳሰብናት ቀላልና ጣፋጭ አይደለችም። ልንመራት ያወጣነውን እቅድ አስጥላ በራሷ ምህዋር ላይ ታሽከረክረናለች። እምቢ ብለን ብናስቸግራት እንኳን ወይ ከራሳችን እቅድ ወይም ሽክርክሪቱ ከሚያመጣው ነገር ሳንቋደስ ሜዳ ላይ እንቀራለን።

ዩንቨርስቲ መግባትን ሳስብ የሚታየኝ ጠንክሮ መማርና መማር ብቻ ነበር። ግቢ ውስጥ ሆኜ ከትምህርቴ የበለጠ ቦታ እሰጠዋለሁ ብዬ የማስበው ምንም ነገር አልነበረም። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ የሆነ ሰው መጥቶ ይህን ጥያቄ ቢጠይቀኝ በመጠየቁ ልናደድበት እችል ነበር። ዛሬ ግን ያን እምነቴን የትላንት እቅዴን ሊያከሽፍ የሚችል ፍቅር ያዘኝ። ያውም ውድድር የበዛበት ፍቅር.....
አብሬው ልሁን ብዬ ባስብ እንኳን ከሱ እኔን አለማፍቀር ውጪ ከደርዘን በላይ ሴቶች ጋር መጋፈጥ ይኖርብኛል..... ያውም እኔ የማውቃቸው ብቻ።

ያለኝ አማራጭ አንድ ብቻ ነው ቢከብደኝም ስሜቴን አምቄ መያዝ እና በሰላም ትምህርቴን መቀጠል። ምንም ሳይተነፍሱ ሁሉንም በልብ መያዝ ከምንም በላይ ህመም ነው.... በተለይ ደግሞ ፍቅር ሲሆን...

ብዙ ጊዜ ይሄን አስባለሁ ለእናቴ ይሄ አይገባትም አይደል? ... ስኬቴን ለምትናፍቅ እናቴ ስል ከመጋፈጥ ይልቅ መሸሽን መርጫለሁ። የምሸሽበት ምክንያት ዋናው ቁም ነገሩ እኮ ማፍቀሬ አይደለም ፍቅር በየትኛውም ጊዜ እና ሁኔታ ውስጥ ሊከሰት የሚችል ስሜት ነው። ችግሩ ለዚህ ፍቅር ስል ብፋለም ለትምህርት የሚሆን ነፃ አይምሮ ላገኝ እችላለው ወይ? የበለጠው ችግር ደግሞ ያፈቀርኩት ሰው ሁሉንም ቀማሽ መሆኑ ነው።
፧፧፧፧፧፧
ከዛን ቀን ጀምሮ ማለትም ከመጀመሪያ የትምህርት ቀናችን ጀምሮ በዮኒ ፍቅር ተለክፊያለሁ። ፍቅር እንደያዘኝ እንኳን እያወኩ ላለማመን ከራሴ ጋር ለወራት ተከራክሪያለሁ። የትናዬት በየቀኑ እኔን ማስበርገግ ስራዬ ብላ ከያዘች ቆይታለች። በተለይ ዮናታን አስተምሮን ሲወጣ ወይ ከጎኔ ናት ወይም ከፊት ለፊቴ.... እልፍ ጊዜ እኮ አብረው አይቻቸዋለሁ... ብዙ ጊዜ ቢሮው ስትገባ ያዩዋት ነግረውኛል...... እኔ ደግሞ በተቃራኒው ከሱ ጋር የሚያገናኘን ድልድይ ሁላ ላፈርስ የምሞክር ሰው ነኝ። ለምን ይሄን ያክል የቤት ስራ እንደሆንኩባት አላውቅም። አሁን ግን መሮኛል ፀብ ላለመፍጠር እያልኩ እንደፈሪ መታየት መሮኛል።

ዛሬም እንደለመደችው ከጥሩ ትወና ጋር የአሽሙር ንግግሯን ተናግራኝ ከክፍሉ ወጣች። ብሽቅ ብዬ ወረቀቶቼን ሰብስቤ ተከትያት እየወጣሁ እያለ አንድ ሰው ከኋላዬ ያዘኝ። ዞር ስል ቢኒ ነው ከተማሪዎች ሁሉ የተለየው ዝምተኛ ልጅ።

"አቤት ቢኒ" አልኩት ኮስተር ብዬ... ግንባሬን አይቶ እጁን ከክንዴ ላይ አነሳ እና

"ይቅርታ ህያብ.... ጣልቃ ልገባ ፈልጌ አይደለም ግን እኔ የታየኝን አንድ ነገር ልበልሽ..."

"ምን"
5.1K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 06:25:04 የእናቴ ልጅ
ክፍል ሃያ አምስት

ጨለማውን ፈራውት አፉን ከፍቶ ሊበላኝ የተዘጋጀ መሰለኝ ፡ ለማንም የማይመለሰው ልቤ ተልፈሰፈሰብኝ ፡ እናቴን ሳስባት ደሞ ይበልጥ ሆዴ ባባ ።አቅም አጥቼ በተዘረርኩበት መሬት ላይ ሆኜ ስለሷ አዘንኩ ። ደጋግማ አስጠንቅቃኝ ነበር 'ወንድምህን መውደድ ትችላለህ ግን እንዳታምነው ተጠንቀቅ ከኔ ከእናቱ የበለጠ ወዳጅ የለውም ነገር ግን ለኔም አይመለስም' የሚለው የናቴ ንግግር ጆሮዬላይ አቃጨለ ፡ እራሴን ለማበረታታትና ለመነሳት ሞከርኩ  ነገርግን ተህዛዝ የተቀበለው ልጅ በርግጫ ብሎ አስተኛኝ ምቱ አይለኛ ነው  በጣም አመመኝ ጥርሴ ተናጋ ከአፌ ደም ሲፈስ ይሰማኛል ።
"አዝናለው እኔ እንዲ እንዲሆን አልፈለኩም ፡የወንድምህ ትህዛዝ ነው ፡ እንዲ ካላደረኩ ደሞ የማጣው ነገር አለ "አለኝ ።ድምፁን አወኩት ፡በስልክ ወንድምህን ይዘውታል ያለኝ ሰው ነው ። በራሴ ተናደድኩ እንዴት የእናቴን ማስጠንቀቂያ ችላ አልኩ ፡ይህ ሰው ስልኬን ከየት አምጥቶ ሊደውል ይችላል ።አቤል እስካልሰጠው ድረስ ፡እንዴት አልመረመርኩም ።
"ይኽውልህ ወንድም በፍፁም ወደውጪ የመሄድ እቅድ የለውም እሱ የሚፈልገው እዚሁ ቀርቶ ለብቻው የእናቱ ወራሽ መሆን ብቻ ነው  ያደሞ አንተ እስካለህ አይሆንም ስለዚህ አንተ ዞር ማለት አለብህ ለዚ ደሞ ከኔ ጋር ስምምነት ደርሰናል ፡ ከሚያገኘው ውርስ አንድ ሦስተኛው የኔ ነው የሚሆነው ፡ ይህን ስምምነት  እውን ለማድረግ ደሞ እኔ ስራዬን መጨረስ አለብኝ ፡እና በጣም ይቅርታ አድርግልኝ በሰላም ልሸኝህ እገደዳለው "ብሎ ከለበሰው ኮት ኪስ ውስጥ በጨለማውስጥ የሚያብለጨልጭ ስለት አወጣ ፡እናም በአይል ወደኔ ሲሰነዝር አይኔን ጨፈንኩ ፡ ስለቱ ግን ሲወድቅ ተሰማኝ እሱም ከፍተኛ ድምፅ አሰማ ፡በፍጥነት አይኔን ገለጥኩ ፡ለማመን በሚከብድ ሁኔታ ፡ባለጩቤው የአቤል ቅጥረኛ መሬት ወድቋል ፡በሱ ፈንታ ሌላ ሰው ወፍራም ዱላ ይዞ ወደኔ አጎንብሶ እየነካካኝ ቁና ቁና ሲተነፍስ አየው ፡ ሰውዬው ከወደቀው ሰው የሞባይል ስልኩን ወሰዱና ፊቴላይ አበሩብኝ እና "ልጄ የኔ ልጅ ናቲ ደና ነህ ደርሼልሃለው ለትንሽ ነው እኮ የቀደሙኝ  አብሬህ መሮጥ ባለመቻሌ ነው ወይኔ "አሉ ።አወቅኳቸው ቤታችን የሚመጡት ሽማግሌ አቶ መብራቱ ። በጣም ተደነቅኩ በዚ ሰአት እሳቸውእዚ ምን ይሰራሉ ።እጃቸውን ሰጡኝ እጃቸውን ለመያዝ ሞከርኩ አቅም አጣው "የኔ ልጅ ለእናትህ ስትል በርታ እባክህ "ብለው እጄን ይዘው ሊያቆሙኝ ታገሉ ፡ እናም ተሳክቶላቸው አነሱኝ ፡እሳቸው እራሳቸው ቆፍጠን ብለዋል እንዲ ጠንካራ አይመስሉም ነበር ፡ እኔን እንደምንም ወደ እራሴ እንድመለስ ጥረት አደረጉ ፡ ብዥ ቢልብኝም እራሴን ችዬ ቆምኩ ፡
"መራመድ የምትችል ይመስልሃል "አሉኝ
"እእኔጃ እየዞረብኝ ነው"አልኳቸው
"እኔን ለኔ ይዙርብኝ ልጄ "አሉኝና በዱላ ያጋደሙትን ቅጥረኛ ጎንበስ ብለው በፊትለፊቱ ገለቀጡት እናም የለበሰውን ሸሚዝ ይዞት በነበረው ስለት ቀደው ካወለቁት በዋላ ጭንቅላቴን ጥምጥም አድርገው አሰሩኝ እንዲ ካደረጉልኝ በዋላ ጠንከር አልኩ ከአፌ የሚወርደው ደምም ቀንሷል ፡
"አሁን መጠንከር አለብህ ወንጀለኛውን ፊትለፊት ለማጋፈጥ ፡መጎበዝ አለብህ ፡ይህንን የማይረባ ነብሰገዳይ ፡የምንደብቅበት ቦታ ብናገኝ ጥሩ ነበር  ምክንያቱም በወንድምህ ላይ የሚመሰክረው ብቸኛው ተባባሪ ነው "አሉኝ ይሄንን ስሰማ ለማመን ከበደኝ እሳቸው ወንድሜ እንዳለበት በምን አወቁ ።አፍጥጬ ሳያቸው
"ይገባኛል ደና ስትሆን ለጥያቄዎችህ ሁሉ መልሱን እሰጥሃለው ፡አሁን ግን ይህ ልጅ ከመንቃቱ በፊት ወስደን የምናቆይበት ቦታ ቢኖር ጥሩ ነበር "አሉኝ
"እእሺ ወወደቤት ይይዘነው እንሂድ "አልኳቸው እንደምንም ቃላቶቼን እየጎተትኩ ፡በዛላይ መንፈሴ የሌለ ነው ስብር ያለው ፡
"እንዴ ቤት እናንተ ጋር "አሉኝ በመጠራጠር
"አዎ"አልኳቸው እሳቸው እንዳሉት ልጁ እንዲያመልጠኝ አልፈለኩም ፡ በጭራሽ አቅም አጥቼ እንጂ እዚው ቦጫጭቄ ብጥለው እወድ ነበር ነገር ግን ሰውነቴ ሁሉ ዝሏል ብዙ ደም ሳይፈሰኝ አልቀረም
"ግን እንዴት "አሉኝ
"በመጀመሪያ እኔ ወደ ቤት እሄዳለው እርሶ ከዋላዋላ ተከተሉኝ ምን አልባት ሊፈልጉኝ ወጣ ካሉ ለመጠንቀቅ ነው በር አካባቢ ማንም ከሌለ ወደጊቢ ይዘነው ገብተን ሰርቢስ ቤት እንቆልፍበታለን "አልኳቸው  በአሳቤ ተስማሙ እና ገዳዬን አንስተው እየጎተቱ መራመድ ጀመሩ ፡የጥንካሬ አቸው ሁኔታ አስገረመኝ ፡ ገዳዬን የመቱበት ዱላ ምንኛ አይለኛ እንደሆነ ያስታውቃል እኔ ተደግፌበት እየሄድኩ ነው ከባድ ነው እሱም እንደኔ ደሙ እየወረደ ነው ፡ ቤት አካባቢ ስንደርስ ገዳዬ ነቃ ፡እናም ሽማግሌውን ታገላቸው ፡እሳቸውም የዋዛ አይደሉም ዝም የማይል ከሆነ ጉሮሮውን እንደሚበጥሱለት ተናገሩ ድምፃቸው እንኳን ለሱ ለኔም አስፈራኝ ፡ ፀጥ አለ ጩቤውን ጎኑላይ ሻጥ እንዳደረጉት"ምንም አይነት ድምፅ ሳታሰማ ተንቀሳቀስ ፡ቀጥል ፡አለበለዚያ ያው ልጄን ታውቀዋለህ አሁን ጠንከር ብሎ ቆሟል እድሜለኔ በል ቅድም ገና መሬት ሰትወድቅ ተነስቶ ይገልህ ነበር "አሉት ወደኔ እያሳዩት ፡አይኑ ወደ እኔ ተቁለጨለጩ ፡ፈራኝ ፡ የጊቢያችን በርላይ ደርሰን ቆም አልን ማንም አልወጣም ፡ ደስ አለኝ ለነገሩ አቤል አንድ ነገር ፈጥሮ ነው እንዳይወጡ ያደረጋቸው ፡ይሄ ከይሲ ልቤ የመጨረሻ ጠላው ፡ለሱ የነበረኝ ነገር እንዳለ ተቆርጦ ሲወድቅ ተሰማኝ ።ጊቢ ገቡ ተን በቀስታ ከዚበፊት አቤልን ካሰርኩበት ሰርፒስ ቤት አስገባነው ከነ ማስጠንቀቂያው ።አርፎ ከተቀመጠ ከሱጋር ምንም ፀብ እንደማይኖረኝ ነገርኩት ፡ በፍርሃት አንገቱን ወዘወዘ ፡።
ከዛ ወደ ትልቁ ቤት ከሽማግሌው ጋር ሄድን በመጀመሪያ ሽማግሌው በሩን ሲያንኳኩ
"ጭራሽ ታንኳኳለህ እንዲ አስጨንቀኽኝ ናግባ አሁን ሆሆ"አለች እናቴ ሽማግሌው
"እኔ ነኝ "ብለው ሲገቡ
"ምን እርሶ እንዴት ገቡ ቁልፍ ከየት አመጡ"በጭንቀት ተናግራ ሳጨርስ
"አንተ ለማኝ በዚ ሰአት ደሞ ምን ትሰራለህ "አለ አቤል በድንፋታ
"እኔም አለው እናቴ "ብዬ በደም የተበከለ ሰውነቴን ይዤ ስገባ እናቴ ኡኡ ታዋን አቀለጠችው ደግነሽም ተከተለች ባዩሽም አልቀረች ። ሽማግሌው ሰው እንዳይሰማ እያሉ ተከላከሏቸው እንደምንም እንዲረጋጉ አድርገው ይልቅ ደሙን እንጠበው ።አሉ እናቴ ዱርዬዎች ናቸው ልጄን ያጠቁት ብላ ሽማግሌውን በጥያቄ አጣደፈች እሳቸው መልሰሰ ከመስጠት ይልቅ አቤል ላይ በቁጣ እንዳፈጠጡ ቀሩ አቤል እኔን በማየቱ እራሱን ሊስት ምንም አልቀረውም ፡ ..............

Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.1K viewsTsiyon Beyene, 03:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 21:00:01 "ይቅርታ ዶክተር ፋሲል እናቷ ልትፈቅድልን አልቻለችም"
በሆስፒታል አልጋ እየገፉኝ እየወሰዱኝ እያለ አይኔን ለመግለጥ ሞከርኩ እናቴን በጭላንጭል አየሁዋት የአልጋውን ጠርዝ ይዛ በለቅሶ እየተከተለችን ነው የሆነ ክፍል አስገቡኝና በሩን ዘጉት ለመጨረሻ ጊዜ የሰማሁት የእናቴ ድምፅ

"ልጄን አድኑልኝ.....ልጄን"

እርስ በርሳቸው ሲነጋገሩ ይሰማኛል
"ከሁለት አንዳቸው አይተርፉም ካልፈጠንን ግን ልጅቷንም በሆዷ ያለውንም ነው የምናጣው... ፍጠኑ.... "

በጭንቅ ግራ ቀኝ ስወዛወዝ ከፊት ለፊቴ ያለው የተሳፋሪ ወንበር ላይ ተደፋሁ። ግንባሬን የመታኝ ወንበር ካለሁበት አስፈሪ ህልም ቀሰቀሰኝ.....ተመስገን በህይወት አለሁ።

እጄን ሰድጄ ሆዴን ዳበስኩት አሁንም ያቺ ትንሽዬ እብጠት ነው ያለችው።

ረዳቱ ጮክ ብሎ"ለምሳ ሀያ ደቂቃ ከዚህ በላይ መቆዬት አይቻልም" እለ። እናቴን ዞር ብዬ ሳያት ወደኋላ ለጠጥ ብላ ተኝታለች። እሷም እንደኔ አስፈሪ ህልም እያየች ይሆን? ትከሻዋን ይዤ ወዝወዝ ሳደርጋት ነቃች።

አውቶብሳችን ሲቆም ወርደን ምሳ በልተን እና የሚያስፈልገንን ሸማምተን ተመለስን። ከኔ በላይ እናቴ ፊት ላይ የማየው ተስፋ እና ደስታ አቅሌን ሊያስተኝ ደርሷል። ወንበሩ ላይ እንደተቀመጠን አንገቴን ወደሷ ስባ እቅፍ አደረገችኝ..... ልብ ሰርስሮ የሚገባውን የእናት ጠረኗን አሸተትኩት። "አሁን ማን ሊያቆመኝ ይችላል" አልኩ በውስጤ.... ከፊቴ ደጀን ሆና ወኔ ብርታት የምትሰጠኝ.... ሀዘኔ ከኔ በላይ የሚያሳዝናት በደስታዬ የምትደሰት ችግሮቼን ቀድማ የምትጋፈጥልኝ እናት እያለችኝ..... እኮ ማን?

፧፧፧፧፧

ከወራት በኋላ

አጎቴ ያሰብኩትን ያክል አልጨከነብንም። የራሳችንን ቤት ተከራይተን እስክንወጣ አንድ ክፍል ቤትና ምግባችንን ሰጥቶን ነበር። እኛም ብዙ ጊዜ ሳናስቸግረው ገጠር ያለውን የአባቴ ቤተሰብ ማለትም የአያቶቼ ውርስ የሆነውን የእርሻ መሬት ብዙ አመት መከራዬት ለፈለገ ሰው አከራየንውና ጥሩ ገንዘብ አገኘን። እማዬ ጊዜ ሳታጠፋ ነው በብሩ ከጀበና ቡና ጋር ጠዋት ቂንጬ ጨጨብሳ እና አንዳንድ ለቁርስ የሚሆኑ ምግቦችን ማታ ደግሞ ድንች እየቀቀለች መሸጥ የጀመረችው። በጥቂት ጊዜ ውስጥ ብዙ ደንበኞችን ማፍራት ቻለች። ስራው ትርፋማ እየሆነ ሲመጣ የራሳችን ቤት ተከራይተን ከአጎቴ ቤት በሰላም ወጣን።

፧፧፧፧፧፧
በቀጫጫ እና ባልጠነከረ ሰውነቴ ላይ የሆዴ ትልቅነት ሲታይ ልክ በህልሜ እንዳየሁት ያስፈራል "አምላክ ሆይ ህልሜን እውን አታድርግብኝ" በልቤ ፀለይኩ

በምጥ መውለድ አትችልም ተብሎ ስለተወሰነ በቀዶ ጥገና ልጄን ወለድኩ። እነሱ ባይሉም እንኳን በምጥ አልወልድም ብዬ ኡ ኡ ነበር የምለው። ህልሜማ እውን አይሆንም

ሆዴ ውስጥ እያለ እንደ እንቅፋት እያሰብኩ እጠላው የነበረን ልጅ አምጥተው ክንዴ ላይ ሲያስቀምጡልኝ ስፍስፍ የሚያደርግ ስሜት ተሰማኝ። ሴት ልጅ ናት እናቴ ሀዘናችንን የምንረሳብሽ ስትል ስሟን ምናሴ አለቻት። ልጄ ትንሽ ጠንከር ስትልልኝ ትምህርቴን ካቆምኩበት ሰባተኛ ክፍል ቀጠልኩ። ቀናት ሳምንታትን ሳምንታት ወራትን ወራትም አመታትን እየወለዱ የአስራ ሁለተኛ ክፍል(የዩንቨርስቲ መግቢያ) ፈተናን ተፈተንኩ።

ልጄም ልክ እንደ እኔ እሳት የላሰች ጎበዝ ተማሪ ሆናልኛለች። ከሷ ጋር ስሆን ቦርቄ ያልጨረስኩት ልጅነቴ ይመጣብኛል እና ሁሌም ቢሆን ከልጄ ጋር ልጅ ነኝ። ያለፈኝን ህይወት በሷ እየካስኩ እንዳለሁ ይሰማኛል።

ነሀሴ መጨረሻ ላይ ውጤት መጣ ተባለና አየን ጥሩ ውጤት ነው ያመጣሁት ግን ሩቅ ሀገር ነው የመደቡኝ ጎንደር ዩንቨርስቲ በምፈልገው ዲፓርትመንት(ህክምና)

እናቴን እና ልጄን ትቼ እንዴት ችዬ ይህን ያክል እርቃለሁ..

ይቀጥላል...
5.0K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 21:00:01 #ህያብ


#ክፍል_ሶስት


#ድርስት_ኤርሚ

እና ሁሉም ነገር እንደዚህ ሊቀጥል ነው? አይሆንም! እናቴም እኔም አንገታችንን ከምንደፋ የሆነ ሀሳብ በውስጤ መጣልኝ። እንደማደርገው እርግጠኛ ሆንኩ....
ቤት እንደደረስን ቁጭ አድርጋ የምክር ናዳ አወረደችብኝ ግን አንዱንም ከልቤ ሆኜ አልሰማኋትም..... እንዴት እንደማደርገው እቅድ እያወጣሁ ነበር።

ሁሌም ማክሰኞ ቀን እናቴ ገበያ ትሄዳለች። ያሰብኩትን ለማድረግ ከዚህ ቀን ውጪ የተመቸ እንደሌለ አውቃለሁ ስለዚህ ማክሰኞን መጠበቅ አለብኝ።
....
የምጥ ቀን እሁድ አለፈና ሰኞ መጣ.... ብርድ ልብሴን ክንብንብ ብዬ የተኛሁ መሰልኩ። እማዬ ቤት ውስጥ ውዲህ ወዲያ ስትል እንቅስቃሴዋ ይሰማኛል። አጠገቤ መጣችና
"አንቺ ሚጣ.... ሚጣዬ..... ሚጣ" ብላ ጠራችኝ። ባልሰማ ዝም ብያት የተኛሁ እንዲመስል ጣርኩ ምክንያቱም ከዚህ በኋላ ትምህርት ቤት መሄድ በጓደኞቼ እና በሌሎች ተማሪዎች መዋረድ አልፈልግም።

እኛ ላለንበት ማህበረሰብ ይሄ ከባድ ነገር ነው። መደፈሬን የሚያውቀው ሳይቀር
"የወይንሸት ልጅ ዲቃላ አረገዘች.... ድሮም ሴት ያሳደገው" ብለው እኔን ብቻ ሳይሆን ብርቱዋን እናቴንም ጭምር ነው የሚሰብሩብኝ

"አንቺ ሚጣ... ተነሽ እንቅልፍ እንዳልወሰደሽ አውቃለሁ..." አለችኝ። ምንም ማምለጫ የለኝም ፊቴን ቀስ ብዬ ገለጥኩና አጠገቤ የቆመችውን ድንቅ ሴት ከታች ወደላይ አየኋት..... እምዬን.... እናቴን። ጎንበስ ብላ በስስት እያየችኝ ነው። ከተኛሁበት ቀና ብዬ ቁጭ እንዳልኩ አጠገቤ መጣችና ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ።

"ልጄ የኔ ስስት.... አለሜ እኮ አንቺ ብቻ ነሽ.... በዚህ እድሜሽ እንደዚ ስብር አትበይብኝ። ምን ያክል እንደሚያም ካንቺ በላይ ይገባኛል። ህመምሽ ካንቺ የበለጠ እኔን ያመኛል። ነገር ግን ቁጭ ብለን በእንባ እና ያለፈውን መራር ጊዜ በማሰብ ነጋችንን አናጨልመውም ልጄ ትማሪያለሽ ልክ እንደምትመኝው ዶክተር ትሆኛለሽ..."

"እማ እኔ ትምህርት ቤት አልሄድም" እንባዬ ከአይኔ ክልብስ አለ። እየተንሰቀሰኩ አለቅስ ጀመር።
"አይ እንግዲህ የምን ለቅሶ ነው" አለችኝ ቆጣ ብላ ይሄን ቁጣዋን አውቀዋለው ምናባሽ.... የታባሽ..... የሚባለው አይነት ቁጣ አይደለም። ቃሏ እና ፊቷ ላይ "መፍትሄ አለው" ከሚል መልዕክት ጋር ነው የምትናገረው። ለቅሶዬን አቁሜ የምትለውን ለመስማት ተመቻቸሁ።

"ልብ ብለሽ ስሚኝ የኔ ልጅ...."
በሚገባኝ ቋንቋ አስረዳችኝ።

ሙሉ ለሙሉ ነው ሀሳቤን ያስቀየረችኝ የኔ እቅድ የነበረው ገበያ ስትሄድልኝ የገዛሁትን የአይጥ መርዝ ጠጥቼ ይህችን አለም መሰናበት ነበር። ንቁዋ እናቴ ግን እቅዴን ሁሉ ቀድማ ደረሰችበት። አዲሱን እቅዷን ከነገረችኝ በኋላ እንዲህ አለችኝ።

" ያቀድሽውን ሁሉ ደርሼበታለሁ ሚጣ.... መርዝ ልትጠጭ ነበር አይደል" ክው ብዬ ነው የደነገጥኩት
........

"እንዴት ሆኖ ከኔና ባለሱቁ ውጪ እኮ መግዛቴን የሚያውቅ አልነበረም" አልኳት ምን ያክል እንደምትደነግጥና ልታዝንብኝ እንደምትችል እያሰብኩ... ፊት ለፊቴ ያለችው ሴት ግን ፍፁም መረጋጋት ነው የሚታይባት

"ባለሱቁ ባንዴ ሶስት ስትገዢው ተጠራጥሮ ነው። በመንገድ ሳልፍ ጠርቶ የነገረኝ አልዋሽሽም እንደሰማሁ ምድር ነበር የከዳችኝ... ቶሎ ብዬ ቤት ሰመጣ በረንዳ ቁጭ ብለሽ አገኘሁሽ ያኔ ወደቤት ገብቼ ከደበቅሽበት ፈልጌ አገኘሁትና ወሰድኩት....."

"ይቅርታ እማዬ ሁሉም ነገር ጨለመብኝ ከኔ ብሶ አንቺም አንገትሽን ደፋሽ..."

"ይገባኛል ሚጣዬ አሁን ስለ እቅዱ ምን ትያለሽ...." ብላ ሀሳቤን ጠየቀችኝ። እናቴ ለኔ እንዲህ ናት አስፈላጊ ያለችው ነገር ላይ ምን ታስቢያለሽ ብላ ታማክረኛለች። ምንም እንኳን ከልቤ ባልሰማት............
..........ወይም እሷ እያወራች ለጨዋታ ጓደኞቼ ሲጠሩኝ ሳላስጨርሳት ሮጬ ብሄድ..........
....... ወይም ደግሞ የልጅ ሀሳቤን ነግሪያት ሆዷን ይዛ ፍርፍር ብላ ብትስቅ... እናቴ ልጅ ናት ብላ ልትነግረኝ እንደሚገባ ያሰበችውን ለኔ ከመንገር ወደ ኋላ አትልም። በሀሳብ ጭልጥ ብዬ ስሄድባት

" ምን ትያለሽ እያልኩሽ ነው ሚጣዬ" አለችኝ ዘልዬ ጥምጥም አልኩባትና

"እጅግ በጣም ምርጥ ሀሳብ ነው ቶሎ ብለን እናድርገው አልኳት

"ኦ ኦ ልጄ እስከምትወልጂ ድረስ እንደፈለግሽ መዝለልና መንፈራገጥ የለም። በይ አሁን ተነሽ ቁርስ እንብላና ያልኩሽን እናደርጋለን።

ለብቻዬ ሌላ ጀንበር የወጣችልኝ መሰለኝ ...... ብሩህ ተስፋ.....

የተሳፈርንበትን አውቶብስ መስኮት በትንሹ ከፈትኩት፤ በመስኮቱ የሚገባው ቀዝቃዛ አየር ከነፋስ ጋር ተቀላቅሎ በጆሮዬ ላይ ቢያፏጭም ምቾት አልነሳኝም። በመስታወት ውስጥ አሻግሬ ሰማዩን ስመለከት ፀሀይ ደም የተነከረ ሸማ መስላ ከወደ ምስራቅ ብቅ ማለት ጀምራለች። በፎቶግራፍ መቅረት ያለበት ድንቅ የተፈጥሮ ውበት። አይኔን እድማሱ ላይ ሰክቼ በራሴ ከቀናት በፊት የነበረውን ነገር ማስታወስ ጀመርኩኝ።
................

ልክ እንደዛ ስብር እንክትክት ብዬ በነበረበት ሰዓት...... ራሴን ላጠፋ ጫፍ በደረስኩበት ሰዓት..... ሀሳቤን አስቀይሮ በደስታ ያስፈነጠዘኝ የእናቴ እቅድ ይህ ነበር።

" ሁሉም ሰው የሚያውቀው የአባትሽ ወንድም አጎትሽ ያለው አዲስ አበባ እንደሆነ......." አላስጨረስኳትም

"አዎ ግን የሱ እዛ መሆን ለምን ይጠቅመናል"

"እዛ የምንሄደው እሱ አንቺን ለማስተማር ጠርቶሽ እኔ ደግሞ ካንቺ አልለይም ብዬ ነው አሉ.... ይህን ለሚጠይቀን ሁሉ እንነግራለን"

"እሺ ግን መቼም አጎቴ ጋ እንሂድ አትይኝም አይደል" አይን አይኗን እያየሁ ጠየኳት

"ለጊዜው የምናርፈው እሱ ጋር ነው ትላንትና ማታ ሱቅ ሄጄ ደውዬለት ነበር ባይዋጥለትም ሁሉንም በዝርዝር ነግሬዋለሁ"

"ምን እያልሽ ነው እማ... የወንድሜ ልጅ ብሎ አንድ ቀን እንኳን ዞር ብሎ ላላየኝ.... አንቺን ሳይቀር ወንድሙን እንደገደልሽበት ለሚቆጥረው.... ለሚጠላን ሰው ነገርሽው"
አልኳት ያልጠበኩት ነገር ነው

"አዎ እኔም አንቺም ይህን ተፅዕኖ መቋቋም አንችልም። ይሁን ብንል እንኳን የኔ ችግር የለውም አንቺ ግን ይከብድሻል ለህክምና ክትትሉም ሆነ ለትምህርትሽ አዲስ አበባ ይሻልሻል...."

"ግን እዛ ሄደንስ ምን ሰርተን እንዴት ሆነን ልንኖር..." ግራ ግብት አለኝ

" እሱ እያሳስብሽ እኔ እናትሽ ላንቺ አላንስም አንቺንም ልጅሽንም ማኖር አይከብደኝም ዳገት ወጥቼም ሆነ ቁልቁለት ወርጄ ህልምሽን እንድታሳኪ አደርግሻለሁ። ታዲያ ለዚህ ያንቺ ጥንካሬ ወሳኝ ነው። በይ አሁን ለጠየቀሽ ሁሉ ካልኩት ውጪ እንዳትናገሪ ነገሮችን ላስተካክልና በጥቂት ቀን ውስጥ እንሄዳለን።

ከሀሳቤ ስመለስ እናቴን ዞር ብዬ አየኋት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ናት።
መስኮቱን ተደግፌ አይኔን አድማሱ ላይ ተከልኩ

፧፧
ከኔ አካል ቅጥነት ጋር ሲነፃፀር ሆዴ ትልቅ ሆኖ ላየው ይሰቀጥጣል። ምጤ መቶ ሆስፒታል ገብቻለሁ
"አይዞሽ በርቺ..... ግፊ.... አይዞሽ እንደሱ..... በርቺ..... ግፊ" ብዙ ጊዜ ደጋግመው ቢሉኝም ያለኝን አቅም አሟጥጬ ባምጥም ልጄ ሊወለድ አልቻለም። እኔ ግን እቅት ድክም አለኝ የሚሉት በሰመመን ይሰማኛል...

"የልብ ምቷ በጣም እየወረደ ነው ባስቸኳይ ዶክተር ፋሲልን ጥሪ" ልሞት ነው ማለት ነው። የሰዎች መሯሯጥ ድምፅ ተሰማኝ ትንሽ ቆየት ብሎ

"በአስቸኳይ ወደ ቀዶ ጥገና ክፍል አስገቧት ይህቺን የምታክል ትንሽ ልጅ እንዴት በምጥ እንድትወልድ ታደርጋላችሁ..."
5.0K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 21:40:24 የእናቴ ልጅ
ክፍል ሃያ አራት

አንዳንድ ጊዜ አለ ልብህ አስቀድሞ አንዳች አደጋ እንደመጣ እና አስቀድመህ እንድትጠነቀቅ  የሚያሳስብህ ጊዜ ። ጭንቅ ጭንቅ ይልሃል፣ ፍርሃት ይወርሃል፣ ያቁነጠንጥሃል ፣ ብቻ እንዲ አይነት አጋጣሚ አለ ።
አቤል ከወጣ ጀምሮ አይምሮዬ አላረፈም ማን ይሆን የጠራው ፣ምን ሊፈጠር ይሆን እያልኩ ማሰቤን አልተውኩም ። እናቴ ከነደግነሽ ጋር እየተጫወተች አልፎ አልፎ ወደኔ አየት ታደርጋለች  በግንባሬ ወደ ውጭ ባሳያትም ኮስተር እያለች አርፈህ ተቀመጥ አይነት ምልክት ትሰጠኛለች ፡  ባዩሽ እላዩዋላይ እንደተጣበቀች እንቅልፍ የጣላትን ማማን ፀጉር እያሻሸች በደግነሽ ወሬ ተመስጣ ታዳምጣለች ፡  እኔ ግን የጫወታቸው እርዕስ እንኳ ምን እንደው በቅጡ አላዳመጥኩም ፡ ከረጅም ቆይታ በዋላ ስልኬ እሪ ብላ ስትጮህ እንዴት ከቂጤ ብድግ እንዳልኩ ፡እንዲ ደንግጬ አላውቅም ። እናቴ የኔ ድንጋጤ ተጋብቶባት
"ውይ ናቲዬ ልጄ እኔ ልደንግጥ "አለች የሷ ድንጋጤ እራሱ እያሳበቀባት ። ስልኬን ከጩኽቷ ለመገላገል አነሳዋት "ሃሉ "አልኩኝ ። በስልኩ ውስጥ የሚንሾካሸክ ድምፅ መጣ
"ናታኒየም ነህ"አለኝ
"አዎ ነኝ ማን ልበል "አልኩት የልቤን ምት ለመቆጣጠር እየሞከርኩ
"እኔን አታውቀኝም እባክህ መምጣት ትችላለህ ወንድምህን ይዘውታል  "አለኝ ። አይኖቼ ፈጠጡ
"መጣው ስልኩን እንዳትዘጋው "አልኩት ፡የማላውቀውን ሰው ። ይህን ያደረኩት እናቴን ላለማስጨነቅ ነበር  ሁሉም ወደኔ ሲያፈጡ ።
"ተረጋጉ የአቤልን መሄድ ድንገት የሰማ ጓደኛው ነው እኔንም ስለሚያውቀኝ ፡ወቀሳ ሊያቀርብልኝ ነው ለማንኛውም መጣው በሩ ላይ እየጠበቀኝ ነው እንደውም አቤልን በዛውም ይዘነው እንመለሳለን አታስቡ "ብያቸው ወጣው እናቴ ለማመን የተቸገረች ይመስላል በቀላሉ የምትሸወድአደለችም በእርግጥ ።
ከግቢ እንደወጣው ያልተዘጋውን ስልኬን ወደጆሮዬ አስጠግቼ "እሺ ማነህ አንተ ተናገር አሁን ከቤት ወጥቻለው  በግልፅ ምንድነው የሆነው "አልኩት ማነው እንዲ የተዳፈረኝ እኔ እኮ ናታኒየም ግዛው ነኝ ፡እንዴት ወንድሜን ይይዙታል ለዛውም በዚ ቀን እንዴት በንዴት ጦፍኩ
"እኔ ማንነታቸውን አላወቅኩም እኔና አቤል ተገናኝተን ነበር ሰላም ብሎኝ እንዳለፈ ጩኽት ሰማው ወደዋላዬ ስመለስ ሦስት ሰዎች ናቸው ይዘው ሲያዋክቡት አየው  በጣም ስለደነገጥኩ ጥጌን ይዤ ዝም አልኩ "አለ የሚያወራውን ለመመርመር ጊዜ አልነበረኝም እንዳለ ጭንቅላቴ ወንድሜጋር ነው አንድ ነገር ከመሆኑ በፊት ልደርስለት ብቻ ነው ያሰብኩት
"እና ወዴት ነው የወሰዱት በጋሽ ከድር ሱቅ በኩል ወደታች እየገፈታተሩ ነው የወሰዱት በፍቃደኝነት እየሄደ ስላልሆነ ልትደርስባቸው ትችላለህ ፍጠን እኔም  እዛው አካባቢ ነኝ "አለኝ ።ልቤ ፍጠን በሚል ምቱን ጨመረ ደሞ ለክፋቱ የመንገድ መብራት ጠፍቷል ፡ እየተወለካከፍኩ እሮጥኩ  ። ስሮጥ ከዋላዬ ሰው የተከተለኝ መሰለኝ እና ለአፍታ ዞር አልኩ ስዞር ቀስብሎ የሚራመድ ተለቅያለሰው ያየው መሰለኝ ።ችላ ብያቸው እሮጥኩ በስልክ የተጠቆምኩቀት አካባቢ ደረስኩ ጨለማው ከማየሉ ውጪ ምንም ነገር አይታይም  ። እጠብቅሃለው ያለው በስልክ ያናገረኝም ሰው የለም ፡ ነር ግን በጨለማው ውስጥ ዝምብዬ እሮጥኩ ወንድሜን በደስታው ቀን ምን ሊያደርጉብኝ ነው ። እያልኩ  ብዙ ከደከምኩ በዋላ ለምን ስልክ አልደውልም ብዬ ስልኬን ከኪሴ ለማውጣት ቆም አልኩ ። በዛው ቅስበት አንዳች ነገር አናቴ ላይ አረፈ ምቱ አይለኛ ስለነቀረ መቋቋም አልቻልኩም ተንገዳግጄ መሬት ላይ አረፍኩ ፡ ከተኛውበት ሆኜ ለማየት ሞከርኩ ፡ሁለት ወጣቶች ናቸው በግልፅ አልታዩኝም ፡ ጠጋ ብለው ። ካዩኝ በዋላ በቃ በትክክል መጨረስህን እርግጠኛ ሆነህ ደውልልኝ እኔ መሄድ አለብኝ ፡ አለው አንደኛው እየተንሾካሸከ ቢሆንም ድምፁ አልጠፋኝም ፡ መናገር ግን አቃተኝ ዕንባዬ ወረደ አለቀስኩ ከምር .......


,ደራሲ Unknown


ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.3K viewsTsiyon Beyene, 18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 21:00:02 #ህያብ


#ክፍል_ሁለት


#ድርሰት_ኤርሚ

"አቤት ህያብ" አለኝ ዶክተሩ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ካየኝ በኋላ

'ማስወረድ እፈልጋለሁ' አልኩት

"ምን" የሚል ድምፅ ሰምቼ ስዞር እናቴ ከኋላዬ ቆማለች።

"ምንድነው የምታወሪው እ... ማን ፈቅዶልሽ ነው የምታስወርጂው.... ምን ስልጣንስ ኖሮሽ ነው የእግዜርን ፍጡር የምትገይው......" ወደኔ የበለጠ እየተጠጋች የቁጣ ናዳ አወረደችብኝ። እናቴ በአካባቢው እያለች ከአንደበቴ ይህንን ቃል ማውጣት አልነበረብኝም።
.......
ከውርጃ ጋር ተያይዞ በጣም መጥፎ ትዝታ አለባት። ልጅ እያለሁ ትርሲት የምትባል የዘመዳችን ልጅ አብራን ትኖር ነበር። ታናሽም ታላቅም ስለሌለኝ እንደ እህቴ ነበር የማያት እሷም ሲበዛ ታቀብጠኝ ነበር። በትምህርቷ በጣም ጎበዝ ነበረች። ታዲያ ከጊዜ በኋላ ውጤቷ እያሽቆለቆለ መጣ። መምህሮቿ ቤታችን ድረስ መጥተው እናቴን አናገሯት እማዬ ደነገጠች..... ትርሱ ከሄደችበት ስትመለስ ቁጭ አድርጋ አወራቻት መከረቻት ግን ለውጥ አልነበረውም የባሰ ትምህርት ቤት እያለች ሌላ ቦታ እንደምትውል ተደረሰባት.... እናቴ ይህን ስትሰማ በጣም ተቆጣቻት።
......
የሆነኛው ቀን ላይ መልዕክተኛ መጥቶ ትርሲት ታማ ሆስፒታል መግባቷን ነገሩን እናቴ እየሮጠች ሄደች። ወደቤት ይዛ የተመለሰችው ግን አስከሬን ነበር።
.......
ትንሽ ካደኩ በኋላ እናቴን ጠይቄ እንደተረዳሁት ከሆነ ትርሲት ከአንድ የከተማችን ነጋዴ ጋር የፍቅር ግንኙነት ትጀምራለች። ሁሉ ነገሯን ትታ ነበር ክንፍ ያለችለት .... ግንኙነታቸው በሱ ጎትጓችነት ወደ አልጋ ላይ ጨዋታ ይሸጋገራል.... በዚህ መሀልም ትርሲት አረገዘች። ማርገዟን ስታውቅ ሁሉንም ነገር ዘርዝራ ለጓደኛዋ ከነገረቻት በኋላ ምክሯን ጠየቀቻት
"ስለሚወድሽ ያገባሻል እንዳረገዝሽለት ንገሪው" አለቻት።

በማግስቱ ወደ ፊት የሚኖራቸውን የደስታ ህይወት እያሰበች በፈገግታ የደመቀ ፊቷን ይዛ ወደ ነጋዴው ፍቅረኛዋ ጋ ሄደች። እንዳረገዘችለት ስትነግረው

" ከማናባሽ አርግዘሽ መጥተሽ ነው አረገዝኩልህ የምትይው" አላት።
ከሱ ውጪ ወንድ እንደማታውቅ ያውቃል ግን ሊሰማት አልፈለገም። ትርሲት ለሱ የሆነ ሰዓት ላይ ተጠቅሞባት እንደሚጥላት እቃ ነበረች።
አይንሽን ማዬት አልፈልግም ከነ ዲቃላሽ ገደል ግቢ ብሎ አባረራት..... ለሳምንታት ተስፋ ሳይቆርጡ እሷም ጓደኛዋም ለመኑት.... ጭራሽ አይኑን ወደ ጓደኛዋ ማዞር ጀመረ ነገሩ ሲገባቸው እሱን እርግፍ አድርገው ትተው ሌላ መፍትሄ መፈለግ ጀመሩ እናም ማስወረድ በሚለው ተስማሙ። የትርሲት ጓደኛ ቤተሰቦቿ ወደገጠሩ ስለሚርቁ ቤት ተከራይተውላት ነው ትምህርቷን የምትማረው.... እናም ለእቅዳቸው ተስማሚ የሷ ቤት ስለሆነ ትርሲት እማዬን ለፈተና ለማጥናት ጓደኛዬ ጋር ልደር ብላ አስፈቀደቻት። እማዬም ምናልባት አብረው ሲያጠኑ ውጤቷ ይሻሻላል ብላ ስላሰበች አልተቃወመቻትም።
.......
ጓደኛዋ ቤተሰቦቿ ካሉበት ገጠር ለውርጃ ይጠቀሙታል ያለችውን መድኃኒት ሰጠቻት እናም ግጥም አድርጋ ጠጣችው። ለትንሽ ጊዜ ሁሉም ሰላም ነበር ሌሊት ላይ ግን ከበድ ባለ ሁኔታ ደም ይፈሳት ጀመር። ልጁ እየወረደ ነው ብለው ስላሰቡ የሚሆነውን በዝምታ ጠበቁ..... ከሰአታት በኋላ ግን ትርሲት እየደከመች መጣች። ጓደኛዋ የአከራዮቿን ቤት አንኳኩታ እርዳታ ጠየቀች እናም ወደ ሆስፒታል ተወሰደች ግን አርፍደው ነበር። ትርሲት ብዙም ሳትቆይ አሸለበች ።

አይደለም እኔ ልጇ ማንም ላሶርድ ቢላት ኡ ኡ እንደምትል አላጣሁትም ግን.......

"እማዬ በዘመናዊ መንገድ እኮ ነው በሀኪም" አልኳት

"አይሆንም ብያለሁ አይሆንም..." ጮኸችብኝ.... ንግግራችንን ሲሰማ የነበረው ዶክተር ተነስቶ አጠገባችን መጣና አረጋግቶ ወንበር ላይ ካስቀመጠን በኋላ

"ህያብ ከማስወረድ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም ብለሽ ታስቢያለሽ" አለኝ።

"አዎ ዶክተር መማር እፈልጋለሁ በዛ ላይ የሰው መሳቂያ ነው የምሆነው.... ማንም ተደፍራ ወለደች የሚለኝ የለም...." ንግግሬን ሳግ አቋረጠኝ

"እርሶስ ወይዘሮ ወይንሸት ምን ይላሉ"

"እኔ ቆሜ እያለሁ ልጄን ለሞት አሳልፌ አልሰጣትም በፍፁም አይሆንም" እርግጠኝነት በተሞላበት መንፈስ ተናገረች።
......
"እኔም የእናንተን ሀሳብ ልስማ ብዬ እንጂ ፅንሱ ሶስት ወር አልፎታል በዛ ላይ ልጅ ነሽ ከማስወረዱ ብትወልጂው ይሻላል ለሱም ቢሆን እድሜሽ ገና ስለሆነ ያላቋረጠ የህክምና ድጋፍ ያስፈልግሻል......" ይሄን እና የመሳሰሉትን ሲያወራ እናቴ 'እህ' እያለች አንገቷን እየነቀነቀች ትሰማዋለች።

ትቻቸው በሀሳብ ነጎድኩ ከዛስ አልኩ ለራሴ...... ከዛስ ትምህርቴ ሊቀር..... የሰፈር ሰው መጠቋቆሚያ ልሆን...... ከዛስ እ...... የወደፊት እጣ ፋንታዬስ.... እዚሁ የተወለድኩበት ሀገር በናቴ እግር ተተክቼ ፓስቲ እና ጠላ ስሸጥ ልጄን ለማሳደግ ደፋ ቀና ስል በህሊናዬ ሳልኩ።
....
"አይሆንም" አልኩ ቃል አውጥቼ.... ያልኩት መልሶ አስደነገጠኝ

"ምኑ ነው የማይሆነው ሚጣዬ.... ዶክተር ያለውን ሰምተሻል አይደል እንደዛ እናደርጋ...." ዶክተር! ዶክተር ምንድነው ያለው?...... ምንም ይበል ምን አገባኝ። ዶክተር እኮ ህልሙ ይሁንም አይሁንም ዶክተር ሆኗል አይደል.... ደግሞ እሱ ምን አለበት በሰው ቁስል ላይ እንጨት መስደድ ለሱ ቀላል ነው.... "ውለጂው" አለ አይደል? መውለዴ የሚያሳጣኝ ነገር ግን ግድም አይሰጠው.... ይቺ የአስራ ሶስት አመት ልጅ ከምታስወርድ ትውለድ ሲል ይቺ የአስራ ሶስት አመቷ ህያብ ህልሟን ትቅበረው ማለቱ እንደሆነ አልገባውም።

''ወለድኩ ማለት ህልሜ ሁላ ይቀበራል" አልኩት የመጨረሻ እድሌን ልሞክር ብዬ

"አንቺ ከምትቀበሪ ህልምሽ ቢቀበር አይሻልም" አለችኝ እናቴ.... ምንም ሳልናገር ቢሮውን ለቅቄ ወጣሁና ወደቤት መንገድ ጀመርኩ እማዬ ከኋላዬ ደረሰችብኝ። ምንም ሳንነጋገር ጎን ለጎን ትንሽ ከሄድን በኋላ

"እስኪ ሚጣዬ ሆድሽን ሸፈን አድርጊው" ብላ የለበስኩትን ፎጣ ስባ ሆዴን አለበሰችው.....
..........
እና ሁሉም ነገር እንደዚህ ሊቀጥል ነው? አይሆንም! እናቴም እኔም አንገታችንን ከምንደፋ የሆነ ሀሳብ በውስጤ መጣልኝ። እንደማደርገው እርግጠኛ ሆንኩ.....

ይቀጥላል
4.9K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 20:35:06
ለፕሮፋይል የሚሆኑ ገራሚ ፎቶዎችን ለማግኘት JOIN አድርጉ

https://t.me/+UqU8zCoHqyw2NzQ0
4.0K viewspetelare Stay true, 17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 21:23:47 የእናቴ ልጅ
ክፍል ሃያ ሦስት

ወደ ጊቢ ስገባ ሸማግሌው የሚበሉትን ጨርሰው ውሃ ሲጠጡ አገኘዋቸው። እናቴም እነደግነሽም ወደውስጥ ገብተው ነበር ፡አቤል ብቻ በረንዳው ላይ ቁጭ ብሎ ሰውዬው አንዳች ነገር ያነሱ ይመስል ይከታተላቸዋል የአቤል ሁኔታ ገረመኝ አሁን እኚ ሽማግሌ ምኔን ይነኩኛል ብሎ ነው ጠምዶ የያዛቸው ለራሳቸው የያዙትን ብርጭቆ እንኳ በቅጡ ወደአፋቸው ለማድረስ የተቸገሩ ነው የሚመስሉት ።
  አቤልን ችላ ብዬ ወደ ሽማግሌው ተጠግቼ ቁጭ አልኩ ደንገጥ አሉ ምንም እንዳልተፈጠረ ሆኜ ፈገግ አልኩ እናም የሚንቀጠቀጠው እጃቸው ላይ ያለውን ብርጭቆ ተቀብዬ መሬት አስቀመጥኩት ።
"አአመሰግናለው ልልጄ "አሉኝ
"ኧረ አባት አይጨነቁ "አልኳቸው በተቀደደ ቲሸርታቸው ውስጥ የሚታሁኝ አጥንቶቻቸው የተሸበሸበው ቆዳቸው ብዙ ስቃዮችን እንዳሳለፉ ይናገራሉ
"እሺ ልጄ አሁን በልቼ ጨርሻለው ልሂድ መሰለኝ "አሉ
"አይ ቆይ ቆይ ትንሽ ከኔ ጋር ይጫወታሉ "አልኳቸው
"አይ ልጄ ስለምን ልንጫወት ነው"አሉ ፈራ ተባ ብለው
"እዚ በተደጋጋሚ ይመጣሉ እንዴ ሁሉም ሰው ያውቆሆታል ከኔ በቀር"አልኳቸው
"እእ አዎ አልፎ አልፎ ርሃብ ሲጠናብኝ እዚ እመጣለው እናትህ ደግ ሴት ናት "አሉ አዘን ብለው
"አዎ እናቴ ደግ ናት "አልኳቸው እንዳቀረቀሩ ዝም አሉ
"ስሞት ማነው "አልኳቸው
"አበራ አበራ አይሉ እባላለው "አሉ
"ደስ የሚል ስም ነው አበራ አይሉ ደስ ይላል"አልኳቸው ።ዝም አሉ በጣም የጨነቃቸው ይመስላሉ የበታችነት ስሜት ሳይሰማቸው አይቀርም
"አባት በማንኛውም ሰአት ወደዚ ቤት መምጣት ይችላሉ ምንም ነገር እንዳያሳስቦት ፡ ከፈለጉ ደሞ እርሶ እሺ ይበሉኝ እንጂ እዚ እኛጋር አትክልተኛ ሆነው እንዲሰሩ እናቴን ላሳምንሎት እችላለው "አልኳቸው ።ይሄን ስላቸው አሻግረው ወደ አቤል አየት አደረጉ
"ምነው አልፈለጉም "አልኳቸው
"አይ ይቅርብኝ ያለውበትን ሁኔታ ለምጄዋለው አታስብ "አሉ
"በቃ አሳቦትን ከቀየሩ በማንኛውም ጊዜ ይጠይቁኝ "አልኳቸው ።እሺ በሚል እራሳቸውን ነቀነቁልኝ ለምን እንደው አብሬ አቸው መቆየት ፈልጌ ነበር እሳቸው ግን ተጣደፉ ።ይሁን ብዬ አሰናበትኳቸውና ወደ ትልቁ ቤት ሄድኩ አቤል ሽማግሌው እንደወጡ ካረጋገጠ በዋላ ወደውስጥ ገብቷል ስገባ ቁርሰሸ ቀርቦ ቡናው ተጥዶ ሞቅ ሞቅ ብሏል ። ይሄ የቤተሰብ ስብስብ ይመቸኛል ደስስስ የሚል ስሜት ይሰጠኛልም።
ሕይወት እኔንና ቤተሰቤን በፍቅር ይዛን ወደፊት መጓዛን ቀጥላለች ።እናቴ ደግነሽ ባዩሽ ማማ አቤልን ጨምሮ ሁላችንም ሰላማዊ በሆነው ትልቁ ቤታችን በደስታ እያሳለፍን ቀናቶች ተቆጠሩ ። የኔ የደስታ ምንጭም ጨምሯል በብሌን ግልፅና ያልተገደበ የፍቅር አዙሪት ምክንያት።  የብሌንን ፍቅር ብፈራውም እስካሁን የፈራውት አልደረሰም። ያልተለመደው ግልፅነቷ የኔንም ድብቅነት ገላልፆ ፊለፊት አውጥቶ ከማሳየት በስተቀር አልተጎዳውም ። እንደዛተችው ጥላኛለች እቅፏ ውስጥ ፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የሴትልጅ ገላ እንዳውቅ ስሜቱንም እንዳጣጥም አድርጋኛለች ፡ በፍቅር ጠብ አድርጋኛለች ። እናም በዚ ደስተኛ ነኝ ዙሪያዬን የሚያስብልኝ ሰው ነው የከበበኝ ማለት እችላለው ፡ አቤልም ደና የሆነ ይመስላል  እናቴም አቤልን ወደ ውጭ ለመላክ ያሰበችው አሳብ ሊሳካላት ተቃርቧል ፡ መጀመሪያላይ እሱም አቅማምቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ግን ፍቃደኛ ሆኗል  በተለይ የሚሄድበት ሀገር ሲዊዲን ነው ሲባል እዛ ያስቀመጠው ነገር ያለ ይመስል ደስ ብሎታል ፡ እኔ ግን በአቤል መሄድ እርግጠኛ መሆን ከብዶኛል ፡የሚሄድም ከሆነ ደርሶ የሚመለስ ነው የሚመስለኝ  አቤል እኮ ነው። ተቀብሎ መኖር የለመደ እጁ ለስራ ይሰለጥናል ማለት ከበደኝ ።
እናቴ ደሞ የመጀመሪያ ስራዋ አቤልን ከእኛ ማራቅ የሆነ ይመስል በገንዘብም ላይታች በማለትም እየበረታች ነው ። እሷ አሁንም ድረስ አቤል ላይ ያላትን አቋም አልቀየረችም እሱን ማመን ከብዷታል ከእኛጋር በቆየ ቁጥር አንዳች ዱብዳ እንደሚያወርድ ነው የምታስበው  እኛ ሽማግሌ እንኳ ሲመጡ ሁሌም አቤል እንደተቆጣ ነው እሷ ደሞ ስለ አቤል ሆና ይቅርታ እንደጠየቀች ነው ። ይሄ በራሱ እንኳ እንድትፈራው አድርጓታል ፡ሁሌም እኔን ወንድምህ ነው ውደደው ነገርግን እየተጠነቀከው ትለኛለች ።
ከቀናቶች በዋላ የአቤል የውጪ ፕሮሰስ ጉዳይ ተሳካና የሚሄድበት ቀን ተቆረጠ እናቴ ትልቅ እፎይታ ሆነላት የሚያስፈልጉትን ነገር ሁሉ አዘጋጀች  ባዩሽና አክስቴ ደግነሽም ዳቦ ቆሎ በርበሬ ሲያዘጋጁ ከረሙ ።ብሌን እራሱ አልቀረችም ስለ እኔ ብላ ስዊዲን አገር ከሚኖሩ ጓደኞቿ ጋር ተደዋውላ ነገሮችን በማመቻቸት   የበኩሏን ስትወጣ።  እኔ ግን በጣም ቅር ብሎኛል አቤል ምን ሊሆን ነው እዛ ሄዶ ስራ ሰርቶ አያውቅ በሰው አገር ሲቸገር ሲያዝን እየታየኝ ጨነቀኝ ።
የማይቀር ነገር ሆነ እና ይኽው ልንሸኘው ተዘጋጀን   እንደነገ ሊሄድ ማታ ላይ ተሰባስበን የመጨረሻ ምሽት እያሳለፍን ነው ሁላችንም ዘና ልናረገው ሞከርን እሱ ግን ምንም አይነት የስሜት ለውጥ ሳያሳይ ቆይቶ ነበር ወደ ምሽት አራት ሰአት አካባቢ ግን የስሜት ለውጥ ይታይበት ጀመር ምን አልባት ሰአቱ ሲደርስ ተረብሾ ይሆናል ብዬ ነበር ፡ እናቴ በትኩረት ትከታተለዋለች ፡ አቤል መቁነጥነጥ ጀመረ ፡አሁንም አሁንም ወደውጪ እየወጣ ይመለሳል ፡ በመጨረሻ ስልክ ተደውሎለት ወጣ ፡ደግነሽ ተከተለው ብላኝ ነበር ልከተለው ስንቀሳቀስ እናቴ ተመለስ አለችኝ እሱም ሰው አግኝቼ እመለሳለው አታስቡ ብሎን ፈጠን አለ እርስ በእርስ ተያየን ። እናቴ በቤት ውስጥ ወዲ ወዲያ እያለች ታስባለች እኔም እስኪመጣ ተጨነኩ ፡  ለምን ድነው ተጣድፎ የወጣው የሁላችንም አሳብ እሱው ጋር ሆነ,,,,,,,


ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.5K viewsTsiyon Beyene, 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ