"ሐመር ላይ ሴት ልጅ ማህፀኗ ባዶ ከሆነ አፏ አለብላቢት እንደበላች ፍየል ሰውን ይረብሻል ቅስም ሰባሪ ተስቦ በሽታዋ ሁሉንም ተአጠገቧ ያርቀዋል ከዚያ ተከብቱም ተሰውም በረት ርቃ
ብቻዋን ሆና እህል የማያበቅል እማይጠጣ እንደ በረዶ እየቀዘቀዘ
በመንዠቅዠቅ የማያባራ
ዝናም ላይዋ ላይ እየወረደ ጥርሷን እያፋጨች ስትንቀጠቀጥ እናቷ እንኳ አትደርስላትም"
መከራዋን ስታዳምጥ
ማንጎራጎሩን ከልቦናዋ ትረሳዋለች የኢቫንጋዲ ዳንሱ ትዝታ ሙልጭ ብሎ ይጠፋል . ያን ጊዜ ካርለቴ
የኩራት ክብሩ ቀርቶ ሆደ ባሻነት እንደ ሰንበሌጥ ሣር በውስጥሽ በቅሎ በቅሎ ይውጥሻል" ለሐመር ሴት እውነተኛው ለቅሶ እንደ
አባቷ መፎከሪያ በሬ እየተፎገራች ግረፉኝ ስትል እየተንጠራራ ጎረምሳ በባራዛ አርጩሜ ጀርባዋን ሲሸነቁጣት ሰንበሩ እንደ እባብ ጀርባዋ ላይ ተጋድሞ: ደም ፍጭጭ ሲል ከዐይኗ የሚፈሰው እንባ አይደለም ያማ ስቃይሽን እንዲያጠፋ በአባትሽ ደንብ ከተሞላው
ልብሽ የሚደፋ የሥቃይ ማጥፊያ ውሃ እንጂ ለቅሶ አይደለም ካርለቴ! የኔ እህት ለቅሶ ማለት የውስጥ ቃጠሎ ነው" ውስጥሽ
የሚንቀለቀልን እሳት ማጥፋት ሲቸግርሽ ነው ወደ እሳቱ የምትደፊው የእንባ ውሃ ስታጭ ነው ..." ሳግ ተናነቃት ጎይቲ
ውስጧ ጤሶ ተቀጣጠለ ካርለት ደነገጠች
"ኦ! ጎይቲ ካርለት ጎይቲ እንዲህ አዝና ተስፋ ቆርጣ አይታት አታውቅም
ሃዘኗ አሸበራት ፊቷ እንደ በሰለ ቲማቲም ቀላ አንጀቷ በኃዘን ተላወሰ ጎይቲ ንፍጧን ተናፍጣ እንባዋን
በአይበሉባዋ ጠርጋ
"እንዲያ ታያ ደልቲና ተጎረምሶች ጋር በየጫካው ስቃበጥ ጓደኞቼ ማህፀናችንን እንፈትሸው' ሲሉ እኔ ውበቴ ጠላት ሆኖኝ
ጨረቃን እያየሁ: እየተጠነቀቅሁ መቅበጥ እንጂ ልቤን ደፍኖኝ
ለማርገዝ አልሞከርኩም ነበር ... ስትል ካርለት ንግግሯን አቋርጣት,
"ጎይቲ ምንድን ነው ደግሞ ማህፀን መፈተሽ'? አለቻት
ጎይቲ ወዘናው በቀነሰ ፈገግታ ፈገግ ብላ "ይእ አንች ሰው! ምኒቱ
ልብ አድርቅ ነሽ እቴ! ይህን ይህን ታላወቅሽ እህ እሱን ጭሮሽሽን አስደፍኝና ቦርጆን እንዳሁላ
አብቅልልኝ ብለሽ ሳዳጎራሽን አገልድመሽ ተወንዶች ጋራ አደን ውረጂያ!"
"አትሰልችኝ ጎይቲ! ስለማላውቀው እኮ ነው የምጠይቅሽ?" አለች ካርለት ለጥናቷም ትልቅ ፍንጭ በማግኘቷ ባንድ በኩል ደስ እያላት
"ይእ! አታምርሪ የኔ ሸጋ ጨዋታየን እንጂ እንኳን ይህን አያ ደልቲና አንች ጫካ ስትገቡ … ብለሽስ
ጠይቀሽኝ መልሸልሽ
የለ ላላወቀ ደግሞ መመለሱ ምኑ ያሰለቻል
ደንብ ነው!" ብላ
"ማህፀን መፈተሽ ማለት ማርገዝ ማለት ነው በሐመር ልጃገረድ ቀብጣ ስታረግዝ አትጠነቀቅም
ነበር ተብላ ላይ ላዩን
ብትወቀስም ማርገዟ ግን ጥቅም አለው
አባቷንም የሚያስደስት
ፅንሱን ብታስወርድም ማህፀኗ የተቀደሰ ነው' ትባላለች ባልም
እጮኛ ሊያረጋት ይሽሎኮሎካል ያን ጊዜ አባቷ ጥሎሹን ጨምሮ
ይጠይቅባታል፤ ጥሎሽ ከፋዩም ማህፀኗ የተቀደሰ ስለሆነ ይሁን ብሎ ይስማማል" ያን ነው ልጃገረዶች ማህፀን መፈተሽ የሚሉት" ብላ
እሷ ያን ባለማድረጓ መበሳጨቷን እጅዋን በእጅዋ እየደበደበች
አሳየች ካርለት ዐይን ዐይኗን ስታያት ቆይታ
"ጎይቲ መሃን ሴት በምን ትታወቃለች?" አለቻት"
"ይእ! በቀንዷ!" ብላ ጎይቲ ቀለደችና ስትስቅ ካርለትም
አብራት ሳቀች
"ጎይቲ እየቀለድሽብኝ ነው?"
"ይእ! እህ ምናባቴ ላርግ ካርለቴ ሴቱ ሁሉ የሚያውቀውን
አንች አዲስ ሆነሽ ስትጠይቂኝ መቀለድሽ አይደለ?"
"የለም ጎይቲ አልቀለድሁም ቁም ነገር እየተጫወትን
አልቀልድም "
"ይእ! ምን ነበር እቴ የጠየቅሽኝ?"
"መሃን ሴት በምን ትታወቃለች?"
"… በጥንት ጊዜ ቦርጆ እዚሁ እቅርብ ተሐመሮች ጋር ነበር አሉ የሚኖረው" ታዲያልሽ አንድ ጊዜ ከአንዲት ሴት ጋር ይጣሉና
ሴቷ ቦርጆን በጋሊ አርጩሜ ትደበድበዋለች እና በጥፋቷ ያዘነው
ቦርጆ መሐን ሁኝ ብሎ ረገማትና የሐመር ወንዶችን ሰብስቦ አብሬያችሁ በመኖሬ እየተናናቅን ነው
ዝናብ ስትፈልጉ
ተሰብስባችሁ ጥሩኝ እርስ በርሳችሁ አትጣሉ
ከተጣላችሁ ደግሞ
ሽማግሎች ያስታርቋችሁ
በቡድን ሁናችሁ አትጣሉ
ያገኛችሁትን ተካፍላችሁ እንድትበሉ በራችሁ ቀን ከሌሊት አይዘጋ ካለበለዚያ
ዝናብ አልሰጣችሁም"
ሁሉም ሴቶቻችሁ አይወልዱም
ከብቶቻችሁም አይራቡም በሽታም እልክባችኋለሁ ብሎ ነው አሉ ርቆ ሰማይ ላይ የወጣው" እና መሐን ሴት ቦርጆን : ደብድባ
የተረገመች ናት ስትሞት እንኳ ነፍሷ መጀመሪያ እሳት ውስጥ ተዚያ ተተከማቸ ትል ውስጥ ነው አሉ ስትባዝን የምትኖረው ንግግሯን አቋርጣ ጎይቲ | ስቅስቅ ብላ አለቀሰች ካርለት ጎይቲ ባለችው ባታምንም
“እምነቷ ምን ያህል
እንደረበሻትና ባለመውለዷም የሚጠብቃትን ጣጣ አስታውሳ ለእሷና ለሌሎችም መሐኖች አዘነች" ካርለት የምታውቀውን ለጎይቲ እንዴት እንደምታስረዳት ስታስብ ቆየችና
"ጎይቲ መሐንነት የትም አገር አልፎ አልፎ አለ ችግሩ ግን
ከሴቷ ብቻ ሳይሆን ከወንዱም ሊመጣ ይችላልኮ" ስትላት ጎይቲ
ቅንድቧን ሽቅብ ሸብሽባ
"ይእ! የባሰው መጣ!
ኧረ ዝም በይ ያገር መሳቂያ
እንዳትሆኝ. የዘራሽው እህል
ባይበቅል ችግሩ ተመሬቱ
ነውዐኸዘሪው? አንች እውነትም ዝናብ በዝቶበት ፍሬ ያልያዘ ማሽላ ነሽ"
አለቻት" ካርለት በምን ዘዴ እንደምታስረዳት ጨንቋት መላ ፍለጋ መሬቷ ላይ አፈጠጠች
ይቀጥላል
1.6K viewsአትሮኖስ, 18:00