Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 159.61K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-06-04 21:00:02 "ኧረ ተይ እንደዚህማ አትበይ እናቷ እኮ መድሀኒት ቤት ልካት ስትሄድ አግኝቷት ነው አሉ" የእናቴ ጓደኛ አየለች

"ኡኡቴ እና ምን ልትልልሽ ኖሯል ልጄ ከኔ ተደብቃ ወንድ ፍለጋ ሄደች ትበልልሽ እናቷ እኮ ነች። ደግሞስ ከመች ጀምሮ ነው ሚጣን መድሀኒት ማስገዛት የጀመረችው...."

ከዚህም የባሱ ብዙ ሽሙጥና ስድቦችን በተቃራኒውም ብዙ አይዞሽ በርቺ የሚሉ ቃላቶችን እሰማለሁ። ለኔ ግን ከአስር አይዞሽ አንድ ምናባሽ ልቤን ያርደው ነበር። ጭምትና በትንሽ ነገር የምበረግግ ፈሪ ሆንኩ።

እኔ እምቢ ብልም በእናቴ ጉትጎታ ወደትምህርት ቤት ሄድኩ። እዛም የባሰው ነገር ጠበቀኝ አንድም ሊቀርበኝ የሚፈልግ ልጅ የለም ሁለም ራቅ ራቅ ብለው በዩኒፎርማቸው ኮሌታ አፋቸውን ሸፍነው ይንሾካሾካሉ።

ሁሉም ነገር ሊያሳብደኝ ደረሰ የሚያውቁኝ እንደማያውቁኝ ሲሆኑብኝ ጓደኞቼ እኔን ለመቅረብ ሲፈሩ ማየት አሳመመኝ። ምንም ሳልል ቦርሳዬን ይዤ ከትምህርት ቤት ወጣሁ። አረማመዴ ሁላ የእልህ ነበር። ቤት ስደርስ እማዬን አሻሮ እየቆላች አገኘኋት...

" ከዚህ ከተማ አስወጪኝ... እማ ለምን እልም ያለ ገጠር አይሆንም ሄጄ የከብት እረኛም ቢሆን እሆናለሁ ብቻ ከዚህ አርቂኝ ' እግሯ ላይ ተደፍቼ እየተንሰቀሰኩ ለመንኳት

"ችግርሽ ሳይገባኝ ቀርቶ መሰለሽ እኔም ወሬው ሰልችቶኛል የኛ ሰፈር ሰው እንኳን ይቺን አግኝቶ.... እህ.. መች አጣሁት... ግን የፖሊሶቹ ምርመራ አልቆ ያን እርኩስ ሰው ታስሮ ሳላይ ከዚህ ንቅንቅ አልልም። ያኔ እውነቱ ሲታወቅ አንቺም ቢሆን አንገትሽን ቀና አድርገሽ ትሄጃለሽ" እንባዬን ጠራርጋ እና አባብላ ብዙ መከረችኝ ምክሮቿም ብርታት ሆኑኝ።

ምንም እንኳን በተኛሁበት መበርገጌ የምጥ እንቅልፍ መተኛቴ ባይቀርልኝም የሰፈሩ ሰው ግን ቀስ በቀስ ወሬውን እየረሳው ጓደኞቼም " ነይ እንጫወት" እያሉ መምጣት ጀመሩ።

ትምህርት ቤትም ተማሪዎቹ እንደድሯቸው ሆኑልኝ እኔ ግን እንደድሮዬ መሆን አቃተኝ ትምህርት ስማር በሀሳብ ጭልጥ ብዬ እሄዳለሁ... ወንድ አስተማሪ ሲገባልን እሱም ልክ እንደዛ ሰው አውሬ እንደሆነ አስብና እጠላዋለሁ ከመምህሩ እኩል የሚያስተምረውም ትምህርት ያስጠላኛል። እንዳዛ እንደዛ እያለ የእናቷ " ሚጣ" እኔ 'ህያብ በዛብህ' ከማንነቴ ተፈናቅዬ እንዳልነበርኩ ሆንኩ። ሰው ሲያየኝ እንደበፊቱ ብመስልም ውስጤ የተረበሸ ከተማ ሆነ።
....
ከአራት ወር የፓሊሶች ምርመራ እና ድካም በኋላ ውጤቱ ፍሬ አልባ መሆኑን ለእናቴ ነገሯት.... ደፋሪዬ ደብዛውም የለም። እኔ በነገርኳቸው ትንሽ ምልክት ብቻ እሱን ለማግኘት መሞከር እንደሚከብዳቸው ስለገባኝ አላዘንኩባቸውም።
...

ከእለታት በአንደኛው እሁድ
ፀጉሬን ከታጠብኩ በኋላ ገላዬን ልታጠብ የበርሜል ጉራጅ ላይ ቁጭ ብዬ ሙቅ ውኋዬን እስከምታመጣ እናቴን እየጠበኩ ነው። ውሃው መጣና እኔ ከፊቴ እናቴ ደግሞ ከጀርባዬ እያጠበችኝ
"እስኪ እጅሽን ዞር አድርጊ አሁን በዚህ ጭራሮ እጅሽ አሽተሽው ነው የሚጠራው..." ሁሌም እናቴ ከፊት ለፊቴ ልታጥበኝ ስትል የምትለው ነገር ነው። ልማዴ ስለሆነ እኔም አልቃወማትም እጄን ከፍ አድርጌላት እያጠበችኝ ድንገት የያዘችውን ውሃ የያዘ ጆግ ለቀቀችው። በርሜል ውስጥ ስለወደቀ ከስር ያለው ውሃ ተፈናጥሮ አለበሰኝ።

'እንዴ እማ ምን ሆነሽ ነው ታጥቤ ታጥቤ' ተነጫነጭኩና ጆጉን አንስቼ ውሃ ልቀዳ ስል

"ቆይ ቆይ ቆይ እስኪ አንዴ ቁሚ" አለችኝ። ቀና ብዬ ሳያት ደንግጣለች

'እማዬ ምን ሆነሻል' አልኳት

"ወሬውን ትተሽ ያልኩሽን አድርጊ" ብላኝ እየተርበተበተች እጄን ይዛ አቆመችኝና ፍጥጥ ብላ ሆድ ሆዴን ካዬች በኋላ

"ልጄ" አለችኝ በሚያሳዝን ቅላፄ

'ወዬ እማ ለምን ነው እንደዚህ የምታይኝ'

"ሆድሽ" ጎንበስ ብዬ አየሁት እኔንም አስደነገጠኝ

'አብጦ ነው እማ? ወይስ እንደ ምንትዋብ ቁዝር ልሆን ነው' አልኳት። ቀጫጫዋ እና ሆዷ ቁዝር ያለውን የክፍላችንን ልጅ ምንትዋብን አስታውሼ ማንም ምንትዋብ ብሎ የሚጠራት የለም ሁሉም "ቁዝር" ነው የሚሏት። እኔም እንደሷ ቁዝር እየተባልኩ የተማሪዎች መሳለቂያ ልሆን ነው.... ወይኔ... ከሄድኩበት ሀሳብ እናቴ ልብሴን እላዬ ላይ ስታሳርፈው ተመለስኩ

'እንዴ እማ በደንብ ሳልታጠብ' እንዳልሰማ ዝም ብላ አለበሰሽኝና እየተጣደፈች ወደቤት ገባች። ተከትያት ገባሁ ነጠላዋን ለበሰችና እኔንም አነስ ያለች ፎጣ አለበሰችኝ

'ወዴት ልንሄድ ነው እማዬ'

"ሀኪም ቤት"

'ሳልታመም'

"አይ ታመሻል" እጄን ይዛኝ ስትሄድ በዝምታ ተከተልኳት
....
እናቴ ቁጭ ብላ እንባዋን ታዥጎደጉደዋለች። እኔ በድንጋጤ ደርቄ ምን ማሰብ እና መናገር እንዳለብኝ ግራ ገብቶኝ ቆሚያለሁ። ድንገት የሆነ ሀሳብ መጣልኝና ከቆምኩበት ኮሊደር ላይ ሳላንኳኳ የዶክተሩ ቢሮ ገባሁ።

"አቤት ህያብ" አለኝ ዶክተሩ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ካየኝ በኋላ

'ማስወረድ እፈልጋለሁ' አልኩት

"ምን" የሚል ድምፅ ስምቼ ስዞር እናቴ ከኋላዬ ቆማለች።

ይቀጥላል
4.8K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 21:00:01 #ህያብ


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_ኤርሚ

ከቤት ስወጣ ማንም ያየኝ የለም ለነገሩ ማን ሊያየኝ ይችላል... እንደሚሰበር እንቁላል የሚንከባከቡኝን ሁሉ አጥቻለው..... እየሄድኩ ነው....መነሻዬን አስታውሳለሁ መድረሻዬን ግን እንጃ.....

ማሰብና ማስታወስ ቢደክመኝም አይምሮዬ ወደማልፈልገው ጊዜ ሽምጥ ጋለበ.... ወደዛ የሁሉም ነገር ጅማሬ የመከራዬ ሀ ወደሆነው ጊዜ....

በአንድ አነስተኛ የገጠር ከተማ ውስጥ ከእናቴ ጋር ነበር የምኖረው። አባቴን ገና በልጅነቴ ነው በካንሰር በሽታ ያጣሁት። የልጅነት ጊዜዬን እንደማንኛውም ልጅ በጨዋታ እና በሳቅ ነው ያሳለፍኩት። ምንም እንኳን በቤታችን ብዙ የጎደሉ ነገሮች ቢኖሩም እናቴ ለኔ ደስታ አብዝታ ትደክማለች።

ፓስቲ እና ጠላ በመሸጥ ለኔም ሆነ ለሷ የሚያስፈልጉንን ነገሮች ታሟላለች። ሁል ጊዜም ባይሆንም ችግር እና ረሀብ አልፎ አልፎ ቤታችንን ያንኳኳል፤
እናቴን ሲያማት.....
.....
በዛን ሰዓት ምን እንደሆነ ባይገባኝም እናቴን አልፎ አልፎ ከበድ ባለ ሁኔታ ያማት ነበር። አንዴ አሟት ከተኛች ሳምንት እና ከዛ በላይ ያስተኛታል። ሀኪም ቤት እንድትሄድ ደጋግሜ ብጨቀጭቃትም የሁል ጊዜም መልሷ አይሆንም ነው፤ ብያት ብያት እምቢ ስትለኝ በሚያማት ሰዓት ከአጠገቧ ሳልለይ እንከባከባት ነበር።
....
ከእለታት በአንዱ ቀን ከትምህርት ቤት ስመለስ በራችንን ተዘግቶ አገኘሁት.... እናቴ በዚህ ሰዓት የጠላ ጣሳዎቿን ደርድራ ፓስቲዋን በርንዳ ላይ እየጠበሰች መገኘት ነበረባት....
.....
በሩን ከፍቼ ወደ ውስጥ ስገባ የሽቦ አልጋዋ ላይ እጥፍጥፍ ብላ ተኝታ አገኘኋት

"እማ ምን ሆነሽ ነው አመመሽ እንዴ?' እጄን ግንባሯ ላይ አድርጌ ትኩሳቷን አየሁ.... በጣም ግላለች

'እማዬ አተኩሶሻል እኮ እባክሽ ዛሬ እምቢ አትበይኝ ሆስፒታል እንሂድ' ከወገቧ ቀና ለማለት ስትሞክር አገዝኳትና ትራሱን ከጀርባዋ አስደገፍኳት....
.....
"አይሆንም ልጄ.... ደግሞ ልሂድ ብልስ በምን ገንዘብ .... ይልቅ መድሀኒት አልቆብኛል ሂጂና ግዢልኝ፤ ይህን ወረቀት ስታሳያቸው ይሰጡሻል...." የሆነች ትንሽዬ ወረቀት ከእጅ ቦርሳዋ ውስጥ አውጥታ ከብር ጋር ሰጠችኝ....
......
..
" በይ ታዲያ መጀመሪያ መክሰስሽን ብይና ነው የምትሄጂው" እሺ ብያት ዩኒፎርሜን ቀይሬ ምግብ አቀረብኩና እምቢ ብትለኝም በግድ እያጎረስኳት ትንሽ አብራኝ በላች።
....
....
ከተማችን ያለው አንድ የመንግስት ፋርማሲ ብቻ ነው። እሱም ለሰፈራችን ራቅ ስለሚል በሩጫ መሄድ ይጠበቅብኛል። የእናቴን ጉንጭ ስሜና ቶሎ እንደምመለስ ነግሪያት እየሮጥኩ ከቤት ወጣሁ
....
....
ነፋሻማው አየር ቀሚሴን ወደላይ እያነሳው እኔም እንዳይገልጠኝ ለመከላከል እየሞከርኩ እየሮጥኩ እያለ አንድ ሰው ስሜን የጠራኝ መሰለኝ። ድጋሚ
" ሚጣ" አለኝ ማነው የጠራኝ ብዬ ዞር ስል ሸክም ከአጠገቡ ያስቀመጠ ጎረምሳ ልጅ እጁን አውለበለበልኝ። አቅጣጫዬን ቀይሬ በፍጥነት አጠገቡ ደረስኩና
' አቤት የሚያሸክምህ አጥተህ ነው አልኩት' ከሁኔታው ሳየው ምኑም የኛን ከተማ ሰው አይመስልም ምናልባት ከሌላ ቦታ ለስራ መጥቶ ይሆናል ብዬ መላ ምቴን አስቀመጥኩ።
...
...
ያልገባኝን ፈገግታ ከለገሰኝ በኋላ "አዎ ሚጣዬ እስኪ አሸክሚኝ" አለኝ።
'የምችለው አይመስለኝም ግን እሺ ልሞክር' አልኩትና ጎነበስ ብዬ ሸክሙን ያዝ አደርኩና ቀና ብዬ አየሁት የማይገባኝን አስተያዬት እያየኝ ነው።
'ምነው መሸከም አትፈልግም እኔ እቸኩላለሁ ለእናቴ መድኃኒቱን መግዛት አለብኝ' አልኩት ቆጣ ብዬ

"አይ እንደዛ አይደለም ይሄን አንቺም ለማሸከም ይከብድሻል እኔም እንጃ የምችለው አይመስለኝም... ውስጥ አነስ ያለ ሌላ ሸክም አለ እንደውም እሱን አሸክሚኝ አይዞሽ አትቆይም" ምላሼን ሳይጠብቅ ፊቱን አዙሮ በጭቃ እየተሰራ ወዳለ ጅምር ቤት ገባ። ዘግዬት ብዬ ተከተልኩትና ወደ ውስጥ ስገባ ዘሎ በጥፊ ደረገመብኝ። ተንደርድሬ መሬቱ ላይ ተደፋሁ.... ለመጮህ አፌን እንደከፈትኩ ፀጉሬን ይዞ አፌ ውስጥ ጨርቅ ጠቀጠቀብኝ።
.....
በመንፈራገጥ እና በድብደባ በዛለ ሰውነቴ ላይ ከላዬ ሆኖ በስሜት ይጨፍራል....
......
ከባድ የሆነ የህመም ስሜት ይሰማኛል........
ቀስ በቀስ በእንባ የራሰው አይኔ መከደን ጀመረ......
ከላዬ ላይ ያለው ሰው ምስል ወደ ብዙ ሰውነት ተቀየረ.......
ከዛ ደግሞ ድብዝዝ እያለ መጣ...... በስተመጨረሻም ድርግም ብሎ ጠፋ...

ጨለማ

ከምን ያክል ሰዓት በኋላ እንደሆነ አላውቅም.... ራሴን እዛ ጅምር የጭቃ ቤት ውስጥ ተኝቼ አገኘሁት። እንደምንም እየተንገዳገድኩ ከቤቱ ውስጥ ወጣሁ... ልብሴ በደም ተነክሯል፣ የሚሰማኝ የህመም ጥዝጣዜ ራሴን ሊያስተኝ ደርሷል ግን እንደምንም ተቋቁሜ ለመራመድ ሞከርኩ።
.....
ብርሀን ለጨለማ ቦታዋን ብታስረክብም ደማቋ የምሽት ጨረቃ አካባቢውን በብርሀን ሞልታዋለች....

በቀስታ እየተራመድኩ ወደ መንገዱ ወጣሁ። አሁንም ደሜ አልቆመም በቀስታ ከጭኔ ላይ ሲወርድ ይሰማኛል። ከሩቅ ነጠላ ለብሶ የሚመጣ ሰው አየሁ አንደበቴን ከፍቼ ለመጣራት መከርኩ ግን በምጥ የወጡት ቃላቶች እንኳን ለሌላ ለኔም የሚሰሙ አልነበሩም።

ያለኝ አማራጭ ወደሚመጣበት አቅጣጫ ተራምጄ እንዲያየኝ ማድረግ ነው። እየቀረብኩት ስመጣ ቄስ እንደሆኑ ተረዳሁ.... አጠገባቸው ለመድረስ ትንሽ ሲቀረኝ ጉልበቴ ተብረከረከ፣ አቅሜ ተሟጠጠ፣ አጠገቤ መጥተው ያዙኝና

" ምነው የኔ ልጅ ችግር አለ ምን ሆነሽ ነው?" ድምፃቸው ከሩቅ የሆነ ያክል ይሰማኛል ። ልቤን ስልብ የሚያደርግ ህመም ተሰማኝ ከዛ በኋላ አላስታውስም
......
"ልጄ የኔ ስስት.... ምን አድርገውብኝ ነው? እባክሽ ተነሽ ሚጣዬ ተነሽልኝ..... የኔ ብቸኛ ልጅ... ያላንቺ ማን አለኝ.... ትተሽኝ እንዳትሄጂ.... ተስፋዬ.... ነገን የማይብሽ.... " አይኔን ሳልገልጥ የሰማኋቸው የእናቴ በሳግና በለቅሶ የታጀቡ ቃላቶች ናቸው... ከዛ ከባዱ ጨለማ ይውጠኛል።
ትንሽ ትንሽ ዙሪያዬ እየተፈጠረ ያለውን ነገር ባውቅም አይኔን ለመክፈት ወሰድ መለስ የሚያደርገኝን ጨለማ እና የተጫነኝ ከባድ ነገር መታገል ግድ ሆኖብኛል።
.....
"አሁንስ አልነቃችም አይደል" አለ የሆነ ጎርናና ድምፅ

" አልነቃችም ኢንስፔክተር ልጄን እንደዚህ ያደረገውን ሰው አገኛችሁት?" እማዬ ናት

" አይ... ወይዘሮ ወይንሸት አላገኘነውም እሱን ለመያዝ የልጆት ቃል ያስፈልገናል" የበር መዘጋት ድምፅ ተሰማኝ እኔም ወደዛው ጨለማ የሄድኩ መሰለኝ.... እንቅልፍ
....

ዛሬ የተሻለ ጥንካሬ ይሰማኛል። ልክ አይኔን ስግልጥ እናቴን አጠገቤ አየኋት የአልጋውን ጠርዝ ተደግፋ እንቅልፍ ወስዷታል። እጄን አንቀሳቅሼ ፊቷን ስዳስሳት ተነሳች... ወዲያው እልልታዋን አቀለጠችው።

"ልጄ ነቃሽልኝ የኔ ስስት.... ተመስገን ልጄ ነቃች" ዶክተሩ ምርመራ እስከሚያደርግልኝ ውጪ እንድትቆይና ነገራትና አንዳንድ ህክምናዎች ካደረገልኝ በኋላ

"ፖሊስ መጥቶ ቃልሽን ይወስዳል... እንደዚ ያደረገሽ አውሬ እንዲያዝ ከፈለግሽ ምንም ሳትፈሪ ሁሉንም ለመናገር ሞክሪ.... ደግሞ አይዞሽ በሚያስፈልግሽ ሁሉ ከአጠገብሽ አለን..." ብሎኝ ክፍሉን ለቆ እንደወጣ ሁለት ፖሊሶች ተከታትለው ገቡ።
....
ከ አንድ ወር በኋላ
የሰፈር ሰው ሰምቶ ስለነበር ግማሹ ሲያዝን ግማሹ ደግሞ የራሱን መላምት ማስቀመጥ ጀመረ።
"ፈልጋ ነው እንጂ ሳትፈልግ ማን ሊነካት..." በነገር የምትታወቀው ብርቄ
4.8K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 20:41:32 የብሌን መኪና ከቤታችን ፊት ለፊት ቆሟል ጥድፍ ጥድፍ እያልኩ ተጠጋዋት የመኪናዋን በር ከፍታ አስገባችኝ ስገባ ያየሚያስደነግጠኝ ፊቷ ቀረበኝ
"አንተ የመጨረሻ የምታናድድ ልጅ "አለችኝ
"ምን አደረኩ "አልኳት
"ለምንድነው ስልክ የምትዘጋው በጣም ነው የተበሳጨውብህ ግን ሳይህ እረሳውልህ "ብላ ጉንጬን ሳመችኝ ኡፍፍፍፍ እሳቷን ለቃ ምንም እንዳልተፈጠረ ነው የምትሆነው
"ቻርጅ ጨርሶ ይሆናል "አልኳትና ጉንጬን ዳበስኩ
"እና ቻርጅ ማድረግ ነው እኔ መጥቼ ላርግልህ እንዴ"
"አይ እኔ አደርገዋለው"
"አድርገዋ ታዲያ"ብላ ተጠጋችኝ
"ተይ በቃ አታስጨንቂኝ እንዴ ማታ ኳስእያየው ስለነበር እረስቼው ነው ያደርኩት"አልኳት እኔን ማሳፈር ደስ ይላታል ፡
"ኪኪኪኪ ደስስስ ይለኛል አንተን ማስጨነቅ ፡አሁንማ ይሄንን ሁኔታህን ለምጄው ነው መሰል ከጠዋት እስከማታ ነው የማስብህ "
"ስራ የለሽም ማለት ነው"
"ስራዬ አንተ ሆነሃል ከልቤ ነው እየወደድኩህ ነው መሰል"
"አሂሂሂ ያዋከቡት ነገር ሆኖ በጊዜ እንዳታባርሪኝ "
"እንዳትባረር ከፈለክ ፀባይ ይኑርክ ፡አሁን ለምን ቁርስ አብረን አንበላም "
"አይ ቤት እየጠበቁኝ ነው በዛላይ ሻወር አልወሰድኩም  በዋላ እንገናኝ "አልኳት
ዝምብላ አየችኝ አስተያየቷ አንዳች ነገር የፈለገሰው ይመስላል ስሜት አለው
"ምነው "አልኳት
"ይሄን ሰውነት ያለ ጨርቅ ሳልኩት እናም በቃ......."ብላ ዝም አለች
"አንቺ ልጅ ግን እኔ ማለት ያለብኝን ሁሉ አንቺ ካልሺው እኔ ምን ልል ነው  ግልፅነትሽ በዛብኝ"አልኳት እያፈርኩ
"አንተ ማለት አይጠበቅብህም በታማኝነት ድርጊቱላይ ተሳተፍ ፡ አሁን አንድ ቦታ ብንሄድ በጣም ነበር ደስስስ የሚለኝ ግን ያው በቃ እንዳልክ በዋላ ላግኝህ ስልክህን እንዳትዘጋው ደሞ"አለችኝ
"እሺ አደራ ግን ይሄ የምታሯሩጭኝን ነገር በልኩ አድርጊው "አልኳት ፈገግ እያልኩ
"እጠነቀቃለው "ብላ ጠጋ አለችኝ እናም ሳላስበው ከንፈሬን ምጥጥጥ አድርጋ ሳመችኝ ፡ሰማይ ምድሩ ሲዞር ይሰማኛል ፀሐይ ሙቀቷን እንዳለ ከላይ የለቀቀችብኝ መሰለኝ ኧረ ደግነሽም እልልልልልልልልልልል ያለች መሰለኝ ,,,,

ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.7K viewsTsiyon Beyene, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-03 20:41:32 የእናቴ ልጅ
ክፍል ሃያ ሁለት

እናቴ  ይዛ የቆየችውን ሚስጢሯን ሁሉ ስለነገረችኝ ከእሷው እኩል ነው እፎይ ያልኩት እሷላይ ያለኝ ጥያቄ ሁሉ ተመልሶልኛል ፡ ነገርግን አዲስ አሳብ ደሞ ተተክቷል ያባቴ ጉዳይ ፡ አባቴን የገለፀችበት መንገድ ብዙም ውበት ባይኖረውም ፡ እሱን በሕይወት ባገኘው ብዬ ተመኘው ፡ ምንገጥሞት ይሆን የት ሄዶ ይሆን ፡ገለውት ይሆን እያልኩ ፡ ማሰቤ አልቀረም ፡ ለእናቴም ብንፈልገውስ ብያት ነበር እሱ የማይሆን ነው እሱ በሕይወት ካለ በፍፁም እኛን ፈልጎ አያጣንም ምክንያቱም እንኳን እኛን ሆነ ብሎ የሚደበቀውን ጠላቱን እንኳ ፈልፍሎ የሚያወጣ ሰው ነው ብላ አሳቤን ውድቅ አደረገችብኝ እናም እኔ ስለአባቴ መሞት በከፊል ይሆናል ብዬ አመንኩ ........
በጠዋት ተነስቼ ጊቢውስጥ እሮጥ እሮጥ እያልኩ ስፖርት እየሰራው ነበር ላለመረበሽ ብጠነቀቅም ፡እናቴ ግን ሰምታኝ ነው መሰል ቱታዋን አድርጋ መጣች ሳኩባት ደሞ እንዴት ነው የሚያምርባት ይሄ ቱታ መቼም ለመዝናናት ነው የሚሆነው ነጭ ከመሆኑ ሰውነቷ ላይ ስትር ማለቱ  እናቴ አልመሰለችኝም ፡ሁላ በዚ ቱታ ስፖርት አያዋጣም አልኩ ለራሴ ፡አጠገቤ ሮጥ እሮጥ እንደማለት ስትል ቀልድ እንደነገሩት ሰው ፍርፍር ብዬ መሳቅ ጀመር ከአለባበሷ ጋር አሯሯጧ ያስቃል "ኧረ እናቴ ምንድነው ማበረታቻ ነው ወይስ ከምርሽን ነው"አልኳት መሮጤን ሳላቋርጥ
"እንዴ ምን ችግር አለው ስፖርት ለጤንነት "ብላ ሳቀች ፡
"ግን እኮ አይን በሚያጠፋ ነጭ ቱታ አይሆንም አታበላሺው ወጣ ስንል ታደርጊዋለሽ "አልኳት
"እ ኪኪኪኪ ስለሌለኝ እኮ ነው ስፈልግ ይሄንን ነው ያገኘውት በተቻለኝ መጠን እንግዲ መሬት አልቀመጥም "ብላ ሳቀች እና ትንሽ ዱብ ዱብ አለች አብራኝ ትንፋሿ ቁርጥ ቂርጥ እያለ ማውራት ሲከለክላት ቆም አለች  ሰውነቷን እንድታላቅቅ እና ለዛሬ እንዲበቃት ነገርኳት ሳያት ግን ዋና አላማዋ እስፖርት መስራት አልመሰለኝም ።ትንሽ ጠበቀችኝና እኔንም አስቆመችኝ እና ጊቢ ውስጥ ካለው አንድአግዳሚ ወንበር ላይ ሄደን ተቀመጥን
"ናቲዬ አንድ ማስተካከል ያለብኝ ጉዳይ አለ እና ጊዜው ደሞ ደርሷል "አለችኝ
"ምንድነው እናቴ አብረን እናስተካክለዋለን ብቻሽን ከአሁን በዋላ አትቸገሪም ማድረግ ያለብኝን ሁሉ ለእናቴ ያለ ገደብ አደርጋለው " አልኳት
"ምን መሰለ ወደፊት ምን እንደሚፈጠር አይታወቅም ፡እና ስለመገናኛው ቤታችን ነገሬህ የለ ይህንን የምታውቀው አንተ ብቻ ነህ እንደእውነቱ ከሆነ በፊት ላይ ወንድምህ ትክክለኛ አስተዋይ ነገሮችን መቆጣጠር የሚችል ይመስለኝ ነበርና ለሱ ነበር ያንን ቤት ያሰብኩት ነገር ግን አሁን እሱን አሳቤን ትቼዋለው ቅጣቱንም ያገኛል ፡ እና ምን ልልህ ነው መሰለህ ቤቱን ባንተ ስም ማዘዋወር እፈልጋለው ይህንን ስናደርግ ደሞ ማንም እንዲያውቅ አልፈልግም እሺ ፡ወደፊት ትዳር ስትሂዝ ያለምንም የቤት አሳብ እንድትኖር እፈልጋለው ላደረገንህ ነገር ሁሉ መካሻዬ ነው በእርግጥ ዞሮ ዞሮ ያው ለእናንተ ነበር "አለችኝ እጄን ያዝ አድርጋ
"እናቴ ግን አቤል ..."ከማለቴ አቋርጣኝ
"አቤል ማለትህን አቁም እሱን መስተካከል የኔ ፈንታ ነው እሱ የሰራኝን መስማት ከፈለክ  እንግዲ ስማ ፡ አንተ በሌለህበት ጊዜ ቤቴን በቁሜ ሊያሸጠኝ ያላረገው ጥረት የለም ፡ከዚ ከማነው ...ጋሽ ግዛው ከተባለ ሰው ጋር ለዛውም ቤት ድረስ እያመጣው ፡ አይሆንም በማለቴ እንዴት እንደተቀየረብኝ ፡ከዛእንግዲ ያቺ የማማ እናት መጥታ ጉዴን ስትነግረኝ በድንጋጤ እንደዛ ሆንኩኝ እሱ ግን ሁኔታዬ ሳያሳስበው አሳቡ ቤቱ ላይ በመሆኑ ደና አኪም እንኳ አንዳያየኝ ቤት ዘግቶ ትድናለች እያለ አፍኖኝ ነበር  የቤቱን ካርታ ያልፈለገበት ቦታ አልነበረም እንደማልናገር እያወቀ አስሬ ጠይቆኛል በግዴታ ሊያስፈርመኝ አስቦ ነበር ፡እሱ እንደማይሳካለት ሲያውቅ እኔን ተስፋ አሳጥቶ እንድሞትለት በማሰብ ሴት ቤቴድረስ እያመጠ አይኔ እያየ ያሳድር ነበር ።እንደውም ደግነሽ ባትኖር አንቆ ይገለኝ ነበር ብዬ ነው ማስበው አሁንም አስተያየቱን አልወደውም ፡ብቻ ልጄን የቱጋር ስህተት ሰርቼእንዳጣውት አላውቅም አንተ ግን ተጠንቀቅልኝ አደራህን እንዲ ባይባልም እንኳ የእናትህ ልጅ ቢሆንም እንኳ ተጠንቀቀው አደራ ወንድምህን ውደደው ነገርግን ባህሪው ከባድ ነው እሱን ተጠንቀቅ  ከኔ የሚበልጥ ወዳጅ የለውም እናቱ ነኝ ግን ለኔም አይመለስም ፡ስለዚ እኔ አንድ ያሰብኩለት ነገር አለ እሱን አስተካክዬ ከአገር እንዲወጣ አደርገዋለው እስከዛው እራስህን ጠብቅ "አለችኝ ኡፍፍፍፍ ይጨንቃል ወንድሜ ቤቱን በላይዋላይ ስለመሸጥ መደራደር ምን አይነት የገንዘብ ፍቅር ነው የገባበት ፡ከባድ ነው ፡ከእናቴ ጋር ስናወራ ቆየን ስለወደፊቱ ስንመካከር  ስለ እኔም ስትጠይቀኝ ስለ አዲሷ ጓደኛዬ ብሌን ነገርኳት እሷም ሴትልጅን እንዴት መያዝ እንዳለበኝ ስታስረዳኝ ቆየች እነደግነሽ ተነስተው ቁርስ ለመስራት ተፍ ተፍ ሲሉ ማማም ተነስታ ወደኛ መጥታ መጫወት ጀመረች ።አቤል እናቴ የነገረችኝ ነገር ውስጤ ቢቀመጥም ፡አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ ግን እንደዛ አይመስልም እሱም እንደተነሳ ሁላችንንም በፍቅር ነው ሰላም ያለን ፡በእርግጥ መች እንደሚናደድ አያስታውቅም ።
በራችን መጥሪያው ሲጮህ በር ሊከፍት በፍጥነት ሲሄድ እናቴ ተስፋ በቆረጠ አተያይ ከዋላው ስትመለከተው ጨነቀኝ በዚመጠን እናቴ አቤል ላይ ትሆናለች ብዬ አላውቅም በጣም ጎድቷታል
"ምን ፈለክ "ብሎ አቤል ሲጮህ እናቴ ወደኔ አየች ተነስቼ ወደበሩ ሄድኩኝ ስደርስ አንድ አባት እየለመኑ ነው ሲያዩኝ ደነገጡ ለሁለት አንድ ነገር የምናረጋቸው ይምሰላቸው እንጃ
"ምንድነው የምትጮህባቸው ስለ እግዚያብሄር የሚልስው በዚ መልኩ ነው እንዴ የምታስተናግደው ኑ ግቡ "አልኳቸው አቤል ጨሰ ሽማግሌው ተርበተበቱ
"ማንንም ግቡ የማለት መብት ያለህ ነው የሚመስልህ "አለኝ ተናዶ
"ድጋሚ መልስ ብትሰጠኝ ከመሬት ነው የማደባልቅህ እሺ ደነዝ አቀመ ደካማ ናቸው ምን ያረጉኛል ብለህ ነው እርቧቸው ይሆናል "አልኩት እና አስገብቼ ጥግላይ አስቀመጥኳቸው አቤል እየተነጫነጨ ሄደ
እናቴ መጥታ ሽማግሌውን እያየች "እንዴ አባባ እርሶ ኖት ለልጄ ይቅርታ ያድርጉለት  ስላላወቀ ነው ደግነሽ ቁርስ ታመጣሎታለች "ብላ ጠቀሰችኝ
"ምንድነው እማዬ ታውቋቸዋላቹ እንዴ "ብዬ ጠየኳት
"ያው እዚ አልፎ አልፎ ይመጣሉ በልመና ነው የሚተዳደሩት አስፖልቱ ጫፍ ላይ ላስቲክ ወጥረው ነው የሚኖሩት ፡እንደውም አንዴ ዝናብ ላስቲካቸውን አፍርሶባቸው ኑ እኔጋር ብላቸው ደግነሽ ብትለምናቸው እሺ አላሉም የሚገባኝን ኑሮ ነው የምኖረው አሉን አቤል ደሞ ጠልቷቸው ሊሞት ነው "አለችኝ ደግነሽ ምግብ በሰአን ጠቅጥቃ መጥታ ሰጠቻቸው ሽማግሌው በዛ ሲሏት ደግነሽ በፌስታሉ እንዲይዙትም ጭምር ነው ፡ዋላ ይበሉታል ብላ ወደስራዋ ተመለሰች ።ሽማግሌው አመሰገኑ ፡አንድ እየጎረሱ እኔን ቀስ ብለው አየት ያደርጉኛል እኔ ደሞ አጠገባቸው ቆሜ በማዘን እያየዋቸው ነው ለምን እንደው አላውቅም አንጀቴን በሉኝ ሽቁጥቁጥ ማለታቸው እረዘም ያለው ቁመናቸው ወደፊት ማዘንበሉ የለበሱት ስስ ቲሸርት የአጥንታቸው መቆጠር ፊታቸውን ሊሸፍነው በተቃረበው ጢማቸው ውስጥ ደከም ያለችው አይናቸው በቃ አሳዛኝ ፍጥረት ናቸው  ምስኪን አልኩ ።የጊቢ አችን በር ሲንኳኳ እዛው ስለነበርኩ ከፍቼ ወጣው አንድ ትንሽ ልጅ ነው ሲያየኝ እጁን ወደ ቆመ መኪና አመላክቶኝ እሮጠ  
5.2K viewsTsiyon Beyene, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 08:14:40 የ እናቴ ልጅ
ክፍል አስራ ሦስት

መጥሪያውን ተጭኜ ብዙ ነገር ወደውስጤ ተመላለሰብኝ ፡ፍርሃቴም ጨመረ ፣የእናቴ ቁጡ ፊት መጥቶ ሲደቀንብኝ ፣ወይም የአቤል ተንኮለኛና ትህቢተኛ ፊት ፣ በአንዴ ተመላለሱብኝ ፣ግን ልቤ እየመታ ከዚአካባቢ ተሰወር ቢለኝም እግሬ ግን አልንቀሳቀስ አለ ፣እግሬ በራሱ መመራት ጀመረደሞ ዛሬ ፣ አስገድዶ ያስቆመኝ መሰለኝ ፡ ከቆይታ በዋላ በሩ ተከፈተ ፡ በሩ ሲከፈት ያየውትን ማመን አቅቶኝ ዝም አልኩ ፡ በንሩ የከፈተችልኝ ተለቅ ያለች ሴትዮ ናት ፡በትንሹ እናቴን ትመስላለች ነገር ግን እናቴ አይደለችም ፡ ግራ ተጋብቼ ፈዝዤ ሳያት
"ምን ፈልገህ ነው ጌታው "አለችኝ ድንግርግር አልኩኝ
"ኧራ አንተው ምን ይዘጋሃን ፡አትናገር ከሆን በሩን መልሼው ልግባ"አለችኝ ፡እናቴ የት ሄዳ ነው በሕይወቴ እኛቤት ሌላ ሰው ገብቶ አይቼ አላውቅም ፡እና ማናት ወይስ አዲስ ፀባይ አምጥታ ብቸኝነት ሰልችቷት ፡ማከራየት ጀመረች ፡ወይስ አቤል ቤቱን አሸጣት ፡ዘገነነኝ ፡"አንቺ ማማነሽ "አልኳት ቀጥሎ የምሰማው ነገር እንዳያሳምመኝ ፡እየፈራው
"ኧራ አንተ እራስ ማነኝ ነው የምትል ፡ምን ፈልገህ ነው?"አለችኝ ትህግስቷ እያለቀ
"እኔ የዘውድነሽ ልጅ ነኝ ፡ናታኒየም እባላለው አንቺ ማነሽ ፣እሷ የት ሄዳ ነው?"ብዬ እየተናነቀኝ አከታትዬ ጠየኳት፡ልክ ተናግሬ እንደጨረስኩ መጮኽ ጀመረች ፡ድንብርብሬ ወጣ ፡ ጩኽቷን ሳታቋርጥ ጎትታ ወደውስጥ አስገብታኝ ተጠመጠመችብኝ፡ጭንቀቴ እና ድንጋጤዬ ይበልጥ ጨመረ ፡
"እናቴስ እናቴ ምን ሆና ነው እባክሽ ?ሞታ ነው አንቺ ማነሽ "አልኳት ከእቅፏ ለመውጣት እየታገልኩ ፡ልክ እንደኔ ግዙፍ ናት ፊቷ ብቻ ነው የሴት ቅርፅ ያለው ፡
"እናትህ አለች መቼስ መኖር ከተባለ ፡ብላ ዕንባዋን ማዝራት ጀመረች ፡ከዚ በዋላ ትህግስት አጣው ፡ሴትዮዋን ባለችበት ጥዬ ፡ወደማውቀው ቤት ሮጬ ገባው ፡ስገባ ያየውት ነገር አሳቆ እና አስደንግጦ ባለውበት አቆመኝ ፡ትልቁ ሳሎናችን ልዩ ሆኖ አምሯል  ነገር ግን ፡ ማሃል ላይ በዊልቸር የተቀመጠች ሴት አለች ፡ ምን ልሁን በቁሜ ነበር ከፊቷ ሄጄ የተንበረከኩት ፡እናቴ  እኔ ዘንበል ልበልላት አንገቷን ወደጎን ዘንበል አድርጋ ተቀምጣለች ፡ ሳላስበው ስሜቴ ፈንቅሎኝ ወጣ ፡ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፅ አውጥቼ አለቀስኩ ፡ እናቴ እጇ መንቀጥቀጥ ጀመረ  አፍጥጣ ስታየኝ ቆይታ ፡አፏን ለመክፈት ታገለች ፡ልትናገር ፈልጋ ግን አልቻለችም ሲያቅታት የዕንባ ዘለላዎችን ታወርድ ጀመር ፡ ይሄኔ ሴትዮዋ ድንገት ወደቤት ገብታ "እልልልልል ....."ማለት ጀመረች ፡ ቀናብዬ አየዋት ምንድነው እልል ታው የኔ መምጣት ነው  ፡የእናቴን እጅ ያዝኳቸው እንቅጥቃጤ አቸው ለጉድ ነው 
"እሰይ እሰይ ዘውድዬ ተንቀሳቀሰች ፡እንኳን መጣህላት ፡ልጇን ስታይ አነባች "አለች  ተነስቼ ወደ ሴትዮዋ ሄድኩና ያዝኳት"ማነሽ አንቺ ?ምን ሆና ነው?"አልኳት
"ኧረ ዋይ እኔን ልቀቀኝማ ፡ "አለችኝ እያረጋጋችኝ
"እሺ ምን ሆና ነው እናቴ "አልኳት
"እሷማ እንግዲ የዛሬ አመት አካባቢ ነው ፡እኔም እንደው ተቀይማ ከቤተሰቡ ተነጥላ የቆየች እህቴን አፈላልጌ ያገኘውበት ሰሞን ነው ፡ እንደው ይቅርታዋን ተቀብዬ ተደስቼ ፡ ለባለቤቴም ጎጃም ነው የምንኖረው ደውዬ አሳውቄ እህቴን ማገኘቴን ፡ እሱም ፡በደስታዬ ተደስቶ ነበረ ፡መቼም ካገኘዋት በዋላ በቃ እንግዲያውስ ያለችበትን ካወቅኩ ፡ተመልሼ ወዳገሬ ልሄድ እያሰብኩ ፡ እንደው በደንገት አይሆኑ ወነች ዋይ እህቴ ፡  "ብላ ለቅሶዋን ጀመረች
"እሺ ምን ተፈጥሮ ነው "አልኳት ፡አንድም ቀን  እህት አለኝ ስትል ሰምቻት አላውቅም ፡ ለነገሩ መቼ ምን ተናግራ ታውቅና
"እንደው ወደ ማታ ነው አቤልም አልገባ እኔና እሷ እየተጫወትን በር ተንኳኳ ልትከፍት ሄደች ፡እና ብዙ ስትቆይብኝ ምን ሆነች ብዬ ስወጣ ፡ በሩ ላይ ተዘርራ አገኘዋት ፡ እንደው አንዴ ጩኽቴን ብለቀው ፡ እንደው አቤል ከየት መጣ ሳይባል ደረሰልኝ ከዛማ ለሁለት ሆነን ምኑን ከምን እናርገው ፡ ብቻ አቤል ተሸክሟት እኔ ከዋላዋላ ፡ ክኒሊክ አደረስናት ፡ ግን እነሱ የሚችሉትም አልመሰለኝ ፡አንፑላንሱን ጠርተው ከሌላ ወስፒታል ወሰዷት ግን ይኽው እኔ ዝግት ልበል ድንጋጤና አወዳደቋ ከፉመሆን ተጨማምሮ ተዘግታ ቀረች "ብላ ለቅሶዋን ቀጠለች
"እንዴት ማን እንዳንኳኳ አላያችውም ገፍትረዋት ነው"
"ኧረ ምኑን አውቄ  አኪሞቹ ስትወድቅ አናቷን ተመታለች ፡ቀስበቀስ ደናትሆናለች ነው ያሉት ይኽው አመት ሆናት ያው ነው እኔም ከባሌም ተጣልቼ እዚሁ ነኝ እንዴት አንድያ እህቴን እንዲሆና ልተዋት"
"ለፖሊስ አላሳወቃችሁም "አልኳት ግራ ገብቶኝ
"እሱማ እኔ ደጋግሜ ብዬ ነበረ ፡ አቤል ነው ምንም አያረግም ፡ ያለኝ "አለችኝ
"አሁን እሱ የት ነው "ብዬ ጮውኩ ፡ይሄ ተንከሲስ ምን አድርጓት ነው ፡ ድሮም የእናቴና የሱ ግንኙነት በሬ ካራጁ ነው ፡ እናቴን ጠጋብዬ አየዋት በፍቅር አይን ያየችኝ መሰለኝ እጄን እጇ ውስጥ ሳስገባው ያዝ አደረገችኝ ፡ የአቤልን መምጣት በጉጉት መጠባበቅ ጀመርኩ ፡ ወይኔ እናቴን የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ,,,,,,,,,,,,,

ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
3.8K viewsTsiyon Beyene, 05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 21:27:41 የ እናቴ ልጅ
ክፍል አስራ ሁለት

አንድ ነገር ስትይዝ ወይም በበነገው የሆነ ጉዳይ ካለህ ፡ አንተም አትተኛ ሌቱም ቶሎ አይነጋ ፡ የሌለ ነውቅርፍፍ የሚልብህ ፡ በዛላይ እያነሳህ የምትጥላቸው አሳቦች መብዛቱ ፡  በባዩሽ ሁሌም እንደቀናው ነው በነገራችን ላይ ፡ከተኛች  ምንድነው የሚባለው ...አዎ  መትረየስ ቢጮህ  አትነቃም ...ብዙ ጊዜ ማማ ለሊት ጡጦ ፈልጋ ወይም ዳይፐሩ ሲረጥብባት ፡ታለቅሳለች ፡ባዩሽ  አትሰማም ፡ ሐዛ ብዬም ነው  ማማን አዳሯን ከኔጋር የማደርገው ፡ ይህ የለሊቱ የህፃናት መቀስቀስ የሚያውቅ ያውቀዋል ፡ቀውጢ በሆነ እንቅልፍ ውስጥ ስትሆን ፡ የህፃን ለቅሶ ስትሰማ  አስበኽዋል ፡ከዛ ተነስተህ ታባብላለህ ፡አልሆን ይልሃል ወተቱ ማለቁን አስተውለህ ጡጦውን አጥበህ ወተት ትሞላለህ ፡ ዝም አልል ሲሉህ ገለጥለጥ አድርገህ መሽናታቸውን ታያለህ ፡ እናም ተራርሰው ታገኛቸዋለህ ፡ ዳይበር ትቀይራለህ ፡እንቅልፍ እንደሰካራም ቢያንገዳግድህም መፍትሄው እሱው ነውናትችለዋለህ  ፡ አስበው እኔ በድንገት ከነዚ ሁሉ ነገሮች ጋር ነው የተፋጠጥኩት ፡ከኑሮ መክበድ ብቻጋርም አይደለም ፡ አንዳንዴ ሳስበው የእናቴን መከራ ሊያሳየኝ ይሆን እንዴ ፡ እላለው ፡ ለብቻዋን በዕድሜ ተቀራራቢ የሆንነውን ልጆቿን አሳድጋለች አንድም ሰው ነብስ እስካወኩበት ጊዜ ድረስ ሲያግዛት አላየውም ፡እና ሳስበው የሁሉም እናቶች ብርታት አስደናቂ ነው ክብር ይገባቸዋል ብያለው። ስለ እናቴ ግን ሌላው ቀርቶ በምን ገቢ እንደምታስተዳድረን እስከዛሬም ድረስ ግልፅ አልሆነልኝም ፡  በእርግጥ በግንብ የተከለለ የተንጣለለ ግቢ ያለው  ቤት አለን  የክራይቤት አደለም ሰርቢስ ቤቶች ቢኖሩም አንድም ቀን አከራይታ አታውቅም ፡ ነገርግን ከሆነ ቦታ ገቢ አላት ግን አትነግረንም ፡ በወር አንዴ ብቻ ትወጣና ቆይታ ትመጣለች የዛን ሰሞን በወሩ መጀመሪያ ማለቴ ነው ፡ጤፉም አስቤዛውም ፡ለኔም የኪስ ገንዘብ ትሰጠኛለች ፡ከየት መጣ ምናምን የመጠየቅ መብት የለኝም ፡  እንዲ ናት እንግዲ እናቴ በሚስጥሮች የተሞላች ፡ ማውራት የማትወድ ..........
ባዩሽን ቀስቅሼ ከማማጎን እንድትተኛ ነገሬ ፡ወጣው ፡ የጠዋቱ ብርድ ያንዘፈዝፋል የአምሌ ዝናብ ነው ፡ወይ አይዘንብ ንጭንጭ ያደርገዋል ፡የለበስኩት ባለሹራብ ጃኬት ከብርዱም የሚያስጥል አይመስልም ፡ በዛላይ ከሰውነቴ ተጣብቋል  ሰውነቴ ጨምሯል ፡የምወፍረው እንደው ዝምብሎ ስላልሆነ ተመስገን እላለው በተስተካከለ ቁመናላይ ፈርጠም ያለ አካል ነው ያለኝ ፡ ብዙዎች ይወዱልኛል ፡አዲስ የያዝኩት ጓደኛዬ ወፈር ያለ ነው ፡እና ብዙ ጊዜ ይሄን ሰውነት ይዤ ስንቷን ነበር ጠብ የማደርግበት ይለኛል እስቃለው ፡ እውነት ሴቶች በቁመናህ ማማር ብቻ ጠብ የማለት ጉዳይ አልዋጥልህ ይለኛል ፡  ምናልባት ለሳምንታት ሊሆን ይችላል ፡ከዛ በዋላ ሴት ልጅ ከአንድ ወንድ የምትፈልገው ብዙ ነገር አላት ፡ እሱን ለሴቶቹ ልተወውና ፡  .....
ከአጠና ተራ    ሰባተኛ አቶቢስተራ በሚለው ታክሲ ተሳፍሬ ገባው ፡ የተቀመጥኩት ሦስተኛ ተደርቤ ነበርና ምቾት አልሰጠኝም ፡ እስከምወርድ ተጨነኩ ፡ ይሄ አዲሳባውስጥ የእዝብ ቁጥር መጨመር በየሄድንበት እንግዲ ምርጫ ስለሌለን ያቻችለናል አልችልም ብትል ምን ታመጣለህ !
ሰባተኛ ወርጄ የእስታዲየምን ታክሲ ለመያዝ ተወዘወዝኩ ፡ በዛላይ ካፊያው ፡ ከምሆድበት ቦታጋር ተዳምሮ ይብስ አሸበረኝ ፡ ወደታች አንድ ታክሲ ገንጠል ብሎ ሲሄድ ሰውን ቀድሜ ሮጥ አልኩኝ ፡ ስደርስ 'ይቅርታ አይጭንም 'አለኝ ኤጭ ብዬ ስመለስ  ፡ አንድ ፖጃሮ መኪና ውስጥ የተቀመጠሰው እጅ ተውለበለበልኝ ፡ ጠጋ ስል ሴት ናት ፡ ዕድሜም ተቀራራቢ ነን 'ውይ ለዚች ደሞ ይሄን መኪና ማን ሰጥቷት ነው ፡መቼም በዚ እድሜዋ ሰርታ አትገዛውም ፡ወይ ከውጪ መጥታ ፡ወይ አባቷ አብታም ነው ወይም ሙሰኛ ነው ፡ወይም አብታም ባል አላት ፡ወይ ወይም...'አልኩ ግን ምን አገባኝ ፡! በጣም ስጠጋት ፡አሁን ገባኝ በራሴ መንገድ ትንፋሽን ለሰከንድ የሚያቋርጥ ውበት ፡ ለዚማ እንኳን መኪና ዓለምን ይሰጧታል አልኩ ፡
"ግባ ወንድም "ብላ የመኪናውን በር ስትከፍተው ፈዘዝኩ
"ምነው ወደ እስታዲየም አይደለህም እንዴ?"አለችኝ
"ነኝ እሱማ "
"እና ግባሃ ታዲያ እኔም እኮ ወደዛው ስለሆንኩ ላድርስህ ብዬ ነው ፡ "አለችኝ ተረጋግታ እና በትላልቅ ውብ አይኖቿ ውስጤ ድረስ ሰርስራ እያየችኝ ፡አስተያየቷ አስጨነቀኝ ፡የሌለ አይን አፋር አድርጎኝ ቁጭ አለ
"እሺ ካላስቸገርኩሽ "አልኳትና ገባው ዋው ድሎቱ ፡ ቅድም ካጠና ተራ ስመጣ መቀመጫዬ አሳዝኖኝ ነበር ኪኪኪኪ
"ለምን ታስቸግረኛለህ ፡በነገራችን ላይ አውቅሃለው ፡ግን እረጅም ጊዜ አላየውህም "አለችኝ
"እኔን ታውቂኛለሽ ከምር?የት?"ብዬ ጠየኳት
"የሚገርም ትውውቅ ነው ያለን እዛው ኤግዚብሽን አካባቢ ነው የማውቅህ ከጉርምስናህ ጀምሮ ሁሌም ግን ስትደባደብ ነበር የምታጋጥመኝ ፡ እውነት በጣም ነበር የምትገርመኝ ፡ አንድም ቀን እረፍት የለውም እንዴ ፡ብዬ ሁላ እናቴን ጠይቄያት አውቃለው ፡"
"ከምርሽ !?"አልኳት አፈር ብዬ
"አዎ የእኛ ቤት ከእናተ ቤት በርግጥ ወደውስጥ ገባ ይላል ነገርግን ከእናቴ ጋር ወደ ሱቅ ስንሄድ ብዙ ጊዜ ሰፈር ውስጥ አይክ ነበር ወይ ሰትደባደብ ወይ ስትጎማለል ኪኪኪኪኪ እውነትበጣም ነበር በመገረም የማይህ ፡አሁንእንደዛ አነህ ግን "አለችኝ እየሳቀች ሳቋ እንዴት እንደሚያምር ፡  ይገርማል ሰፈራችን እንደዚህችም አይነት ሴት ነበር ኧረ እኔ ማንንም ልብ ብዬ አይቼም አላውቅ ፡ እንዳለችው ትንሽ ነገር ያስከፋኝና ሰው ካልገደልኩ ነው በዛላይ የሱሴ ብዛት ፡ ይኽው አሁን በማማ ምክንያት ሁሉም ቢቀርም ፡  እኔ የሌለብኝ የሴት ሱስ ነው  ቢኖርብኝማ ይእችን ልጅ አያት ነበር ሆሆሆ እንዴት ነው የምታምረው ፡ ወንድነቴን አስታወሰችኝ እኮ ....
እስታዲየም ስንደርስ ወሬያችን አላለቀም ነበር ፡ፀብ ማቆሜን ስነግራት እየሳቀች ተመስገን አለች ሆሆ የዚን ያክል አሸባሪ ነበርኩ እንዴ አልኩ ለራሴ ፡
ስልኳን ሰጠች ለማመን ከበደኝ ፡እንዲ ታደርጋለች ብዬ አላሰብኩም እንኳን በራሷ ፍቃድ ተጠይቃም የምትሰጥ አትመስልም ፡ ተስገብግቤ ነው የተቀበልኳት ፡እሷ እስታዲየም ጥላኝ የምሄድበት ስላለ ነው እንጂ ሰፈር አደርስህ ነበር አለችኝ አመስግኛት ሄድኩ፡የልቤን ምት ጨምራብኝ ሌላ ስራ ጀመርኩ ልቤ ውስጥ
ሰፈር ስደርስ ላለመታወቅ ሽልሽል እያልኩ ነበር ፡ተሳክቶልኝ ፡ማንም ሳያየኝ ቤት ደርሼ የቤቱን መጥሪያ ተጫንኩት ,,,,,,,,,


ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.3K viewsTsiyon Beyene, 18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 21:52:44 ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ?
113 viewspetelare Stay true, 18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 21:45:18
ሙሉቀን ስትስቁ መዋል ከፈለጋችሁ ቻናላችንን በመቀላቀል በሚለቀቁ ቀልዶች እራሳችሁን አዝናኑ

Https://T.me/+GlFsizX-_8sxNjM0
Https://T.me/+GlFsizX-_8sxNjM0
246 viewspetelare Stay true, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 21:39:12
ሙዚቃ ይወዳሉ እንግዲያውስ ይሄ ቻናል ሊያመልጦት አይገባም አዳዲስ ሙዚቃዎች የድሮ ሙዚቃዎች በቃ ምን ልበላችሁ የፈለጋችሁትን ሙዚቃ ማግኘት ትችላላችሁ።
የTelegram ምርጥ ምርጥ ሙዚቃ መረጥ መረጥ አርገው join ይበሉ ይደሰቱ ደሞ በትንንሽ Size መሆኑን አይዘንጉ
ከናንተ ሚጠበቀው JOIN ማለት ብቻ ነው

https://t.me/joinchat/AAAAAFZz4SvSUUi_7-bXwQ
303 viewspetelare Stay true, 18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 19:03:13 የ እናቴ ልጅ
ክፍል አስራ አንድ

አንዳንድ ሰዎች ልብ ብለን ካየን አብዛኛውን ጊዜ ከራሳቸው ይልቅ በሌላሰው ችግር ነው የሚቸገሩት ፡ የቤተሰባቸው አካል የሆነ ሰው ወይም ጓደኛቸው ፡ በሆነ ሰው የተበላሸውን ነገር ለማስተካከል ሲጥሩ ፡ ጊዜ አቸውን አቅማቸውን ያለ አግባብ ያባክናሉ ፡  እንደ እውነቱ ሁሉም የየራሱን የቤት ስራ ቢሰራ ኖሮ  ስንት አስቸጋሪ ነገሮች በተቀየሩ ነበር !! ነገርግን አንዱ በሕይወት ውስጥ ደክሞ ሲሸሽ ሌላው  ከራሱ ጋር አብሮ የሱንም ድክመት ተሸክሞ ለመለወጥ ይፍጨረጨራል ፡  ከእይወት እንደተረዳውት  ማንም የማንንም ሸክም መሸከም የለበትም ፡የሚለውን ነው ። ከቻልክ ሸክሙ እንዲቀልለት መንገዱን ማሳየት ነው!
ባዩሽ ሰሞኑን እንደ አዲስ ሰው ነው ስገባም ስወጣ የምታየኝ ከለት እለት አስተያየቷ ከበደኝ ፡ እይታዋ ውስጥ አዘኔታም ቢኖርም እንደሞኝ አድርጋም የቆጠረችኝ መሰለኝ ፡  ይህ ሁኔታዋ ደሞ እራሴን ደጋግሜ እንድፈትሽ አደረገኝ ፡  ለምንድነው እውነታውን የማላወጣው ፡ ለምን ለእናቴ ደብዳቤ አልፅፍላትም ፡እኔን ማየት ባትፈልግ እንኳ ፅሑፉን ማንበቧ አይቀርም ብዬ አሰብኩ ፡ይሄን አሳብ ደጋግሜ አወጣው አወረድኩት ፡ በመጨረሻ ወሰንኩና ለባዩሽ አማከርኳት ፡
"በዩ አንድ አሳብ አለኝ "አልኳት እራት በልተን ፡ማማንም አስተኝታት ፡ቡና ለማፍላት ስትቀመጥ ጠብቄ።አይን አይኔን እያየች ፡በጭንቅላቷ እንድቀጥል ምልክት ሰጠችኝ
"ምን መሰለሽ ለእናቴ ደብዳቤ ለመፃፍ አስቤ አለው ፡ "ስለምን ጉዳይ ?"አለች ባላወቀ
"ስለ አቤል ፡እንደዋሻት እና ዕፃኗ የኔ አለመሆኗን  ፡ብቻ ብዙ ነገር ወቀሳም ጭምር "አልኳት
"እንዴ ናቲዬ አሁን እሱ በድንገት የሚነገር ነገር አይደለም በመጀመሪያ ዝም ብለህ ወደቤት ተመልሰህ የእናትህን ደንነት ማረጋገጥ አለብህ እሱ ቀስ በቀስ የሚደርስ ነው "አለችኝ
"እና ዝም ብዬ ሄጄ የማትፈልገኝን እናቴን ማየት አለብኝ?አንቺኮ ስላልገባሽነው  የጥላቻዋን ጥግ ብታዪው ኖሮ አጠገቧ መድረስ ያስፈራሻል ፡ እኔ ምን ወዲወዲያ አስባለኝ እስካሁን ንዴቷ ይበርዳል ስለዚህ ዕፃኗ የኔ አለመሆኗን አስረግጬ ነው የምፅፍላት ፡ "
"እንደሱማ አይሆንም እውነት ብትቀበል እንኳ ከዚ በዋላ ማማን አሳልፎ የመስጠት አንጀት አለህ ፡ "አለችኝ ፡ የሰላም እንቅልፋን ወደምትለጥጠው ማማ እያሳየችኝ ፡ፈገግ አልኩ
"በዩ ማማ እኮ መቼም አትለየኝም ምክንያቱም በተዘዋዋሪ ያው ደሜ ናት የትም አላጣትም ቤተሰቤ ናት ፡"አልኳት ፡ ያ ተንከሲስ ልጅ ቢያምን እንኳ ማማን አሳልፌ አልሰጠውም የምፈልገው የእናቴን ይሁንታ ብቻ ነው ፡
"እሺ እናትህ ማወቋን እኔም የምፈልገው ጉዳይ ነው ነገርግን ከደብዳቤው በፊት ሄደህ እያት ምን አልባት ነገሮች ተቀይረው ይሆናል ሁለት አመት ቀላል አይደለም የሰውልጅ አሳቡን ለመቀያየር አንድ ቀን ይበቃዋል ባሁን ጊዜ ፡ ስለዚ ሄደህ በአካል ተገናኛቸው ወንድምህም ቢሆን ተፀፅቶ ይሆናል ፡የዕፃኗ እናትም ብትሆን አርፋ ላትቀመጥ ትችላለች ፡ "አለችኝ አንገቴን በመነቅነቅ ተስማማውላት ፡  ነገ ሁለት አመት ሙሉ ጨክኜ ከጠፋውት ሰፈር የእናቴ ቤት ልሄድ ቆረጥኩ ፡ ስወስን አካባቢው ናፈቀኝ ለገሐር ኤግዚቢሽን ማህከል እስታዲየም ፡ እሲጢፋኖስ ቤተክርስቲያን መስቀል አደባባይ ፡እሄድባቸው የነበሩት የሰፈሬ አቅርያቢያ በሙሉ ናፈቁኝ ፡ይገርማል ሁለት አመት እንዲ አጭር ናት ለካ እራሴን በማማ እና በስራ ወጥሬ አልታወቀኝም ፡ በሁለት አመት ውስጥ ቁም ነገር የሰራውት ማለቴ ለኑሮዬ የተመኘውትን መንጃ ፍቃድ በቅርቡ ማውጣቴ ነበር ፡ የገንዘብ ችግር አሁን የለብኝም እድሜ ለጉልበቴ የአቅሜን አግኝቻለው ፡  የወደፊትም አሳቤ ከዛም በላይ ነው ብዙ እቅዶች አሉኝ ማማ ጠንካራ ሰራተኛ አድርጋኛለች ፡ የነገ መሄዴን እና እናቴን ማግኘቴን ሳስበው ጨነቀኝ ፈርሃት ፍርሃትም አለኝ ፡ ,,,


ደራሲ Unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
1.5K viewsTsiyon Beyene, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ