Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 159.61K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-05-08 12:28:46 የ እናቴ ልጅ
ክፍል ሦስት .

ከቤት ወጥቼ ሰፈር ውስጥ ከሚገኝ አንዲት አነስተኛ ሱቅ ጋር ቆምኩኝ ፣ የሱቁ ባለቤት ልጅ ፣በድሪያ ትባላለች ፣ ፈራ ተባ እያለች " ምን ልስጥህ "አለችኝ ዝምብዬ ሳያት ወደዋላዋ አፈግፍጋ ቆመች ልጅ ናት የቀድሞ በጥባጭነቴ እሷም ጋር ተፅህኖ ሳያሳርፍ አይቀርም "እ ብስኩት ስጪኝ ካፒችኖ አለሽ "አልኳት በጨዋ ደንብ "አለኝ "ብላ ሰጠችኝ ብሯን ከፍያት ፣ልሄድስል ከኛ ጊቢ እልፍ ብለው የሚኖሩ ሴት ቀስ እያሉ መጥተው ቆሙ እናም ወደኔ በመዞር "ናቲ እንዴት አደርክ "አሉኝ ከዚ በፊት አናግረውኝም ሆነ ስሜን ጠርተውኝ ስለማያውቁ ደንገጥ አልኩ በዝምታ ሳያቸው "ምነው ናታን የእግዜር ሰላምታ እኮ አይከለከልም "አሉ ለስለስ ብለው
"አይ እኔ ከዚበፊት አናግረውኝ ሰለማያውቁ ገርሞኝ ነው "አልኳቸው በግልፅ
"አሂሂሂ መቼስ ልባችን ቢፈልግስ በየት በኩል እናንተ ከሰው አትቀርቡ ፣ለነገሩ ችግሩ የእናንተም አይደለ እናታቹ ናት እንጂ እንዳትቀርቡ ያደረገች እናንተማ ያው ልጆች ናቹ የተመራችሁትን ነው "ብለው ሽሙጥ መሰል ነገር ተናገሩ ፣ዝምብዬ አየዋቸው እንደ እውነቱ ከሆነ እማማ ሸዋዬ ትልቅ ሰው ባይሆኑ በናቴ የመጣ ቱግ ባልኩ ነበር "እማማ እሺ አሁን ሰላም ይዋሉ "ብዬ መንገድ ልጀምር ስል "ቆይ ቆይ እንደው መጀመሪያ ለደናደርኩ ' ደና ይመስገን ነው መልሱ እእእ የሆነስ ሆነና እኔስ ድንገት ሳገኝህ በውስጤ የሚመላለስ ነገር ነበርና ስለ እናንተ ቤተሰብ ላናግርህ ነበር መቼም አንተ በክፉም ሆነበደግ ታገናኘን ነበር ፣"አሉ
እኚሴቲዮ እየተፈታተኑኝ ነው ግን ትህግስት ላድርግ ብዬ "እሺ ቶሎ ይበሉና ይንገሩኝ"አልኳቸው ወደበድርያ ሳይ የጨነቃት ይመስላል እጇን ታፍተለትላለች ድንቡሽቡሽ ቀይ ፊቷ ያሳዝናል ፣ወደ እማማ ሸዋዬ አተኮርኩ መልሼ
"እኔማ ምን መሰለህ መቼም እዝች ምድር ላይ በሕይወት ስትኖር ክፉ ደግ አለ እንዳማሩ ዘላለም አይኖርም ደስታም እንዳለ አዘን አለ ማገኘትም ማጣትም እንደዛው ፣ እና ከሰው ተለይቶ ምንም ነገር አይሆንም ምንድነው ሁልጊዜም ስለ እናንተ ሳስብ ምንም ብትሆኑ ለኔ ይጨንቀኛል ፣እነዚ ልጆች እናታቸው አንድ ነገር ብትሆን እድር የለ ምን የለ ከሰው አይግባቡ እላለው እንደው በሌላ ነገር አትይብኝ እና ሰው ነንና ነገ ምን እንደሚፈጠር አይታወቅም ናቲዬ አይለኛም ብትሆን አንተን ማናገር ለኔ ይቀለኛል ፣ እስኪ አንተ እናትህን እንደምንም ጨቅጭቀ የሰፈሩን እድር እንድትገባ አድርጋት ከሰው ቀስ በቀስ ትቀላቀል "አሉ መጀመሪያ ስላሟረቱብን ውስጤ ደስ ባይለውም የተናገሩት ነገር ከምር አሳሰበኝ ፣ እውነት አንድነገር ቢፈጠር አይበለውና ሆሆሆ እማማ ሸዋዬ ጭንቀት ፈጠሩብኝ
"እእእ እውነት ነው እማማ ልክ ነዎት አናግራታለው ለመልካም አሳቦት አመሰግናለው "ብያቸው ነገር ከመቀጠላቸው በፊት ፈጠን ብዬ ተራመድኩ
"ሰው ነው ብዬ ቀውስ..."ሲሉ ትንሿ በድሪያ ስትስቅ ሰማዋት "አንቺ ደሞ ጥርስሽ ይርገፍ ሻማ ስጪኝ አሁን "ብለው የውሸት እርግማን ሲያወርዱባት ፣ስትስቅ ሳልወድ በግድ ፈገግ እያልኩ ለራሴ የገዛውትን ካፒቺኖ ጨምድጄ እንደያዝኩ ሰፈሩን ለቅቄ ሌላቦታ ለመዋል ፈጠንኩ ፣ወይ እማዬ,,,,,..ኀ
እሷ እንደው ከማንም ጋር ምንም ነገር ለመነጋገር ፍላጎቱም ስሜቱም የላት እና እኔ ምን ማድረግ እችላለው ፣ በተለይ በአሁን ጊዜ ከወንድሜ አቤል በስተቀር ሰውም የላት እሱ ሁሉ ነገሯ ሆኗል አማካሪዋ መልህክተኛዋ አዛኟ ተንከባካቢዋ ...እኔን ማቅረብ በጭራሽ አትፈልግም ኧረ እሱም አልፈቀደልንም ፣አንዳንዴ እልም ብዬ ብጠፋስ እላለው እውነት ያን ያክል ለነሱ ችግር ከሆንኩ ።ሌላ ቦታ ሄጄ እራሴን ልፈትን ብዬ አስባለው የእናቴ በሚስጥር የተሞላ ሕይወት እና የታናሽ ወንድሜ እኔላይ ያለው ጥላቻ መጨመር እያሳሰበኝ መጥቷል ለምን ይሆን?,,,,,,

ደራሲ unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.7K viewsTsiyon Beyene, 09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 11:46:54 አትሮኖስ pinned «#ባል_አስይዞ_ቁማር ፡ ፡ #ክፍል_አርባ ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ያልተኖረበት የአንድ ወር ቅድመ ክፍያ ቃል ከፍሎ የሄደ ቢሆንም እሷ የስድስት ወር ተጨማሪ ቅድመ ክፍያ ከፈለች...ይሄንን ቅድመ ክፍያ ቃል ሲኖርበት ለነበረ ክፍል ብቻ ሳይሆን ከዛ ቀጥሎ  ለነበረች አንድ ክፍል ቤትም ጭምር ነው የከፈለችው። ክፍሏን እንደአዲስ ቀለም አስቀባችው.....ሙሉ እቃ ፤ አልጋ፤አነስተኛ ፍሪጅ፤ቴሌቪዠን አንድ…»
08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 11:45:58 #ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_አርባ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ያልተኖረበት የአንድ ወር ቅድመ ክፍያ ቃል ከፍሎ የሄደ ቢሆንም እሷ የስድስት ወር ተጨማሪ ቅድመ ክፍያ ከፈለች...ይሄንን ቅድመ ክፍያ ቃል ሲኖርበት ለነበረ ክፍል ብቻ ሳይሆን ከዛ ቀጥሎ  ለነበረች አንድ ክፍል ቤትም ጭምር ነው የከፈለችው። ክፍሏን እንደአዲስ ቀለም አስቀባችው.....ሙሉ እቃ ፤ አልጋ፤አነስተኛ ፍሪጅ፤ቴሌቪዠን አንድ ጠረጰዛና ሁለት ወንበሮች አስገባችበት ...እንዲህ ያደረገችው የቃልን አባት ከመቄዶንያ አስወጥታ እቤት በማምጣት እራሷ  ልትንከባከባቸው ስለወሰነች ነው።አዎ ይሄንን ዕቅድ ካቀደችበት እለት አንስቶ  በውስጧ ደስታ እየተሠማትና ከድብርቷም በመጠኑም ቢሆን እየተላቀቀች ነው።

አሁን ሙሉ በሙሉ ዝግጅቷን ስላጠናቀቀች ወደሜቅዶኒያ ሄዳ አባትዬውን   የምታመጣበት ቀን ነው።ከመውጣቷ በፊት በሞባይሏ ያዘጋጀችውን ቤት ፎቶ ደጋግማ አነሳችው...ለመምጣት  አሻፈረኝ እንዳይሏት ምን ያህል ተጨንቃ እንዳዘጋጀችላቸው   በምን ያህል መጠን ቁርጠኛ መሆኗን  እሳቸውን ለማሳመን እንዲያግዛት አስባ ነው።በዛ ላይ በማሳመኑ ስራ ቀላል እንዲሆንላት ከእሷ በላይ የሚያውቋትንና ከልጃቸው ባልተናነሰ ያሳደጓትን ጊፍቲን ይዛ ነው የምትሄደው።

የራሷን መኪና እየነዳች እግረ መንገዷን ጊፍቲን ካለችበት አንስታ መቂዶኒያ ደረስን.... መኪናዋን አቁማ ከጊፍቲ ጋር ጎን ለጎን በዝግታ እርምጃ(ያው እርጉዝ ስለሆነች)ወደ ቃል አባት ያሉበት አካባቢ ሲደርስ ያልተለመደ ግርግር ነገር ገጠማቸው...ጊፍቲን ወደኃላ ተወችና ፈጠን ፈጠን እያለች ወደፊት ተጓዘች.... ደረሰች፡፡ ከአስር የሚበልጡ ሰዎች በቦታው ይተረማመሳሉ...አንዳንዶቹ ከንፈራቸውን ይመጣሉ...የሆነ ቀፋፊ ስሜት ሳትፈልግ በግድ ወደ ሰውነቷ ሲሰርግ ታወቃት..ወደ አንድን አዛውንት ተጠጋችና"አባባ ምን ተፈጥሮ ነው?"ስትል  ጠየቀቻቸው፡፡

"ያው ሰው ከንቱ አይደል?አንድ ጓደኛችን ሞቶ ነው"

"ወይ እግዚያብሄር ነፋሱን ይማር."አልኩኝ፡፡

‹‹ወዬኔ ጋሽ ሞገስ...በቃ ሞተ "እያለች አንድ ሴት በስሯ አለፈች፡፡

"ጋሽ ሞገስ?  ይሄን ስም የት ነው የማውቀው? ስትል እራሷን ጠየቀች ተምታባት..በዚህ ጊዜ ከኃላዋ ቀርታ የነበረችው ጊፈቲ ስሯ ደርሳ ነበር.."

"ምን ተፈጠረ ?"ስትል ጠየቀቻት፡

"ሰው ሞቶ ነው?ጋሽ ሞገስ የሚባሉ ሰውዬ ናቸው አሉ"ነገረቻት

"ሞገስ?ሞገስ ማን?"አደነጋገጧ አስፈሪ ነበር፡፡

‹‹ምነው ታውቂያቸዋለሽ እንዴ?››

"የቃልዬ አባት...."
ዠው አለባት...‹‹የተምታታብኝ ለካ ለዛ ነው?"አለች፡፡

‹‹ምንድነው እየሆነ ያለው? ማነው የነካሽው ሁሉ ወድያው ይብነን ወይ ይክሰም ብሎ የረገመኝ?።ስትል አማረረች
""""
ከጊፍቲ ጋር ሆነው የቃልና አባት ቀብር በተገቢው መንገድ አስፈፀሙ....ቅልብጭ ያለች የእብነበረድ ሀውልትም አሰራችላቸው። እሳቸው ከሞቱ በኋላ በፊት የሚሰማት  ሀዘን ብቻ አይደለም እየተሰማት ያለው ።ጉልበት የማጣትና ተስፋ የመቁረጥ ሰሜት ጭምር ውስጧን እያወደመው ነው። አሁን በዚህ ሰአት እሳቸው ሀውልት ጋር ቁጭ ብላ እየተከዘች ነው፡፡

ፊት ለፊቷ ዝርፍፍ ያለች የብሳና ዛፍ ትታታለች ...የበጋው ንዳድ እሷን ብቻ ሳይሆን ዛፏንም የጎዳት መሰላት።ቅርንጫፎቾ የተሸከሞቸው አብዛኛው ቅጠሎች ወይበዎል።አረንጎዴ ቀለማቸው ተመጦ ወደ ቢጫነት እያዘገሙ ነው።ድንገት ከወደ ምዕራብ በኩል ብዛት ያላቸውና ከእሷና ከዛፉ በተቃራኒው በውበት ያሸበረቁ ወፎች ተንጋግተው  መጥተው ሰፈሩበት ...ግማሽ የሚሆነው ቅጠሉ እየተቀነጠሰ ወደ መሬት ረገፈ...፡፡አዘነች ውስጧ እስኪሰበር ድረስ አዘነች..፡፡ያዘነችው ለዛፉ በማዘን አይደለም ለራሷ እንጂ...የእሷም ለዘመናት የገነባችው ተስፋዋ ድንገት መጥቶ ህይወቷን በነቀነቀው መከራ ልክ እንደዚህች ዛፍ ቅጠሎች ነው እርግፍ ያለው።እርግጥ ዛፍ ከጥቂጥ ሳምንታት በኃላ ክረምት ገብቶ ዝናብን ሲያርከፈክፍለት በደስታ ከድርቀቱ አገግሞ እንደሚለመልም መወየብ ታሪክ ሆኖ አረንጓዴ እንደሚለብስ ታውቃለች .‹‹.የእኔስ  ዝናብ መቼ ይሆን አስገምግሞ መጥቶ የሚያርሰኝ እና ከድርቀቴ የሚፈውሰኝ።›ስትል ጠየቀች…

ሰው ግን  በሚሊዬን ህያዋን መካከል እየኖረ ሚሊዬን ህያዋንን በመንገድ ላይ እየገፈተሩና እየገላመጡ መጥቶ እንዲህ  በድን ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ ከበድን ጋር ማውራት.?››ስትል በራሷ  ድርጊት ተደመመች፡፡

"ያው የቃል አባት ስለሆኑ የእኔም አባት ኗት...ደግሞ ያው አባትም የለኝም። ምን አልባትም እንደእርሶ የሞተ ይመስለኛል..እንደዛ ከሆነም  የሁለታችሁንም ነፍስ አምላክ ይማራት።››ትንፋሽ  ወስዳ ጉሮሮዋን በምራቋ ካረጠበች በኃላ ንግግሯን አራዘመች፡፡

<<እና ይሄውሏት ቃል ጥሎኝ ከጠፍ በኃላ ለቀናት ሳዝንና ስጨነቅ ከርሜ ነበር እና ድንገት ስለእርሶ ትዝ ሲለኝ ውስጤ ተስፋ ሰነቀ...የፈለገ በእኔም ሆነ በጠቅላላ አለሙ ቢጨክን በአባቱ አይጨክንም ስል አሰበኩ፡፡በእርሶ ላጠምደው ወሰንኩ። ያው ያውቁ የለ እኛ ሴቶች ያፈቀርነውን ወንድ የራሳችን ለማድረግ የተለያዩ ስውር ዘዴዎችን እንጠቀማለን...ለምሳሌ የምናፈቅረው ወንድ አልጨበጥ ብሎ ካስቸገረን ሌሎች ወንዶች እየፈለጉንና እየተከተሉን እንደሆነ እንዲያውቅ እናደርጋለን...ቅናት ውስጥ ገብቶ ከመቀደሜ በፊት ልቅደም እንዲል እኮ ነው ።ወይም ደግሞ የተሳሳትን በማስመሰል  ልጅ እናረግዝና ውሳኔው ከባድ እንዲሆንበት እናደርጋለን ….አዎ በፍቅር ጉዳይ ሴቶች ቁማርተኞች ነን፡፡

እንደሚያውቁት እኔ ደግሞ ቃልዬ አብሮኝ ስለሌለና  የት እንዳለም ስለማላውቅ እንደዛ ማድረግ አልችልም..ስለዚህ የነበሩኝ ብቸኛ የመጫወቻ ካርዴ እርሶ ነበሩ  ። ወደቤታችን ማለቴ ወደቃል ቤት ልወስዶት ለቀናት ለፍቼ ብዙ ብዙ ነገር አዘጋጅቼ  ያማረች ክፍል አዘጋጅቼሎት ነበር...የምትንከባከቦትም ወጣት ነርስ ቀጥሬሎት ነበር..እናም ደግሞ እስከመጨረሻው ድረስ ልንከባከቧት አልሜና ወስኜ ነበር...ከአሁን በኃላ አስርና ሀያ አመት ይኖራሉ የሚል ግምት ነበረኝ...እና በዛ የጊዜ ርዝመት ውስጥ ቃል አንድ ቀን እርሷን ለማየት ሲል ብቻ  ተመልሰሶ ሊመጣ ስለሚችል አንድ ላይ ሲያገኘን ይደሰታል..እናም ምን አልባት ዳግመኛ ጥሎኝ ለመሄድ  ልቡ አሻፈረኝ ትላለች የሚል ምኞት ሰንቄ ነበር ...እንደው ያ ባይሆን እንኳን  አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል እያልኩ ነፍሴን በተስፋ ሞልቼ ህይወቴን በጥበቃ ለማስቀጠል  ወስኜ ነበረ...ግን ምን አልባት የልቤን ሀሳብ አማልዕክቱ ሰምተው መጥተው ሹክ ብለዎት መሠለኝ የሀሳቤ ተባባሪ ላለመሆን ሞተው ጠበቁኝ። ግድ የለም አሁን በሁሉ ነገር ተስፋ ቆርጬያለሁ...እሱን ለመጠበቅ ያለኝን እቅድም እርግፍ አድርጌ ትቼዋለሁ..ግን ህይወቴን እንዴት እንደምቀጥል ምንም አላውቅም..?መቼ መሳቅና መቼ ደግሞ ማልቀስ እንዳለብኝ ግራ ገብቶኛል...በሉ ደህና ይሁኑ...አልፎ አልፎ ብቅ ብዬ አዬዎታለሁ።ቃልዬ አደራ ብሎኛል።

ልፍለፍዋን  ጨርሳ ከመቃብሩ ድንጋይ ላይ ተነሳች፡፡

ይቀጥላል
5.8K viewsአትሮኖስ, 08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 10:03:07 አትሮኖስ pinned «#ባል_አስይዞ_ቁማር›› ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ክረምቱ ሲመጣ ሰውነቷ ይሸማቀቃል።ዝናብ ትወዳለች ግን ነጎድጓድና መብረቅ ያስፈራታል። በሰማዩ ላይ ቀስተደመና ሲነጠፍ ልቧ ላይ የተጠመጠመ ኒሻን ይመስለትና ትፈነጥዛለች፡፡ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለሙ ከኢትዬጰያ መቀነት ጋር መመሳሰሉ ሁሌ እንዳስደመማት ነው።እርግጥ ሳታድግ የቀሰት ደመና የተሸመነባቸው ቀለሞች ሶስት ብቻ ሳይሆኑ…»
07:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 09:58:46 "የማይሆን ነገር ለምን ታወሪያለሽ...?መጠበቅም ከሆነ ችግር የለውም..? የገዛ ቤትሽ ሆነሽ እስከፈለግሽበት መጠበቅ ትቺያለሽ…እዚህ ማይመጥንሽ ቤት ውስጥ ግን አይሆንም፡፡"

"አይ እማዬ   አባቱ አረጋዊያን መኖሪያ ውስጥ ነው የሚኖሩት... አደራ ብሎኛል፡፡ ስለዚህ እሳቸውን ወደ እዚህ አመጣቸውና እየተንከብኮቸው እጠብቀዋለሁ..፡

."ልጄ አንቺ  ሁሉም ነገር ያለሽ ለጋ ወጣት ልጅ ነሽ.. እንዲህ ባለ የኪራይ ቤት ኩርምት ብለሽ የምትኖሪበት ምክንያት አይታየኝም ..ወደ አደግሽበት ቤት መመለስ ካልፈለግሽ እንኳን  የራስሽ አፓርትመንት አለሽ...እዛ ገብተሽ መኖር ትቺያለሽ..ከፈለግሽም አባቱን ወደ እዛ ወስደሽ በሞጎዚት እንክብካቤ እንዲደረግለት ማድረግ ትቺያለሽ… እኔ ምንም ተቃውሞ የለኝም፡፡
እናቷ ቀኑን ሙሉ እሷን ለማሳመን ስትጨቀጭቃት  ውላ በመጨረሻም ተስፋ በመቁረጥ በሀዘን ተሰብራ ወደቤቷ ተመለሰች፡፡

ይቀጥላል
5.9K viewsአትሮኖስ, 06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 09:58:46 #ባል_አስይዞ_ቁማር››


#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ክረምቱ ሲመጣ ሰውነቷ ይሸማቀቃል።ዝናብ ትወዳለች ግን ነጎድጓድና መብረቅ ያስፈራታል። በሰማዩ ላይ ቀስተደመና ሲነጠፍ ልቧ ላይ የተጠመጠመ ኒሻን ይመስለትና ትፈነጥዛለች፡፡ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለሙ ከኢትዬጰያ መቀነት ጋር መመሳሰሉ ሁሌ እንዳስደመማት ነው።እርግጥ ሳታድግ የቀሰት ደመና የተሸመነባቸው ቀለሞች ሶስት ብቻ ሳይሆኑ ሰባት እንደሆኑ ማወቅ ችላለች።ግን ደግሞ ማወቅና ማመን ይለያያል...ዛሬም አይኖቾን አንጋጣ ቀስተደመናውን ሳታይ በትክክል ወደውስጧ ደምቀው በመግባት የሚውለበለብት እነዛው በልጅነቷ የምታውቃቸው ሶስቱ ቀለማት ብቻ ናቸው።አረንጓዴ ቢጫ ቀይ..."አንዴ አትለከፍ"ትላለች አክስቴ አዎ ልክፍት ነው።››አለች
በማግስቱ ጥዋት መድህኔ መጥቶ ጊፍቲን ወሰዳት….ስራ ስለምትገባ ቅያሪ ልብስና ለሁለቱም የሚሆን ቆንጆ ቁርስ አሰርቶ ነበር  ይዞ የመጣው….ልክ የእሷ እንዳልነበረና ከዚህ በፊት እንደማታውቀው ወንድ አይነት ትክ ብላ አየችው…አሳዛኝና እንስፍስፍ ወንድ ሆኖ ነው ያገኘችው...እንስፍስፍ ያለችው አፍቃሪ ላለማለት ጎርብጦት ነው….‹‹አሁን ጊፊቲን ካገኘ በኃላ ተቀይሮ ነው ወይስ በፊትም ከእኔ ጋር እያለ እንዲህ ነበር ..?››በወፍ በረር ወደኃላ መለስ ብላ ለእሷ የሚያደርግላትን እንክብካቤዎች ለማስታወስ ሞከረችና ሽምቅቅ ብላ ቶሎ ተመለሰች‹‹…ከእሱ ምንም የተለወጠ ነገር የለም ልዩነቱ እኔ መሆኔና ጊፊት መሆኗ ላይ ነው…እሷ ከእሱ የሚሰጣትን ፍቅርና እንክብካቤ በትህትና እና በምስጋና ተቀብላ በፈገግታ ምላሽ ስትሰጥ እኔ ግን በወቅቱ አደርግ የነበረው በብስጭት በመግፋትና በተቃውሞ ነበር ሞራሉን የምሰብረው….እንደውም አሁን መጠየቅ ያለብኝ ያን ሁሉ ጊዜ እንዴት ታግሶኝ ኖረ….?. ›ስትል ድምዳሜ ላይ ደረሰች፡፡
ልብሷን ቀየረችና ካመጣው ቁርስ አንድ ሁለቴ ጎርሳ ጉንጩን ሳመችውና ስትወጣ መድህኔ ደግሞ ወደልዩ ዞሮ‹‹…እንዴት ነው ግፍቲን ቢሮ ካደረስኮት በኃላ መጥቼ ወደቤት ልውሰድሽ እንዴ.?.››ሲል ጠየቃት
‹‹አይ አልፈልግም..አላየህም እንዴ .?.መኪናዬ እኮ እዚህ ግቢ ውስጥ ነች…››
‹‹እንዴ..ለመንዳትም አቅም የለሽ ..መጥቶ ይውሰድሽ››ጊፍቲ መሀከል ገባች…‹‹.ይቺ ልጅ በፊት ሳገኛት እንደገመትኮት አይነት አይደለችም..ቀናና ጥሩ ሰው ነች..አሁን ሌላ ሴት ብትሆን እኮ ጭራሽ እንዲህ ስላለ ፍቅረኛዋን በግልምጫ ነበር የምታደባየው..መልሳ ብትወስድብኝስ በሚል ስጋት እራሷ ደንብራ አካባቢዋ ያለውን ሰዎች ሁሉ ታስደነብር  ነበር…››ስትል አብሰለሰለች
አይ ..አልፈለግም..እኔ በአሰኘኝ  ሰዓት መንዳት እችላለሁ..ደግሞ ብሔድም ከሰዓት ነው››
‹‹እሺ በቃ ቁረሱን  ተነሺና ብይ..እና ከፈለግሺኝ ደውይልኝ››አለና  ቤቱን ዘግተውላት ተያይዘው ሄዱ ፡እሷም መልሳ እራሷን ትራስ ውስጥ ቀበረችና ወደትካዜዋ ገባች..እራሷን ትራስ ውስጥ ስትከት የቃልን ጠረን በአፍንጫዋ እየተሹለከለከ ወደመላ ሰውነቷ በደምስሯ አማካይነት ተሰራጨና የንዝረት ስሜት በሰውነቷ ለቀቀባት፣
//
በሶስተኛ ቀን እናቷ መድሀኔ እየመራት ያለችበት ድረስ መጣች....ስታያት እንባዎን መቆጣጠር ነው ያቃታት....፡፡

"ምነው መድህኔ ..ምነው ልጄ እንዲህ እስክትሆን እንደው ሁሉ ነገር ቢቀር እህትህ አይደለች?"በማለት ወቀሰችው፡

"እትይ...ከገባችበት ነገር እንድትወጣ በተቻለኝ አቅም ያልጣርኩ ይመስልሻል...?..ሰሞኑን ስራ እንኳን በቅጡ መስራት አልቻልኩም...በቀን ከሶስት ጊዜ በላይ እየተመላለስኩ ለምናታለሁ..ግን ያው እንደምታይው ነች"አለ ..ጥረቱና ልፋቱ መና ስለቀረበት ቅር እንዳለው በሚያሳብቅ የምሬት ንግግር

የልዩ እናትም ከጠንካራ ንግግሯ መለስ አለችና"ልጄ የቻልከውን እንደምትሞክር አውቃለሁ ..የምናገረውን አትይብኝ ደንግጬ ነው"አለችው

"ችግር የለም ይገባኛል....አሁን እናንተ አውሩ ...እዚሁ አካባቢ ነኝ… ስትጨርሺ ደውይልኝ።"ብሎ እናትና ልጅን አፋጦ ወጥቶ ሄደ...እንደዚህ ያደረገው በነፃነት እንዲያወሩ በማሰብ እንደሆነ ሁለቱም ገብቷቸዋል ።ልዩ ግን ምንም የምታወራበት ጉልበት የላትም...ለዛውም ከእናቷ ጋር"

"ልጄ በራሴ አፍሬያለሁ...እኔ እኮ እራሴን እንደዘመናዊና ግልፅ እናት ነበር  የምቆጥረው ..ግን ተመልከቺ ልጄ በዚህ ልክ የምታፈቅረው ሰው ኖሮ እንኳን አላውቅም...."

"እማዬ እሱ የእኔ ጥፍት ስለሆነ አትዘኚ..."አለቻት።

‹‹አይ ልጄ ...ለነገሩ ተይው አሁን ነገሮች ከተበለሻሹ በኃላ ብናወራው ምን ፋይዳ አለው....?..አሁን ይበቃሻል ማልቀሱም ማዘኑም በገዛ ቤት ያምራል...ልጄ ወደ ቤታችን እንሂድ"አለቻት ፈራ ተባ እያለች...ልዩ ምንም አላለቻትም… የውስጧን ጥንካሬ አሰባስባ ቀስ ብላ ተነሳችና እግሯን እየጎተተች ወደ መኝታ ቤት ስትራመድ ውስጥ ገብታ በራሷ ላይ ልትቆልፍ መስሏት የሰጋችው እናት"ወዴት እየሄድሽ ነው ልጄ?"ስትል ጠየቀቻት፡፡

"መጣሁ… የማሳይሽ ነገር አለ›› በማለት ወደ ውስጥ ገባችና  ማንጠልጠያ ላይ ከተንጠለጠለው ቦርሳዋ ውስጥ እጇን ሰዳ  የምትፈልገውን እቃ ያዘችና ወደሳሎን ተመለሰች..."
እናቷ ፊት ለፊት አስቀመጠቻት ...እናቷ ደንግጣ አንዴ እሷን አንዴ ጠረጰዛው ላይ ያለውን ዕቃ በማፈራረቅ ታየው ጀመር… ‹እማ ..በቀደም ለት  ዝግጅት አለብኝ ብዬ እንደዛ ለግማሽ ቀን አምሬና ተሽቀርቅሬ እነዚህን ሁለት ቀለበቶች  ገዝቼ  ወደ እዚህ ቤት የመጣሁት ለቃልዬ ቀለበት ላስርለት ነበር..፡፡.በድፍረት እንዳፈቀርኩት ነግሬው እንዲያገባኝ ልጠይቀው ነበር...ስደርስ ግን ሁሉን ነገር ጣጥሎ ገዳም እንደገባ  የሚገልፅ ደብዳቤ ጥሎልኝ ሄዷል...ይሄ ሁሉ የእኔ ጥፍት ነው ። አረባም ፡፡››

"ምን አጠፋሽ የእኔ ማር....?.."

‹‹ምን ይሄን ሁሉ ጊዜ አዘገየሸ...ከ15 ቀን በፊት ላደርገው እችል ነበር እኮ...ከወር በፊትም ባደርገው ጥሩ  ነበር"

"ልጄ እንደው ቢጨንቅሽ ነው...ይሄ እንደሚመጣ በምን ልታውቂ ትቺያለሽ....?.."

"ደግሞ የዛሬ ሳምንት በጣም አበሳጭቼዋለሁ..››

"ምን አድርገሽ ልታበሳጪው ትቺያለሽ?"

‹‹ሰርቄ ነዋ...ሆቴል ልጋብዝህ ብዬ ወስጄ ሰረቅኩ...በእፍረት አንገቱን ደፍቶ የሠረቅሽውን መልሺ አለኝ .....እኔም መለስኩ ..ከዛ ሲመክረኝ ዋለ ..በማግስቱ  ይቅርታም ልጠይቀው እንደማፈቅረውም ልነግረው ቀጥሬው በሰዓቱ  ብገኝ  እንዳልኩሽ ሆነ...ዳሩ ሌባን ማን ማፍቀር ይፈልጋል?"
"ልጄ አሁን እኮ ባለፈ ነገር ዝም ብለሽ ነው የምትጨናነቂው... እንዳልኩሽ ተነሽና ወደቤታችን እንሂድ፤ከዛ  በእርጋታ እንደ እናትና ልጅ አናውራ። የሚስተካከለውን እናስተካክላለን"

"የምለውን አልሰማሽም እንዴ እማዬ?"

"ምን አልሽ?"

"እሱ ሸሽቶ ቢሄድም እኔ እኳ አግብቼዋለሁ ....ከተቀመችበት ተንጠራራችና ቀለበቶቹን አነሳች የራሷን ቀለበት አጠለቀች
"...እማዬ ደግሰሽ ባትድሪኝም እኔ አግብቼያለሁ...እና እዚሁ ሆኜ መጥቶ ይሄን ቀለበት እስኪያጠልቅ እጠብቀዋለሁ።"

"ምን ነካሽ...?በግልፅ እኳ መቼም ላይመለስ አንደኛውን ወደ ገዳም እንደገባ ነግሮሻል?..እና ምንድነው የምትጠብቂው ?እስከመቼስ ነው የምትጠብቂው?"

"እማዬ ልቤ ተመልሶ እንደሚመጣ እየነገረኝ ነው...ከሁለት አመትም ሆነ ከሀያ አመት በኃላ አንድ ቀን ተመልሷ ይመጣል...እና እዚሁ ቤት ሆኜ እጠብቀዋለሁ።››
6.3K viewsአትሮኖስ, 06:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 10:30:59 የ እናቴ ልጅ
ክፍል ሁለት

እናቴ ለረጅም ጊዜ ቤቷን ዘግታ ታስተዳድረን ነበርና ነገሩ እየገረመኝ የመጣው ማስተዋል በጀመርኩ ጊዜ ነበር እንዴት ሁለት ልጆቿን ያለምንም ስራ የሚፈልጉትን እያሟላች ማኖር ቻለች በእርግጥ ያትልቁ ቤታችን ከሰፊ ግቢው ጋር ከአባቷ በውርስ እንዳገኘችው አውቄአለው እሱንም ከታናሽ ወንድሜ አቤል ነው እሱ እንዴት እንዳወቀ እንኳ ጊዜ ሰጥቼ አልጠየኩትመ በወቅቱ ነገርግን ስራ ሳይኖራት ያን ያለፈችውን አመታት እኛን ዘግታ እራሷንም ዘግታ ባኖረችን ግዜ ገንዘቡን ማለትም ወጪዎቿን የሚሸፍንላት ማን ነበር ይሄን ለማወቅ ስል አንድ ሁለቴ ጠይቄያት ነበር ነገርግን እናቴ ለኔ መልስ ከመስጠት ይልቅ አፌን ማዘጋት ይቀላታል !
"እናቴ ?"ስላት ገና ፊቷን እንኳ ወደኔ ሳታዞር
"አቤት" አለችኝ ደረቅ ባለ ድምፅ፣ አቤል ግን ወደኔ ዞረ ምን ሊል ነው በሚል አስተያየት ተመለከተኝ
"እኔ የምልሽ ግን ያንን ሁሉ አመታት እኔ ማስተዋል ከጀመርኩበት ጊዜጀምሮ አስታውሳለው ከቤት ወጥተሽ አታውቂም ነበረ እና እንድትመልሺልኝ የመፈልገው ነገር ቢኖር ፣ እንዴት ነው የሁለታችንንም ወጪ ሸፍነሽ ልታኖሪን የቻልሽው እስከማስታውሰው አንድም ነገር አላጎደልሽብንም ይሄን እንዴት ማድረግ ቻልሽ ? ሌላው ለምን ብለሽ ነው ከቤት የማትወጪው የነበር ?"ብዬ ለመልሷ ተዘጋጅቼ አይኖቿን ፈልጌ ለማየት ሞከርኩ ፣ ለመልሱ ዘገየች አቤል ሲነጫነጭ ወደሱ ዞርኩ ገላመጠኝ የእናቴ አሳቢ ልጅ ምን ብዬ ጭንቅላቴን በምልክት ነቀነቅኩ ፣እናቴ ድንገት ብድግ ብላ " አይመለከትህም ትኩረትህን እራስህ ላይ አድርግ ሌላውን ለኔ ተውልኝ እሺ ሲጀመር የልፋቴን ውጤት እንኳ አንተ ላይ አላየውም ! ትልቅ ቦታ ጠብቄህ ነበር ተመልከት በአጉል ባህሪክ የተነሳ ከኮሌጅ ተማሪነት የዘለለ ውጤት አላመጣህም ፣ይባስ ብለህ እኔ በምሰጥህ የኪስ ገንዘብ አጉል ልምዶች አመጣህበት አንተ ስለምንም የመጠየቅ መብት የለህም ያባቱ ልጅ ..."አለች ከላይ እስከታች ስትወርድብኝ ምንም አልመሰለኝም ፣ነገርግን ሞቷል ያለችንን አባታችንን ስትወቅስ ግን ለዛውም ከኔጋር አገናኝታ አልተመቸኝም ግን የዛን ለት ምነው አፌን በዘጋው ነበር ያልኩት በላዬላይ የናቴን ጥላቻ ይብስ ጨመርኩ ፣ምግብ እንኳ ስትሰጠኝ ፊቴን አታየውም ፣
አቤል ደሞ እሳት ላይ ቤንዚን ማርከፍከፍ ይችልበታል እሷ ፊት የሚያሳየኝ ባህሪና እደጅ አንድ አይደለም ፣ በዚ ትንሽ ብናደድበትም መቼም ታናሽ ወንድም ነውና እታገሳለው የሚገርማቹ እኔ እንዲ አትንኩኝ ባይ የሰፈሩ አንበሳ ተብዬ እንኳ አቤል እንደፈለገ ቢሆን እጄን አንስቼበት አላውቅም በጣም ነው የምወደው ከእናቴስ ቀጥሎ ያለሱ ማን አለኝ ፣,,,,,,,,
ዛሬ ሃያ አንድ አመቴ ነው እና ሁሉም ነገር ጥያቄ የሚፈጥርብኝ ወቅት ላይ ደርሻለው የእናቴ ብቸኝነት ከሷውጪ ሌላ ዘመድ አለማወቅ የወንድሜ ከኔጋር ያለው የሻከረ የመጣ ግንኙነት ,,,,,,,???
ሰኞ ቀን ጠዋት ነው ክፍሌ ውስጥ ጋደም እንዳልኩ ነው ከሳሎን ቤት የሰአን እና የበርጭቆ ድምፅ ይሰማኛል እናቴ ለቁርስ እያዘጋጀችው መሆን አለበት ፣መሃዛው የሚያውድ የሻዪ ሽታም ይሰማኛል ፣ማታ ጠጥቼ ነው የገባውት እና በውስጤ ያለው ምግብ እልቅ ብሏል ስጠጣ እንኳ ብዙም አልበላሁም ፣እና ሆዴ በረሃብ ተላወሰብኝ ፣ወጥቼ ቁርስ ከነሱጋር እንዳልቀመጥ ይሄንን ልምድ በነሱ ግልምጫ የተነሳ ትቼዋለው ፣ ማድረግ ያለብኝ ወይ አፍንጫዬን መዝጋት ነው ወይም በቱን ጥሎ መውጣት ፣አፍንጫዬን ለመዝጋት ሞከርኩ አልሆነም ፣ስለዚ ተነስቼ ልብሴን ለባብሼ ፣ ወጣው ስወጣ እየበሉ ነበር ፣እናቴ "ወዴት ነው ችኮላው "አለችኝ አብሬያቸው እንድበላ የፈለገች ትመስላለች ምንም እንኳ ኮስተር ብትል ። አቤል ግን ቀበል አድርጎ "ያው በጠዋቱም ሊጋት ይሆናላ መቼም ትምህርቱም ተመርቆ ቢያልቅም ስራም አላስገኘለት እኔማ እየወሰደ የነበረው የመጠጥ ኮርስ ነበረ እንዴ ኪኪኪ"ብሎ ሳቀ ቅስሜን ሰባበረብኝ ግን ምንም አላልኩትም ከሱ ንግግር ለማምለጥ እየተጣደፍኩ ወጣው ,,,,,,,


,ደራሲ unknown

ይቀጥላል......
    ሀሳብ አስተያየታችሁን 
@Tsiyon_awit አድርሱኝ
   ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
6.8K viewsTsiyon Beyene, 07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 17:28:55 አትሮኖስ pinned «#ባል_አስይዞ_ቁማር ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ_ስምንት ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ..ይገርማል እሱ በማንኛውም አእምሮዋ በሚያመርታቸው ሀሳቦች ውስጥ የሆነ ቦታ ፈልጎ ተሸንቅሮ ሲወጣ ነው የምታየው....ስለሰማይም ታስብ ስለምድር…ስለእግዚያብሄር ይሁን ስለሰይጣን እሱ አለበት….፡፡.ደግሞ በሀሳቧ ብቻ አይደለም በህልሟም ጭምር እንጂ…..ህልሟ እኮ ስለ ምንም ሊሆን ይችላል ብቻ እሱ አለበት…ለምሳሌ እሷ እናቷ …»
14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 17:28:45 ‹‹እና ምን አለሽ…ቆይ እስኪ ልገምት…ያው እኔ ጠንከር አድርጌ የነገርኩሽን እሱ ለስለስና ሸፈንፈን አድርጎ ነገረሽ ..እንደዛነው አይደል?››..›
‹‹አዎ ትክክል ነሽ….ከእኔ ጋር ያወራነውን ነግሮሻል ማለት ነው››
አይ በፍፅም ቃልዬ እንዴት እንደሚያስብ ስለማውቅ ነው..ስለእሱ ሰዎች ሲጠይቁኝ እስከመጨረሻው እንደምቀደድ ስለሚያውቅ…..ከእኔ ጋር የተጣረዘ ወሬ ነግሮቸው እኔን እንዳይታዘብኝ ስለሚፈለግ ነው ከእኔ ጋር ተመሳሳይ ወሬ የሚያወራው››ብላ አስገረመቻት፡፡

ይቀጥላል
6.3K viewsአትሮኖስ, 14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 17:28:45 #ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

..ይገርማል እሱ በማንኛውም አእምሮዋ በሚያመርታቸው ሀሳቦች ውስጥ የሆነ ቦታ ፈልጎ ተሸንቅሮ ሲወጣ ነው የምታየው....ስለሰማይም ታስብ ስለምድር…ስለእግዚያብሄር ይሁን ስለሰይጣን እሱ አለበት….፡፡.ደግሞ በሀሳቧ ብቻ አይደለም በህልሟም ጭምር እንጂ…..ህልሟ እኮ ስለ ምንም ሊሆን ይችላል ብቻ እሱ አለበት…ለምሳሌ እሷ እናቷ  መኝታ ቤት አልጋዋ ላይ ወጥታ ፀጉሯን ስትዳብሳት በህልሟ ብታይ እሱም ወይ በመስኮት ተደብቆ ሲያያት..ወይ ደግሞ እራሱን ወደቢራቢሮ ቀይሮ ክንፉን እያማታ መጥቶ ግንባራ ላይ ሲያርፍ ታየዋለች፡፡ይሄ ሁሌ ለራሷም ሳታስበው ግርም ይላታል፡፡እንዴት የሆነ ቦታ ላይ አትረሳውም…እንዴት የሆነ ሀሳብ አሰናድታ አጣጥፋ ስትጨርስ ድንገት ከሆነ ቦታ ተስፈንጥሮ መጥቶ ከላይ በቀላሉ ይደረባል…?ይሄ እንግዲህ በዚህ ከተማ በዚህ ቤት ውስጥ ሲኖር ነበር..አሁንስ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ከሄደ በኃላ…….ምንድነው የምትሆነው?የቀንም ሆነ የሌት ህልሟ እንደሆነ ይቀጥላል? ከቀጠለስ እንዴት ልትቋቋመው ትችላለች?
እጇን ዘረጋችና አጠገቧ የተኛችውን የጊፊቲ ሆድ ላይ በቀስታ አሳረፈች…ጊፍቲም ከትራሷ ገልበጥ አለችና ፊቷን ወደእሷ ዞራ በሀዘኔታ አየቻት፡፡
‹‹ምን አለ እኔም እንደአንቺ ለቃልዬ አርግዤ ቢሆን…ማለት ልጅ አስረግዞኝ  ጥሎልኝ ቢሄድ?››
‹‹እኔም አንድ ነገር ልንገርሽ…››
‹‹ምንድነው ንገሪኝ››
‹የቃልዬን እስከ ወዲያኛው ጥሎኝ መሄድን ስሰማ ወደውስጤ ከመጣው የፀፀት ሀሳብ አንዱ ምን አለ ይሄ የፀነስኩት ልጅ የቃልዬ በሆነ የሚል ነበር..እርግጥ መድህኔ በጣም ጥሩ ኃላፊነት የሚሰማው መልካም አባት እንደሚሆን አውቃለሁ…እሱን ስላገኘሁም እራሴን እንደእድለኛ ነው የምቆጥረው…የልጅነት ህልሜንና  የዘመናት ፍላጎቴን ሁሉ ሊያሞላልኝ የሚችል ሰው ነው…ግን መድህኔን የማፈቅርበት ጥልቀት የኩሬ ያህል ሲሆን የቃልዬ ግን ውቅያኖስ አይነት ነው..እና ለዛ ነው እንደዛ ልመኝ የቻልኩት››
ዝም ብዬ ፈዛ አየቻት..ይሄን የተናገረችው ከቀናቶች በፊት በሰላሙ ጊዜ ቢሆን ኖሮ በርግጠኝነት ልዩ አንገቷን ፈጥርቃት ልትገላት ሁሉ  ትችል ነበር..አሁን ግን ያንን ማድረጉም ብቻ ሳይሆን እንደዛ አይነት ስሜት ማስተናገዱም ጥቅም አልባ እንደሆነ ተረድታለች....በዛ ለይ በመንፈስም ሆነ በስጋዋ ደንዝዛለች…
‹‹ግን ከቃልዬ ይሄን ሁሉ አመት ሳታረግዤ እንዴት በዚህች በጥቂት ወራት ከመድህኔ ልታረግዢ ቻልሽ?፡፡››
‹‹ከቀል ጋር በትንፋሽ ነው ማረግዘው?…››
‹‹ማለት….?››
‹‹እኔና ቃል እኮ  ወሲብ ፈፅመን አናውቅም››
‹‹ማለት…ብዙ ቀን እኮ እሱ ጋር አድረሽ እንደወጣሽ… ሲያደክመኝ እንዳደረ ምናምን እያልሽ ስትጎሪርብኝ ነበር››
‹‹ፈርቼሽ ነዋ…..ቃልዬን እንዳትመኚውና እንዳትቀሚኝ ..ተስፋ ላስቆርጥሽ ብዬ ነው…ማለት ከአመታት በፊት  አብሬው ብዙ ጊዜ አድር ነበር..በኃላ ግን ዝም ብሎ ማደሩ ስቃይ ስለሆነብኝ ወስኜ አቆምኩ…..››
‹‹አረ የምን ጉድ ነው..ቆይ ለምን…..?››
‹‹ምነው ገረመሽ..አንቺስ ከመድህኔ ጋር ለምን;?››
‹‹እኔ እንጃ ብቻ የእናንተን በጣም ደጋግሜ ስላመነዠግኩት ነው መሰለኝ አልተዋጠልኝም…››
‹‹መድህኔን ስለወደድኩት..ወይም ቃልዬ ሀብታም ስላልሆነ ይመስልሻል ከቃልዬ ጋር አቋርጬ ከመድህኔ ጋር የሆንኩት ነው  ወይስ አንቺ ስላለስፈራራሺኝ…?››
‹‹እና ለምንድነው?››
‹‹ሳላውቅ ድንገት ከመድህኔ ጋር ተሳሳትኩና ወሲብ ፈፀምኩ..ድንግልናዬን አስረከብኩት ….ወደቃልዬ ጋር እንዴት ልመሰለስ .. ?ሌላ ሰው ቢሆን ችግር የለውም ቃልዬ ግን?
‹‹ቃል ምን ይልሻል..?ምንም አይልሽም እኮ ነበር አንደውም በግልፅ ነበር ይቅርታ የጠየቀሽ፡››
‹‹አውቃለሁ ..ችግሩም እሱ ነው….እኔ በአእምሮው ካለሁበት ቦታ ተንሸራትቼ ወርጄያለሁ.ቃልዬ...የወርቅ ካባ አድርጎ  በብር የተለበጠ  ጫማ ተጫምቶ ወደቤቴ ሲመጣ ውስጤ በሀሤት ትደንሳለች ...ድንግልናዬን በክብር ልሰጠው ለዘመናት ጎጉቼያለሁ ።.እሱ ፍጽም ድንግል እንደሆነ አውቃለሁ.....ማወራሽ ስለስጋዊ ድንግልና አይደለም….ለዛ ግድ የለኝም...ልብ ከቆሻሻ ሀሳብ ጋር ያልተዋሰበ ንፅህ ፤ከክደትና ከማጭበርበር ጋር ያልተጋደመ  ክብር  ነው ።ለዚህም ማረጋገጫው እስሬ ሆኖ ሲያወራኝ  ልቤ ውስጥ ብርሀን ሲፍለቀለቅ ይታወቅኛል….የሆነ አካሉ የሰውነቴን ጫፍ ሲነካው ነፍሴ ድረስ የሚዘልቅ ደስታ ይሰማኛል……ድንገት አግኝቼው  ሰላም ሊለኝ  ከንፈሩ ጉንጬን በስሱ ሲነካው እንኳን .....ከልቤ  የፍቅር ደም ሲንጠባጠብ ይሰማኛል ...
‹‹ከዚህ በፊት ስለእሱ ምን እንደሚሰማኝ ነግሬሽ ነበር …? የእኔን ስሜት እኮ ነው እየነገርሺኝ ያለሽው…››
‹‹አየሽልኝ..ቃልዬ ማለት እንዲህ ነው..ሁለት ሴቶችን ጫፋቸውን ሳይነካ በተመሳሳይ የእብደት በሚመስል ስሜት አንዲያፈቅሩት ማድረግ የሚችል የተለየ ሰው ነው፡፡እሱ ለእኔ መስታወቴ ነው.. ፊት ለፊቴ ተቀምጦ በተመስጦ  ሳየው በጥልቀት ርቄ ሄዳለሁ…. እያንዳንዷን የልጅነት ጊዜዬን በምልስት አስታውሳለሁ… ሀዘኔንና ደስታዬን መልሼ አጣጥማለሁ…. እንዴት እንደተሰራው…? የት ጋር  ማደግ እንደጀመርኩና? የት ጋር ደግሞ እንደተሰበርኩ? ሁሉ እንዳስታውስ ያደርገኛል…እናም በዛ ምክንያት ቃልዬን ሳገኝ  ነፍሴ ሀሴት ታርጋለች…ውስጤ ይፍነከነካል..፡፡ግን ይሄ ስሜት ሁሌ አይደለም የሚያስደስተኝ ..አንዳንዴ ትናንቴ ፈፅሞ የሚያስጠላኝ ጊዜ አለ..አንገቴን ወደኃላ አዙሬ አይኖቼን ትናንቴ ላይ ተክዬ ማሰላሰል የሚያስከትልብኝን ህመም መቋቋም አቅም በማጣበት ጊዜ እሱን ለማግኘት ከራሴ ጋር ትግል እገባለሁ  …ምክንያት ፈጥሬ እሸሸዋለሁ….
ግን የሰዓታ ክፍተት እንኳን መቆየት ተስኖኝ  ግራ ይሁን ቀኝ ልቤ ላይ ብቻ በማለውቀው ቦታ በሆነ የልቤ ክፍል ብቸኝነት  ይለበልበኛል…መለብለብ ብቻም ሳይሆን እብጠትና ጥዝጣዜም አለው…ግን ደግሞ መቻል እስከምችል ደረስ እችለዋለሁ…ለአንድ ወይም ለሁለት ቀን..ከዛ መተንፈስ ሲያቅተኝና ከአቅሜ በላይ ሲሆን ያለምን ማቅማማት ወደ አለበት በርሬ እሄዳለሁ ፡፡ፊቱ እገተራለሁ…የተጨማደደ ፊቱ በደስታ ፀደል ሲፈካ…ተከርችሞ የነበረ ጥርሶቹ ተፈልቅቀው  መሳቅ ሲጀምሩ አይና እደሰታለሁ....ተንደርድሬ ሄጄ እንጠለጠልበታለሁ….ያለምንም ቅሬታና ወቀሳ ወደላይ አንጠልጥሎ ልክ እንደእርግብ በአየር ላይ ያንሳፍፈኛል…..እና አሁን ያ የልጅነተ መስታወቴ ነው የተሰነጣጠቀዉ… የትዝታ ድልድዬ ነው ተንዶ የተሰበረው…..ወደትናንቴ ለመሻገር በጣም ይከብደኛል….ግማሽ  ሆኜያለሁ
‹እውነትሽን  ነው…..አሁን ሳስበው ቢነካንስ ኖሮ…ማለቴ ያው ነካክቶን ጥሎን ሂዶ ቢሆንስ..?››
‹‹እሰከ መጨረሻ ያበቃልን ነበራ…››ብላ መለሰችላት፡፡
‹‹እኔ እኮ አሁንም እስከመጨረሻው ነው ያበቃልኝ…›
‹‹ቆይ ግን ወደ ወሬሽ ልመልስሽና..ቃልዬንም እኮ ከዚህ በፊት ማለቴ አንቺ ከመድሀኔ ጋር ተገናኝተሸ ከመጀመርሽ በፊት ስለሁለታችሁ ግንኙነት ጠይቄው ነበር…››
6.8K viewsአትሮኖስ, 14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ