Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 159.61K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 44

2022-12-11 09:45:45
አሳዛኝ ዜና

በኢትዮጵያ የፊልሙ ኢንደስትሪ ትልቅ ድርሻ የነበረው አርቲስት ታሪኩ ብርሀኑ (ባባ) በድንገተኛ ህመም ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጆቹ እንዲሁም ለአድናቂዎቹ በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።

ነብስ ይማር
3.4K viewsE D U , edited  06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 21:00:03 "አዝናለሁ ካርለት: »አንችና ደልቲ ፍቅር ስትሰሩ
እየኋችሁ ከዚያ እሱን ተመኘሁት አለምሁት... እና
የተስገበገብሁትን ከጨረቃዋ ግርጌ ጫካው መሃል አቀፍሁት የተስገበገብኩትን አይቶ
አይቶ እሱም እስክጠግብ በአፍ ባፌ አጎረሰኝ ይቅርታ ካርለት ፈገግ አለች ካርለት ቀጥላ ከት ከት ብላ ሳቀችና “አንችኮ ያላገባሽ ልጃገረድ ነሽ ደልቲም ወንድ ነው ካሻው ልጃረድ ጋ
ፍቅር መስራት ይችላል! በሐመር ባህል የሁለታችሁ ግንኙት ነውርነትም የለውም እዚህ ስንሆን እንደ ሐመሮች አስበን ይህን
እውነት መቀበል አለብን" አለችና ካርላት ደግማ ሳቀች

ኮንችት ከካርለት ጋር የተነጋገሩትን
ኤርቦሬዎችን ሐመሮችን እያሰበች! ደስታና ድንጋጤዋን እያለመች
ወደ ማድሪድ ባቀናው ኤሮፕላን ጭንቅላቷን በመቀመጨዋ ትራስ አጋደመች።ይጥማል ህልሟ! ውስጡ ግና አደራና ቃል ኪዳን ቋጥራል::

“አልረሳችሁም አካሌ ቢርቅም መንፈሴ ከናንቱ ጋር ነው ያሰብሁትም ይሆናል” እያለች እንቅልፍ አሸለበች ኤሮፕላኑ ግን
በረረ  ወደ ማድሪድ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የእንቁላል ቅርፅ ካለው አዳራሽ “ቀጭ ቋ… ቀጭ ... ቋ‥" የሚል ኮቲ ደጋግሞ ተሰማ: ኮቴው ቀስ በቀስ እየቀነሰ ሄደ
በርካታ ህዝብ ጓጉቶ የዝግጅቱን መጀመር ይጠብቃል።

በስፔን ፈረንሳይ እንግሊዝ ካናዳ , ታይቶ በተለያየ
ጋዜጦች የራዲዮና ቴሌቪዥን ፕርግራሞች
ብርሃን ያልደረሰባት በሰው ሰራሽ ግንብ የተከለለች ሃገር በሚ ርዕስ ብዙ የዘገቡበት ዝግጅት በሲውዘርላንድ ጄኔቭ ይቀርባል ሲባል
መግቢያ ትኬቱን ለማግኘት የተራኮተው ብዙ ነው ተመልካቹ ካለምንም ኮሽታ የዝግጅቱን መጀመሪያ ሰዓት ይጠባበቃል።

“የስልጣኔ ምሳሌ የነፃነት ምድር የአባይ የአባይ ወንዝ ምንጭ የዓለም የባሀል ቅርስ ሙዚዬም... ኢትዮጵያ አስተ ጋባ ድምፅ ማጉያው የአዳራሹ መብራት ጎላ እያለ መድረኩን በብርሃን
አጥለቀለቀው ::

የሐመር የኩዩጉ የወላይታ የኤርቦሬ የዶርዜ የአፋር•
የኢትዮጵያውያን ባህላዊ ልብሶችን የአማራ የኦሮሞ የትግሬ የኢትዮጵያውያን ባህላዊ ልብሶችን የዓለም ዕውቅ የፋሽን ሞዴሊስት ለብሰው ውበታቸውን ሊያሳዩ ተመልካቹ ትናንትና ዛሬን በምሳሌነትዠ የሚቀርብለትን ትዕይንት እያዩ በደስታ ጮኸ  የባህል ብዛት የዐገር ውበት ነው... ኢትዮጵያ ድምፅ ማጉያው ያችን የሰው ልጅ መገኛ ለአለም ህዝብ አበሰራት:

“እናቴ ኢትዮጵያ ውቢቷ ሃገሬ” የተስፋዩ ገብሬ
ሙዚቃ አስተጋባ ቀጥሎ እውቅ የኢትዮጵያ ዘፋኞችና ዳንኪረኞች የየብሔረሰቡን ጭፈራ አሳዩ: ዳንhራው ውዝዋዜ እስክስታው….
ወረደ እልልታው ደመቀ አፍሪካ ኋላ የቀረችባትን የበኩር ልጇን ኢትዮጵያን አቀፈቻት እንባና ሳቅ ሳቅና
እንባ  በሃፍረት አንገታቸውን የደፉትን ልጆችዋን ተናነቃቸው።

ለሳምንት በቆየው 'ኢትዮጵያን እንወቃት' ሳምንት የየብሔረሰቡ ቤት አሰራር ስለ ብራና መፃህፍት ስለ ባህላዊ አስተዳደር ስልት ስለ ምግብ አይነት
. ሁሉም በየአይነቱ ቀረበ
ኢትዮጵያ እንደ አልማዝ ፈርጥ አንፀባረቀች እልልታው ቀለጠ

መምሰሉን ትተን ባለን እንኩራ ማድነቁን ትተን ለመደነቅ እንስራ አገራችንና አህጉራችንን የሚያሳፍር ሳይሆን ስማቸውን የሚያስጠራ ድል እናጎናፅፋቸው ሃይሌ ገብረስላሴ በእያንዳንዱ
“ኢትዮጵያዊ ጆሮ አምርሮ ተናገረ።

ኢትዮትጵያ ተራሮች ሜዳዋ
ሸንተረሩ እንደ በቄላ አሹቅ
ሀፍረታቸውን እያወለቁ ወረወሩ።

የዝግጅቱ አቀነባባሪ ፔሶ ቢኒ ኮንቺት ካርለት አልፈርድ  ከሎና ሶራ የመጀመሪያው ምኞታቸው ሲሰምር ፈነደቁ ኩዩጎዎች
ሐመሮች ኤርቦሬዎች በመገናኛ ድልድይ ማንነታቸው  ታውቀ ክራሩ እምቢልታው ማሲንቆ ዋሽንቱ ቶም ቶም  በገናው
ወይሳው ጥዑም ዜማቸውን አሰሙ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኮንቺት በመጨረ  ያሰብነው ተሳካ  ሁለት ዓመታት በፈጀው ውጤታችን ረክቻለሁ ሶራ ደስታው ፍንቅል እያደረገው
ቡድኑ ወደ ሩቅ ምስራቅ ከማቅናቱ በፊት።

ረክቻለሁ  ኮንቺት
ሶራ የተነገረውን አጣጣማችው።

ሶራ ምን ሰራንና ረካህ መርካት ማለት እኮ ከባድ አባባል ነው።በሩን ከፍተነው እንጂ መቼ ጓራችን ለማ የመስኖ ምርቱ መቼ አደገ... ያለውን አሳየን እንጂ መች የነበረው ተሻሽሎ ተበልቶ
የተረፈው ጎተራ ተከተተ። ለውጥ ሳናመጣ እርካታ ሺ ኪሎ ሜትር የውድድር ጉዞ ከፊት በመቅረባችንና ማንነታችን በመገለፁ እርካታ ኮንቺት እልህ ሲተናነቃት ሶራ ሽምቅቅ አለ።

“አሁን ይበልጥ ለመስራት እልህ ያስፈልጋል የዓለም
ህዝብ ከአመት በኋላ ˚
በነበርንበት ሊያገኘን  አይፈልግም: ለውጥ
ይፈልጋል አዲስ ነገር  ይጠብቃል! እና አንተም ሆንክ ሌላው ወጣት አፍሪካዊ ግቡ መታወቅ መሆን የለበትም
ማሸነፍ. መቅደም ውጤቱን አሻሽሎ  ክብረ ወሰኑን መጨበጥ አለበት
ፍቅራችንን ለጊዜው እርሳው፧ አቅመ ቢስ ነኝ ብለህ የምታስበውን
ከአዕምሮህ አውጥተህ ወርውረው….. ደካማ፤
ካልጎተቱት የማይሄድ፤ ካለነጭ ፍርፋሪ የማይኖር...” መባሉ ይብቃ!
እልህ ይታይ፤ የመስራት የመፍጠር  ሰው  የመሆን
ይመስከር እንጂ ሳይጀምሩ የምን እርካታ አመጣህ!" ኦለችው ኮንችት

ሶራ ስሜቱ ጭምትርትር ሲል ኮስተር  ብሎ  አይኖቹን አድማሱ ላይ ሰካ ንስር አሞራ ሰማዩ ላይ ይበራል፤ ደኑ ሸንተረሩ
ሜዳው ተራራው... ተፈጥሮ አምራ ሰው ትጠብቃለች! ህሊና ያለው፤ መስራት የሚችል ትፈልጋለች፦

“ኢትዮጵያ እውን በስልጣኔና እድገቷ የአፍሪካ ቀንዲል
መሆኗ ተመልሶ እውን ይሆን?" ግራ እጁን ጉንጩ ላይ አስደግፎ
አዝኖ አጉተመተመ የመለሰለት ግን የለም ካለ ተግባር ይህን የተተበተበ ውል የሚፈታ አይኖርም
በአፍሪካዊነት
በኢትዮጵያዊነት ለመኩራት ጥረት ያስፈልጋል! ያላሰለሰ  ተስፋ የማያስቆርጥ እልህ የተሞላበት... ጥረት!... ያኔ ውጤት ሲገኝ ጨረቃን ተንተርሶ የፀሐይን ሙቀት እየኮመኮሙ በአባትነት ወግ
ዛሬን ለነገ ልጆች ማስረከብ ይቻላል። እውን ግን ያች ቀን ትመጣ ይሆን!

ተፈፀመ ሌላው ይቀጥላል

አስተያየታችሁን እጠብቃለው ድርሰቱም ላይ እንዲሁም በሌላ
3.6K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 21:00:03 #ኢቫንጋዲ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት 


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ

ካርለት ከዳንሱ ቦታ ራቅ ብላ ጀግናዋን በአይኖቿ
ስትፈልገው በጆሮዋ ስልምልም የሚያደርግ የሙዚቃ ቃና ሰማች።
እንግዳ ነው ያ ሙዚቃ ለጆሮዋ! ሳባት ሙዚቃው
ተጎተተችለት: ቃናው ጆሮዋን እየላሳት ወደ ውስጧ ዘለቀ የህሊናዋን ጓዳ! የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው። አሻት፤ ዳሰሳት…..እሷም
አንኳኳ የሆሊናዋን ጓዳ የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው አሻት፤ ዳሰሳት
ሁለመናዋን ነካካው
አንሸራተታት ደመቅ
ደመቅመቅ... የሚለው ዜማ ፍል ውኃ ውስጥ እንደገባች ሁሉ ቁልቁል እየፈሰሰ ሰውነቷን አጋላት ደስ አላት ሰውነቷ ሲግል‥. ጡቶችዋ ግን ተቆጥተው ቆሙ፤ ዳሌዋ አኩሩፎ አበጠ ፤ ጭኗ አዝኖ ለሰለሰ… ሙዚቃና ልብ ወለድ ጽሑፍ ካለ እሳት ሰውነቷን ሲያጋግሉት ደስ ይላታል... የረሳችው ስሜት
ፈረሰኛው አረፋ እንደሚያስደፍቀው ወራጅ ወንዝ ሞተሯን አሽከረከረው፤ አቃሰተች ያኔም ስርቅርቁ ዜማ በጆሮዋ መግባቱን
አላቆመም:

እየቀረበች ስትሄድ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ወይሳውን እየነፋ ጥዑም ዜማ የሚያወጣውን ጀግና አየችው። የሙዚቃው
ቅላፄ እንደ “ቤቶሆቨን ሞዛርት ሲንፎኒ" ቃናው እየቆዬ ጣማት።እሰይ እሱ ነው ብላ አጉተመተመች..

ከዚያ ዱካዋን አጥፍታ በሙዚቃው ስልት እርምጃዋን አስተካክላ ተጠጋችው፡
ባለወይሳው አይኖቹ ከጨረቃና ከዋክብቱ ጋር ይጫወታሉ ቅላፄው
ወዲያና ወዲህ ይመላለሳል። ሙዚቃው እንኳን ሌላውን ራሱንም
መስጦታል። እውነተኛ የኪነ ጥበብ ሥራ ውጤት ስቃይና ደስታዋ፤ሐዘንና ትካዜዋ. እፍታውን ቀማሹ ጣዕሙን አስተካካዩና ፈጣሪው
ያኔው ነውና ወይሳው ደልቲን መስጦታል! ወጥሮታል...

ካርለት ደልቲን በሚጫወተው የሙዚቃ ቃና ተመስጦ በማየቷ ይበልጥ ወደደችው፡ ደልቲ
ለስሜቱ ታማኝ ነው አይቀጥፍም አያስመስልም...
ስርቅርቁ የሙዚቃ ቃና
የሚንቆረቆረው ለህሊናው እርካታ ነው::

ካርለትን የሙዚቃው ስልት አቅም አሳነሳት: ሁለመናዋ
እንቅስቃሴ ፍጥነቱን ስለጨመረ ደካከመች: ስሜቷን አፋጭቶ
ሃይሏን መልሶ ለመሳል አጋዥ ያስፈልጋታል
ባለወይሳው ያን ሰው አጥታው ከርማለች! አሁን ግን አጠገቧ ነው።

እጆችዋ ትከሻው ላይ አረፉ። ባለወይሳው ስርቅርቅ ዜማውን አቁሞ ቀና ብሎ አያት። ቆዳዋ ተገልቧል፣ ከርቀት ጠቆር
ብለ የታየው አካሏ ቁልቁል ወደሱ ሲመጣ እየጎላ ታየው። የራቀው
ሽለቆ ቀረበው።

ንጥት ያለው ገላዋ  በተለይም ጭኗን ትክ ብሎ እያዬ፡ “ካርለትት አላትና አይኖቹ ሳቁ። ሃይል ያጣችው ካርለት
የተሸበሸበ ርጥብ ከንፈሯን ለጠጥ አርጋ ደካማ ፈግታዋን አሳየችው።

ባለወይሳው አስተውሎ አያት ውስጧንም አየው
የተቀጣጠለውን ስሜቷን ነካው፡

ጭኖቹ ላይ ያለውን ወይሳ አንስቶ ለጨረቃ ሰጣት!
ጨረቃም ወይሳውን ተቀብላ እየነፋች ጥዑም ዜማዋን ማንቆርቆር ጀመረች። በጨረቃ የሙዚቃ ቃና ደልቲ ቀኝ እጁ እየተንከላወሰ ወደ
ነጩ ጭኗ ገባ። ነዘራት
በሽተኛዋን! “በሽታውን የደበቀ..." እንዲሉ እሷም ሃኪሟን ረዳችው የሚያቃጥላትን የሚቆረጥማትን እጁን
በእጅዋ ይዛ አሳየችው።
ጆሮ ግንዱን ፀጉሩን
ማጅራቱን...እየደባበሰች የእርዳኝ ጥሪዋን አሰማችው። ሀኪሟ በስሜቷ እሱም ተሽፈነ። ለጋራ በሽታቸው ግን የሚበጀውን ያውቃል። ስለዚህ ማገገሚያ ቀንዱን አቁሞ ይዞ ከተቀመጠበት ተነሳ።

ሙዚቃው ይስረቀረቃል! ዳንሱ ጦፏል... ጨረቃ
ታዜማለች ! ቅጠሉ እስክስታ ይወርዳል! ነፋሱ አታሞውን
ይደልቃል... ጥቁርና ነጭ ቀለሙ ማራኪ ዜብራም ያናፋል...

ኮንችት ጭፈራውን በጉጉት እያየች እንደቆየች ስለ ነገው
ጉዟቸው ካርለትን ለመጠየቅ ፈልጋ አጣቻት የኩችሩ መንደር ኗሪ
ጥበቃውን አላቆመም። ነጩ እባብና ሎካዬ ግን አልመጡም። ኮንችት
በየዋህነታቸው ብታዝንም ማድረግ የምትችለው ባለመኖሩ በዝምታ
ሁኔታውን ስትከታተል ሰነበተች። የመቆያ ፈቃዷ  እያለቀ ነው:: ስፔን ስትመለስ ብዙ ልትሰራ አስባለች በተለይ ስለ ኢትዮጵያ  ስለ ኩጉዩ፡ ከመሄዷ በፊት ግን ሐመርን ኤርቦሬን ከካርለት ጋር በሷ
መኪና ለማየት ተስማምታለች ጉዞዋን በተመለከተ ግን ከካርለት
ጋር መነጋገር ያለባት ቁም ነገር ነበር።

ኮንቺት ካርለትን ስታጣት ደልቲን በጨረቀዋ ብርሃን  ፈለገችው የለም:

ካርለት የሄደችው እሱ ዘንድ ይሆን?' አብረው ሆነው
ለማየት ጓጓች: ፍቅር ሲለዋወጡ እንዴት ይሆን?' ለማስብ ሞከረች:: መልሳ ደግሞ ሃጢያት እንደሰራች ሁሉ አስበችው አፈረች። ሆኖም ግን አልቻለችም ጉጉቷ ጨመረ።

በዚህ መካከል ድክምክም ያለውን የወይሳውን ድምፅ
ኮንችት ከርቀት ሰማችው። በድፍረት ሄደች  ወደ ጫካው! ድንገት ግን ክው ኦለች ! ባለበት የሚሰግር
ዜብራ አየች ፈራችው
ዜብራውን ይጋልባል ... በስሜት ተውጣ አይኖችዋን ጨፈነች:
"...የፍቅር እንጥሌን ሌሎች ተንጠራርተው ሲያጡት የነካው እሱ ብቻ ነው" ኮንችትን የነገረቻት ትዝ አላት።

“ዋው! ጎመጀች በዜብራው
ግልቢያውን አሰጋገሩን
አደነቀችው። ወደደችው ያን ስሜት ሰላቢ ጥዑም ዜማ... ፈውስ ሰጭ ዳንኪራ… ንፁህ የጫካ ፍቅር... ማራኪ ተፈጥሮ ተጋግዘው እንግዳዋን መልሀቋን አስጥለው በጉጉት ገተሯት!  ተጣራች በሲቃ ሶራ ግን አልሰማትም! ኤጭ! ብላ ከንፈሯን ጣለች። ጎደሎነት
ተሰማት ያማራትን የዜብራ ግልቢያ ግን የሚያቀምሳት አጣች.የጎመጀችለትን ያጣችው ኮንችት አዘነች። ...ዛፉ ቅጠሉም አዘነላት ላልተጠራችው ተመልካች!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

“እ. እ..." አቃሰቱ እምቡዋ እ. እ" ሳግ ተናነቃቸው
ህፃናት ወጣቶች አዛውንቶች ኦሞ ወንዝ ዳር ጫካ ተሰባስበው እንግዶች በእንጨቷ ታንኳ ኦሞን ሲያቋርጡ አያቸው።

ኮንችት እጅዋን አውለበለበችላቸው “ቻው... ባባይ... አለቻቸው። ዝም አሉ ኩዩጉዎች የነሱ የጥልቅ ፍቅር መግለጫቸው ዝምታ ነው። ሳግ ያበት “እ... እ..." እሚያሰኝ ከጥጃዋ በሃይል እንደተነጠለች ላም የሚያንሰፈስፍ ዝምታ! “እ. እ. እምቡዋ.. እያሰኘ የማይፈስ እንባ የሚያስነባ, የማይገልፁት ግን የሚታይ
የሚነካ... የመለየት ጭንቀት የሚታይበት ስሜት..

“እወዳችኋለሁ! ከናንተ በመለየቴ አዝናለሁ. ምንጊዜም አልረሳችሁም..." ኮንችት በስፓኒሽ ለመግለፅ ለፈለፈች¦ ምላሽ ግን
አልነበረም። “ፀጥታ ብቻ! ለኩዩጉዎች የመለየትን መጥፎነት የሚገልፅ ቋንቋ የላቸውም ካለ ዝምታ በቀር።

ኮንችት አነባች::
የካርለትን ትከሻ ተደግፋ አነባች አለቀለች  ሌሎች ግን ዝም ረጭ ብለዋል  እንደ ሌሎች ወንዞች
የማይጮኸው የማይደነፋው.
የኩዩጉዎች ህይወት የመልክ ማያ መስታዋታቸው የሆነው የኦሞ ወንዝም በዝምታ ድባብ እንደ ተዋጠ
ነው: ወፎች ግን ይበራሉ ያዜማሉ! እዕዋት ያሽበሽባሉ...

“እሷ ሄደች በሉ
ሉካዬንና የሰላም አድባራችን
የነበረውን ነጩን እባብ እንጠብቅ ! ተከፍተን ታዩን መምጣቱን እንዳይተዉት እንዝፈን እንጫወት.."
ሽማግሌዎች ለኩችሩ መንደር ህዝባችው ተናገሩ ኮንችት ካርለት ከሎ ሶራ… ኦሞን ከተሻገሩ በኋላ ዞር ብለው አዩ: ኩዩጉዎች የሉም!.ሲደልቁ ግን ይሰማል ለዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ለረጅም ጊዜ አልቅሶና አዝኖስ መኖር እንዴት ይቻላል!
2.8K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 19:58:43 «አንተ አብረኸኝ ስላለህ ደስ ነው ያለኝ!! የማለቅሰው አጎቴ ስለሚናፍቀኝ ነው!! ሰፈሩ ስለሚናፍቀኝ ነው!! ባንተ አይደለም እሺ!!» እያልኩት ተደጋግፈን እንቅልፍ ወሰደን!!

አዲስ አበባ

አዲስ አበባ <እንኳን ደህና መጣችሁ!> ብላ አልተቀበለችንም!! አውቶብስ ተራ እንደወረድኩ ነው ይሄ ከእኔ ዓለም በምንም የማይገጣጠም ውቅያኖስ እንደሆነ የገባኝ!! አዲስ አበቤዎች ሲያወሩ እንኳን የሚደማመጡ አይመስሉም። ሁሉም ያወራል፣ ሁሉም ይራወጣል፣ የተረጋጋ የለም! የት ሊሄዱ እንደሚቸኩሉ እንጃ ቸኩለው እያወሩ ቸኩለው እየተገጫጩ ይተላለፋሉ። ከራሱ መንገድ ውጪ ማንም በአካባቢው ያለውን አያስተውልም። በጩኸቱ ጆሮዬ ዛለ። ኪዳንን በአንድ እጄ ጥፍንግ አድርጌ ይዤ በሌላ እጄ ልብሳችን ያለበትን ፔስታል ይዤ <አልጋ> የሚሉ ልጆችን ተከትዬ የዛን ቀን የትኋን እራት ሆነን አደርን!! አዲስአበባ ቀማኛው ብዙ ነው ሲሉ ስለሰማሁ ምግብ ልንበላ በገባንበት ሁሉ የማየውን በጥንቃቄ እከታተላለሁ። በሀገሬ ባለፍኩ ባገደምኩበት ሰው የሚጎነበስልኝ ፣ ሁሉ የሚያውቀኝ ነበርኩ:: ….. እዚህ ባዳነት ተሰማኝ። እዚህ ማንም ነኝ!! ከኪዳን ውጪ የሚያነጋግረኝ እንኳን የሌለ ማንም ነኝ!!

በበነጋታው ስልክ መደወያ ቦታ ፈልጌ አሰልጣኙጋ ስልክ ደወልኩ እና ያለንበት መጣ!!! የምንከራየው ቤት እስካገኝ እቤቱ ይወስደኛል መቼም የእግዜር እንግዳ ዝም አይባልም ብዬ ስጠብቅ እሱ እቴ!! የዛኑ ቀን በእጁ በያዛት ስልክ ለደላሎች ደውሎ ቤት እንዲፈልጉ ነግሮልኝ የማላውቅበት ምድረ ገበያ ህዝብ የሚተራመስበት ሰፈር አልጋ አስይዞን ሄደ። አሁን ብቻዬን እንደሆንኩ አወቅኩ!! አባት እና እናቴ የሉም! አጎቴ የለም! አሁን ለኪዳን እነሱን መሆን ያለብኝ እኔ ነኝ ለካ!!

አንዲት ትንሽዬ የጭቃ ቤት በአስጠኚው በኩል አጊንተን ተከራየን!! የምንተኛበት እና የምናበስልበት ዕቃ ገዛን!! ኑሮ ተጀመረ!! መጀመሪያ አካባቢ መኪና ማጠብ ስራ አገኘሁ። አምስት መኪና በነፃ ካጠብኩ በኋላ ነው የቀጠሩኝ። ሰፈሩን መውጫ መግቢያ ተሽሎክልኬ አወቅኩት። የሆነ ቀን ጠዋት ከኪዳን ጋር ዳቦ በሻያችንን በልተን ከቤት ልወጣ ስል

«ሜል?»
«ወዬ»
«እንዳትቆጭኝ! አልቆጣህም አባባ ይሙት በይ!» አለኝ ከዓመታት በኋላም የሞተውን አባቴን እየገደልን ነው የምንምለው።
«አባባ ይሙት አልቆጣህም ምንድነው?»
«እኔምኮ ትልቅ ልጅ ሆኛለሁ!! ስራ ፈልጌ የማልሰራው ለምንድነው?» አለኝ እንዳልቆጣው እየተሳቀቀ

«አባባ ይሙት እቆጣሃለሁ!! ሁለተኛ እንዲህ እንዳትለኝ!! አንተ አርፈህ ተቀመጥ ከወር በኋላ ትምህርት ሲጀመር ትምህርትህን ወጥረህ ትማራለህ!! ስራህ ትምህርትህ ነው!! ተግባባን?» ብዬ እንደፈራውም ጮህኩበት

«አዎ» ሲለኝ ስቅቅ ብሎ አሳዘነኝ እና አቀፍኩት።

«ላንተ ብዬኮ ነው!! ታውቅ የለ እንደምወድህ? አንተ ተምረህ ስራ ስትይዝ ያኔ አንተ ትሰራለህ እኔ እቤት እቀመጣለሁ!! አሁን ግን እኔ ታላቅህ አይደለሁ? እኔ እሰራለሁ አንተ ትማራለህ!!» ስለው ጭንቅላቱን ነቀነቀ። እናት መሆን ፣ ልጅ ማሳደግ : እናት መቼ እንደምትቆጣ: መች እንደምታባብል : መች እንደምትቀጣ ... ምኑም በቅጡ ሳይገባኝ ለካ እናትም የመሆን ሀላፊነትን ወስጃለሁ።

የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት አንዱ በጉልቤነቱ የሚፈሩት ጥጋበኛ ሴት ሆኜ ከወንዶቹጋ መኪና ማጠቤን ሊያፌዝበት ሞከረ። ያልፈጠረብኝን አይ አለመተዋወቅ ብዬ ታገስኩት። በሌላኛው ቀን መጥቶ ግን ከኋላ ቂጤን ሲመታኝ መታገስ የምችልበት ልብ አጣሁ እና አፍንጫውን አልኩት። በቦታው የነበረው ሁሉ ደንግጦ ብድግ አለ። ልጁ ያልጠበቀው ቡጢ ስለጠጣ መጀመሪያ ተደናግጦ የደማ አፍንጫውን መጠራረግ ጀመረ። ቀጥሎ ግን ያዙኝ ልቀቁኝ ብሎ ሊገለግሉት የያዙትን ሁሉ እየተወራጨ ደነፋ!! እኔ በናታችሁ ልቀቁት ስል ፣ እሱ ከወድያ ልቀቁኝ ሲል …. አንድ በአንድ ሰው እየተሰበሰበ የፈሪ ድብድብ ሆነ። ድንገት ለቀቁት እና እኔና እሱ ተያይዝን። ለካስ ሲገላግሉ የነበሩት ልጆች የሸሹት ፖሊሶች መምጣታቸውን አይተው ነው። ፖሊሶቹ ማናችንንም ምንም የጠየቁትም ያጣሩትም የለም! አፋፍሰው ብቻ ፖሊስ ጣቢያ ወሰዱን።

<እባካችሁ ትንሽ ወንድሜ ብቻውን ነው> ብል ማን ይስማኝ? ጀርባዬ ላይ ካሳረፈው ጥቁር ዱላ ህመም በላይ የተሰማኝ የኪዳን ብቻውን በፍርሃት መራድ ነው። ትቼው የጠፋሁ ይመስለዋል? ሊፈልገኝ ወጥቶ መንገድ ይጠፋበት እና የማያውቀው መንደር መንገድ ላይ ሲያለቅስ ታየኝ። ብዙ ክፉ ነገር ታየኝ። ተንዘፈዘፍኩ። ደቂቃ ባለፈ ቁጥር ፍርሃት ከአንጀቴ ይተራመሳል። ሰዓቱ አይሄድም!! ማልቀስ እፈልጋለሁ ግን እንባ አይወጣኝም።

<ጥጋባቸው በርዶላቸዋል> ብለው በሚቀጥለው ቀን ጠዋት ሲለቁን እግሬ መሮጥ አቅቶት ተንቀጠቀጠ። የቤቱን በር አልፌ ስገባ ኪዳን ባይኖር የት ብዬ ነው የምፈልገው? ራሴን ረገምኩ! ደህና ተደላድሎ ከሚኖርበት ቤት ይዤው የወጣውበትን ቀን ረገምኩ። ሰውነቴ እየተንቀጠቀጠ በሩን ከፍቼ ስገባ ኪዳን ኩርምት ብሎ ፍራሹ ላይ ተቀምጧል። ሲያየኝ ዘሎ እላዬ ላይ ተሰቅሎ እንደህፃን ድምፅ አውጥቶ ማልቀስ ጀመረ። የሱ መርበትበት ይብስ አርበተበተኝ እና አብሬው እዬዬ ማለት ጀመርኩ። እህል ሳይበላ ከአሁን አሁን መጣች ብሎ ኩርምት ብሎ በር በሩን ሲያይ ነው ያደረው።

ፈሪ ሆንኩ! ለኪዳን ስል ፈሪ ሆንኩ!! ለእሱ ስል ብቻዬን ብሆን የማልውጠውን ብዙ መናቅ ዋጥኩ። ለእሱ ስል የማላልፈውን ውርደት አለፍኩ። አንገቴን ደፋሁለት!!! ከብዙ ስራ ቅየራ በኋላ …… ኪዳንም ትምህርቱን ብዙ ቀን ከተማረ በኋላ ….. ብዙ ጥጋበኛ አንገቴን ደፍቼ ካሳለፍኩ በኋላ …..….. በራሴው ሰውንም ከተማውንም መልመድ ከጀመርኩ በኋላ……. የከተማ ሚኒባስ ወያላ ሆኜ እቁብ መጣል ከጀመርኩ በኋላ …… አንድ ቀን ተሰብስበን ተራ የምንጠብቅበት ቦታ ኪዳን መጥቶ ሲፈልገኝ በእድሜ በጣም ከሚበልጠው ልጅ ጋር ነገር ተፈላለጉና ኪዳንን በቁመቱ አንስቶ በጠረባ ጣለው። ደርሼ ልጁን ሳንጠለጥለው ከሚፈላው ደሜ ውጪ የሚሰማኝ ነገር አልነበረም። ምን እንዳደረግኩ አላውቅም!

«ሜል!» ብሎ ኪዳን ሲለምነኝ ነው ጆሮዬ ድምፅ መስማት የቻለው። ፖሊስ ከመቼ መጥቶ ብዬ ስሳቀቅ ግርግሩ ሰክኖ የሆነ ሰውዬ ተጠጋኝ እና

«ስራ ልስጥሽ! እዚህ ከተሳፋሪ ፍራንክ እየለቃቀምሽ ፀሃይ እና ዝናብ እየተፈራረቀብሽ ከምታገኝው እልፍ እጥፍ ደመወዝ የሚከፈልሽ ስራ ላስቀጥርሽ! » አለኝ

«እንዴ ምንድነው ስራው ?» አልኩት

«ደውዪልኝ» ብሎ ስልኩ ያለበት ቢዝነስ ካርድ ሰጥቶኝ ሄደ። ተሰብስቦ የነበረውን ወሬኛ አላስተዋልኩትም ነበር።

«ኸረ በለው! በአንድ ቦክስኮ ስሙን ሁሉ ነው ያስረሳሽው!! መሬት ሲደርስ ኦልሬዲ ቤተሰቡን ዘንግቷል!!» እያሉ ትከሻዬን አቅፈው ማውራት ጀመሩ። ሊያዋራኝ ይኮራ የነበረ ሁላ ጓደኛዬ ሊሆን ሰበብ ይፈልግ ጀመር።

.ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
2.6K viewsTsiyon Beyene, 16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 19:58:43 #የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ሀያ)
(ሜሪ ፈለቀ)

እነዛ ጫማ ያልለበሱ እግሮቻቸው ፣ የከብት ሽታ የሚሸት አዳፋ ልብሳቸው ፣ ያለፉበት መከራ የተፃፈበት የግንባራቸው መስመር ፣ ዘመናቸው ድሎት እንዳልጎበኘው የሚያሳብቁት ሻካራ እጆቻቸው ፣ ብራቸውን ስወስድባቸው እንድራራላቸው የሚለማመጡ ከርታታ ዓይኖቻቸው …….. ከአጠገባቸው ርቄ እንኳን አልራቀኝም!! የስንት ቀን የልጆቻቸው ምሳና እራት ይሆን? ምናልባት የሚያፈስ ቤታቸውን ሊያድሱ ይሆናል! ምናልባት የሚከፍሉት እዳ ይኖርባቸዋል! …… ብዙ ርቄያቸው ከሄድኩ በኋላ በጉልበቴ መሬቱ ላይ ዘጭ አልኩ!! አባቴ <ጀግና አያለቅስም!> ብሎ ቢያሳድገኝም ዛሬ መጀገን አቃተኝ! ለአፍታ ተመልሼ ሄጄ ብሩን ሰጥቻቸው የመምጣት ሀሳብ ሁላ ሽው ብሎብኝ ነበር። ይሄ ምስላቸው ለዓመታት ስቃዬ ነበር። ከበደሉኝ ሰዎች እኩል የበደልኳቸው ሰዎች ፊት እንቅልፍ የማያስተኛ ቅዠቴ ነበር። ለደቂቃዎች እዛው በጉልበቴ ከተንበረከኩበት የመጨረሻዋን አውቶቡስ ተሳፍረን አሁኑኑ ካልወጣን ፖሊሶቹ እኛ ቤት ለመድረስ ምንም የምርመራ ሂደት እንደማይፈጅባቸው ሳስታውስ ተነሳሁ::

እንባዬን ጠራርጌ ሮጥኩ!! ያገኘሁትን የእኔን እና የኪዳንን ልብስ በፔስታል ጨመርኩ። ያለችንን አንድ ለእናቱ ጫማ ተጫምተን ወደመነሃሪያ እጁን ይዤ መሮጥ ጀመርኩ። መነሃርያው አካባቢ ስንደርስ ከኋላዬ ሁለት በእድሜ ጠና ያሉ የኛ አካባቢ የማይመስሉ ሰዎች ሲያወሩ ወሬያቸው ጆሮዬን ጠለፈው።

«የወዲያ ቀዬ ሰዎችን ዛሬ ሽፍታ ዘረፋቸው የሚሉትን ወሬ ሰማህ?»

«ኸረ አልሰማሁም!! ወደየት ግድም?»

«ከገበያው ጫፍ ትንሽ ቢርቁ ነው አሉ!! አንደኛው ይሄ በሬ ሻጩ አያልነህን አታውቀውም?»

«አያልነህ? አያልነህ?»

«ይሄ ሲያወራ ምራቁን እንትፍ የሚለው? ይህ እንኳን ወንድ ወልዳለሁ ብሎ ሲተኛ ስድስት ሴት ያሳደገው? በመጨረሻ ሚስቱ ወንድ ልጅ ሰጥታው እንዴየውም ደግሶ ያበላ ጊዜ አቅልህን እስክትስት ጠጥተሃልይ!!»

«እንዴ? እንዴ? አያልነህ በሬ ሻጩ?»
«ኤድያ እንዴት ያለው እንከፍ ነው? ምን እያልኩት ምን ይላል?»

ፍጥነቴን አቀዝቅዤ ወሬያቸውን ከሰማሁ በኋላ ድጋሚ መፍጠን ጀመርኩ። <አያልነህ> የሚለው ስም ጭንቅላቴ ውስጥ ልክ እንደዛ የአባቴን ሬሳ ተራምዶት እንዳለፈው ሰውዬ ኮቴ ታተመ።

«ሜል? ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው?» ብሎ ኪዳን ዓይን ዓይኔን እያየ ሲቁለጨለጭ ነው እንባዬ እየወረደ መሆኑን ያወቅኩት።

«ምንም አልሆንኩም!!»
«ምንም ሳትሆኚ ታዲያ እንባሽ ይፈሳል? እኔ ይዘሽኝ ካልሄድሽ ብዬ ስላስጨነቅኩሽ ነው?»

«ይሄ ደግሞ! ለምን አርፈህ አትሄድም? እኔ አስጨንቀኸኛል አልኩህ?» እየተነጫነጭኩ እንባዬን ጠርጌ ትኬታችንን ቆርጠን አውቶብስ ውስጥ ገባን!! ከከተማዋ እየወጣሁ በአውቶብሱ መስኮት ወደኋላዬ የሚያልፈውን ተወልጄ ያደግኩበት መንደር ሸኘሁት። ድብልቅልቁ የወጣ ስሜት ተሰማኝ። ትቼው ስሄድ ሀዘን ካጠላበት ጊዜያቶች ይልቅ የታሰበኝ

የአባቴ ትከሻ ላይ እሽኮኮ ተደርጌ ከጫካው እስከ ጠላ ቤት ግርግሩ ስዞር ጠላ ቤት እግሩ ላይ አስቀምጦኝ በሰዓቱ የማይገቡኝን ወሬዎች እየቀደደ ጠላውን ሲጠጣ እናቴ ከሩቅ እየተራገመች መጥታ «ልጅቱን ጭራሽ አምቡላችሁ መሃል ይዘሃት ትመጣ?» ብላ ከእግሩ አንስታኝ የምትሄደው

አባቴ ገበያ መሃል ጠብመንጃውን እንዳነገተ ሲያልፍ አላፊ አግዳሚ ከአንገቱ ጎንበስ ብሎ ከልብ በሆነ አክብሮት ሰላምታ ሲያቀርብለት ትከሻው ላይ ሆኜ የተቆነንኩት

ከወዳጆቹጋ ሰብሰብ ብሎ ዳማ ከሚጫወትበት አብሬያቸው ሳነግስ እማዬ ትመጣና <ልጄን በቃ ወንዲላ አድርገህ ባልም ልታሳጣብኝ ነው!> ብላ ገና በ10 እና በ11 ዓመቴ ሀሳብ የሚገባት የነበረው

አንድ ቀን አባቴ ሽጉጡን አስይዞኝ ስታይ ለቅሶ እንደተረዳች ጭንቅላቷን ይዛ እሪሪሪሪሪሪ ብላ ጮሃ ጎረቤት አሰብስባ «ይሄን ሰው አንድ በሉኝ» እያለች ወገቧን ይዛ የተንጎራደደችው

እናቴ ከምትሸጠው ፍራፍሬ ላይ ከገበያ ስትመለስ ለምድረማቲ ትሰጥና እኛ ቤት ደጅ ላይ የተሰጠንን እየበላን የምንዘለው

ከትምህርት ቤት ስንመለስ ከቤተሰብ ተደብቀን ወንዝ ወርደን እየተንቦጫረቅን ባልተገረዘው ልጅ ወ*ላ ንፍር ብለን የምንስቀው

ክረምት ላይ እማዬ ቡና እያፈላች የተቀቀለ በቆሎ እየጋጥን እጣኑን ስትሞጅረው <አስካል ጥይት ያልገደለኝን ጀግና በጭስ ልትገይኝ ነው ሀሳብሽ?> ሲላት ከተናገረው ውጪ እሷ ምን እንደገባት ሳይገባን እንደመሽኮርመም እያደረጋት <እንደው ወሬ ስታሳምር ቅም!> እያለች ጭሱን በተን በተን ስታደርግለት የነገሩ ውል ምን እንደሆነ ባይገባንም እኔና ኪዳንም አብረናቸው የምንሽኮረመመው

<አስካል ነይ እስኪ ጀርባዬን ዳበስ ዳበስ አድርጊኝ በሞቴ!!> ሁሌም መምጣቷ ላይቀር ጓዳ ሆና <እስኪ ስራ አታስፈታኝ አንተ ሰውዬ> ስትል <ተይዋ ነይማ አምሳሌ!> ይለኛል እንደመጥቀስ እያደረገኝ። እጇን እያደራረቀች እያጉረመረመች መጥታ ትከሻውን ጀርባውን የምታሸው

እንዲህ እንዲህ ዓይነቱን ቀን ነው ያስታወስኩት! አስታውሼም በአውቶብሱ መስኮት የሸኘሁት!! አባቴ የሞተ ቀን ይሄ ሁሉ አብሮ ከአባቴ ጋር የተቀበረ ሳይሆን ልቤ ያን ንፁህ የልጅነት ጊዜም ልብም ዳግም ላላገኘው ልክ የዛን እለት የተሰናበትኩት ያህል አንሰፈሰፈው ……. ሁሉም ነገር ልክ የዛን ቀን የተሰናበትኩት ያህል….. የሚገጥመው አቀበት ታውቆት ነበር መሰለኝ! የአብቶብሱ መቀመጫ ላይ አጠገቤ የተቀመጠውን ኪዳን ጭምቅ አድርጌ አቅፌ
2.4K viewsTsiyon Beyene, 16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 18:00:10 ‹‹አይ እዬብ እውነትህን ነው…ስለ ሰሪውን ነው መጠየቅ፤እሺ ሰሪው እንዴት ነው?››
‹‹ይመስገነው..››በአጭሩ መለስኩለት፡፡
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ?››
‹አይ የለም..ያው ትንሽ ስራው እዛው ሞላ እዛው ፈላ ነገር ሆነብን እንጂ ሌላው ነገር አሪፍ ነው፡፡››
‹‹አዎ ይገባኛል …ግን ከበረታህ የማይቀየር ነገር የለም፤.ለመሆኑ ትማራለህ?››
‹‹ጋሼ ከረጅም ግዜ በፊት የሰማኋትን አንድ ቀልድ ልንገርህ…  አንዱ ዲያስፖራ ኢትዬጵያ ውስጥ መጣና በየመስሪያ ቤቱ እየዞረ እንዲቀጥሩት ማስረጃውን ይዞ ዞረ ዞረ ሁሉም ቦታ የለንም እያሉ መለሱት ..፡፡ከዛ በቃ ወደመጣሁበት ሀገር መመለስ አለብኝ ብሎ ዝግጅት ጀመረ..‹አንደኛህን አልነበረ እንዴ የመጣኸው ምነው?ለምን ትመለሳለህ ?››ሲሉ ጓደኞቹ ጠየቁት ‹አይ መሮኛል ይህቺ አገር ድሮም ለተማረ ሰው አትሆንም ..ከምድረ አሜሪካ ማስተርስ ድረስ ተምሬና ተመራምሬ  መጥቼ ስራ ተነፈገኝ?›ብሎ አማረረ…ሰዎቹም እውነትም ይህ ሰው ተበድሏል ብለው ቁጭት ውስጥ ገቡና ይበልጥ ለማጣራት ..‹ ለመሆኑ በምን ሞያ ነበር የተመረቅከው.. ?ብለው ይጠይቁታል ‹‹በበረዶ ሸርተቴ›ብሎ እርፍ››
አቤት የሳቁት ሳቅ…እንባቸው እስኪንጠባጠብ ድረስ ነው ሆዳቸውን ይዘው እየተንፈቀፈቀቁ የሳቁት ….ደስ አለኝ፡፡.ቀልድ የሚገባው ሰው ደስ ይለኛል…አዕምሮ ንቁና ፈጣን የሆነ ሰው ነው ለቀልድ ፈጣን ምላሽ የሚሰጠው ብዬ አምናለሁ፡፡
‹‹ቆይ ቆይ ቀልዱ እውነት ይሆን ፈጠራ አስቆኛል..ግን  ከጠየቅኩህ ጋር ምን አገናኘው?››
አላልኳችሁም ሰውዬው ነቄ ነው ፤ ወደዋናው ቁምነገር ጫወታውን አዞረልኝ፡፡
‹‹ጋሼ ሰው እንዳይሰማን  ቀስ ብዬ ልንገሮት.. እኔም  ከአለማያ ዩኒቨርሲቲ በእፅዋት ሳይንስ በዲግሪ ተመርቄያለሁ…እና ስራ ፍለጋ የተሰማራሁት ግን አዲስ አበባ ነው……እና እንደዲያስፖራው ይህቺ ሀገር ድሮም ለተማረ ሰው አትሆንም እያልኩ እራሴን እያፅናናሁ ነው፡፡›.
‹‹እውነትህን ነው?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው››
‹‹እንግዲያው…›› አሉና ከጃኬት ኪሳቸው ውስጥ ቢዝነስ ካርዳቸውን አውጥተው እየሰጡኝ…..ቢያንስ ከዚህ ትንሽ የተሻለ ስራ ልሰጥህ የምችል ይመስለኛል፤ነገ ተነገ ወዲያ ሲመችህ ደውልልኝ›› ብለውኝ እንደፈዘዝኩ መኪናቸውን አስነስተው ተፈተለኩ ....ከዛ ያለ ዋስ የለምንም አንጃ ግራንጃ ሁለት ስራ ተሰጠኝ፡፡የመጀመሪያው ስራ አስተናጋጅ ሆኜ እንድሰራ ሲሆን ሁለተኛው ስራ  የሆቴሉን ንብረት መቆጣጠር ነው፡፡የተሰበረ ካለ ማስጠገን፤የጠፋ ካለ  ሪፖርት ማድረግ፤የጎደለ ካለ እንዲገዛ ማድረግ ወዘተ..ለሁለቱም ስራዬ በተናጠል ደሞዝ ይከፈለኛል፡፡በዛ ላይ የአስተናጋጅነት ስራ ከደሞዙ በላይ ቲፑ አስደሳች ነው፡፡....

ይቀጥላል
2.7K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 18:00:09 #እህቴ_በባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ፡፡
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አንድ
///

ይሄን ታሪክ እንደባዬግራፊ ውሰዱት፡፡ በነገራችን ላይ ባዬግራፊ ማንበብ ደስ ይለኛል፡፡ግለ-ታሪክ በጥልቅ ሳንሱር የተደረገ፤ የተስተካከለ እና የተሞረደ የግለሰብ ፍፅማዊ ታሪክ ነው ብዬ አምናለሁ ፡፡
ግለ-ታሪክ በተለየ መለኩ  ታዳጊዎችን ለመቅረፅና ሞዴል ኖሯቸው የወደፊቱን ህይወታቸውን  መስመር  እንዲያሲዙትና ጉዞቸውን ከመዝረክረክ፤ እራሳቸውንም ካላአስፈላጊ ውጤት አልባ መስዋዕትነት ለመታደግ  ጥረት እንዲያደርጉ ያግዛቸዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ግን ያው ሄዶ ሄዶ ህይወታቸው መዝረክረኩ፤ በየሂደቱም ለማይረቡ ነገሮች መሰዋዕትነት መክፈላቸው የማይቀርላቸው የህይወት ዕዳ ነው፡፡ ቢሆንም ጥረታቸው  የመዝረክረክ መጠኑ ላይ ልዩነት ያመጣል፡፡

ሌላው አዎ ግለ-ታሪክ ግለሰቦችን ብራንድና፤ ሪብራንድ የማድረጊያ ውጤታማ ዘዴ ነው፡፡ የማይሰበረው፤ሰውዬው፤የታፋኙ ማስታወሻ፤የበጋው  መብረቅ፤ የህይወቴ ጉዞና የፖለቲካ ህይወቴ  ፤የመንግስቱ ትዝታዎች ፤የመለስ ዜናዊ የህይወትና ትግል ታሪክ ፤ዳኛው ማን ነው?፤ ማማ በሰማይ ወዘተ…..
ቢሆንም ይሄን የእኔ ታሪክ ከእነዚህ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ግለ-ታሪኮች የሚለየው ድንግል በመሆኑ ብቻ ነው፡፡ድንግል ግለ-ታሪክ ግን ምን አይነት ነው? ፡፡ለማለት የፈለኩት ስለባለታሪኩ ከዚህ በፊት በየትኛውም የመገናኛ  ዘዴ ፤በመፅሀፍ፤ በሬዲዬ ሆነ በጋዜጣ  አልሰማችሁም ፤አላነበባችሁም ማለቴ ነው፡፡

ከእኔና በዙሪያዬ ካሉ ጥቂት ሰዎች በስተቀር ማንም የማያውቀኝ ተራ ግለሰብ ነኝ፡፡ያው አናንተም እንደእኔ ተራ ከሆናችሁ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ግለ-ታሪኮች ይልቅ የሚመጥናችሁም የሚያስተምራችሁም ይህ የእኔ የተራው ሰው ተራ ታሪክ ነው፡፡ምክንያቱም እኔ ራሴን ብራንድም፤ ሪብራንድም የማድረግ  ዓላማ የለኝም፤ምን ሊረባኝ..?እኔ መተንፈስ ብቻ ነው የምፈልገው፤ እናንተም አድማጭ እንድትሆኑኝ ብቻ ነው የምጠይቀው…በቃ ይሄው ነው፡፡

ከደብረብርሀን ወደአለማያ ዩኒቨርሲቲ ..ከአለማያ ደግሞ ወደአዲስ አበባ ከገባሁ ሁለት አመት ሆነኝ።  የተመረቅኩት በእፅዋት ሳይንስ ሲሆን ስራ ፍለጋ ከአንድ አመት በላይ የኳተንኩት ግን አዲስአበባ ነው። እርግጥ ወደ እድገት ከተማዬ ደብረብርሀን  ተመልሼ ቢሆን ኖሮ በቀላሉ በሁለት እና ሶስት ወር ውስጥ በተማርኩበት ትምህርት የሚገባኝን ወይንም ደግሞ ለጊዜውም ቢሆን የሚያኖረኝን ስራ አገኝ እንደነበረ እርግጠኛ ነኝ፤ግን እኔ ያንን ማድረግ አልቻልኩም… አልችልምም።
ለጊዜው ሰው እንደጉንዳን በሚርመሰመስባት  ፤ የህንፃ ጫካ የተጥለቀለቀባት  አዲስአበባ ምርጫዬ ሆናለች? ለምን? እራሴን ልደብቅባት፡፡ለምን ?ከሚያውቁኝ ዘመድ ወዳጅ አብሮ አደጎቼ መሠወር የምችልባት አስተማማኝ  ዋሻ አድርጌ ስለወሰድኳት።ለምን ?ባላድግባትም እትብቴ የተቀበረባት የትውልድ ከተማዬ ስለሆነች፤ ስለምወዳት፡፡የእኔ አዱ ገነት፤የእኔ ሸገር፡፡

እውነት እውነቱን እንነጋገር ከተባለ በዚህ ዘመን በኢትዬጵያ ዘመድ ወይም ወገን የምትለው ሰው በዙሪያህ ከሌለ ከዛም አለፍ ብሎ ባለጎሳና ባለ ብሄር ካልሆንክ መኖር የምትችለበት ቦታ እየጠፋ ነው…፡፡እንደእኔ ነጠላና መለመለውን ያለ ግለሰብማ ከሸገር ውጭ ለመኖር መወሰን አይደለም ማሰብ እራሱ አደጋ  ነው፡፡በዚህ ምክንያትም ይመስለኛል ሰዉ ከአራቱም አቅጣጫ በየምክንያቱ ጓዜን ማቄን ሳይል መጥቶ እየተጠቀጠቀባት ይሄው አሁን ሞልታ የሰውን ልጅ እንደ ውሻ ቡችሎች በየጎዳናው እና ስርቻው እያዝረከረከች ያለችው፡
ያው እንደነገርኳችሁ ብቸኛ ነኝ፡፡ ዋናዎቹ ቤተሠቦቼ ማለት እናትና አባቴ በህይወት የሉም።ልጅ ሆኜ ነው በድንገተኛ አደጋ ተያይዘው የሞቱት ።እህትና ወንድምም በፊቱንም የለኝም፡፡ያሳደገችኝ የእናቴ ታናሽ እህት አክስቴ ነች። አክስቴ ከእኔ ውጭ የራሷ ሶስት ልጆች አሏት ፡፡ሶስት ሴቶች  እኔ አራተኛ ልጅ ነኝ።ምን አልባት ብቸኛ ወንድ ልጅ ስለሆንኩ  ወይንም የሙት  ልጅ  ስለሆንኩ አላውቅም  ልክ እንደ ስለት ልጅ በልዩ በእንክብካቤና በሀዘኔታ ነው ያደኩት።

አሁን ግን አድጌ ዩኒቨርሲቲ ገብቼ ከተመረቅኩ በኃላ ከዘመዶቼ በመቆራረጤ አየር ላይ ቀርቼያለሁ፤ወደዛ ቤተሠብ ፊቴን ማዞር የማልችልበት ሁኔታ ውስጥ ከገባው አመታት አልፏኛል።እንዴት? ቤተሠብን አፍርሻለሁ፡፡ እከሌ ከእከሌ ሳይባል ቤተሰቦቼ ምላቸውን የሁሉንም ልብ ሰብሬያለሁ..የዚህ ሁሉ መጥፎ ስራ ውጤት ደግሞ በድምሩ ወደራሴው ተመልሶ ሙሉውን የህይወት ተስፋዬን ደረማምሶ አፍራርሶብኝል፡፡ዓላማ ቢስ …ምንም ተስፋ የሌለው ተንቀሳቃሽ ሬሳ ሆኜያለሁ፡፡ዝርዝሩን ሌላ ጊዜ ከመነሻ ታሪኩ አንስቶ ተርክላችኋለሁ፡፡
///

እንደነገርኳችሁ እንዲህ ሆናለሁ ወይም እዚህ ቦታ ደርሳለሁ የሚል እንጥፍጣፊ ምኞትና እቅድ ውስጤ የለም…ተስፋዬ ከፈረሰ ቆይቷል.. ቢሆንም ዝም ብሎ  ለመኖር ብቻ ቢሆንም እንኳን መብላት ያስፈልገኛል።ለዛውም በቀን ሁለቴ እና ሶስቴ ። እናም ያንን ለማሟላት ደግሞ በየቀኑ መስራት የግድ ይላል።አዎ ወይ መብላት ማቆም አለብኝ ወይ ደግሞ ስራ መስራትና ገንዘብ መስራት አለብኝ። ግን ምንድነው የምሰራው?ምን ችሎታ ወይም ሞያ አለኝ?ስራ ለመፈለግ ስነሳ ይሄንን ጥያቄ  ነው እራሴን የጠየቅኩት፡፡

ከአለማያ ወደአዲስ አበባ እንደገባው እጄ ላይ አጠራቅሚያት የነበረችውን ጥቂት ሳንቲም እስክታልቅ ስራ በመፈግ በመኳተን አራት ድፍን ወራቶች አሳልፌያለሁ፡፡በስተመጨረሻ ተስፋ ከቆረጥኩና ኪሴ መራቆቱ እርግጥ ከሆነ በኃላ ያገኘሁትን ማንኛውንም ስራ ለመስራት ወሰንኩ፡፡ ,…ለሁለት ወራት በኮንስትራክሽን ድርጅቶች በቀን ስራ ለመስራት ሞክሬ ነበር….ግን በእውነት በጣም ወገብ ቆራጭ ብቻ ሳይሆን ተስፋ አስቆራጭ ስራ  ነው የሆነብኝ…በፊቱኑም የሌለ ተስፋ ሲቆረጥ ይታያችሁ፡፡ዕድሜውን ሙሉ በቤቱ ምንም አይነት የጉልበት ስራ የመስራት ልምድ ለሌለው ሰው ይቅርና ልምድ ላለውም ጉልበተኛ አርማታ መግፋትን መሸከምን የመሰለ ሌላ ፈታኝ  ስራ መኖሩን እጠራጠራለሁ…ምን አልባት የምድር ውስጥ የመአድን ቁፋሮ ሊበልጠው ይችላል፡፡ ስራው እኮ በተለይ ከሰዓት በኃላ ሲሆን ምላስ ታጥፋ ጉሮሮው ውስጥ ነው የምትወተፈው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ለመስራት የሞከርኩት የፓርኪንግ ስራ ነው…፡፡ከቀን ስራው ቢሻልም ገቢው ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም…፡፡ቢሆንም የፓርኪንግ ስራው ወደሌላ ስራ መሸጋገሪያ ድልድይ ሆነኝ….፡፡የፓርኪንግ ስራ የምሰራበት ቦታ በሁለት ቀንም ሆነ በሶስት ቀን እየመጣ ከሚጠቀም ሰው ጋር ቀስ በቀስ ተግባባን፡፡እንዲሁ ያለምክንያት ሲመጣ ደስ ይለኛል....፡፡ከሌላው የተለየ ፈገግታ እና መሽቆጥቆጥ አስተናግደዋለሁ..፡፡እሱም ቲፕ አስጨብጦኝ ይሄዳል፤ሳይመጣ አራት አምስት ቀን ካሳለፈ ቅር ይለኛል፤ለቲፑ አይደለም…እንዲሁ ለመልካምነቱ…፡፡
አንድ ቀን ታዲያ እንደወትሮ መጥቶ ፓርኪንግ ተጠቀሞ ሊሄድ ሂስብ እየተቀባበልን ሳለ ድንገት ወሬ ጀመርን፡፡
‹‹እዬብ እንዴት ነው ስራ?››
‹‹ጋሼ ሰሎሞን  ሰሪው ነው እንጂ ስራ ምን ይሆናል  ብለህ ነው?››አልኩት(ይህቺን ንግግር ከሆነ ጓደኛዬ ነው የሰማሁት)
2.8K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 14:00:09 #አኩርፈሻል_መሰል…

ግራ እጄን አመመኝ…
ከበረዶ በልጦ ይሄው ቀዘቀዘ
መራመድ አቃተው…
ለእርምጃ ሰነፈ ቀኝ እግሬም ተያዘ
የጎረስኩት ሁሉ…
አልጣፍጥህ አለኝ ጣእም ጣ'ሙን አጣ
የመሬት መንቀጥቀጥ…
የሚያስነሳ ንዝረት አናቴ ላይ ወጣ
ሁሉም ፉርሽ ሆነ
ህዝበ አዳም ተቀጣ ሕዝበ አዳም ተቆጣ
አኩርፈሻል መሰል…

ካልጋዬ ተኝቼ..
የምሰማው ዜማ እንቅልፍ እንዲወስደኝ
የነካውን እንጃ …
ባላሰብኩት ቅጽበት እንቅልፌን ነጠቀኝ
ለሽራፊ ጊዜ…
ዜማው አልዘመመም ቅኝቱ አልፈረሰም
ልክ እንደ ጥንቱ ነው የጎደለው የለም
የሆነው ሆኖ ግን…
እንዳረጀ ወንበር…
የሚንቋቋ ሆኖ ለኔ ይሰማኛል
በጨቀየ መንገድ…
ፍሬን እንደያዘ የመኪና ጎማ
ድምጹ እንደሚረብሽ
ልብስ እንደሚያበላሽ
ሰባት አይነት ዘፈን…
እንደለቀቁበት የገበያ አዳራሽ
እንደ ቆራሌው ድምጽ…
እንደ ልዋጭ ጥሪ እንደ ፍራሽ አዳሽ
እንደ ደፈኑት ቦይ …
እንደ አጥር ምሰሶ እንደ ግንቡ ፍራሽ
እንደ ጉቶ ጥላ…
እንደ ጫካ መንገድ እንደ ነገር ብላሽ
እንደ…እንደ…እንደ…እንደ
እንዲያ ይሰማኛል
አኩርፈሻል መሰል…

የቀየዷት በቅሎ …
የጎፈላ በሬ ያልተገራ ፈረስ
መስኮት የሌለው ዳስ…
በር የሌለው ድንኳን የጨበራ ድግስ
ምስክር የፈራው…
ማህላ የረሳ ሰው ናፋቂ መቅደስ
ከራስ የተጣላ…
ሩሁን የሳተ ጥምጣም የጣለ ቄስ
መምጫው ያልታወቀ…
መሄጃው የጠፋ ከባድ አውሎ ንፋስ
እንዲያ እንዲያ…እንዲያ እንዲያ
እንዲያ ይሰማኛል እንዲያ ይታየኛል
አኩርፈሻል መሰል…

ሰለሞን ሳህለ
3.7K viewsአትሮኖስ, 11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 20:37:36 የማይቆጠር ጊዜ ቀዬውን ጥዬ ልሄድ አስቤ አውቃለሁ። አንድ ቀን ኪዳን ከትምህርት ቤት ሲመጣ እኔ እቤት አልነበርኩም!! እያለቀሰ ስሜን እየተጣራ ሲፈልገኝ አገኘሁት
«ምን ያስለቅስሃል? ማን መታህ?» ነበር እንዳየሁት ያልኩት
«እ እ…. አንቺም እንደእማዬ ትተሽኝ አትሂጂ !! እንደአባዬ አትሙቺብኝ!» ብሎ ሲንሰቀሰቅ መቼም እንደማልተወው ለራሴ ቃል ገባሁ። በጊዜው እኔ ራሱ የሚያባብለኝ የሚያስፈልገኝ እንጭጭ ብሆንም ከእድሜዬ በላይ ሀላፊነትን ለራሴ ሰጠሁት። ከዛ በኋላ ነው ትምህርት ቤት ራሴ አድርሼ እመልሰው የጀመርኩት። ሁሌ ለሊት ተኝቶ ሲነቃ መጀመሪያ የሚያረጋግጠው የእኔን አልጋዬ ላይ መኖር ነው። ድንገት ቀድሜው ተነስቼ ካጣኝ በማጣት ሰቀቀን ሲፈልገኝ አገኘዋለሁ። የትም ጥየው እንደማልሄድ እንዲያምነኝ ብዙ ለሊት አቅፌው ካደርኩ በኋላ ነው ያመነኝ። የአባቴን ገዳዮች ከጠላኋቸው በላይ ጠላኋቸው።

በሽምግልና የታረቁ ጊዜ የተሰማኝ አጎቴ እንዳለው ቁጣ ብቻ አይደለም። መከዳት ነው የተሰማኝ!! የራሴን ወገኖችም ነው የተቀየምኩት። የእኔ እና የኪዳን ህመም ያላመማቸው ፣ እኔን አግልለው እነሱ የደስታ ጠቦት ጥለው የተቃቀፉ ……

አልገባቸውም!! አድጋ የአባቷን ደም ትበቀላለች ብለው ያጀገኑት ልቤ ውስጥ የበቀል ጥንስሴን እርሾ አድርገውበት ልቤ ልትፈነዳ እንደደረሰች። አልገባቸውም እሷማ ይሄን መንደር ታስከብራለች እያሉ ባሽሞነሙኑኝ ቃላት በጭንቅላቴ ውስጥ ያሉ ሌሎች የሰው ልጅ የመኖር መሰረታዊ ፍላጎቶቼን ሁሉ አንድ በአንድ በበቀል እንደተካሁ። አይዞሽ፣ በርቺ ብለው እጄን ይዘው ከድልድዩ ካደረሱኝ በኋላ እነርሱ ከጠላቶቼ ጋር ተመሳጥረው ቺርስ የተባባሉብኝ ዓይነት ስሜት ነው የተሰማኝ።

የአባቴ ገዳዮች ላደረጉት ነገር ሊቀጡ ሲገባቸው ግፋቸው ጭራሽ ክብር ሆኗቸው ስልጣን ሲሾማቸው የእኔው ወገን ሲያጨበጭብላቸው ብቸኝነት አጥንቴን ሰረሰረኝ። ብቻዬን የቀረሁ። ያውም ከነበቀል ጥማቴ!!

ባገኘሁት ሰው ላይ ሁሉ ከመደንፋት እና ከመደባደብ ውጪ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ስላላወቅኩ የማደርገው ጠፍቶኝ ሳለ ነበር አንድ ቀን ለክረምት ለክረምት አዲስ አበባ የሚሄደው ካራቴ አሰልጣኛችን በጉራ ሰውመሆንና የእሱ ቤተሰቦች አዲስ አበባ የሚጠያየቁ ወዳጃሞች መሆናቸውን ሲያወራ የሰማሁት ……. የዛን ቀን እንቅልፍ አልወሰደኝም!!! ከብዙ ጊዜ በኋላ የበቀል እቅዴን የማሳከበት መንገድ ጭላንጭል የታየኝ ስለመሰለኝ ሳቅኩኝ።

አዲስ አበባ መሄድ የሚለውን ሳስብ ደግሞ ከዚህ መንደር መራቅን አብዝቼ ሻትኩ። አዲስ ህይወት መጀመር የሚል ሀሳብ ልቤን በሀሴት ሞላው። አዲስ ያልኩት ህይወት መሰረቱ በቀል መሆኑ ካለፈው ህይወት ጋር እያመላለሰ እንደሚያላትመኝ የምረዳበት የአዕምሮ ብስለት አልነበረኝም!! ጭራሽም ከበቀል እና ከጥላቻ የተረፈ አዕምሮም አልነበረኝም!! የሚጠረጥርበት ምንም ፍንጭ ያልነበረው አሰልጣኝ አዲስአበባ ለክረምት መሄድ ማሰቤን እና ከተማውን እንዲያስለምደኝ ስጠይቀው ደስ ብሎት ነው የተስማማልኝ። ሰዎችን መጠቀሚያ ማድረግ የጀመርኩበት የመጀመሪያ ቀን መሆኑ ነው። ደሜ ውስጥ ከሚንቀለቀል በቀል ውጪ የሚሰማኝ የህሊና ደውል ስላልነበረ ያደረግኩት ብልጠት እንጂ ክፉት አልነበረም!! እንድደውልለት ስልክ ፅፎ ሰጠኝ።

«ኪዳንዬ ለሆነ ጉዳይ አዲስአበባ ደርሼ እመጣለሁ። ከዛ ግን መጥቼ እወስድህና አብረን እንኖራለን» አልኩት በራችን ላይ ቆሜ እሱ ከትምህርት ቤት መጥቶ እግሩን እየታጠበ ነበር። ያሰብኩት የነበረው ብቻዬን ሄጄ ከሸክም ጀምሮ ምንም ብሰራ ፣ ከዛ የተወሰነ ፍራንክ አጠራቅምና ኪዳንን አዲስ አበባ አምጥቼ አስተምረዋለሁ። ነው። የያዘውን ጆክ በቁሙ ለቀቀው እና እኔጋ መጥቶ እግሬ ላይ ተጠመጠመ። 15 ዓመቱ ነበር። ሁለቱንም እግሬን እንዳልፈናፈን አንድ ላይ ጨምቆ ይዞ

«የትም ትቼህ አልሄድም! ብለሽኝ አልነበር? ለምንድነው ይዘሽኝ የማትሄጂው? በዛው ልትቀሪ ነውኣ? አብሬሽ እሄዳለሁ!!» አለኝ እየጎረመሰ ባለ ድምፁ። አያለቅስም ግን ድምፁ ውስጥ ከለቅሶ የከበደ ሀዘን አለው።

«ኪዳንዬ አሁን ወስጄህ ምን አደርግሃለሁ? የምናድርበት ባይደላን ምን በወጣህ ውጪ ታድራለህ? የምንበላው ባይመቻች በምን እዳህ ትራባለህ? አንተ ገና ልጅ ነህ!! እኔ ይሰናከልብኛል የምለው የለኝም። አንተ ከትምህርትህ ለምን ትሰናከልብኛለህ?»

«ይኸው ትተሽኝ ሄደሽ ላትመለሽ ነው እንዲህ የምትዪኝ» አለ እግሬን ሳይለቅ

«እሺ በቃ ትቼህ አልሄድም!! አብረን እንሄዳለን!» ስል ራሴን ሰማሁት!! እዛው ላይ እንዴትም ብዬ ገንዘብ ማግኘት አለብኝ የሚለውንም አሰብኩ።

አስቤው አቅጄው ተለማምጄው ያደረግኩት ነገር አይደለም። 19 ዓመት እስኪሆነኝ ድረስ መግደልን እንጂ መስረቅን ለዓፍታም አስቤው አላውቅም!! ለመግደል ለራሴ በቂ ምክንያት ስለሰጠሁት ከመግደል ይልቅ መስረቅ ፀያፍ መሆኑን ነው ህሊናዬ የመዘገበው። በዛው ሳምንት ከአጎቴ ጋር እህል ልንሸጥ ትልቁ ገበያ አጅቤው ሄድኩ። አጎቴ እህሉን እያስረከበ አይኔ ተሻግሮ ከብት የሚገበያዩት ጋር ቀላወጠ። ነጋዴው ምን ያህል ከብት ቢሸጥ ነው እጁን ሞልቶ የተረፈ ገንዘብ የያዘው ብዬ እያሰብኩ ጭንቅላቴ ወዲያው ይሄ ሁሉ ብር ቢኖረኝ ኪዳንን ይዤ አዲስ አበባ የምኖረው ህይወት ታየኝ። ሰውየውን አየሁት አየኝ። ራሴን ገሰፅኩ!!

መረኑ ሀሳቤ <ያውም ጠላትሽ ነው> አለኝ። ለምሰራው ከእነርሱ ለባሰ ክፋት እና በቀሌ የምሰጠው ምክንያት ያ ነው። ድክመቴ!! እናት እና አባት ያሳጡኝ ሰዎች ናቸው!! ከሰውየው አይን ተሰውሬ ገበያውን ለቆ ሲወጣ ተከተልኩት። መውጫው ላይ ከሌሎች ሁለት ሰዎች ጋር ገጥመው ወደቀያቸው የሚወስዳቸውን መንገድ ተያያዙት። አድብቼ ተከተልኳቸው። አስር ወንድ ገጥሜ የማልፈራዋ ሴት እግሬ ተልፈሰፈሰብኝ!! እጄ አላበው!! በጥሻው አልፌ ከፊታቸው ብቅ አልኩ

«ልጎዳችሁ አልፈልግም!! እንደዛ እንዳደርግ አታስገድዱኝ!! ብር ነው የምፈልገው ብራችሁን ብቻ አውጥታችሁ እዚጋ አስቀምጡና ሂዱ!» አልኳቸው። እኔ መሆኔን ሲያውቁ ገና ብርክ ያዛቸው ….. ሽጉጥ መያዜን ሲያዩ በያዙት ሽመል ተስፋ ቆረጡ። አንደኛው ግን ወንድነቱ አነቀው። ሁለቱ ብራቸውን አስቀምጠውት መንገድ ሲጀምሩ እሱ ካልገጠምኩሽ አለ። አልምታህ ብዬ ለመንኩት።

«ግደይኝ» አለ። ቶሎ ካልሄድኩ መንገደኛ መጥቶ ሌላ አምባጓሮ ሊፈጠር እና ፖሊስ ሊመጣ ሆነ። በቆመበት ጉልበቱን ወደጎን ስረግጠው ህመሙ የእኔ ጉልበት እስኪመስለኝ ታወቀኝ። ብሩን አንስቼ ጢሻው ገባሁ። ለዘመናት ያላነባሁትን እንባ እያነባሁ ወደቤት ሮጥኩ። ሰውነትንም ከእንባዬጋ አብሬ አጥቤ ከሰውነቴ አስወጣሁት።

ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
5.6K viewsTsiyon Beyene, 17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 20:37:33 #የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል አስራ ዘጠኝ)
(ሜሪ ፈለቀ)

እንዲህ ነው የሚመስለኝ :- የራሴን ህይወት ራሴው ኖሬው እና ሌላ ሰው ሆኜ ደግሞ ከውጪ ሳየው!! ራሴን ሌላ ሰው ሆኜ ባየው ምን አይነት ሰው ነኝ ብሎ አስቦ የሚያውቅ ሰው ይኖራል? እድሉ ተሰጥቶትስ ራሱን ከውጪ ቢያየው ስንት ሰው ራሱን ይወደዋል? ወይስ ይፀየፈዋል?

እንግዲህ መታደል ይሁን መረገም እኔ የደረሰኝ ይህ እጣ ነው!! እንደ ሌላ ሰው ከውጪ ያየኋትን የድሮዋን ሜላት ድጋሚ መኖር ወይም ሌላ ሜላትን መፍጠር ደግሞ ከፊቴ ያሉ ምርጫዎች ናቸው። ሁለቱም አስፈሪ ምርጫ ነው!!!

በደም በተለወሰ ልብሴ ደሙ እጅና ፊቴ ላይ ደርቆ የሆስፒታሉ መጠበቂያ ቦታ ለሰዓታት ከአንዱ ቦታ ወደሌላው እንደፌንጣ እየዘለልኩ ነው ይሄን የማስበው። ስንት ሰዓት እንደጠበቅን ከማላውቀው ጊዜ በኋላ ከዛ ውጥንቅጥ ቦታ ይዞን የመጣው የጎንጥ ወዳጅ ወንበሩ ላይ ከነበረው ሰውነት በግማሽ ያነሰ መስሎ ተኮራምቶ እንደተቀመጠ

«መታጠቢያ እኮ አለ ቢያንስ ደሙን ከሰውነትሽ ታጠቢ!! ወይ መቀየሪያ ልብስ ላምጣልሽ?» ያለኝ እሱም እንደእኔ ሰውነቱ በደም መቅለሙን ሳያውቀው ይሆን እንጃ!! <አንተምኮ ደም ብቻ ነህ!> ማለት እፈልጋለሁ ግን አፌ ተለጉሟል። አውልቄ የጎንጥን ደም ለማስቆም ቁስሉ ላይ ይዤው የነበረውን ሹራቤን ይዞት ነው የተቀመጠው። - የኪዳን መልዕክት!! ዘልዬ ተነስቼ ሹራቡን ስወስድበት ብርግግ ብሎ አፈጠጠብኝ!!

«ሜል ይቅርታ እሺ!! ብዙ የምፅፍበት ጊዜ እና ሁኔታ ላይ አይደለሁም!! ማስታወስ እንደማትችዪ ሲያወሩ ሰምቻለሁ። ነገሮችን ስገጣጥማቸው ገባኝ!! እመቤትን እመኛት!! ያለችሽ ብቸኛ ጓደኛ እሷ ብቻ ናት!! ሌላው እኔ ማን እንደሆነች ብዙ ያልገባኝ አምነሽ ቪዲዮዎቹን ኮፒ ያስቀመጥሽባት ሴት አሁን ከእነርሱ ጋር ናት!! በቢዲዮዎቹ እየተደራደረች ነው!! እንዳታምኛት!! ታውቂ የለ እወድሽ የለ?»

«ይህቺ ከንቱ!» አልኩኝ ሳላስበው!! ወትሮም ጓደኛዬ አይደለችም!! ጥቅም ነው ያገናኘን!! እኔ ለጥቅሟ የምደምርላት ነገር እንደሌለ ባወቀች ቅፅበት ልትቀብራቸው ጉድጓድ ስትምስ የኖረችባቸው ሰዎች ጋር ሌላ የጥቅም ወጥመድ የዘረጋችበት ፍጥነት ……. ድሮም ትርፍ ካገኘችበት የገዛ ባሏን ከመሸጥ የማትመለስ ነጋዴ መሆኗን አውቃለሁ። የከንቲባው ሚስት ናት!! ባሏ ከንቲባ ከመሆኑ በፊት ከደሳለኝ (ኪዳንን ያገተው ሰውዬ) ጋር ወዳጃሞች ነበሩ!! ለአንድ ቦታ ለመመረጥ ፉክክር እስከጀመሩባት ጊዜ አንዳቸው ከሌላቸው ቤት የማይጠፉ፣ ልጆቻቸው እንደእህትና ወንድም የተቋለፉ ፣ ሚስቶቻቸው ከፀጉር ቤት እስከ ትልልቅ የህዝብ መድረክ ተቆላልፈው የሚተያዩ ዓይነት ነበሩ። ከንቲባው ሞተሩ ሚስቱ ናት እንደፈለገች በቀን ሙዷ የምታሾረው እንጂ የዋህ ቢጤ ነው። ደሳለኝ በገዛ ፍቃዱ ከውድድሩ ራሱን እንዲያገል ያን መረጃ ከእኔ ጋር በልዋጭ ጥቅም ተደራድራ ነው!! ተማምነን አይደለም የጠላቴ ጠላት በሚለው ተወዳጅተን እንጂ!! እከኪልኝ ልከክልሽ ተባብለን ነገር ……. እኔ አደጋ ላይ ብወድቅ እሷጋ ያለው ቅጂ ማስያዣ እንዲሆን ፤ እሷ አደጋ ላይ ብትወድቅ እኔ ጋር ያለው ቅጂ መገበያያ እንዲሆን ነበር ውላችን!! ድንገት በአንድ ቀን ጀንበር ያለድካም የተገነባ መተማመንም አልነበረም!! ከአንዲት 10 ሺህ ህዝብ ከሚኖርባት መንደር ወጥቼ ስልጣኑና አቅሙ አለን ከሚሉት ወንበዴዎች ጋር ለመግባት ለመውጣትስ የተጓዝኩት ጉዞ ቢሆን በቀላል ድካምና ላብ የተገነባ መች ነበር?

«የአቶ ጎንጥ ቤተሰቦች?»

ዘልዬ ተነሳሁ!! ዶክተሩ ከማውራቱ በፊት ነገረ አካላቴን በሀዘኔታ እያየ ነው ቀዶ ጥገናውን በስኬት መጨረሱን የነገረን።

«እስኪነቃ ድረስ እቤት ሄደሽ ተጣጥበሽ ልብስሽን ቀይረሽ መምጣት ትችያለሽ!!» አለኝ የጎንጥ ወዳጅ!! አልሄድኩም!! ተናኜጋ ደውዬ የምቀይረው ልብስ እንድታመጣልኝ አደረግኩ። ስልኩን ስዘጋ ተናኜ መርሳቴን አስታክካ የተቀበለችውን ደሞዝ ድጋሚ እንደተቀበለችኝ አስታውሼ ፈገግ አልኩ። የጎንጥን መመታት ስነግራት ያዙኝ ልቀቁኝ ማለቷስ? የአባቷን ለቅሶ የተረዳች አስመስላ አረፈችው። ልብሴን ቀያይሬ እንድትረጋጋ ላሳያት የተኛበት ክፍል ይዣት ብገባ ተኝቶ ስታየው ያን ለቅሶዋን አመጣችው። የልብሷን አንገትጌ በእጇ ጨምድዳ ይዛ ወደአፏ አስገብታ ንክስ አድርጋ…… <ህእእ > እያለች ሳጎን ወደ ውስጥ እየሳበች ተነፋረቀች።

«ምን ልሁን ነው ምትይ?» ሲል ነው መንቃቱን ያየነው። ይሄኔ ግራ የገባው ስሜት ተሰማኝ። የሆነኛው ልቤ (የሁለት ወሯ ሜላት ልብ ይመስለኛል) ስለነቃልኝ መፈንጠዝ ፣ አጠገቡ ሄጄ መነካካት ያምረዋል። የሆነኛው ልቤ (የድሮዋ ሜላት ልብ ይመስለኛል) ቆጠብ ማለት ፣ ኮስተር ማለት ያምረዋል። አጠገቡ ደረስኩ ግን እጁን ሊይዘው የተዘረጋ እጄ መንገድ እንደሳተ ነገር የአልጋውን ጫፍ ጨበጠ። ቅድም ሁለት ምርጫ አለኝ አላልኳችሁም? ወይ አሮጌዋን መሆን ወይ አዲስ መሆን? ሁለቱንም መሆን እንደማልችል እዚህ ጋር ገባኝ!! ቢያንስ በጎንጥ ጉዳይ!! ልቤ እና ሰውነቴ እንዳልተስማሙ ገብቶታል መሰለኝ ተናኜም ወዳጁም እግራቸው እንደወጣ ጠብቆ

«ተቀይመሽኝ ነው እንዴ?» ሲለኝ እስካሁን ስለማንነቱ፣ ስለዋሸኝ ዘበኝነቱ …… ተያያዥ ነገር ጭራሽ አለማሰቤ ገረመኝ። እዛ መኪናው ጋር ራሱን ከፊቴ አድርጎ የእኔን ሞት የተጋፈጠልኝ ሰዓት መቀየሜን ተውኩት? እዛጋ የበደለኝን አጣፋሁት?

«ቅያሜ አይደለም ያለኝ ጥያቄ ነው» አልኩት። ፈገግ ብሎ <ጠይቂኝ> እንደማለት በእጁ ወዲህ በይው ዓይነት ምልክት ሰራ። ወንበሩን ስቤ ከፊቱ እየተቀመጥኩ። <እዝህችው ቆመን 19 መቶ ብዬ እንዳወጋሽ አይደለማ ሀሳብሽ?> ብሎ የጮኸብኝ ትዝ ብሎኝ

«ገና ከመንቃትህ 19 መቶ ዓመተምህረት ብለህ ልታወጋኝ አይደለምኣ ሀሳብህ? (ፈገግ አለ) አንተ ጥለኸኝ የመጥፋት ሀሳቡ ከሌለህ በቀር እኔ የትም አልሄድም ያንተ እና የእኔ ጉዳይ ይደርሳል። ኪዳንን ጭረት ሳይነካው ዛሬውኑ ከዛ ቤት እንዲወጣልኝ ማድረግ አለብኝ።» አልኩት።

******

ልጅነቴ አጎቴ እንዳለው በጀግንነት እና ጀብድ ብቻ የተሞላ አልነበረም። ያ እነሱን ሆነው ሲያዩት የገባቻቸው ሜላት ናት። አባቴ የሞተበት ቦታ እየሄድኩ ሬሳው የነበረበት ቦታ ተቀምጬ በለቅሶ የምደነዝዝባቸውን የትዬለሌ ሰዓታት እሱ አያውቅም!! እናቴን የደፈራት ሰውዬ ፊት ለዓመታት በህልሜ እኔኑ ሲደፍረኝ እያየሁ በላብ ተጠምቄ ስንቀጠቀጥ የነጉትን ቁጥር አልባ ለሊቶች እሱ አያውቅም። ከሞቱ በፊት የነበረው የአባቴ ፊት ጠፍቶብኝ አባቴን ሳስብ የማስታውሰው የዛን ቀን ያየሁትን ፊቱን እየሆነብኝ ተሰቃይቼ ፎቶውን አቅፌ ማደሬን አያውቅም!! እናቴ ተመልሳ ትመጣ ይሆናል ብዬ ስንት ቀን እንደጠበቅኩ አያውቅም። አባቴን የገደሉብኝን ሰዎች ኮቲያቸውን ልኬት ሳይቀር በጭንቅላቴ ውስጥ ስዬ እንዳስቀመጥኩ አያውቅም!! ብዙ አያውቅም !! ብዙውን አልተናገርኩም!!
4.5K viewsTsiyon Beyene, 17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ