Get Mystery Box with random crypto!

‹‹አይ እዬብ እውነትህን ነው…ስለ ሰሪውን ነው መጠየቅ፤እሺ ሰሪው እንዴት ነው?›› ‹‹ይመስገነው. | አትሮኖስ

‹‹አይ እዬብ እውነትህን ነው…ስለ ሰሪውን ነው መጠየቅ፤እሺ ሰሪው እንዴት ነው?››
‹‹ይመስገነው..››በአጭሩ መለስኩለት፡፡
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ?››
‹አይ የለም..ያው ትንሽ ስራው እዛው ሞላ እዛው ፈላ ነገር ሆነብን እንጂ ሌላው ነገር አሪፍ ነው፡፡››
‹‹አዎ ይገባኛል …ግን ከበረታህ የማይቀየር ነገር የለም፤.ለመሆኑ ትማራለህ?››
‹‹ጋሼ ከረጅም ግዜ በፊት የሰማኋትን አንድ ቀልድ ልንገርህ…  አንዱ ዲያስፖራ ኢትዬጵያ ውስጥ መጣና በየመስሪያ ቤቱ እየዞረ እንዲቀጥሩት ማስረጃውን ይዞ ዞረ ዞረ ሁሉም ቦታ የለንም እያሉ መለሱት ..፡፡ከዛ በቃ ወደመጣሁበት ሀገር መመለስ አለብኝ ብሎ ዝግጅት ጀመረ..‹አንደኛህን አልነበረ እንዴ የመጣኸው ምነው?ለምን ትመለሳለህ ?››ሲሉ ጓደኞቹ ጠየቁት ‹አይ መሮኛል ይህቺ አገር ድሮም ለተማረ ሰው አትሆንም ..ከምድረ አሜሪካ ማስተርስ ድረስ ተምሬና ተመራምሬ  መጥቼ ስራ ተነፈገኝ?›ብሎ አማረረ…ሰዎቹም እውነትም ይህ ሰው ተበድሏል ብለው ቁጭት ውስጥ ገቡና ይበልጥ ለማጣራት ..‹ ለመሆኑ በምን ሞያ ነበር የተመረቅከው.. ?ብለው ይጠይቁታል ‹‹በበረዶ ሸርተቴ›ብሎ እርፍ››
አቤት የሳቁት ሳቅ…እንባቸው እስኪንጠባጠብ ድረስ ነው ሆዳቸውን ይዘው እየተንፈቀፈቀቁ የሳቁት ….ደስ አለኝ፡፡.ቀልድ የሚገባው ሰው ደስ ይለኛል…አዕምሮ ንቁና ፈጣን የሆነ ሰው ነው ለቀልድ ፈጣን ምላሽ የሚሰጠው ብዬ አምናለሁ፡፡
‹‹ቆይ ቆይ ቀልዱ እውነት ይሆን ፈጠራ አስቆኛል..ግን  ከጠየቅኩህ ጋር ምን አገናኘው?››
አላልኳችሁም ሰውዬው ነቄ ነው ፤ ወደዋናው ቁምነገር ጫወታውን አዞረልኝ፡፡
‹‹ጋሼ ሰው እንዳይሰማን  ቀስ ብዬ ልንገሮት.. እኔም  ከአለማያ ዩኒቨርሲቲ በእፅዋት ሳይንስ በዲግሪ ተመርቄያለሁ…እና ስራ ፍለጋ የተሰማራሁት ግን አዲስ አበባ ነው……እና እንደዲያስፖራው ይህቺ ሀገር ድሮም ለተማረ ሰው አትሆንም እያልኩ እራሴን እያፅናናሁ ነው፡፡›.
‹‹እውነትህን ነው?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው››
‹‹እንግዲያው…›› አሉና ከጃኬት ኪሳቸው ውስጥ ቢዝነስ ካርዳቸውን አውጥተው እየሰጡኝ…..ቢያንስ ከዚህ ትንሽ የተሻለ ስራ ልሰጥህ የምችል ይመስለኛል፤ነገ ተነገ ወዲያ ሲመችህ ደውልልኝ›› ብለውኝ እንደፈዘዝኩ መኪናቸውን አስነስተው ተፈተለኩ ....ከዛ ያለ ዋስ የለምንም አንጃ ግራንጃ ሁለት ስራ ተሰጠኝ፡፡የመጀመሪያው ስራ አስተናጋጅ ሆኜ እንድሰራ ሲሆን ሁለተኛው ስራ  የሆቴሉን ንብረት መቆጣጠር ነው፡፡የተሰበረ ካለ ማስጠገን፤የጠፋ ካለ  ሪፖርት ማድረግ፤የጎደለ ካለ እንዲገዛ ማድረግ ወዘተ..ለሁለቱም ስራዬ በተናጠል ደሞዝ ይከፈለኛል፡፡በዛ ላይ የአስተናጋጅነት ስራ ከደሞዙ በላይ ቲፑ አስደሳች ነው፡፡....

ይቀጥላል