Get Mystery Box with random crypto!

#እህቴ_በባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ፡፡ : : #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ፡ ፡ #ክፍል_አንድ /// ይሄን | አትሮኖስ

#እህቴ_በባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ፡፡
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አንድ
///

ይሄን ታሪክ እንደባዬግራፊ ውሰዱት፡፡ በነገራችን ላይ ባዬግራፊ ማንበብ ደስ ይለኛል፡፡ግለ-ታሪክ በጥልቅ ሳንሱር የተደረገ፤ የተስተካከለ እና የተሞረደ የግለሰብ ፍፅማዊ ታሪክ ነው ብዬ አምናለሁ ፡፡
ግለ-ታሪክ በተለየ መለኩ  ታዳጊዎችን ለመቅረፅና ሞዴል ኖሯቸው የወደፊቱን ህይወታቸውን  መስመር  እንዲያሲዙትና ጉዞቸውን ከመዝረክረክ፤ እራሳቸውንም ካላአስፈላጊ ውጤት አልባ መስዋዕትነት ለመታደግ  ጥረት እንዲያደርጉ ያግዛቸዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ግን ያው ሄዶ ሄዶ ህይወታቸው መዝረክረኩ፤ በየሂደቱም ለማይረቡ ነገሮች መሰዋዕትነት መክፈላቸው የማይቀርላቸው የህይወት ዕዳ ነው፡፡ ቢሆንም ጥረታቸው  የመዝረክረክ መጠኑ ላይ ልዩነት ያመጣል፡፡

ሌላው አዎ ግለ-ታሪክ ግለሰቦችን ብራንድና፤ ሪብራንድ የማድረጊያ ውጤታማ ዘዴ ነው፡፡ የማይሰበረው፤ሰውዬው፤የታፋኙ ማስታወሻ፤የበጋው  መብረቅ፤ የህይወቴ ጉዞና የፖለቲካ ህይወቴ  ፤የመንግስቱ ትዝታዎች ፤የመለስ ዜናዊ የህይወትና ትግል ታሪክ ፤ዳኛው ማን ነው?፤ ማማ በሰማይ ወዘተ…..
ቢሆንም ይሄን የእኔ ታሪክ ከእነዚህ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ግለ-ታሪኮች የሚለየው ድንግል በመሆኑ ብቻ ነው፡፡ድንግል ግለ-ታሪክ ግን ምን አይነት ነው? ፡፡ለማለት የፈለኩት ስለባለታሪኩ ከዚህ በፊት በየትኛውም የመገናኛ  ዘዴ ፤በመፅሀፍ፤ በሬዲዬ ሆነ በጋዜጣ  አልሰማችሁም ፤አላነበባችሁም ማለቴ ነው፡፡

ከእኔና በዙሪያዬ ካሉ ጥቂት ሰዎች በስተቀር ማንም የማያውቀኝ ተራ ግለሰብ ነኝ፡፡ያው አናንተም እንደእኔ ተራ ከሆናችሁ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ግለ-ታሪኮች ይልቅ የሚመጥናችሁም የሚያስተምራችሁም ይህ የእኔ የተራው ሰው ተራ ታሪክ ነው፡፡ምክንያቱም እኔ ራሴን ብራንድም፤ ሪብራንድም የማድረግ  ዓላማ የለኝም፤ምን ሊረባኝ..?እኔ መተንፈስ ብቻ ነው የምፈልገው፤ እናንተም አድማጭ እንድትሆኑኝ ብቻ ነው የምጠይቀው…በቃ ይሄው ነው፡፡

ከደብረብርሀን ወደአለማያ ዩኒቨርሲቲ ..ከአለማያ ደግሞ ወደአዲስ አበባ ከገባሁ ሁለት አመት ሆነኝ።  የተመረቅኩት በእፅዋት ሳይንስ ሲሆን ስራ ፍለጋ ከአንድ አመት በላይ የኳተንኩት ግን አዲስአበባ ነው። እርግጥ ወደ እድገት ከተማዬ ደብረብርሀን  ተመልሼ ቢሆን ኖሮ በቀላሉ በሁለት እና ሶስት ወር ውስጥ በተማርኩበት ትምህርት የሚገባኝን ወይንም ደግሞ ለጊዜውም ቢሆን የሚያኖረኝን ስራ አገኝ እንደነበረ እርግጠኛ ነኝ፤ግን እኔ ያንን ማድረግ አልቻልኩም… አልችልምም።
ለጊዜው ሰው እንደጉንዳን በሚርመሰመስባት  ፤ የህንፃ ጫካ የተጥለቀለቀባት  አዲስአበባ ምርጫዬ ሆናለች? ለምን? እራሴን ልደብቅባት፡፡ለምን ?ከሚያውቁኝ ዘመድ ወዳጅ አብሮ አደጎቼ መሠወር የምችልባት አስተማማኝ  ዋሻ አድርጌ ስለወሰድኳት።ለምን ?ባላድግባትም እትብቴ የተቀበረባት የትውልድ ከተማዬ ስለሆነች፤ ስለምወዳት፡፡የእኔ አዱ ገነት፤የእኔ ሸገር፡፡

እውነት እውነቱን እንነጋገር ከተባለ በዚህ ዘመን በኢትዬጵያ ዘመድ ወይም ወገን የምትለው ሰው በዙሪያህ ከሌለ ከዛም አለፍ ብሎ ባለጎሳና ባለ ብሄር ካልሆንክ መኖር የምትችለበት ቦታ እየጠፋ ነው…፡፡እንደእኔ ነጠላና መለመለውን ያለ ግለሰብማ ከሸገር ውጭ ለመኖር መወሰን አይደለም ማሰብ እራሱ አደጋ  ነው፡፡በዚህ ምክንያትም ይመስለኛል ሰዉ ከአራቱም አቅጣጫ በየምክንያቱ ጓዜን ማቄን ሳይል መጥቶ እየተጠቀጠቀባት ይሄው አሁን ሞልታ የሰውን ልጅ እንደ ውሻ ቡችሎች በየጎዳናው እና ስርቻው እያዝረከረከች ያለችው፡
ያው እንደነገርኳችሁ ብቸኛ ነኝ፡፡ ዋናዎቹ ቤተሠቦቼ ማለት እናትና አባቴ በህይወት የሉም።ልጅ ሆኜ ነው በድንገተኛ አደጋ ተያይዘው የሞቱት ።እህትና ወንድምም በፊቱንም የለኝም፡፡ያሳደገችኝ የእናቴ ታናሽ እህት አክስቴ ነች። አክስቴ ከእኔ ውጭ የራሷ ሶስት ልጆች አሏት ፡፡ሶስት ሴቶች  እኔ አራተኛ ልጅ ነኝ።ምን አልባት ብቸኛ ወንድ ልጅ ስለሆንኩ  ወይንም የሙት  ልጅ  ስለሆንኩ አላውቅም  ልክ እንደ ስለት ልጅ በልዩ በእንክብካቤና በሀዘኔታ ነው ያደኩት።

አሁን ግን አድጌ ዩኒቨርሲቲ ገብቼ ከተመረቅኩ በኃላ ከዘመዶቼ በመቆራረጤ አየር ላይ ቀርቼያለሁ፤ወደዛ ቤተሠብ ፊቴን ማዞር የማልችልበት ሁኔታ ውስጥ ከገባው አመታት አልፏኛል።እንዴት? ቤተሠብን አፍርሻለሁ፡፡ እከሌ ከእከሌ ሳይባል ቤተሰቦቼ ምላቸውን የሁሉንም ልብ ሰብሬያለሁ..የዚህ ሁሉ መጥፎ ስራ ውጤት ደግሞ በድምሩ ወደራሴው ተመልሶ ሙሉውን የህይወት ተስፋዬን ደረማምሶ አፍራርሶብኝል፡፡ዓላማ ቢስ …ምንም ተስፋ የሌለው ተንቀሳቃሽ ሬሳ ሆኜያለሁ፡፡ዝርዝሩን ሌላ ጊዜ ከመነሻ ታሪኩ አንስቶ ተርክላችኋለሁ፡፡
///

እንደነገርኳችሁ እንዲህ ሆናለሁ ወይም እዚህ ቦታ ደርሳለሁ የሚል እንጥፍጣፊ ምኞትና እቅድ ውስጤ የለም…ተስፋዬ ከፈረሰ ቆይቷል.. ቢሆንም ዝም ብሎ  ለመኖር ብቻ ቢሆንም እንኳን መብላት ያስፈልገኛል።ለዛውም በቀን ሁለቴ እና ሶስቴ ። እናም ያንን ለማሟላት ደግሞ በየቀኑ መስራት የግድ ይላል።አዎ ወይ መብላት ማቆም አለብኝ ወይ ደግሞ ስራ መስራትና ገንዘብ መስራት አለብኝ። ግን ምንድነው የምሰራው?ምን ችሎታ ወይም ሞያ አለኝ?ስራ ለመፈለግ ስነሳ ይሄንን ጥያቄ  ነው እራሴን የጠየቅኩት፡፡

ከአለማያ ወደአዲስ አበባ እንደገባው እጄ ላይ አጠራቅሚያት የነበረችውን ጥቂት ሳንቲም እስክታልቅ ስራ በመፈግ በመኳተን አራት ድፍን ወራቶች አሳልፌያለሁ፡፡በስተመጨረሻ ተስፋ ከቆረጥኩና ኪሴ መራቆቱ እርግጥ ከሆነ በኃላ ያገኘሁትን ማንኛውንም ስራ ለመስራት ወሰንኩ፡፡ ,…ለሁለት ወራት በኮንስትራክሽን ድርጅቶች በቀን ስራ ለመስራት ሞክሬ ነበር….ግን በእውነት በጣም ወገብ ቆራጭ ብቻ ሳይሆን ተስፋ አስቆራጭ ስራ  ነው የሆነብኝ…በፊቱኑም የሌለ ተስፋ ሲቆረጥ ይታያችሁ፡፡ዕድሜውን ሙሉ በቤቱ ምንም አይነት የጉልበት ስራ የመስራት ልምድ ለሌለው ሰው ይቅርና ልምድ ላለውም ጉልበተኛ አርማታ መግፋትን መሸከምን የመሰለ ሌላ ፈታኝ  ስራ መኖሩን እጠራጠራለሁ…ምን አልባት የምድር ውስጥ የመአድን ቁፋሮ ሊበልጠው ይችላል፡፡ ስራው እኮ በተለይ ከሰዓት በኃላ ሲሆን ምላስ ታጥፋ ጉሮሮው ውስጥ ነው የምትወተፈው፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ለመስራት የሞከርኩት የፓርኪንግ ስራ ነው…፡፡ከቀን ስራው ቢሻልም ገቢው ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም…፡፡ቢሆንም የፓርኪንግ ስራው ወደሌላ ስራ መሸጋገሪያ ድልድይ ሆነኝ….፡፡የፓርኪንግ ስራ የምሰራበት ቦታ በሁለት ቀንም ሆነ በሶስት ቀን እየመጣ ከሚጠቀም ሰው ጋር ቀስ በቀስ ተግባባን፡፡እንዲሁ ያለምክንያት ሲመጣ ደስ ይለኛል....፡፡ከሌላው የተለየ ፈገግታ እና መሽቆጥቆጥ አስተናግደዋለሁ..፡፡እሱም ቲፕ አስጨብጦኝ ይሄዳል፤ሳይመጣ አራት አምስት ቀን ካሳለፈ ቅር ይለኛል፤ለቲፑ አይደለም…እንዲሁ ለመልካምነቱ…፡፡
አንድ ቀን ታዲያ እንደወትሮ መጥቶ ፓርኪንግ ተጠቀሞ ሊሄድ ሂስብ እየተቀባበልን ሳለ ድንገት ወሬ ጀመርን፡፡
‹‹እዬብ እንዴት ነው ስራ?››
‹‹ጋሼ ሰሎሞን  ሰሪው ነው እንጂ ስራ ምን ይሆናል  ብለህ ነው?››አልኩት(ይህቺን ንግግር ከሆነ ጓደኛዬ ነው የሰማሁት)