#የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ሀያ) (ሜሪ ፈለቀ) እነዛ ጫማ ያልለበሱ እግሮቻቸው ፣ የከብት ሽታ የሚሸት አዳፋ ልብሳቸው ፣ ያለፉበት መከራ የተፃፈበት የግንባራቸው መስመር ፣ ዘመናቸው ድሎት እንዳልጎበኘው የሚያሳብቁት ሻካራ እጆቻቸው ፣ ብራቸውን ስወስድባቸው እንድራራላቸው የሚለማመጡ ከርታታ ዓይኖቻቸው …….. ከአጠገባቸው ርቄ እንኳን አልራቀኝም!! የስንት ቀን የልጆቻቸው ምሳና እራት ይሆን? ምናልባት የሚያፈስ ቤታቸውን ሊያድሱ ይሆናል! ምናልባት የሚከፍሉት እዳ ይኖርባቸዋል! …… ብዙ ርቄያቸው ከሄድኩ በኋላ በጉልበቴ መሬቱ ላይ ዘጭ አልኩ!! አባቴ ብሎ ቢያሳድገኝም ዛሬ መጀገን አቃተኝ! ለአፍታ ተመልሼ ሄጄ ብሩን ሰጥቻቸው የመምጣት ሀሳብ ሁላ ሽው ብሎብኝ ነበር። ይሄ ምስላቸው ለዓመታት ስቃዬ ነበር። ከበደሉኝ ሰዎች እኩል የበደልኳቸው ሰዎች ፊት እንቅልፍ የማያስተኛ ቅዠቴ ነበር። ለደቂቃዎች እዛው በጉልበቴ ከተንበረከኩበት የመጨረሻዋን አውቶቡስ ተሳፍረን አሁኑኑ ካልወጣን ፖሊሶቹ እኛ ቤት ለመድረስ ምንም የምርመራ ሂደት እንደማይፈጅባቸው ሳስታውስ ተነሳሁ:: እንባዬን ጠራርጌ ሮጥኩ!! ያገኘሁትን የእኔን እና የኪዳንን ልብስ በፔስታል ጨመርኩ። ያለችንን አንድ ለእናቱ ጫማ ተጫምተን ወደመነሃሪያ እጁን ይዤ መሮጥ ጀመርኩ። መነሃርያው አካባቢ ስንደርስ ከኋላዬ ሁለት በእድሜ ጠና ያሉ የኛ አካባቢ የማይመስሉ ሰዎች ሲያወሩ ወሬያቸው ጆሮዬን ጠለፈው። «የወዲያ ቀዬ ሰዎችን ዛሬ ሽፍታ ዘረፋቸው የሚሉትን ወሬ ሰማህ?» «ኸረ አልሰማሁም!! ወደየት ግድም?» «ከገበያው ጫፍ ትንሽ ቢርቁ ነው አሉ!! አንደኛው ይሄ በሬ ሻጩ አያልነህን አታውቀውም?» «አያልነህ? አያልነህ?» «ይሄ ሲያወራ ምራቁን እንትፍ የሚለው? ይህ እንኳን ወንድ ወልዳለሁ ብሎ ሲተኛ ስድስት ሴት ያሳደገው? በመጨረሻ ሚስቱ ወንድ ልጅ ሰጥታው እንዴየውም ደግሶ ያበላ ጊዜ አቅልህን እስክትስት ጠጥተሃልይ!!» «እንዴ? እንዴ? አያልነህ በሬ ሻጩ?» «ኤድያ እንዴት ያለው እንከፍ ነው? ምን እያልኩት ምን ይላል?» ፍጥነቴን አቀዝቅዤ ወሬያቸውን ከሰማሁ በኋላ ድጋሚ መፍጠን ጀመርኩ። የሚለው ስም ጭንቅላቴ ውስጥ ልክ እንደዛ የአባቴን ሬሳ ተራምዶት እንዳለፈው ሰውዬ ኮቴ ታተመ። «ሜል? ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው?» ብሎ ኪዳን ዓይን ዓይኔን እያየ ሲቁለጨለጭ ነው እንባዬ እየወረደ መሆኑን ያወቅኩት። «ምንም አልሆንኩም!!» «ምንም ሳትሆኚ ታዲያ እንባሽ ይፈሳል? እኔ ይዘሽኝ ካልሄድሽ ብዬ ስላስጨነቅኩሽ ነው?» «ይሄ ደግሞ! ለምን አርፈህ አትሄድም? እኔ አስጨንቀኸኛል አልኩህ?» እየተነጫነጭኩ እንባዬን ጠርጌ ትኬታችንን ቆርጠን አውቶብስ ውስጥ ገባን!! ከከተማዋ እየወጣሁ በአውቶብሱ መስኮት ወደኋላዬ የሚያልፈውን ተወልጄ ያደግኩበት መንደር ሸኘሁት። ድብልቅልቁ የወጣ ስሜት ተሰማኝ። ትቼው ስሄድ ሀዘን ካጠላበት ጊዜያቶች ይልቅ የታሰበኝ የአባቴ ትከሻ ላይ እሽኮኮ ተደርጌ ከጫካው እስከ ጠላ ቤት ግርግሩ ስዞር ጠላ ቤት እግሩ ላይ አስቀምጦኝ በሰዓቱ የማይገቡኝን ወሬዎች እየቀደደ ጠላውን ሲጠጣ እናቴ ከሩቅ እየተራገመች መጥታ «ልጅቱን ጭራሽ አምቡላችሁ መሃል ይዘሃት ትመጣ?» ብላ ከእግሩ አንስታኝ የምትሄደው አባቴ ገበያ መሃል ጠብመንጃውን እንዳነገተ ሲያልፍ አላፊ አግዳሚ ከአንገቱ ጎንበስ ብሎ ከልብ በሆነ አክብሮት ሰላምታ ሲያቀርብለት ትከሻው ላይ ሆኜ የተቆነንኩት ከወዳጆቹጋ ሰብሰብ ብሎ ዳማ ከሚጫወትበት አብሬያቸው ሳነግስ እማዬ ትመጣና ብላ ገና በ10 እና በ11 ዓመቴ ሀሳብ የሚገባት የነበረው አንድ ቀን አባቴ ሽጉጡን አስይዞኝ ስታይ ለቅሶ እንደተረዳች ጭንቅላቷን ይዛ እሪሪሪሪሪሪ ብላ ጮሃ ጎረቤት አሰብስባ «ይሄን ሰው አንድ በሉኝ» እያለች ወገቧን ይዛ የተንጎራደደችው እናቴ ከምትሸጠው ፍራፍሬ ላይ ከገበያ ስትመለስ ለምድረማቲ ትሰጥና እኛ ቤት ደጅ ላይ የተሰጠንን እየበላን የምንዘለው ከትምህርት ቤት ስንመለስ ከቤተሰብ ተደብቀን ወንዝ ወርደን እየተንቦጫረቅን ባልተገረዘው ልጅ ወ*ላ ንፍር ብለን የምንስቀው ክረምት ላይ እማዬ ቡና እያፈላች የተቀቀለ በቆሎ እየጋጥን እጣኑን ስትሞጅረው ሲላት ከተናገረው ውጪ እሷ ምን እንደገባት ሳይገባን እንደመሽኮርመም እያደረጋት እያለች ጭሱን በተን በተን ስታደርግለት የነገሩ ውል ምን እንደሆነ ባይገባንም እኔና ኪዳንም አብረናቸው የምንሽኮረመመው ሁሌም መምጣቷ ላይቀር ጓዳ ሆና ስትል ይለኛል እንደመጥቀስ እያደረገኝ። እጇን እያደራረቀች እያጉረመረመች መጥታ ትከሻውን ጀርባውን የምታሸው እንዲህ እንዲህ ዓይነቱን ቀን ነው ያስታወስኩት! አስታውሼም በአውቶብሱ መስኮት የሸኘሁት!! አባቴ የሞተ ቀን ይሄ ሁሉ አብሮ ከአባቴ ጋር የተቀበረ ሳይሆን ልቤ ያን ንፁህ የልጅነት ጊዜም ልብም ዳግም ላላገኘው ልክ የዛን እለት የተሰናበትኩት ያህል አንሰፈሰፈው ……. ሁሉም ነገር ልክ የዛን ቀን የተሰናበትኩት ያህል….. የሚገጥመው አቀበት ታውቆት ነበር መሰለኝ! የአብቶብሱ መቀመጫ ላይ አጠገቤ የተቀመጠውን ኪዳን ጭምቅ አድርጌ አቅፌ 2.4K viewsTsiyon Beyene, 16:58