Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163.71K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 43

2022-12-13 20:06:10 «ከትናንት እስከአሁን በ24 ሰዓታት ያልተፈጠረ ነገር የለም ብልሽ ይቀላል። አንድ ቀን ሳይሆን አንድ ዓመት የሆነ ነው የሚመስለው። ኪዳንን ላስለቅቅ በነበረ ሂደት የተኩስ ልውውጥ ነበር። በዛ መሃል ሲመስለኝ የሽጉጥ ተውሱ ትውስታዬን የወሰደብኝ ተኩስ አደጋን አስታወሰ እና ትውስታዬን ቀሰቀሰው። አላውቅም የተከሰተውን ብቻ አስታወስኩ ሁሉንም!!»

«wait a minute …. It’s too much information eko (ጭንቅላቷን የሆነ ከደነዘዘበት እንደማባነን፣ እንደማንቃት ያለ እየወዘወዘች) እሺ የትውስታ መሄድ መምጣቱ ይቆየኝ! ኪዳን safe ሆነ? ሆ! አይገርምሽም?  I felt it ደግሞ እኮ……. Something was off » አለች አሁንም ዓይኗ እላዬ ላይ መርመስመሱን ሳታቆም!

«አልሆነም!! አሁንም እነሱጋ ነው ለዛ ነው እርዳታሽን የምፈልገው!!»
«ምንም እየገባኝ አይደለም! ተኩስ ነበር አላልሽኝም? አንቺ ታዲያ እንዴት እዚህ ተገኘሽ?»
«እሙዬ እመኚኝ ስናወራ ውለን ብናድር አይገባሽም!! ጎንጥ ከነርሱ አንዱ ነው። እኔ በሱ ምክንያት ነው እዚህ ያለሁት! እሱ ደግሞ ሆስፒታል ነው ተመትቶ!! (ይበልጥ ሲዞርባት አየሁ) ሌላ ቀን እነግርሻለሁ እሱን!!»

«ጎንጤ ጥጋቡ የእነሱ? እኮ ዘበኛሽ ሰላይ? እመኚኝ አመትም ብትነግሪኝ ይሄ ነገር አይገባኝም!!»
«እኔም ብዙ አልገባኝም ኪዳኔን ቅድሚያ ልስጥ ብዬ እንጂ!!»
«እሺ ምንድነው እንዳደርግልሽ የምትፈልጊው?»
«እናንተ ቴሌቭዥን ጣቢያ አሁን በምርጫው ዙሪያ እየሰራ ያለ ጋዜጠኛ እንዲተባበረኝ እንድታደርጊልኝ እፈልጋለሁ። እና ደግሞ ዛሬ የሁለት ሰዓቱን ዜና የሚያነበውን ሰው!»

«እሺ አገኘሁልሽ! ምን አስበሽ ነው?» አለች ጭራሽ ግራ ተጋብታ!!
«የምርጫው ዜና ሲተላለፍ አቶ ደሳለኝም አንዱ እጩ ተወዳዳሪ እንደመሆናቸው አንዱ ጋዜጠኛችሁ እቤታቸው ተገኝተው ላይቭ አጭር ቃለመጠይቅ ያደርጉላቸዋል። የምታደርጉትን አድርጉ ስትፈልጉ ሙሉውን ቃለመጠይቅ ከዜና በኋላ ያቅርቡት። እኔ የምፈልገው ከእኔጋ በተቀናጀ ሰዓት ላይቭ መግባታቸውን ነው።»

«እየገባኝ አይደለም!! የማስበውን እያሰብሽ ከሆነ በጣም ሪስክ አለው!»
«አውቃለሁ ግን ከዚህ የተሻለ ደም ሳይፈስ፣ ህይወት ሳይጠፋ ኪዳንን ላገኝ የምችልበት ምንም አማራጭ አልታየኝም!! ብቻ አንቺ ይሄን ማድረግ ትችዪ እንደው ንገሪኝ?»

«ወይ ጉድ! እስኪ ስልክሽን ስጪኝ ልደዋውል!!»

«እሺ በስልኬ ግን ምንም አይነት መረጃ እንዳትቀያየሪ! ከእኔ ጋር እንዲገናኑ ብቻ በሆነ መላ ንገሪያቸው። ምናልባት አላውቅም!! ስልኬን ሲሰጡኝ ውስጡ የነበረ ብዙ ነገር አፅድተው ነው የሰጡኝ። ሁሉንም ሶሻል ሚዲያዎቼን አዘግተውታል። መቼም የማላስታውስ ነበር የመሰላቸው መሰለኝ ወይም ከማስታወሴ በፊት እንደሚደፉኝ እርግጠኞች ነበሩ።»

«እንደዛ ከሆነ መደወሉ በራሱ ሪስክ አለው!! (ዘወር ብላ ወደ ጠባቂው) ሼባው? ዛሬ ለሚስትህ ዓመትበዓል ማስመሰል አላማረህም? ስልክህን ለ5 ደቂቃ ልደውልበት ?» አለችው። የጠባቂውን ስልክ ተቀብላ ሁለት ቦታ ስልክ ደዋወለች። ስልኮቹንም ለእኔ እንድመዘግብ ነገረችኝ። እኔ በምፈልገው መንገድ አዘጋጀችልኝ። መልሳ ለጠባቂው ከሰጠኋት ብር ጋር ስልኩን እየሰጠችው

«ሳመኝኮ!» የሚለው ቃል አፌን አምልጦ ሲወጣ እኔው ራሴ ስሰማው እና እሷ ጆሮ ጠልቆ ሽው ብላ ዞራ ስታፈጥብኝ አንድ ቅፅበት ነው።

«ጎንጥ! ከንፈሬን አይደለም ደግሞ እጄን ነው! እዚህጋ! » ብያት የሳመኝን እጄን እንደሌላ ሰው ባዕድ እጅ ሳየው አይታ

«እርፍ መጃጃል!! እጅሽን ስሞሽ ድንግልናዋን ዛሬ እንደሰጠች ልጃገረድ እንዲህ የተሽኮረመምሽ ሌላ ነገር ቢያደርግሽ ክንፍ አውጥተሽ ልትበሪ ነው?» ብላ መሳሜን ስላቀለለችብኝ ተናደድኩ። እንዲህ ያለ መሳም ተስማ ባታውቅ ነው ያልገባት። ወዲያው ቀጥላ  «እንዴ ደግሞ ቆይ አሁን ከደቂቃዎች በፊት የእነርሱ ወገን ነው አላልሽኝም? አንቺ ሴት ዛሬ ግራ ያልተጋባ ምንም ወሬ ያለሽ አልመሰለኝም!»


«እንዳልሽው ነው ሁሉም ነገር ግራ የተጋባ ነው!! እጄን የሳመኝ ግን ግራ አያጋባም ሃሃሃሃሃሃ ኩልልል ብሎ ጥርት ያለ ነው።» ብያት ዝርዝሩን ከሰሞኑ መጥቼ ልነግራት ተስማምተን ተለያየን።

ተመልሼ ወደከተማ እየሄድኩ ተናኜጋ ደውዬ የተወሰነ ጥሬ ብር እና ለእንዲህ አይነት ጊዜ ለመጠቀም ገዝቼ አስቀምጫቸው ከነበሩ ሲሞች አንዱን እንድታመጣ ቦታውን ነገርኳት። በመንገዴ አዲስ የስልክ ቀፎ ገዛሁ። ዳዊትጋ ስልክ ደውዬ መኪናዬ ስለተበላሸች አሁኑኑ የእርሱን እንዲያውሰኝ ስጠይቀው በዛ ጭንቅንቅ መንገድ ነድቶ ሳይሆን በአየር ላይ በሮ በሚመስል ፍጥነት ያልኩት ቦታ ደረሰ። መኪናዋን ልነዳ ከተቀመጥኩ በኋላ ምንም እንኳን ሁሉም ትውስታዬ ቢመለስ ለሰከንዶች መንዳት መቻሌን እርግጠኛ አልሆንኩም ነበር። ወይም ፍርሃት ተሰምቶኝ ነበር።

ሁሉንም ነገር ባቀድኩት መሰረት ማስተካከሌን ለመቶኛ ጊዜ ካረጋገጥኩ በኋላ መፀለይ አሰብኩ። ሰዓቱ ገና ስለነበር የቀረበኝ ቤተክርስቲያን ገባሁ እና በሩ አካባቢ ቆምኩ። ከዛ ግራ ተጋባሁ!!! ላለፈው በደሌ ሁሉ አንድም ቀን መጥቼ ንሰሃ አልገባሁም!! በደም የተነከረ እጄን ወደ እርሱ መዘርጋት ድፍረትም ሆነብኝ!! ከዛ ደግሞ ያለፈውን ሁ,ለት ወር ከምናምንኮ ፀልዬ ነበር!! ሰምቶኝ ይሆን ወይስ አያውቀኝ ይሆን? ወይስ ባኮረፈ ፊቱ ነው ሲያየኝ የነበረው? ደግሞ መልሼ ከሰማኝ ይስማኝ ብዬ መፀለይ ጀመርኩ።

«አምላክ ሆይ ታውቀኛለህ ብዬ አስባለሁ። ካላወቅከኝ ሜላት ነኝ። ያለፈውን ሀጥያቴን ሁሉ ብናዘዝ መሽቶ ይነጋል። ከዛ በፊት ግን ያንተን እርዳታ እሻለሁ ተለመነኝ!! አሁንም የምሰራው ባንተ ዘንድ ልክ ይሆን ስህተት አላውቅም! ግን የተሻለ የመጨረሻ አማራጭ የምለውን ነው የመረጥኩት። እኔም ራሴ የድሮዋን ሜላት መሆን አልፈልግም! አንተም እንደማትወዳት ነው የማስበው!! ያለፈውን ሁሉ ማረኝ እና ለእኔ ስትል ሳይሆን ለወንድሜ ስትል፣ ለዛች ደጅህ ለማትጠፋ ምስኪን እናቴ ስትል ….. ወንድሜን ይዤው እንድመለስ እርዳኝ!! እባክህ እ? ከፈለግክ አትማረኝ! ከፈለግክም ቅጣኝ ግን በወንድሜ አትቅጣኝ!! እ? » የሆነ ከሰማይ <እሺ> የሚል ድምፅ እሰማ ይመስል አንጋጥጬ ቆየሁ!!

መኪናዬ ውስጥ ገብቼ ኪዳን ወዳለበት ቦታ መንዳት ጀመርኩ። ትናንት ከነበረበት ቤት ቀይረውታል። ከምሽቱ 3 ሰዓት የሚፈልገውን ይዤለት እንደምመጣ ስለነገርኩት እኔን ለመጠበቅ በጊዜ ከሚስትየው ጋር ወደዛው መሄዳቸውን አረጋግጫለሁ። የእሱ እቅድ ያው እንደተለመደው የራሱን ሰዎች እና መኪና ልኮ ይዘውኝ ልሄዱ ነው። እኔ ቀድሜ እዛው እንደምደርስ የሚጠረጥርበት ምንም ፍንጭ የለውም። በገዛሁት ስልክ እቤቱ ውስጥ የተጠመዱትን ካሜራዎች መቆጣጠር እችላለሁ። ሳሎኑን በሁለት አንግል፣ ኮሪደሩን እና ኪዳን ያለበትን ክፍል። ኪዳን አልጋው ላይ ኩርምት ብሎ ከመጋደሙ ውጪ ምኑም ታግቶ ያለ አይመስልም። ደጁ ላይ ጠብደል ጠባቂ ቆሟል። ለአፍታ ጎንጥን አሰብኩ> አሁን በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ሆኜ የእሱን አሳሳም ማሰብ ነበረብኝ? አስቤስ እጄን መሳም ነበረብኝ?
990 viewsTsiyon Beyene, 17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 20:06:10 #የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ሀያ ሁለት)
(ሜሪ ፈለቀ)

የሳመውን እጄን ተቀብዬው ከሆስፒታሉ ወጥቼኮ ታክሲ ተሳፍሬ ወደቃሊቲ መንገድ ከጀመርኩ ቆይቻለሁ። እጄን ተቀብዬው አልኩኝ እንጂ እየተሰማኝ ያለው ወይ ከንፈሩ እጄ ላይ የቀረ ወይ ደግሞ እጄ እዛው እሱጋ ከንፈሩ ላይ የቀረ አይነት ስሜት ነው። የሳመኝን እጄን የሳመኝን ቦታ አንዳች የእግዜር ተአምር የፈለቀበት ነገር ይመስል እየደጋገምኩ አየዋለሁ። ደግሞ እየደጋገምኩ እሱ እንደሳመው እስመዋለሁ። ቀስ ብሎ ልስልስ ያለ …… እርጥበት ያለው ግን የሚሞቅ …….. ከዛ ደግሞ ከእግሬ ጥፍር ድረስ እስከ አናቴ እንደኤሌክትሪክ ሞገድ ጥዝዝዝ ብሎ በደምስሬ ውስጥ ይሆን የተጓዘው ፣ ከጅማቶቼ  ጎን ለጎን ባገኘው ክፍት ቦታ ይሆን እየተሽሎከለከ የተጓዘው ባልገባኝ አካሄድ የናጠኝ …… የሆነ መለኮታዊ የሆነ መሳም ነገር …..

ስሳም የመጀመሪያዬ ሆኖ አይደለም። በትግል ፣ ኑሮን ለማሸነፍ በመጋጋጥ ፣ ኪዳንን ትልቅ ቦታ እንዲደርስ በመታተር ፣ በበቀል ፣ ሴራ በመጎንጎን ፣ ገንዘብ እና ጉልበትን በማካበት …… እና ሌሎች ብዙ ለሌላው ሰው ስሜት የማይሰጡ ነገሮችን በማድረግ ውስጥ ከወንድ ጋር የሚደራረጉ አልባሌ ነገሮችን ከማድረግ አልታቀብኩም። እንደእውነቱ ከሆነ ብዙ አድርጌያለሁ። አብሮ በመግባት እና በመውጣት እንደፍቅረኛ ወግ ያሳለፍኩት ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከዳዊት ጋር ነበር። ዳዊት በከተማችን ውስጥ አለ የሚባል ባለሃብት ልጅ ነው። አባቱ በገንዘቡ ባለስልጣናትን የሚሾፍር ተፅዕኖ ፈጣሪ ነው። የእድሜ ልክ እስራት ፍርዴን በ6 ዓመት ያቀለለልኝ እሱ ነው። ውለታ ውሎልኝ አይደለም! በልዋጩ ሶስት ነገር ሰጥቼዋለሁ። አንድ የነበረኝን 48% የሚሸፍን የአንድ ባንክ አክስዮን (እሱ 20% ስለነበረው የእኔን ሲጨምር በባንኩ ላይ ፈላጭ ቆራጭ ያደርገዋል።) ሁለት የራቁት ዳንስ ቤቱን ግማሽ ልሸጥለት (ዳዊት የገባው በዛ ነው) ሶስተኛው እና ዋነኛው (ሌሎቹ ተጨማሪ ናቸው) የአንድ እሱ የሚፈልገው ከፍተኛ ባለስልጣን ሚስጥር (ለምን እንደፈለገው አልገባኝም ምክንያቱም እስካሁን አልተጠቀመበትም። ወይም እያስፈራራበት እየተጠቀመበት ይሆናል አላውቅም! ሰውየው ግን እስካሁን ስልጣኑ ላይ ነው።)

አንዲት ከትንሽ መንደር መጥታ ኑሮን ለመግፋት ትፍጨረጨር የነበረች ሴት የባለስልጣናት ሚስጥር እጇ ላይ እንዴት ወደቀ? ይሄ ሁሉ ሀብትስ እንዴት ተቆለለ? የሚሆን አይመስልም አይደል? ሆኗል!!

እዚህ ሀገር አንድ የገባኝን ነገር ልንገራችሁ! በተለይ  እላይኛው የኑሮ መደብ እና ስልጣን ላይ የተፈናጠጡት ሰዎቻችን ዘንድ ….. በገንዘብ አቅም የማይሆን ምንም ነገር የለም። የሚለያየው የገንዘቡ መጠን ብቻ ነው። በመቶ ሺህዎች <ሀቀኝነቴን ፣ እምነቴን ፣ ህሊናዬን > ሲል የነበረ ለሚሊየኖች እጅ ይሰጣል። ለሚሊየኖች <ቤተሰቤን ፣ አምላኬን ፣ ቃሌን ፣ ህዝቤን > ያለው ደግሞ ለቢሊየን ወድቆ ይሰግዳል። ገንዘቡን የምታቀርብለት ሰው ወይም ድርጅት የሌለውን ያህል ወይም በቀላሉ ሊያገኝ የማይችለውን ያህል ገንዘብ መጠን አቅርብለት! የምትፈልገውን ይሸጥልሃል። ለምን ሚስቱ አትሆንም!!! በስህተት አምልጦ የሾለከ <በገንዘብ የማልሸጠው ህሊና አለኝ> ያለ ጎርባጭ ከተገኘ …… በነዛኛዎቹ ይሰለቀጣል። <ህዝብን በተገቢ ሁኔታ ባለማገልገል፣ የህዝብን ጥቅም ባለማስቀደም > ምናምን ምናምን የሚባሉ ፖለቲካዊ ሀቅ የሚመስሉ ውስልትናዎች ተለጥፈውበት እንደ እድሉ አርፎ የማይቀመጥ ቅብጥብጥ ከሆነ ወደ እስር ቤት ……. ለቤተሰቤ አንገቴን ልድፋ ያለ የቤተሰብ ሰው ከሆነ ደግሞ ወደቤት ይላካል።

እንግዲህ ከዳዊት ጋር አብረን መስራት የጀመርነው ከእስር ቤት ከወጣሁ በኋላ መሆኑ ነው። ወድጄው አይደለም! ማለቴ እንደፍቅረኛ! እንደስራ ባልደረባ ጭንቅላቱ ለቢዝነስ የተፈጠረ፣ ለተንኮል እና ሴራ እኔን የተስተካከለ ፈጥኖ አሳቢ ፣ አባቱ ስለሚንቀው ለአባቱ የሆነ ጀብድ ሰርቶ ራሱን ማስመስከር አብዝቶ የሚሻ ሰው ነው። ከምለብሳቸው የወሮበላ ልብሶች ውስጥ ያለ የሴት ገላዬን ራቁቱን ሳያየው የተመኘ ብቸኛ ወንድ ይመስለኛል። ባለገንዘብ ፣ ባለጉልበት ፣ ባለሀይል ከሆንኩ በኋላ ለአመታት በዙሪያዬ ያለ ሰው ሁሉ እንደአለቃ የሚፈራኝ ፣ እንደሰው የሚያከብረኝ ፣ በዛ ካለ ትንሽ የሚቀርቡኝ እንደወዳጅ የሚያዩኝ ሴት ነበርኩ እንጂ ማንም በሴትነቴ የተመኘኝ አላስታውስም። ሴት መሆኔ ትዝ የሚላቸውም አይመስለኝም። እሱ ግን እንደስራ ባልደረባው ሳይሆን እንደሴት አየኝ!! የሚጋረፍ ፊቴ ሳያግደው ለወራት አበባ አመላለሰልኝ (እያየ ፊቱ ላይ አበባውን በጫጭቄ እበትነዋለሁ) ። <ደነዝ ነህ ወይ አትሰማም? አንተ ምኔም መሆን አትችልም!> እያልኩት በየቀኑ ቆንጆ መሆኔን ነገረኝ። በግልፅ <አይደለም ፍቅረኛዬ ልትሆን ለአንድ ቀን ተሳስቼ አብሬህ ብተኛ የምፀፀትብህ አይነት ሰው ነህ!> እያልኩት እንኳን በየቀኑ ሳይደክመው እንደሚወደኝ እየነገረኝ ዓመት ተቆጠረ። አንድ ቀን ከአባቱ ጋር ተጣልቶ ቢሮ ተቀምጦ እንደ ትንሽዬ ሴት ልጅ ሲንሰቀሰቅ ደረስኩ። ምን እንደሆነ ስጠይቀው እንባውን ከንፍጡ እየደባለቀ ማልቀሱን ሳያቆም በአባቱ ፊት ሁል ጊዜ ትንሽ መሆኑን ነገረኝ። አሳዘነኝኮ ግን ከማልወደው ነገሩ አንዱ ይሄ ልፍስፍስ ሴታ ሴት ነገሩ ነው። የዛን ቀን ግን

«ዛሬ እራት ልጋብዝህ?» አልኩት። እንባው ጥሎት ጠፋ! ከዛ በኋላ እንደፍቅረኞች የሚፈፃፀመውን ነገር ሁሉ እንፈፃፅማለን። አልጋ ላይ ሲያዩት ስልባቦት እንደሚመስለው ገላው አይደለም ወይም እንደሴታሴት አኳኋኑ። ስለዚህ ሴታዊ ፍላጎቴን ለማግኘት የማላውቀው ሰው ጋር ከምሄድ ጥሩ ቅብብሎሽ ነበር። አንዳንዴ ምንችክ ሲልብኝ እዘጋዋለሁ። ደግሞ መልሰን እንጀምራለን። ስለእውነቱ ግንኙነታችን ምን እንደሆነ ወይም ወዴት እንደሚሄድ እንኳን ውልም ስምም የለውም ነበር። እንኳን እጄን ስሞኝ የስሜቴ የመጨረሻ ጡዘት ጠርዝ ላይ እንኳን እንዲህ ዛሬ ጎንጥ እጄን ሲስመኝ እንደተሰማኝ  አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም!! ኸረ እንኳን ሊሰማኝ መኖሩንም አላውቅም!! ፊልም ላይ እንኳን ትኩረታቸው ከንፈር እንጂ እጅ እና ከንፈር ሲገናኝ እንዲህ አስማታዊ ስሜት እንዳለው መች ይነግሩናል?
ቃሊቲ በሩ ላይ እንደደረስኩ ዘበኛው ሲያየኝ እንደተለመደው በወዳጅነት  «ቁርጠትዬ እስቲ ዛሬ ደህና ጊቢልኝ ታውቂ የለ ሚስትየው ስታላምጠኝ ነው የምትከርመው?» አለኝ።

«ይገባልሃል! ሂድ ባርችን ጥራልኝ!! እዚህ ስትቅለሰለስ እኮ እኔን አማክረህ አራት የወለድክ ነው የምትመስለው!»

«እሱማ ይጠራልሻል!! ግን ሰሞኑን ምርጫ ደርሷል ብለው የሌለ ህግ እያጠበቁ ነው!!»

«በቃ እሱ ታሳቢ ተደርጎ ይገባልሃል! መርዶ ሊነገራት ነው …. ወንድሟ ራሱን አጥፍቶ ነው …. መዓተኛ አይደለህ? አንዱን ቀባጥርና ጥራልኝ» ብዬ ከኪሴ ብር አውጥቼ አቀበልኩት። እሱ ወደ ውስጥ ሲገባ እየሆነ ያለውን ባላየ ዝም ብሎ የተቀመጠውን ሌላ ጠባቂ ብር በያዘ እጄ ጨበጥኩት። እየወተወተ አመሰገነኝ!!

«ያልጠየቅሽኝን እያካካስሽ ነው በየቀኑ?» አለች እሙ ገና ከመድረሷ «ጎንጤ ጥጋቡስ ዛሬ የለም?»

« ሁሉንም ነገር ላስረዳሽ ጊዜ አይበቃኝም!! እርዳታሽን ፈልጌ ነው የመጣሁት!! ከዛ ደግሞ በአጭሩ ትናንት ላይሽ የመጣሁ ጊዜ የማውቀው ታሪክ አልነበረም። የተመታሁ ጊዜ ሚሞሪዬን እንዳለ አጥቼ ነበር።»

«እና አሁን?» ብላ ግራ ገብቷት ከላይ እስከታች አስተዋለችኝ።
1.0K viewsTsiyon Beyene, 17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 18:00:15 እጆቼን ከትከሻዋ ወደ ጀርባዋ..ከጀርባዋ ወደ ወገቧ እያንሸራተትኩ በንቃትና በትጋት ስራዬን ቀጠልኩ...፡፡ከስካሩ ጋር ተዳምሮ ከፍተኛ ሙቀት በሰውነቴ እየተራወጠ ነው...፡፡በረሀብ ምክንያት ይገላባበጥ የነበረው አንጀቴ አሁን አደብ ገዝቶ ፋታ ሲሰጠኝ ወሲብ በተመለከተ የሚመለከታቸው የሰውነቴ ክፍሎች ግን በተቃራኒው እንደ ጃርት እሾህ በያሉበት ቀጥ ብለው  ወጣጥረውኛል....፡፡

"ኸረ ትንሽ ታገሱ ...ግብዣው ሙሉ በሙሉ  ከእሷ እስኪመጣ አደብ ግዙ...ያው የክብር ጉዳይ ነው››"እያልኩ የገዛ ብልቶቼን ለመምከር ብሞክርም ብዙም ሊሰሙኝ ፍቃደኞች አይደሉም፡፡...ግን ሙሉ ፍቃድ እስኪያገኙ ከመጠበቅ ውጭ ሌላ ምርጫ አልሰጠኋቸውም፡፡...አሁን ከወገቧ እስከአንገቷ በችሎታዬ ልክ በደንብ አሽቼያታለሁ...ቀስ ብዬ ወደታች ወረድኩና ቀኝ እጄን በመቀመጫዋና በፓንቷ መካከል ሰንቅሬ በማሸት ሙድ ጨመቅ ጨመቅ  ማድረግ   ስጀምር ለመጀመሪያ ጊዜ ቀኝ እጇን አንቀሳቀሳችና እጄን ክርኔ አካባቢ አፈፍ አድርጋ ይዛ በቀስታ መዛ አወጣችና ‹‹..እንደዛ ብፈልግ ቀድሞውኑ ፓንቴን አወልቅ ነበር"አሁን ወደ ቤትህ መሄድ ትችላለህ...ለሁሉም አመሰግናለሁ...የተረፈውን ውስኪ ይዘህ ሂድ"አለችኝ

አቤት የደነገጥኩት ድንጋጤ... ኩምሽሽ ነው ያልኩት..ስኳር ሲሰርቅ በወላጆቹ የተያዘ ህፃን ልጅ በሉኝ" ከተቀመጥኩበት ሹክክ ብዬ ተነሳሁ እና በቀሰስተኛ እርምጃ ወደ በራፍ መራመድ ጀመርኩ

አውልቃ የነበረውን ቢጃማ ጡቶቾን እና ሆዷን ሸፍና ከተጋደመችበት ተነሳችና "ምነው ቅር ያለህ ትመስላለህ? ሌላ ነገር ጠብቀህ ነበር እንዴ?"ብላኝ እርፍ..

በፈጣሪ እስኪ አስቡት… የማላውቃት ሴት በውድቅት ለሊት ጋብዛኝ..ጎትታ ክፋሏ አስገብታኝ፤ አጠጥታኝ..  ፊት ለፊቴ ልብሷን አውልቃ እርቃኗን አስጎብኝታኝ...በጣቶቼ ከፊል ሰውነቷን  እንድነካና እንድዳስስ ፈቅዳልኝ "ሌላ ነገር ባስብ ይፈረድብኛል"እንኳን እንደእኔ ደመ ሙቅ ወጣትና  ሙሉ ብልቱ ጤነኛ የሆነ ሠው ይቅርና ጃነደረባስ ቢሆን   በዚህ አይነት  ሁኔታ ውስጥ አልፎ ሌላ ነገር ማሰብ ይቀራል...?

ይቀጥላል
2.0K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 18:00:15 #እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አራት
////

እንዳትሰማኝ ድምፄን ዝቅ አድርጌ‹‹የእውነት አድናቂሽ ነኝ"አልኩ  ..እውነቴን ነው ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ብቻዋን ገልብጣ ገድገድ ሳትል ...እኔ ገና በግማሽ ብርጭቆ ጉልበቴ  እየተብረከረከ ነው።

ተነሳሁና የተከፈቱ መስኮቶችን መዘጋጋት ጀመርኩ..ማብራቶችን አጠፍሁ፡፡ የሴትዬዎን ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ይዤ ወጣሁና የሆቴሉን በራፍ ቆልፌ ቁልፉን በጥንቃቄ ሚስጥር ኪሴ ውስጥ ሽጉጬ  ወደ አልጋ ክፍል አመራሁ...አቀብያት በዛው ወደ ቤቴ ሄዳለሁ ሞባይሌን አውጥቼ ሰዓት ሳይ 7፡40 ይላል።
ደረስኩና አንኳኳሁ...

‹‹ግባ ክፍት ነው››

የሚል ድምፅ ስሰማ ቀስ ብዬ በራፍን ወደ ውስጥ ገፋ አደረኩትና  ውስኪ ጠርሙስ የያዘ እጄን አስቀድሜ አንገቴን አሰገግኩ፡ መሀል ወለል ላይ ቆማ ተበትኖ ጀርባዋ ላይ የተኛውን ፀጉሯን አንድ ላይ ጠቅልላ እያሰረችው ነው..ቅድም ለብሳ የነበረውን ጅንስ ሱሪ አውልቃ ስስ የለሊት ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች...፡፡ ቢጃማው ሮዝ ቀለም ሲኖረው አጭር እና በቀላሉ አይን ውስጥ የሚመሰግ ነው...አስተውሎ ላየው ቀሚስ ሳይሆን ቁምጣ ነው የሚመስለው..እና ያ የሚንቀጠቀጥ እና ሊፈርጥ የደረሰ ዳሌዋ በከፊል እርቃን ነው...፡፡

"በራፍ ላይ ተገትረህ ታድራለህ ወይስ ትገባለህ ?"

"እ እሺ ገባለሁ ››አልኩና ወደውስጥ ገብቼ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ ለመውጣት ዞር ስል  እሷ ከቦታዋ ተንቀሳቅሳ ወደበራፍ እያመራች ነው፡፡

‹‹...ብርድ አስመታሀኝ ››"በሚል ሰበብ  ክፍት ጥዬ የመጣሁትን በራፍ ዘጋችና ቆለፈችው፡፡

"ቆይ እኔ ሳልወጣ?"አልኩ ደንግጬ፡፡

"ትንሽ አጣጣኝ እና ትሄዳለህ.. ያውልህ ብርጭቆ…

"ቅዳልኝ" የንግግሯ ቃና ወደ ትዕዛዝ ያዘነበለ ነው.፡፡
ግራ በመጋባትና በመርበትበት  እንዳለቺኝ አደረኩና እዛው ጠረጴዛ ጎን ያለ ደረቅ ወንበር ላይ ቁጭ አልኩ..፡፡እሷም ወደእኔ መጣችና ብርጭቆዋን አንስታ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች ...፡፡አቀማመጧ በእኔ ትክክል ነው...፡፡አይኔ ወደታች ወደተጋለጠው ጭኗ እየተንሸራተተ አስቸገረኝ ፡፡...እሷ የእኔን ሁኔታ ከቁብም የቆጠረች አይመስልም፡፡ጭኗ እንደሴቶች ጭን ልል እና ለስላሳ አይደለም…፡፡እንደስፖርተኛ የዳበረ እና ፈርጣማ ነው፡፡ሲነኩት ትንቡክ የሚል አይነት ሳይሆን ሲነካ ጭፍልቅ  የሚያደርግ አይነት፡፡

"አሁን ጋሼ እንዲህ ከእንግዳ ጋር በውድቅት ለሊት ቤርጎ ውስጥ  ገብቼ ዘና ስል  ቢያየኝ ምን ይለኛል? ጓደኞቼስ ቢያዩ ተረባቸውን እችለዋለሁ?››

በዝምታ ውስጥ ሆና የቀዳሁላትን  ጠጥታ  ጨረሰችና ከተቀመጠችበት ተነስታ እራሷ ለራሷ ቀዳች ፡፡..ልትቀዳ ስትል ታከከቺኝ..እናም ደግሞ የተቀባችው ሽቶ ያለፍላጎቴ በአፍንጫዬ ሰርጎ ገባ...እና እየጠጣሁ ካለሁት መጠጥ ጋር ተጋግዞ አነቃቃኝ...፡፡

ወደቦታዋ ተመልሳ ተቀመጠች ፡፡አቀማመጧ ግን እንደቅድሙ እግሮቿን አጣምራ ሳይሆን ፈርክክ አድርጋ ከፍታ ነው፡፡ ...እና በክፍተቱ አይንን ሚያጥበረብር ቀይ ፓንት አየሁ..፡፡ለምን አየህ ?ብላ ተነስታ የምታንቀኝ መስሎኝ  ከመርበትበቴ የተነሳ ብርጭቆ ውስጥ ያለችውን መጠጥ በአንድ ትንፍሽ ገርገጭ አድርጌ አጋባኋት፡፡

"በቃ እግዜር ይስጥልኝ አሁን  መሸብኝ ልሂድ..›› ለማለት አስቤ ገና አፌን ሳልከፋት ከተቀመጠችበት ተነስታ በድጋሚ ቀዳችልኝ፡፡ ..ለመናገር የተከፈተ አፌን ቀስ ብዬ ዘጋሁትና  አንዴ መጠጡን አንዴ እሷን እያፈራረቅኩ ማየት ጀመርኩ።"አሁን ብዥ እያለብኝ ነው..፡፡ሞባይሌን አወጣሁና ሰዓት ተመለከትኩ...8:18 ይላል።

"ምነው መሸብህ እንዴ?"

"አይ አንቺን እንቅልፍ ነሳሁሽ ብዬ ነው"

"ጥሩ አስመሳይ ነህ"አለችኝ.፡፡

‹‹እስቲ በጌታ አሁን እንዲህ ይባላል?››አንገቴን በእፍረት ከማቀርቀር ውጭ ምንም መልስ አልሰጠኋትም፡፡ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደሻንጣዋ በመሄድ መጎርጎር ጀመረች‹‹...ምን ልትሰጠኝ ነው?"ብዬ ሳሰላስል  ክሬም ቅባት አወጣችና አልጋ ላይ ወረወረች..መቀመጫዋን ወደ እኔ ፊቷን በተቃራኒው ወደግድግዳው አዞረችና በቆመችበት አጭሩን የለሊት ቀሚሷን ሞሽልቃ አወለቀች።አይኖቼን ጨፈንኩ..ገለጥኩ...መልሼ ጨፈንኩ...ቅድም በስሱ ካየሁት  ቀይ  ፓንት በስተቀር ምንም የጨርቅ ዘር በሰውነቷ አልቀረም....፡፡ጡቶቾ እንደሩሲያ አስፈሪ ሚሳዬሎች ጫፋቸውን ወደእኔ   ቀስረው ልቤን አራዷት ብላችሁ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን እየታዩኝ አይደለም፡፡ፐ!! ከኃላዋ የሚታየው የሰውነቷ  ቅርፅ  ግን ከአንገቷ በላይ ያለውን መልኳን በሁለት ሶስት እጥፍ ይበልጣል።

ዘለህ ተጠምጠምባት የሚል ስሜት  ከሁሉም የስሜት ህዎሳቶቼ ተሰባስቦ ጉሮሮዬ ላይ ተወተፈብኝ... እጇቼ ገላዋን ለመዳሰስ አይኖቼ ከግራ ወደቀኝ እያገላበጠ  መላ ሰውነቷን በምስጠት ለመመልከት፤ አፍንጫዬ አንገቷ ስር ተደፍቶ ጠረኗን ወደውስጥ መማግ፤ጆሮዎቼ አፍ አካባቢ ተለጥፈው ከአንደበቷ የሚወጣውን ሹክሹክታ በፅሞና ለማዳመጥ እና እንትኔ ደግሞ ጭኖቾን ፈልቅቆ ወደ ውስጠቷ መስመጥ ፈለገ(ውይ እንትኔ ለካ የስሜት ህዋሳቴ አይደለም...ነው እንዴ?)

ዘፍ ብላ በሆዷ አልጋው ላይ ተኛች...አሁን በህይወቴ በአካልም በፊልምም ጭምር ካየኋቸው ባለ እርቃን ሴቶች ሁሉ ተወዳዳሪ የሌላት ፍፅም አማላይ ሆና ታየችኝ፡፡.. ፀጉሯ ብትን ብሎ ከፊል ጀርባዋን እና የተንተራሰችበትን ትራስ ሸፍኖታል..፡፡ከዛ ወረድ ስንል ልምጥ  ብሎ የሚታየው ወገቧ  የሩብ ጨረቃን ቅርፅ ይዞ አይንን ያፈዛል ፡፡..ከዛ ሽቅብ ወደላይ ስንወጣ መቀመጫዋ ቀይ ፅጌረዳ አበባ የሸፈናቸው ግዙፍ መንታ ተራሮች ይመስላሉ፡፡..ከዛ በመነሳት ለሁለት ተከፍለው የተዘረጉት እግሮቾ ለምለም መስክ ላይ የተዘረጋ የአክሱም ሀውልትን ይመስላሉ...እጣቶቾ ደግሞ....

"ትንሽ እሸኝና ትሄዳለህ.."የሚለው ንግግሯ ስለውበቷ ተቀኝቼ ሳልጨርስ ከሀሳቤ አናጠበኝ።

" ሎሺኑን ተጠቀምና እሸኝ.."ደገመችልኝ።

"እሸኝ ማለት ምን ማለት ነው..?እንዴት ነው የማሻት..?የሚታሽና የማይታሽ የሠውነት ክፍል ይኖራት  ይሆን ?ካሸዋትስ በኃላ የሚከተል ነገር ይኖራል..?በሰከንድ ውስጥ በምናቤ  ብልጭ ድርግም ያሉ  ወሳኝ ጥያቄዎች ናቸው..፡፡እጆቼን ሰበሰብኩና ወደአልጋው ተራመድኩ፡፡ ጠርዝ ላይ ተመቻችቼ ተቀመጥኩ..፡፡ጃርባዋን ያለበሰውን ፀጉሯን ሰበሰብኩና ወደትራሱ አሻገርኩት...እና ሎሺኑን አነሳሁና ጨመቅ ጨመቅ አድርጌ እጄ ላይ አፈሰስኩና   ከትከሻዋ ጀመርኩ...፡፡ይህ ሰውነት ከዚህ በፊት እንደማውቃቸው የሴት ገላዎች የሀር ጨርቅ አይነት ልስላሴ የለውም..፡፡በዳበሩ ጡንቻዎች የተገነባና በጠንካራ ቆዳ የተሸፈነ ልዩ አይነት ሰውነት ነው፡፡ቢሆንም ሲያሹት እጅን ሙልጭ ሙልጭ እያደረገ ቢፈታተንም ደስ ይላል፡፡ ‹‹ አዎ ትግስት ካለኝ  ተገልብጣ በጀርባዋ ስትተኛና ከፊት ለፊቷ ያለውን የሰውነት ክፍሏን እንዳሻት ስትመቻችልኝ ቀስ ብዬ ልክ እንደዚህ ሎሺን ጡቶቾን አሸት አሸት እያደረኩ ከውስጣቸው ፍቅር እንዲያመነጩ አስገድዳቸዋለሁ፡፡›› ስል በአይነ ህሊናዬ በመሳል ጎመዣሁ..ምራቄን ገርገጭ እያደረግኩ ዋጥኩ ።
1.9K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 03:08:19 «በአምላክዎት! ግን ሀሳቤን አንስቻለሁ!! ከዚህ ወድያ የእርሶ እርዳታ አያሻኝም!» አለ ሁኔታው ንቀት ወይ ፅያፌ በሚመስል ሁኔታ እየጎፈላ !! የተሰማኝ ስሜት ልሰጠው የነበረውን ኩላሊት አልፈልግም የተባልኩ ሳይሆን ሊሰጠኝ የነበረ ኩላሊት ተከልክዬ ሞቴ የፈጠነ አይነት ነገር ነበር። ምክንያቱን ደጋግሜ ብጠይቀውም መልሱ

«ራሴን እንዳብራራ አያስገድዱኝ!! ሌላ ሰው ተገኝቷል!» ብቻ ነው። የሆነ የማላውቀው ተስፋ ልበለው ደስታ አላውቅም የተነነ! የሆነ ነገሬን የቀማኝ መሰለኝ። ያበሳጨኝ ደግሞ ንግግሩ ትህትና እንኳን ያልነበረው መሆኑ ነው። የሆነ በድክመቴ ያገኘኝ ነገር መሰለኝ።

«ድሮምኮ የሰው ልጅ ያለቦታው ክብር ሲሰጡት ሽቅብ ካልሸናሁ ይላል።» አልኩት ብስጭት እያልኩ

«እትዬ ይልቅ እላፊ አንነጋገር!! ስራዬን መልቀቅ ስለምሻ ሌላ ዘበኛ ቢፈልጉ ጥሩ ነው!» ሲለኝ የተናደድኩበት ምክንያት የቱ እንደሆነ ሳይገባኝ ጨስኩ!

«ለአንድ አመት ነው ልትሰራ የፈረምከው!! ኮንትራትህን ሳትጨርስ ወዴትም አትሄድም! ሞክረኝና ታያታለህ!» ብዬው ገባው።

በነጋታው ለራሴ ራሱ በማይገባኝ ምክንያት ልጁ ደህና መሆኗን ማወቅ ፈለግኩ። አላውቅም ብቻ እጇን ይዤ <አይዞሽ> ማለት አማረኝ። ምናልባት እሙ እንዳለችው የከደንኩት እናት የመሆን ስሜት ይኖር ይሆናል። እልሄን ውጬ ልጁን ላያት እንደምፈልግ ስነግረው።

«ይቅርታ ያድርጉልኝ እትዬ ለጊዜው ከቤተሰብ ውጪ ማንም እንዲያያት አልፈቅድም!! በሌላ አይዩብኝ ልነግሮት በማልችለው ምክንያት ነው!! " አለኝ። የፈረደባት እመቤት ጋር ሄጄ

«ይሄ የማይረባ! ሌላ ሰው ስለተገኘ አያስፈልግም አይለኝም? ቱ! » እያልኩ ስደነፋ እንባዋ እስኪፈስ እየሳቀች

«እንዲህ ያበሳጨሽ ለምን ኩላሊቴ አልወጣም ነው ወይስ ለምን እሱ እንደሌሎች በዙሪያሽ ያሉ ሰዎች እቴጌ እመቤቴ አላለኝም አልተሽቆጠቆጠልኝም ነው? ይሄ ሰውዬማ ከገባ ጀምሮ ነርቭሽን ነክቶታል።»

«ባክሽን አንቺ ደግሞ! ጭራሽ ስራዬን እለቃለሁ ይበለኝ?» እኔ እበሳጫለሁ እሷ ትስቃለች። «ምኑ ነው አሁን ይሄ የሚያስቀው?»

«ለማንም ሰውኮ እንዲህ ቦታ ሰጥተሽ አታውቂም! ያውም ለዘበኛሽ? ጥጋቡ ነው የሚያንተከትክሽ ወይስ ሌላ ነገር አለ?» አለችኝ መሳቋን ሳታቆም። ከዛን ቀን በኋላ ስለጎንጥ ስናወራ < ጎንጤ ጥጋቡ> ነበር የምትለው።

ከቀናት በኋላ እሙ እንዳለችው የመንተክተኬ ምክንያቱ አልገባ ሲለኝ። ስራውን መልቀቅ እንደሚችል ሌላ ዘበኛ እንዳገኘው ስነግረው ደግሞ

«ሀሳቤን አንስቻለሁ! ኮንትራቴን ሳልጨርስ ወየትም ፍንክች አልልም» ብሎ አናቴን በብስጭት አዞሮው።

«እኔ ነኝና ሜላት! ሰውዬ ስትፈልግ እወጣለሁ ስትፈልግ እገባለሁ እያልክ እንደፈለግክ ሀሳብህን የምታነሳ የምትጥልበት የሰፈርህ ጠጅ ቤት አይደለም ይሄ! የቀጠርኩህ እኔ ነኝ! ስፈልግ ደግሞ በቃኝ ብዬ የማባርርህም እኔ ነኝ! ከነገ ጀምሮ ላይህ አልፈልግም!»

«ተናገርኩኮ ፍርማዬን ሳልጨርስ አልሄድም!» ብሎ እያወራሁት ትቶኝ ሌላ ስራ መስራቱን ቀጠለ።

አሁን ሲመስለኝ ያልጨረሰው ስራ ስለነበረ ነው የቆየው። ከዛ ቀን በኋላ የሰላም ቃላት ተለዋውጠን አናውቅም ነበር። አሁን ልለው የነበረው። <ለልጅህ ስልኮ እዛ አልጋ ላይ ተኝቼ ልደነዝዝ ዝግጁ ነበርኩ። ያ እንኳን ለጠላቶቼ ከመስራት አላገደህም!> ልለው ነበር። ይቅር አልኩት እንጂ አልረሳሁትም።

*******


ያቀበልኩትን ስልኩን ባልተመታበት ጎን እጁ እየነካካ ያልኩትን እንዳልሰማ ዝም ብሎ አልፎ!!
«ማንም ሰው እንዳልተከተለሽ እርግጠኛ ሆነሽ እዚህ ቦታ ሂጂ! የምትፈልጊውን ንገሪው።» ብሎ የምንገናኝበትን አድራሻ ሰውየው የሚለብሰው ልብስ እና ኮፍያ ቀለም። የምንግባባበት ኮድ ፣ የምንገናኝበትን ሰዓት እና የሰውየውን ፎቶ በጭንቅላቴ መያዝ እስክችል አስደጋገመኝ።

«እሺ ግን አንተ እርግጠኛ ነህ ምንም አትሆንም?»

«አታስቢ! ለጊዜው እኔን ለማጥቃት ሆስፒታል ድረስ የሚያስመጣ ምክንያት ያለው ጠላት የለኝም!» አለ እንድሄድ መውጫውን እየጠቆመኝ። ተነሳሁ ግን እግሬ አልተራመደም! ቆሜ ግራ በገባው ስሜት ዘቅዝቄ እያየሁት ቆየሁ። እጄን በሚይዘኝ አያያዙ ያዘኝ እና

« ድንገት ካንቺ አቅም በላይ የሆነ ነገር ቢፈጠር ቢያንስ ምንም ምርጫ ከጠፋሽ የምትደውይለት የመጀመሪያ ሰው እንደሆንኩ ቃል ጊቢልኝ!» አለኝ

«ብደውልልህስ? ቀና ማለት እንኳን የማትችል ሰው ምን እንድታደርግ ነው?»
«ብቻ ደውይልኝ! ምልክት ስጭኝ! ያን እንደምታደርጊ ቃልሽን ስጭኝ!!» እያለኝ ስልኩን ወደ ስልኬ ደወለ። «ስልክሽ ፊት ለፊት የኔ ቁጥር ይኑር!»

«እሺ በራሴ የማልወጣው ነገር ከገጠመኝ እደውላለሁ።» አልኩት እጄን አልለቀቀኝም። ላስለቅቀውም አልቸኮልኩም። በእጁ የአውራ ጣት እንደመደባበስ ካደረገው በኋላ አንስቶ ወደ ከንፈሩ አስጠጋው። የእጄን አይበሉባ ሳይሆን ገልብጦ መዳፌን የውስጥ እጄን መሃሉን በከንፈሩ በስሱ ሳመው። ሳመው ወይ ዳሰሰው ወይ ተጫነው። የሆነ ነገር …….. የእጅ ውስጥ ተስሞ ሰው እንዲህ እንደመስከርም እንደመጦዝም ያለ ስሜት ይሰማዋል?

«…. ተደናበርኩልሽ ጥይት እንደሳተው!» ያለው ዘፋኙ እንዲህ ተሰምቶት ነው የሚሆነው።

.ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
3.1K viewsTsiyon Beyene, 00:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 03:08:19 #የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ሀያ አንድ)
(ሜሪ ፈለቀ)

« የበፊቷን ሴት መሆን አልፈልግም!!!» አልኩት ኪዳንን እንዴት እንደምናስወጣው የሚያቀርበው አማራጭ ሁሉ የሆነን ሰው ህይወት አደጋ ላይ የሚጥል ሲሆንብኝ

«ይሆንልሻል ?» አለ ማደንዘዣው እየለቀቀው የቁስሉ ህመም እየተሰማው ሲያወራም ጭምር እየተሰቃየ ።
«ውስጥ ያለህ ሰው ካሜራ መግጠም የሚያስችል ቅርበት አለው?»
«ይመስለኛል!! ምን አስበሽ ነው? ስልኬን ከኪሴ ውስጥ ወዲህ በይውማ እርግጡን ልንገርሽ! በቅድሚያ ግን ያሰብሽውን ልስማው?»

አመነታሁ! ከራሴ ውጪ ማንንም ሰው አምኜ የማውቅ ሰው አልነበርኩም! አለማመን በደሜ ውስጥ ያለ ነገር ነው። በሁለት ወር ከምናምን ጊዜ ሙልጭ ብሎ ሊጠራ አይችልም። የብዙ ዓመት ልምዴ ሁሌም ጀርባ እና ፊቴን ራሴው ስጠብቅ ፣ በመንገዴ የተደገፍኳቸው ሲንሸራተቱብኝ ፣ ከጎኔ ናቸው ያልኳቸው ጎኔን ሲወጉኝ ….. ነው። አውቃለሁ እኮ ደረቱን ለጥይት ሰጥቶልኛል። በማንም ሰው ሚዛን ከዚህ በላይ ከእኔ ጎን መሆኑን ሊያሳይለት የሚችል ምንም ማረጋገጫ አይኖርም። በቃ ግን የዛች ሜላት ልብ አመነታ። ለአፍታ ዝም ስል ገብቶታል።

«አሁንም እምነትሽን አላገኘሁም ማለት ነው?? እንዲያው ምን ባደርግልሽ ነው የምታምኝኝ ዓለሜ?» የጎንጥ ድምፅ አይመስልም። ሳላምነው እንኳን የሚቆጣኝ ድምፅ ሳይሆን ምንም ማድረግ የማይችል በጣም የተከፋ ድምፅ ነው። ለሁለተኛ ጊዜ <ዓለሜ> ብሎ እንደጠራኝ ያላስተዋልኩ መስዬ አለፍኩ።

«እሺ ይሁን!! ዝርዝሩን አትንገሪኝ!! እንዲሆን የምትፈልጊውን ብቻ ንገሪኝ!!» አለ በዛው በከፋው ድምፁ

«ውስጥ ያለህን ሰው ምን ያህል ታምነዋለህ?»
«በመድሃንያለም!! አንች የምታውቂያቸውን ሰዎች አላውቅም!! እኔ የማውቃቸው ግን እስከህይወት የሚታመኑኝ ሰዎች አሉኝ!!»

ለእኔ የማመን ትርጉም እርሱ ካለው ይለያል። አመኔታ ከሚታመነው ሰው ይልቅ የሚያምነው ሰው ላይ ይመስለኛል ጫናው። ማንንም ሰው <እገሌ በፍፁም አይከዳኝም! በፍፁም ፊቱን አያዞርብኝም!> ብሎ መቶ ፐርሰንት ሰውየው ላይ መዘርፈጥ የዋህነትም ጅልነትም ነው። ምክንያቱም ማንም ሰው በማይደራደረው ነገር ከመጡበት አሳልፎ ይሰጥሃል። እኔ እገሌን አምነዋለሁ ስል ፍፁም አይከዳኝም ማለቴ ሳይሆን ቢከዳኝ ወይ ፊቱን ቢያዞርብኝ እንኳን ያለበቂ ምክንያት አልከዳኝም ብሎ ምክንያቱን ለማወቅ ክፍት እስከመሆን የሚደርስ ልብ አለኝ ማለት ነው። ከበቀል በፊት <ለምን?> ብዬ መጠየቅ የምችልበት ልብ ካለኝ ያን ሰው አምኜዋለሁ ማለት ነው።

ሰዎች በፍቅር ለወደቁለት ሰው <አምንሃለሁ> ወይም <አምንሻለሁ> ብለው ልባቸውን ሲሰጡ ያን የወደዱትን ሰው <በፍፁም ልቤን እንደማትሰብረው አውቃለሁ!> እያሉት ነው እንዴ? እኔ አይመስለኝም። <ብትሰብረው እንኳን ልሰጥህ ዝግጁ ነኝ! ብትሰብረው እንኳን ህመሙን እስከመቀበል ድረስ ነው ፍቅሬ!> እያሉት እንጂ!


«አትፍረድብኝ! የመጣሁበት መንገድ ከሚታመኑት ይልቅ የማይታመኑት የበዙበት ነው! በዛ ላይ አንዲት ስህተት ብሰራ አደጋ ላይ ያለው ኪዳን ነው! በሱ ጉዳይ ማንም ላይ ባልታመን ተረዳኝ!! ደግሞም እኮ ጎንጥ ለልጅህ …… » ብዬ ነገሩን መጨረስ ይቅር ያላልኩት ያስመስልብኛል ብዬ ተውኩት

«ላውጋሽ ሁሉንም ከስር መሰረቱ አልኩሽ እኮ ዓለሜ? ስሚኝና ቅያሜሽን ያዥው ካሻሽ!»
«ቅያሜ አይደለምኮ! ግን እረስቼዋለሁ ብልህ ውሸቴን ነው!»

እውነታው ይቅርታ ማድረግ እና መርሳት ይለያያል። ይቅር ብዬዋለሁ ማለት ከዛ በኋላ ያደረገኝን ነገር ሳስታውስ ቁጣ ወይም በቀል ወይም ጥላቻ ሳይሰማኝ አልፈዋለሁ ማለት ነው እንጂ ድርጊቱን ረስቼዋለሁ ማለት አይደለም!! ይቅር ብያለሁ ማለት የበደለኝን ሰው ሳየው ለቡጢ የሚዘረጋው እጄ ለማቀፍ መዘርጋት ይችላል ማለት እንጂ ያ ሰው በዛው ወጥመድ እንደማይጥለኝ አምኜ (መጃጃል ብለው ይቀለኛል) መጠንቀቅ እተዋለሁ ማለት አይደለም!! በኔ ልምድና ፍቺ ይቅርታ ይህ ይመስለኛል። ሀይማኖተኛም ባልሆን ከሰማኋቸው ጥቂት የመፅሃፍ ቅዱስ ስብከቶች በመነሳት እራሱ እግዚአብሄርም ይቅር ብዬሃለሁ ሲል በጥፋትህ አልቀጣህም ምህረት አጊንተህበታል ማለቱ እንጂ ስራህን ረስቸዋለሁ ማለቱ አይመስለኝም። ቢሆን ኖሮ እስራኤሎችን አንድ ሺህ አንድ ጊዜ ይቅር ካላቸው በኋላ አንድ ሺህ ሁለተኛ ጊዜ ባዕድ ሲያመልኩ ከግብፅ ካወጣቸው ጀምሮ የበደሉትን ባልዘረዘረላቸው ነበር።
ጎንጥ እኔጋ መስራት ከጀመረ ከተወሰነ ወር በኋላ ልጁ ታማበት ነበር። ለሳምንት አስፈቅዶኝ ጠፍቶ ተመልሶ ሲመጣ ልቡ ተሰብሮ ልጁ ኩላሊቷ መቀየር እንዳለበት እና የሱ ኩላሊት ማች እንዳላደረገ ሲነግረኝ ምክንያቴ ለሷ ማዘን ይሆን ለሱ ወይም በደም የጨቀየ ህይወቴን በደል መቀነስ ለማላውቃት ህፃን ኩላሊቴን ልሰጥለት ፈቃደኛ ነበርኩ። ሄጄ ምርመራውን አድርጌላት ነበር።

የዛን ቀን ለእመቤት ይገርማታል ብዬ ለጎንጥ ልጅ ላደርግ ያሰብኩትን ስነግራት እሷ ግን በሚያሳዝን አይን እያየችኝ
«ሜልዬ? የመረጥሽውን ህይወት ድጋሚ የማስተካከል እድል ቢኖርሽ ምርጫሽ ይለይ ነበር?» አለችኝ

«አላውቅም! አስቤው አላውቅም! ምናልባት እንደማንኛውም ሰው ዓይነት ህይወት ኖሮኝ ቢሆን ምን እንደምመርጥ አላውቅም!! ግን ማንኛዋም ህፃን እኔ ያለፍኩበትን መንገድ አላለፈችም!! ማንኛዋም ህፃን እኔ ያየሁትን አላየችም!!»

«እኔ ግን ሲመስለኝ እንደማንኛዋም ሴት ሚስት መሆን እናት መሆን ….. ስስ መሆን …. ማፍቀር …. ባፈቀሩት ሰው ልብ መሰበር ….. ማለቃቀስ ….. እነዚህን ሁሉ የማድረግ ፍላጎት ልትሰሚው ስለማትፈልጊ እንጂ የሆነ ልብሽ ጥግ ተደብቆ ያለ ይመስለኛል።» አለችኝ። ጋዜጠኛ አይደለች? ወሬ ማዳመቅ ትችልበታለች።

«ሌላውስ ይሁን ልብ ተሰብሮ ማልቀስ መፈለግ የጤና ነው?» አልኳት ወሬው ሲኮሳተር ራሴን እፈልግ ይሆን አልፈልግ መጠየቅ ሽሽት። አፍቅሬ አላውቅም ወይም ፍቅር ይሉት ነገር በእኔ የህይወት ጉዞ ገደቡን ያለፈ ቅብጠት ነው። ከቅፅበት ስጋዊ መንደድ አልፎ አቅሉን ስቶ በፍቅሬ የነሆለለ ወንድም አላስታውስም!! ጭራሹኑ ከልብሴ ስር የሴት ገላ መኖሩ ትዝ የሚለው ወንድ ልብሴን አውልቄ ያየኝ ብቻ ይመስለኛል።

«እሱ ራሱ ጣዕም እንዳለው ብታውቂ? አፍቅረሽ ጧ ብለሽ! ከሌላ ሴት ጋር አየሁት ብለሽ ግንባርሽ ላይ ሻሽ ሸብ አድርገሽ ትኩስ ነገር የሞላው ኩባያ ይዘሽ ለጓደኛሽ ማውራት ……. »

«በይ እናቴ ያንቺ የጤና ፍቅር አይደለም! ታየኝኮ ማግ ይዤ ለወንድ ስንሰቀሰቅ!» ብያት ስቄ ከደንኩት።

የጎንጥን ልጅ ሆስፒታል ሄጄ ሳያት ተስፋ ባዘሉ የልጅነት ዓይኖቿ ውስጥ የራሴን ልጅነት አየሁት። ኩላሊቴ ሊያድናት እንደሚችል ሲነገረኝ የነበረኝን የደስታ ስሜት የዛሬን ያህል አስታውሰዋለሁ። ከዛን ቀን በፊት ሆስፒታል የመተኛት ከፍተኛ ፍርሃት ነበረብኝ። በተለይ ማደንዘዣ የሚያስወስድ ነገር ከሆነ። ራሴን ባላወቅኩበት ቅፅበት የሆነ ሰው የሆነ ነገር ያደርገኛል ብዬ እፈራለሁ። በጥይት ተመትቼ ሀኪም አምኜ ሆስፒታል የማልተኛ ሴት በገዛ ፈቃዴ ቅደዱና ኩላሊቴን አውጡ ብዬ የሆስፒታል አልጋ ላይ ልተኛ ዝግጁ ነበርኩ። ማንም ምንም ቢያደርገኝ ይሁን ከዛች ህፃን አይበልጥም ራሴን አስቱኝ ብዬ ፍርሃቴን ልውጥ ዝግጁ ነበርኩ። መኪናዋን ጊቢ እስካስገባ እንኳን አቅበጥብጦኝ

«እንኳን ደስ አለህ!!» ስለው ፊቱን ወደሌላ ቦታ አዙሮ እየተገማሸረ
2.9K viewsTsiyon Beyene, 00:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 18:01:01 ‹‹በፈጣሪ ምን ለማለት ፈልጋ ነው?እኔ ምን እመስላለሁ? ምሽቱስ ምን ይመስላል? በእኔና በምሽቱ መካከል ያለው መመሳሰልስ እንዴት ነው ሊመሳጠር የሚችለው?መቼስ ይህቺ ሴትዬ እዚህ መቀመጫ ላይ ከተቀመጠች ሰዓት አንስቶ መጠጧን ከመገልበጥ እና ሲጋራዎን ከማቡነን ሌላ  ፊቷ ሲፈታም ሆነ ጥርሶቾ ለሳቅ ሲገለጡ አላየሁም ...፡፡.ያ ማለት ደግሞ ምሽቱ ለእሷ ደባሪ ነበር የሚለው ድምዳሜ ላይ ያደርሰኛል ..ያ ከሆነ ደግሞ አንተ ደባሪ ነህ እያለችኝ ነው? እሺ ምኔ ነው ደባሪ ? መልኬ ነው?ቁመናዬ ነው?ወሬዬ ነው?
"ምን ትንጠባርብኛለች..እስከጋበዝኩህ ድረስ እንደፈለኩ ልሰድብህ እችላለሁ እያለች ነው እኮ?...ሴቶቹ የስራ ባለደረቦቼ በየቀኑ ከሚጋበዙአቸው ሰዎች  እንደዚህ አይነት ንቀትና መንቀባረር የሚያጋጥማቸው ከሆነ ለትዕግስታቸው ታላቅ አክብሮት አለኝ››ይህንን ሀሳብ በውስጤ ነው እያመነዥግኩ ያለሁት፡፡
"ድንገት ያለምንም ማስጠንቀቂያ ጠረጴዛው ላይ የነበረውን ፓኮ ሮዝማን ሲጋራዎን እና ላይተሯን ይዛ ብድግ ብላ ተነሳች።
በመሄዷ እፎይታ እየተሠማኝ ፈጠን ብዬ"ልትሄጂ ነው… ደህና እደሪ"አልኳት፡፡
"አዎ ልሄድ ነው ..ክፍሌ 104 ቁጥር ነው...መጠጡን ይዘህልኝ ና"ብላኝ እርፍ፡፡

"እሺ ግን ሰው ስለሌለ እስክዘጋጋ እቆይብሻለሁ.."ሰበብ መደርደሬ ነው፡:፡

"እንደፈለክ…ለሊቱ ገና ረጅም ነው…. የትም እልሄድም፤ እጠብቅሀለሁ"ብላኝ የሚያርድ መቀመጫዎን እያማታች ቀጥ ብላ ወጥታ ሄደች..፡፡

እንዳትሰማኝ ድምፄን ዝቅ አድርግ ‹‹የእውነት አድናቂሽ ነኝ"አልኩ..እውነቴን ነው ግማሽ ጠርሙስ ውስኪ ብቻዋን ገልብጣ ገድገድ ሳትል ...እኔ ገና በግማሽ ብርጭቆ ጉልበቴ  እየተብረከረከ ነው።

ይቀጥላል
3.7K viewsአትሮኖስ, 15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 18:01:01 #እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_ሦስት

አስተናጋጅ ሆኜ ከተቀጠርኩ አንድ አመት  አለፈኝ።በሲቪዬ ላይ የስራ ልምድ በሚለው ርዕስ ስር የንብረት ክፍል ተቆጣጣሪ እና የሆቴል አስተናጋጅነት የአንድ አመት የስራ ልምድ የሚለውን አስገብቼ መፃፍ እችላለሁ፤አዎ ይሄ ቀላል ነገር አይደለም።እያንዳንዱን የሠው ትዕዛዝ በትሪ ይዤ አቀርብና በዛው ትሪ ባህሪያቸውን  ያስረክቡኛል። ትሁቱ... ቁጡ.. ጉረኛ... ጋግርታም... እርብትብት... ለጋስ...ንፉግና ተነጫናጭ...በየቀኑ ፀባዩ የሚገለባበጥ ሙልጭልጭ በቃ እኔ ትምህርት ሚኒስቴርን ብሆን ኖሮ ሳይኮሎጂ እና ሶሾሎጂ ለሚያጠኑ  ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ቢያንስ ለስድስት ወር እንደዚህ አይነት ቦታ አፓረንት እንዲወጡ አደርጋቸው ነበር..ሆቴል ማለት የሠው ባህሪ በብፌ መልክ የሚቀርብበት ቦታ እኮ   ነው።

አሁን ከምሽቱ አራት ሰዓት ሆኗል ፡፡ባሩ ውስጥ አንድ ተስተናጋጅ ብቻ ነው ያለው፡፡ ለዛውም ሴት ደንበኛ...፡፡ይሄንን ብላክ ሌብል  ትጋተዋለች ።አሁን አሷ ብትወጣልን ሌላ የቀረን ስራ ስለሌለን ወደየቤታችን እንሄድና አረፍ እንል  ነበር ስል አሰብኩ ስናስተናግድ ከነበረነው  ስምንት ሴትና አራት ወንድ አስተናጋጆች መካከል አምስቱ ሴት ቀድመው መውጫ ቆርጠው ሄደዋል?ምን? መውጫ ምንድነው ?አላችሁኝ... መውጫ ማለት አንድ ሴት አብሯት የሚያድር ሰው አግኝታ የስራ ሰዓቷ ከመጠናቀቁ በፊት መውጣትና ከደንበኛዋ ጋር መሄድ ከፈለገች እንደሰዓቱ እየታየ ከምታገኘው ላይ እንድትከፍል ይደረጋል...ያው ግብር በሉት ።
ብዙውን ጊዜ በኢትዬጵያ የቡና ቤት ሴቶች ግብር አይከፍሉም ይባላል..እኔም እንደዛ አምን ነበር፡፡ አሁን ግን እንዲህ ተጠግቼ ሳይ አመት እስከ አመት እንደውም እንደእነሱ የሚከፍል የለም? ያው ግብር ማለት ከደሀው  መቀነት  ተቀንሶ  ለኃያላኑ ጡንቻ ማፈርጠሚያ  በግዳጅም ይሁን በይሁንታ የሚሰጥ መባ ነው።ኃያሉ መንግስት ሊሆን ይችላል..ባለሀብት ሊሆን ይችላል...የሠፈር አስተዳዳሪ ባለጡንቻ ሊሆን ይችላል...፡፡  ሁሉም በሚስኪኑ ደሀ ጫንቃ ላይ ተፈናጦ ከርሱን የሚሞላ  ብልጉ አውሬ ነው...ውይ በማሪያም አለቃዬን ነው ከሌላው ባለጉልበት ጨምሬ እንዲህ የጨፈጨፍኩት .አምላክ ሰምቶ ውለታ ቢስ ብሎ እንዳይቀየመኝ፡፡

አሁን ሆቴል ውስጥ የቀረነው ሁለት ወንድ  አስተናጋጆች እና አንድ ሴት አስተናጋጅ እና ደግሞ የእለቱን የተሰራ ሂሳብ ተረክቦ   እየደመረ ያለው ባሉካ ብቻ ነኝ...ሽኩክ ብዬ ወደእሱ ሄድኩና ፡፡
"ጋሼ እንዴት ነው?"

"ስለምኑ ነው የምትጠይቀኝ ጎረምሳው?"

‹‹ስድስት ሰዓት ሊሆን ነው...ተስተናጋጇን ልንዘጋ ነው ልበላት እንዴ?"

"አይ አይሆንም...ትልቅ ደንበኛችን ነች ..ቅር እንዲላት አልፈልግም.."

"አይ ለእሷም ቢሆን ይመሽባታል ብዬ እኮ ነው፡፡"

"የእኔ አሳቢ አይመሽባትም... ከተቀመጠችበት ተነስትታ አስር እርምጃ ከተራመደች የተከራየችበት ቤርጎ ትደርሳለች"

"ኦ ረስቼው… ለካ እዚህ ነው አልጋ የያዘችው"

"አዎ ባይሆን ልጇቹ ይግቡ ..ንገራቸው፡፡"

"እሺ ግን ጋሼ እሷ እስክትሄድ ብቻህን ልትሆን ነው?"

"አይ እኔ አይደለሁም ቀርቼ የማስተናግዳት ...አንተነህ.፡፡..በራሷ  ጊዜ በቅቷት ስትሄድ ቆላልፍና ሂድ...እኔ ሚስቴ ትጠብቀኛለች ...አንተ ከአይጥ ጋር ድብብቆሽ ለመጫወት ምን አስቸኮለህ?››

‹‹እንዴ ጋሼ ከጓደኞቼ ጋር የማወራው ነገር ተደብቆ ይሰማል እንዴ...?"ስል በውስጤ አልጎመጎምኩ፡፡ከሶስት ቀን በፊት ነበር ለሴቶቹ አንድ አይጥ አላስተኛ እንዳለቺኝና ልክ ስተኛ ጆሮዬን እየቀረጠፈች፤ ከንፈሬን እየነከሰች  አስቸገረችኝ ብዬ ያወራኋቸው...እነሱ ደግሞ አፍቅራህ ነው እያሉ ሲያሾፍብኝ ነበር..ይሄው አሁን ጋሼም ተቀላቀላቸው...
ጋሼ ሂሳቡን ሰርቶ ጨርሶ ለመሄድ ተነሳ፡፡

"ጋሼ ለመቆየቱ ግን ካሌብ አይሻልም?"

"ጓረምሳው ንብረቴን ለማን አምኜ ጥዬ እንደምሄድ የመወሰኑ መብት የእኔ መሰለኝ?...መልካም አዳር"ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ...፡፡እኔም ሌሎቹ እንዲሄዱ ተናግሬ በዛ ውድቅት ለሊት ከአንድ እንስት ተስተናጋጅ ጋር ተፋጥጬ ተቀመጥኩ...፡፡
እኔም እንደሌሎች በዚህ ሰአት ክፍሌ ገብቼ አረፍ ባለማለቴ ከፍቶኛል ..ግን ደግሞ ጋሼ የተናገራት ነገር ልቤ ላይ አሪፍ  ደስታና ኩራትን አርከፋክፋብኛለች "ጓረምሳው ንብረቴን ለማን አምኜ ጥዬ እንደምሄድ የመወሰኑ መብት የእኔ መሰለኝ?ነበር ያለኝ አይደል?፡፡ "በእውነት መታመን ያስደስታል" ለዛውም አንድ አመት ባልበለጠው ጊዜ ውስጥ ይህን መሳይ ክብር ማግኘት ተስፋው ለፈረሰበት ሰውም ቢሆን  በህይወቱ ጥቂት መነቃቃትን ይፈጥራል፡፡

ጠረጴዛው ተንኳኳ ከነበርኩበት ባንኮኒ ውስጥ ፡ሮጬ ወጣሁና  ወደ ተጠራሁበት ቀርቤ፤ እጇቼን ወደኃላዬ አጣምሬ፤ ከጉልበቴ ሸብረክ ፤ ከአንገቴ ጎንበስ ብዬ"አቤት ምን ጎደለ ? ምን ላምጣ?"አልኩ፡፡

"እ ..ምንድነበር..?."በፈጣሪ ሰክራለች መሠለኝ ..?ለምን እንደጠራችኝ እንኳን  አታውቅም፡፡
"አዎ..ሙዚቃውን በጣም ቀንሰው እናም አንድ ብርጭቆ አምጣልኝ"
ወይ ፈጣሪዬ ሴትዬዋ ገና መጠጣት ልትጀምር ነው..ለዛውም በሁለት ብርጭቆ…. እንዳለችኝ የሙዚቃውን ድምፅ  ቀነስኩና ብርጭቆውን አጣጥቤ ይዤላት ሄጄ ጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጥኩላትና ልመለስ ስል "ተቀመጥ"አለችኝ...
ተቀመጥ በሚለው ቃሏ ውስጥ ምንም አይነት ትህትናም ሆነ ሀዘኔታ አይነበብም፡፡.

"ምን አልሺኝ እመቤቴ?"

"ቁጭ በል..ንግግሬ አይሰማም እንዴ?"

"ኸረ በደንብ ይሰማል"ብዬ ትዕዛዟን በማክበር ሽኩክ ብዬ ቁጭ አልኩ..ፊቷ የተቀመጠውን  የተጋመሰ ብላክ ሌብል ጠርሙስ አነሳችና አዲስ ያመጣሁት ብርጭቆ ውስጥ አንደቀደቀችው፤ስትጨርስ  ወደፊት ለፊቴ አሽከርክራ አሰጠጋችው።

"ኸረ ይሄ ነገር ለእኔ አይሆንም?"

"ባክህ አትንጠባረር ..ዝም ብለህ ጠጣ "ብላኝ እርፍ...
አሁን ይሄ ግብዠ ነው አስገድዷ ደፈራ፡፡ፈራኋት መሠለኝ አነስሁና አንዴ ጎንጨት አልኩለት...
.፡፡‹‹እራት መቼ ነበር የበላሁት?›› ስል እራሴን ጠየቅኩ፡፡ አዎ 12፡30 አካባቢ....‹‹ምንድ ነበር የበላሁት?›› ዳቦ በሙዝ ...፡፡.ሶስት ሙዝና ሁለት ዶቦ....፡፡‹‹አሁን ከስድስት ሰዓት በኃላ ምን እየጠጣሁ ነው›› ውስኪ፡፡...‹‹ይህቺ ጋባዤ አራት ሰዓት አካባቢ ምንድነበር ያዘዘችው..?››ለማስታወስ ሞከርኩ...አዎ ክትፎ ነበረ ያዘዘችው እናም ግማሹን በልታ ግማሹ እንደተመለሠ አይቼያለሁ....አሁን ኪችን ብገባ ግማሹን ትራፊ አገኝ ይሆን?

"እዚህ ሀገር ለስራ መጥተሽ ነው?"ጥያቄውን መጠየቅ ፈልጌ ሳይሆን ዝም ብሎ መቀመጥ ስለጨነቀኝ ነው የቀባጠርኩት። ቢዝነስ የሚሰሩ ሴት  አስተናጋጆች ግን  እንዴት ብለው ነው ከማያውቁት ሰው ፊት ለፊት ተቀምጠው ዘና ብለው የሚጠጡት...ከዛም አልፎ የሚስቁት፤ የሚጫወቱት?ለዛውም በየቀኑ…፡፡ጥያቄዬን ሰምታ ሲጋራዋን ለኮሰች ...እናም ጭሱን አትጎልጉላ እላዬ ላይ በተነችብኝ ፡፡...ልክ እንደቤተመቅደስ ማዕጠንት ዝም ብዬ በፀጋ ተቀበልኩና ወደውስጤ ማግኩት?

"ምሽቱ ደስ ይላል..."ሌላ የማይረባ አስተያየት ከአንደበቴ ድንገት ሾለከ፡፡

"ምሽቱ አንተን ነው የሚመስለው?"አለችኝ፡፡
3.9K viewsአትሮኖስ, edited  15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 22:15:12 ካቻምናን ብንከሰው: ቆመን ካምና ደጅ
መቼ ፈረደልን? ፈረደብን አንጂ!
አምናንም ብንረግመው: ቆመን ከዘንድሮ
አልደረሰበትም ደረሰብን ዞሮ
ከእንግዲህስ ይብቃን…
ሂያጆቹን ለመጡት ማማቱን ትተናል
እኛ ስንተዋቸው ይተውን ይሆናል!

ረድኤት
828 viewsአትሮኖስ, edited  19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 18:00:13 ‹‹አንተ ወሽካታ..አንጀቴን መብላትህ ነው..››.አሉና አንድ የድሮ ፎታቸውን በበር ሰር አሾልከው ወረወሩልኝና…‹‹ያው አያትህ ሙሉአለም ማለት ያ ነው››አሉኝ፡፡
እና ለመጀመሪያ ጊዜ አቶ ሙሉአለም ምን እንደሚመስሉ በፎቶ አየኋቸው….ያምራሉ ፡፡ትንሽ ወፈርና ደንደን ከማለታቸው በስተቀር  ጋሽ ስብሀት ገበረእግዚያብሄርን  ነው የሚመስሉት፡፡ጠይም መላአክ፤ዘለግ ያለ ቁመትና፤የሚስብ ግርማ ሞገደስ አላቸው ፡፡ ፎቶቸውን ካየሁ በኃላ እንደውም ይበልጥ በአካል ፊት ለፊታቸው ቁጭ ብዬ እጃቸውን ትከሻዬ ላይ ጣል እያደረጉ ወይንም ጨበሬ ፀጉሬን እየዳበሱ እንዲያወሩኝ እጓጓ ጀመር….እሳቸው ግን ከአቋማቸው መቼም ንቅንቅ የሚሉ አይነት አይደሉም፡፡

ይቀጥላል
2.2K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ