Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163.71K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 42

2022-12-14 23:09:59
እስቲ ይሄ የፍቅር ሳይኮሎጂ ነው የእናንተን ወይም የፍቅረኛዎትን #የመጀመሪያ ፊደል ይምረጡና ፈታ ይበሉ
397 viewsENFALOT ° , 20:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 21:00:06 "ደልቲስ ነጯን ሐመር እጮኛ ላርግሽ ብሎ በሽማግሌ ጠይቆ
ጥሎሹን መክፈል መጀመር ሲገባው ነጯ ሐመር ጥሎሽ እኔ ልስጥህ
አለችኝ ብሎ በሴት አባባል አኩርፎ የሽማግሌ ውሳኔ መጣሱ እውን ዝምታ የሚገባው ነው!

"ከሎና ጎይቲም
ሽማግሌው ወደ አንተነህ  ጋልታምቤ ሰረቅ አድርገው ተመልክተው፤ "… ከሎና ጎይቲም ተተጋቡ ሁለት
ዓመት አለፋቸው" ከኋላው ያገቡት ሁሉ ለፍሬ ሲበቁ ከሎ የዘራውን ግን የጎይቲ ማህፀን ይኸው አላፈራም ሽማግሌው ንግግራቸውን
ቀጠሉ

"ጎረምሶች ከጎረምሳ ተራራ እየሄዱ ኢላማ ተኩስ
መለማመዳቸውም ቁሟል . ጠላት ሲመጣ የዝሆን ቀንድ አይነፋም ሳይጠበቅ ይመጣል ሳይታጠቁ አጥቅቶ ይሄዳል የኛ ጎረምሶች ደግሞ መሳሪያ መሸከም እንጂ ቃታ መሳብ የሚገባው ጣታቸው እንደ
መዥገር የልጃገረድ ጡት ነክሶ ይውላል እንግዲህ እነዚህን ችግሮች መፍታት አለብን" ብለው፥ የሽማግሎች አለቃ ንግግራቸውን አቆሙ።

ይቀጥላል
1.5K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 21:00:05 #የዘርሲዎች_ፍቅር


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


#ክፍል_ሁለት


የወሮ መንደር ሽማግሎች ከሁለቱ መንደሮች መሃል ካለችው ትንሽ ሜዳ ግማሽ ክብ ሰርተው በርኮታቸው ላይ ተቀምጠዋል" ባለ
ጴሮው፥ ሹልሹላው፥ የሰጎን ላባ ፀጉሩ ላይ የሰካው ሁሉም በተመስጦ ስብሰባው እስኪጀምር ለውይይቱ ህሊናቸውን ይሳስላሉ  ህፃናት ከሽማግሎች ርቀው
እንቧይ እየተቀባበሉ
ይጫወታሉ ጋልታምቤ ከቤቱ ወደ ሜዳው በምትወስደው ቀጭን ጎዳና ሄዶ ከሽማግሎች ጋር ተቀላቀለ ሌሎችም ከያቅጣጫው እየመጡ
ተደባለቁ„

ረጅም ጦር የያዙት የመንደሩ አለቃ (ዘርሲ) ከተቀመጡበት
ተነሱና ከወገባቸው ከታጠቁት ዝናር ጩቤ አውጥተው ጎረምሶች
የያዙትን ለፍላፊ ፍየል በቁሙ ጉሮሮው ላይ ወጉትና ፍየሉ ሲወድቅ
ከደሙ ጦራቸው ላይ ከፈርሱ ደግሞ ባታቸውን ቀባ-ቀባ አድርገው
ሄድ መለስ: ሄድ መለስ ብለው ንግግር ጀመሩ

"ጥሩ ነው! ዝናቡ መጥቷል መሬቷ ሳር አብቅላለች፥
ተራሮች እንደ ልጃገረድ አጊጠዋል ድንጉላ ቢራቢሮዎች፥ ወፎች
ይበራሉ" ንቦች አበባቸውን እየቀሰሙ ወደ ቀፎቻችን ይተማሉ፥ ውሃ የጠማት ምድር እምትጠጣው አግኝታለች እኛም የምንጠጣውን  ከስኬ ይሰጠናል አሸዋውን ስንጭረው ውሃ መሬቷን በጧር  ስንወጋት ማሽላ እናገኛለን ዳመናውን ሰርስራ
በምትወጣው ጨረቃም ልጆቻችን ይደሰታሉ
እንግዲህ ተቀያችን: ከዚች
አባቶቻችን ካቆዩን ምድር ምን ጎደለ!" ብለው ዝም አሉ የሽማግሎች
አለቃ" እንደገና ሄድ መለስ እያሉ ሁሉንም በዐይናቸው እየቃኙ

ብዙዎቹ ተሰብሳቢዎች ዐይናቸው ያለው ሌላ ቦታ ነው ሐመር ላይ ነገር በዐይን አይገባም' ነገር የሚደመጠው በልቦና ነው፤
ልቦና ያያል ልቦና ይሰማል
ልቦና ይመራመራል ልቦና
ይወስናል" በልቦና ለማየትና ለመስማት ግን ፀጥታ ያስፈልጋል ውስጣዊ እርጋታ የሃሳብ ማዕበል የሌለበት መተራመስ የተረጋጋበት ሊሆን ይገባል" ሐመር ላይ ሽበት ብቻ
ለሽምግልና አያበቃም፤
ጀግንነት ብቻ አያስከብርም
ማህበራዊ ችግርን ለመፍታት በጥንቃቄ ውሉን ፈልጎ አግኝቶ ትብትቡን
የሚፈታ ህሊናው ቀልጣፋ ከጀግንነቱም ከፍርድ አዋቂነቱም ሁለገብ ችሎታ ያለው መሆን ያሻል  ለሽምግልና ለመታጨት

"ጥሩ ነው! የአባቶቻችን መንፈስ ከእኛ ጋር አለ እንዳንራብ መከራ እንዳይበዛብን ዝንጉ እንዳንሆን የነሱ መንፈስ እንደ ዛፍ ጥላ ከለላ ይሆነናል ይሁን እንጂ በአባቶቻችን የነበረው ችግር አሁንም
አለ አሁንም የአባት ጠላት አለን አሁንም የአባት ጠላቶች እያዘናጉ የከብቶቻችንን ጅራት ሊጎትቱ የሚስቶቻችንን እጅ ሊስቡ፥ የላሞቻችንን ጡት ሊያልቡ ይፈልጋሉ ተናጋሪው  ንግግራቸውን ገተው ዙሪያ ገቡን እያዩ ፀጥ አሉ የኦሞ ወንዝ ቆሞ ያውቃል? ውሃ ታግዶ ይቆማል? ያባት
ደንብም እንዲሁ ነው፤ ሁሌም ከልጅ ወደ ልጅ ግድቡ በሽማግሎች
እየተከፈተ ከላይ እየወረደ የመጣው ወደሚቀጥለው
ትውልድ እየቶንዶለዶለ
ይፈሳል" ለዚህ ነው ከስኬ ሲጫር ውሃ: የእኛ ልብ
ሲቆፈር ደግሞ ያባት ደንብና ባህል የሚፈልቀው፤ ከእኛ መሃል ልቡ ሲቆፈር የአባት ደንብና ባህል የማያፈልቅ ደረቅ ካለ ግን ከጠላት
የተወረወረብን ድንጋይ ስለሆነ አምዘግዝገን መወርወር፥ ካካባቢያችን
ማጥፋት ይኖርብናል" ተናጋሪው ሽማግሌ ንግግራቸውን ገትተው
የተናገሩትን እንደገና በህሊናቸው አጣጣሙት።

"ወንድሞቼ የአባቶቻችን መንፈስ ከእኛ ጋር ነው
የምንሰራውን እነሱ ካቆዩን ደንብ ጋር ካላመዛዘነው እንደ ዱር ጉንዳን ማን እንደቆመብን ሳይታወቅ፤ ምንነታችንም ሳይጠየቅ አውራ እንደሌለው የሚያስተባብረው እንዳጣ ንብ በየጢሻው እንበተናለን
እንጨት ቆርጠን ሳር አጭደን ለንብ ቀፎ እየሰራን: እኛ ግን ተሰርቶ የቆየንን የአባት ደንብ ደህንነቱን
በመጠበቅ ለልጅ ልጆቻችን ማስተላለፍን ዘንግተናል" ከጉንዳን: ከንብ አንሰን የአባት ደንብ እየሻርን ነው: ትብብራችን እየላላ ነው፥ ወኔያችን ተሸንቁሮ
ንፋስ እየገባው ነው." እንደገና ቃኙት ተሰብሳቢውን  በዝምታ።

"አውሬ ይሁን ወፍ የማይታወቅ ጉድ በአራት እግሩ መንደራችን እየመጣ ሲቆም በሰፊው ሆዱ  ሴቶቻችንን እየሸፋፈኑ
እያቀፈ ሲወስድና ሲመልስ
ሴት ልጅ ወንድ የዘራውን ማብቀል  ሲሳናት እኛ አልተቃወምንም! ኧረ ተው! የተቀበልነውን የማናቀብል ጅብ አንሁን ጅብ የሚኖረውና የሚሞተውም ለሆዱ ነው የአባት ደንብ የለው ለልጄ ማለት አያውቅ አፍንጫው ጥንብ እንዳሸተተ: ሆዱ ለመብላት እንደተስገበገበ
ኖሮ ይሞታል ለልጄ ሳይል ደንብ ሳይኖረው ጥንብ እንደ አማተረ ይሞታል ለሆዱ! የተናጋሪውን ሃሳብ ከሚያዳምጡት መካከል አንዱ ሽማግሌ
የዘርሲዎች አለቃ በተናገሩ ቁጥር "ህም ህም… "አሉ በሐመር የስብሰባ ደንብ አንዱ ሲናገር ሌላው ህም ህም ካለ ልቀጥል ልናገር ማለት ስለሆነ የሽማግሎች አለቃ የንግግር እድሉንና
ተናጋሪው የሚይዘውን ጦር አቀበሉ  ተረኛው ሽማግሌ ጦሩን በቀኛቸው ይዘው ከፍየሉ ፈርስ ባታቸውንና ግንባራቸው ቀባ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ሽማግሎችን: ህፃናትን: መንደሩን: ዙሪያ
ገቡን ቃኙት ጦሩ እጃቸውን ነዘረው ስሜታቸውን በሙቀቱ አጋጋለው፤ ወኔያቸውን እንደ ብረቱ ጫፍ አጠነከረው  የአያት
የአባቶቻቸው መንፈስ ከጦሩ ተነስቶ ወደ ልቦናቸው ተስለከለከ

ጥሩ ነው! የቀጋ ፍሬ ከሾላ ዛፍ የለቀመ ማነው ሾላና
ቀጋን ደባልቆ የሚበላ ግን አስተዋይ ነው ይህ ሰው የተፈጠረው ደግሞ እዚሁ እኛ ዘንድ ቡስካ ተራራ ላይ ነው ያ ሰው እሳት
አንድዶ የሚፈልጋቸውን መልካም መልካም ሰዎች በእሳት ብርሃን
ከያካባቢው ጠራቸው
እንግዲህ አያቶቻችን የባንኪሞሮን እሳት
እያዩ ከያቅጣጫው የተሰባሰቡ ናቸው እኒያን ፍሬዎች  ቀጋና ሾላዎች ባንኪሞሮ ደባልቆ በሐመር ምድር በተናቸው"
አያቶቻችንና አባቶቻችን በቀሉ ከእኒያ ብሩክ ፍሬዎች ደግሞ እኛ በቅለን እህ! በተራችን እንድናፈራ ላደረጉን አባቶቻችን ውለታችን ምንድነው?" ብለው ዝም አሉ ሽማግሌው በጠየቁት ጥያቄ አንጀታቸው እየተላወሰ መልሱን ግን ፀጥታው ዋጠው"

"ወንድሞቼ የአባቶቻችን መልካም ሥራ የሚመለሰው ባህልና.ደንባቸውን በመጠበቅ ነው" ተዚህ ታፈነገጥን የሚያድነው እንሰሳ ላይ ማነጣጠር እንዳልቻለ አነር መሮጥ እንጂ የምንይዘው አይኖርም ሁሉም ያምረናል፤ አረንጓዴ ሁሉ ይበላል? ኮሽም: ዶቅማ ይሆናል?- የእኛ ህይወት የአባቶቻችንን ፈለግ በመከተል የሚመራ
ነው፤ እነሱ ያዩትን ዓለምና ደስታ ለማግኘት ከዱካቸው ዝንፍ ማለት የለብንም ተዚያ ታፈነገጥን ግን እሾህ አለ እንቅፋት አለ… ዳመና
ከሰማዩ ላይ ይጠፋል ከብትና ምድሯ ይነጥፋሉ በሽታ ይበዛል ከዚያ ያኔ ቀያችን አጥንት ሰላማችን ቆምጭሮ ሁከት
ይከመርበታል እፅዋት መብቀል ያቆማሉ፤  ባንኪሞሮ  የአነደደው
እሳት ይጠፋና ጥንት እንደነበረው ቀያችንን ዳፍንት ይውጠዋል
ባዶ ይሆናል! እና ተልባችን እንምከር ወንድሞቼ!" ብለው እጃቸውን
አወራጭተው ጦሩን ስመው ዝም አሉ ሌሎች ሽማግሎችም እንዲሁ
የሚሰማቸውን ሲናገሩ ቆዩና ጥፋቶች በመጀመሪያው
ተናጋሪ ተዘረዘሩ።

በአካል ለዘለዓለም
ለተለዩን በርቲና ቃላ መደረግ የሚገባው ደንብ አልተሰራላቸውም "አሉ” እንዳንል የሉም የሉም
እንዳንል ደግሞ ደንቡን የምትጠብቀው ነፍሳቸው አንዴ በወፍ ሌላ ጊዜ በአሞራ ወይንም በንፋስ … መልክ እየመጣች ከእኛ ጋር ናት ንግግራቸውን ገተው የሽማግሎችን የመንደሯን የአካባቢውን ትንፋሽ አዳመጡና

ነጯ ሐመር ይዛው የመጣችብን ስም የለሽ: ጢስ ተፊ አውሬም እዚሁ ከእኛ ጋር እየኖረ ነው ሲበላ ባናየውም ሲጋት ግን
በዐይናችን በብረቱ አይተነዋል ከዚያ እንደ ጅብ አጉረምርሞ ዐይናችን እያዬ ግማቱን ለቆብን ይሄዳል "
1.5K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 18:00:16 #እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አምስት

////

አሁን ወደ ቤቴ ልሄድ ወሰንኩና ወደ እሷ ዞርኩ ...እና አሁንም በድጋሜ ከፊል  እርቃኗን ስመለከት እርብድብድ አልኩና"አይ በዚህ ሰአት ዘበኞቹ ሰለሚተኙ ግቢውን አይከፍቱልኝ ይሆን እያልኩ እያሰብኩ ነው።››

"ነውእንዴ? ታዲያ እዚህ እደራ!!"ብላ ዘጭ ያለው ሞራሌን መልሳ ሰማይ ሰቀለችው..፡፡እያንቀጠቀጠኝ የነበረው የውስጥ ቅዝቃዜ ከውስጤ እየተወገደ በምትኩ ሙቀት ሲራወጥ ታወቀኝ፡፡

"ይሻላል?"

"አዎ ..ችግር የለውም...፡፡አለችና አንሶላውን እና ብርድ ልብሱን ገልጣ ከውስጥ ገባች...፡፡እኔም በአፌ ምራቅ እየሞላ ጫማዬን ማውለቅ ጀመርኩ፤ ሸሚዜን አወለቅኩ፤ፓክ አውቴንም አልተውኩ አወለቅኩ፤ በመጨረሻ ሱሪዬን አወለቅኩና ልክ እንደእሷ በፓንት ብቻ ወደ አልጋ ላይ እየተስገበገብኩ ወጣሁ።..እያየኋት ብርድልብሱን  ወደእኔ ገፋችና  በአንሶላና አልጋልብሱ ተጠቅልላ አንደኛውን ጠርዝ ይዛ ተኛች ..

"ብርድልብሱን ልበስ..ደህና እደር"ብላኝ መብራቱን አጠፋችና ለሽ...፡፡

"እንደተባልኩት በብርድ ልብሱ እርቃኔን ጠቅልዬ ለመተኛት ሞከርኩ...፡፡ምን አይነቱ እንከፍ ነኝ እስኪ ደህና እደር እንዳለችኝ ያልሆነ ነገር ከምቀባጥር በክብር ፈጠን ብዬ ይሄን ክፍል ለቅቄ ብወጣስ?...እሷ እያንኮራፍች ነው፤እኔ ግን ..?እኔማ በሁለት እጇቼ እንትኔን አፍኜ ይዤ እየተገለባጥኩ ነው።በግድ ጉብ ልበልባት ይሆን ?አይ ይሄ  አይሆንም ጓደኞቼ በፓለቲካ ምክንያት ታስረው ጀግና ሲባሉ እኔ በአስገድዶ ደፈራ ሀያ አመት ....አይ መታገስ መልካም ነው፡፡እኔ ደግሞ በትግስት አልታማም ..በእፅዋት ሳይንስ ከሀረማያ በዲግሪ ተመርቄ አዲስአበባ ላይ በአስተናጋጅነት ተቀጥሬ በመስራት ኑሮዬን እየገፋሁ ያለው ትሁት ትዕግስተኛ። ከዚህ በላይ ትግስት ምን አለ...?በተወለድኩባት አዲስአበባ ከተማ  በተማርኩበት ሞያ ስራ ለማግኘት ከአመት በላይ በየመስሪያ ቤቱ  ተንከራተትኩ ..ምንም ጠብ ያለልኝ ነገር የለም...አንድ መስሪያ ቤት ጋምቤላ ልላክህ ይላል...ሌላው ጋ ስሄድ የበጋ ስንዴ ፕሮጀክት አርሲ ላይ አለን እዛ እንላክህ ይለኛል።"ምነው ውትድርና የሰለጠንኩ መሠላቸሁ እንዴ? "ብዬ በእነሱ ይሁን በራሴ እያላገጥኩ አላውቅም ሁሉንም እርግፍ አድርጌ  ያለሞያዬ ስባክን ይሄው ይሄን የመሠለ ፈተና…..

የባጥ የቆጡን ሳስብ ምንጊዜ እንቅልፍ እንደወሰደኝ አላውቅም፡፡ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስደኝ፡፡ ….....የበር መንኳኳት ነበር ከእንቅልፍ አለም መዞ ያወጣኝ
‹‹...ማነው? ምንድነው ?››በርግጌ ተነሳው፡፡

"ፅዳት ነው ሰዓት ደርሷል"

"ፅዳት "ዙሪያ ገባውን ቀኘሁ፡፡ነግቷል፡፡ክፍሉ ባዶ ነው.፡፡.ልጅቷ የለችም...፡፡ልብሷቾም ሆነ ዕቃዋቾ የሉም...፡፡ጠረኗ ብቻ ነው ያለው...፡፡ሄዳለች ማለት ነው..፡፡.ምኑ እንክርፍፍ ነገር ነኝ በፈጣሪ...?ምን አለ በጥዋት ተነስቼ ቢያንስ ለመጨረሻ ጊዜ እነዛን አይኗቾን ማለቴ መቀመጫዋን አይቼ በተሰናበትኳት...፡፡በንዴት ከላዬ ላይ ብርድ ልብሱን አሽቀንጥሬ  ከላዬ ላይ ወረወርኩ፡፡ ...ከአልጋው ወረድኩ… ጠረጴዛ ላይ ያለውን ልብሴን ሳነሳ የሆኑ ባለመቶ ብር ድፍን ብሮች  እና ብጣሽ ወረቀት ድብ ብሎ ወለል ላይ ወደቀ...ብሩን ተውኩና ወረቀቱን አነሳሁት አነበብኩት።

‹‹ደህና ሁን ቆንጇ...ቁርስ በእኔ ነው"ይላል ...
ብሩን አነሳሁና ቆጠርኩት 500 ብር ነው፡፡
‹‹እኔን ብሎ ቆንጆ›› አልኩና በቅጡ እንኳን ልብሴን አስተካክዬ ሳለብስ  በንዴት ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ፡፡

ከውስጤ እየተንቀለቀለ ያለው ንዴት በቀላሉ ሊበርድልኝ ስላልቻለ እቤቴ ስደርስ እንኳን የበራፍ አከፋፈቴና አዘጋጌ ኃይል የተቀላቀለበት ነበር ፡፡

‹‹አንተ ቀልማዳ….››

‹‹አቤት አያቴ››

‹‹የትአባህ ነው ያደርከው…?ሰው ያስባል አትልም እንዴ…?ከአሁን አሁን መጣ እያልኩ ቁጭ ብዬ እኮ ነው ያደርኩት››

‹‹ውይ በጣም ይቅርታ ..ጋሼ ስራ አዞኝ እስከ 9 ሰዓት ስሰራ ስለነበር ደከመኝና እዛው ተኛሁ፡፡››

‹‹እና ሮጥ ብለህ አንድ አፍታ መጥተህ ላድር ነው ብትል የትኛውን ድንበር ስታቆርጥ ነው››ጠንከር ባለ የንዴት ቃና ሲቆጡኝ እንባዬ በአይኔ ሞላ ..ተበሳጫቼ  አይደለም..፡፡ይሄን ያህል የሚያስብልኝ ሰው ይኖረል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበረ…፡፡
‹ሁለተኛ አይለመደኝም››ቃል ገባሁ፡፡
‹ፍፅምዐእንዳይለመድህ .
ትደግመውናትጣላኛለህ
.በል አሁን እንደደካከመህ ድምፅህ  ያስታውቃል ትንሽ ተኛ፡፡››

‹‹እሺ አያቴ›አልኩና አልጋዬ ላይ ተዘረርኩ፡፡

‹‹ዜና ወርቅ… ›
›.‹‹የዜናወርቅ አዎ እንደዛ ብላ ነበር ስሟን  የነገረችኝ…ለዛም ይመስለኛል የዜናወርቅ የሚለው ስም ከእምሮዬ ሞልቶ እየፈሰሰ ያለው….
‹‹ወይ ጉድ ፍቅር ስለሚለው ቃል እራሱ ያሰብኩት ከስንት ጊዜ በኃላ መሆኑ ነው…?አዎ ከስድስት ረጂም አመት በኃላ …፡፡ ፍቅርን እርም ብዬ ነበር…፡፡ልክ እየደጋገሙ እየተንበገበገ ባለ እሳት እጣቱን ከተው እስኪቆስልና ቆዳወ እስኪገሸለጥ ድረስ እያቃጠሉ እንዳስፈራሩት ልጅ አይነት ነበርኩ፡፡.አዎ ፍቅርን የምፈራው ልክ ያ ህፃን ልጅ እድሜ ልኩን እሳትን በሚፈራበት መጠን ነው፡፡እና ጊዜያዊ ስሜቴን ማስወገድ አለብኝ.››.አስቤ አስቤ ሲደክመኝ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡

‹‹ወይ ዝም ብዬህ ቻው እንኳን  ሳልልህ ሄድኩ አይደል?››

‹‹አዎ…ግራ አጋባሺኝ እኮ››

‹‹አይ አስቸኮይ ነገር ስላጋጠመኝ ነው .ይቅርታ››

‹‹አይ ምንም አይደል…ግን እቤቴን ማን አሳየሽ? ››

‹‹አለቃህ…ማለቴ የሆቴሉ ባለቤት ለመነኩትና ከአንድ ጩጬ ጋ ላከኝ፡፡››

‹‹እሺ የቤቱን በራፍስ ማን ከፈተልሽ...?እኔ ተኝቼ ነበር››

‹እሱን ተወው .በመምጣቴ አልተደሰትክም እንዴ?››

‹‹አረ በጣም ተደስቼያለሁ…ነገሮች ድንገተኛ ስለሆኑብኝ ግራ ተጋብቼ ነው››

‹እንደዛ ከሆነ እቀፈኝ››

‹‹እሺ…ይሄው….ወደራሴ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት…››

‹‹እዬብዬ.›በተሰባበረ እና በሚያቃትት ድምፅ ጠራችኝ፡፡

‹‹ወዬ ዜናዬ.››

‹በጣም ሞቀኝ…ልብሴን ላውልቅ››

‹አዎ አውልቂ…. እንደውም እኔም ላውልቅ.››አልኩና እኩል እየተረዳዳን  ልብሳችንን አወለቅንና እርቃናችንን ተመልሰን እቅፍቅፍ ብለን ተጋደምን….፡፡እርቃናችን ሲፋተግ እሳት ፈጠረ..ነደድኩ… ከንፈሯ ላይ ተጣበቅኩባት…ጭኗን ፈለቀቅኩና ሰርስሬ ከመሀል ገባሁ….ቃተተች…‹‹ወይ የእኔ ጀግና ጎዳኸኝ….ቀስ በል..አመመኝ›››
በእጆቼ አፏን አፈንኳት..እንደዛ ያደረኩት የዜናወርቅን የመቃተት ጩኸት አያቴ እንዳይሰሙንና እንዳይረበሹ ስለፈራሁ ነው፡፡እንኳን እንዲህ የምትቃትት ሴት ይቅርና ጮክ ብሎ የሚያወራ ወንድ ጓደኛ  እዚህ ቤት ይዤ መጥቼ አላውቅም፡ተጨነቅኩ፡፡ ስላፈንኳት እሷ ተንፈራገጠች…፡፡ግራ ገባኝ፤ ልልቀቃትና መጮኸን ትቀጥል ወይስ እንዳፈንኳት ልቀጥል …?ብትሞትብኝስ..?፡፡ከመጨነቄ  የተነሳ ላቤ መንጠባጠብ ጀመረ …ተስፈንጥሬ ከመኝታዬ ተነሳሁ፤መኝታዬ ባዶ ክፍሉም ኦና  ነበር…ዜናወርቅ ሀሳብ ብቻ ነበረች.፡፡ምኞት የፈጠራት ህልም››
‹‹ተመስገን›አልኩ፡፡
‹‹ተመስገን ያልኩት ዜናወርቅ ቤቴ ስላልመጣችና ስላልተዋሰብን ተደስቼ አይደለም..ይልቁንስ የእውነት ሆኖ ጋሽ ሙሉአለም ስላረበሽኳቸውና ስላላስቀየምኳቸው ተደስቼ ነው ተመስጌን ማለቴ..አንዳንዴ ግን ህልም ባይኖር በምኞታችን እና  በምናገኘው ነገር መካከል ያለውን ክፍተት በምን እንሞላው ነበር?››

ይቀጥላል
2.3K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 11:39:09 «መሸነፊያዬም መጀገኛዬም አንተ መሆንህን አታውቅም? ባንተ ሲመጡብኝ ነው እጅ የምሰጠውም አውሬ የምሆነውም! ያን ታውቃለህ አይደል?»

«አውቃለሁ ሜል። ግን አሁንኮ ትልቅ ሰውዬ ነኝ!! ሚስትኮ ላገባ እየተሰናዳሁ ያለው ግብዳ ሰውዬ ነኝ! እስከመቼ ነው የምትጠብቂኝ? (ዞር ብዬ ያለፉትን ቀናት እንደማስታወስ ሳየው) ይሄ የተለየ situation ነው። እንዲህ ያለ አጋጣሚ ከተፈጠረማ በድዴም ቀርቼ እንደምትደርሺልኝ አውቃለሁ። ገብቶሻል ምን ማለት እንደፈለግኩ!! መቼ ነው አንቺ የራስሽ የሆነ ህይወት የሚኖርሽ? ለእኔ ብለሽ ፣ ለአባዬ ብለሽ ወይም ለእማዬ ብለሽ የማትኖሪው። ለሜላት ብለሽ የምትኖሪው ቀን መቼ ነው? (ይሄን ሲለኝ ስለእማዬ ለካ መንገር አለብኝ። ምን ብዬ ነው የምነግረው? የሞተችዋ እናታችን ከሞት ተነሳች! ነው የምለው?)  ደግሞ አባት ልሆንልሽ ነው!» ሲለኝ ስለእማዬ ያሰብኩት ጠፋብኝ። መኪናውን አቆምኩ።

«ሊንዳ እርጉዝ ናት? ስንት ወሯ ነው?» እያልኩት እሺ የአሁኑ እንባ ምን የሚሉት ነው? እንደትናንት በሚመስለኝ የቀናት ርዝመት ውስጥ እግሬ ላይ ተጠምጥሞ ትተሽኝ አትሂጂ ብሎ የሚያለቅስ ትንሽዬ ልጅ ነበርኮ!! አባቱ የሞተበት እናቱ ትታው የሄደች ቀንኮ <አባዬ ዳቦ ገዝቶ ሲመጣ ዳቦ በሻይ ነው የምበላው እንጀራ አልበላም!> ብሎ ያለቀሰ የአባቱ ሳጥን ውስጥ መቆለፍ ያልገባው ሚጢጢ ነበረ።

«ስድስት ወር ሆናት! ሴት ናት!» አለኝ እንደመኩራትም እያደረገው። ዝም አልኩ!! ዝምታዬ ውስጥ ግን ብዙ ጩኸት ነበረ። ደስ የሚል ከዛ ደግሞ የሚከፋ ስሜት እንዴት ተብሎ ይብራራል? የእኔ ኪዳን ፣ ልጄ ፣ ታናሼ ፣ ዓለሜ ፣ ብቸኛ የዓይን ማረፊያዬ አደገልኝ!! እሱ አድጎ ልጅ ሊያሳድግ ነው!! እንዲኖረው የተመኘሁለትን እና የተመኘውን ሁሉ አንድም ሳይጎድልበት አግኝቷል። በህይወቴ ትልቁ ድሌ እና ስኬቴ እኮ እሱ ነው!! ከዛ ግን ለምን የመከፋት ስሜት ተሰማኝ? ለእሱ ደስ አለኝ ለእኔ ግን ከፋኝ። የሆነ እዝህች ምድር ላይ ለመኖር የመጣሁበትን ዓላማ የጨረስኩ ፤ የምኖርለት ምክንያት ምንም ያልቀረኝ ፤ ከዚህ በኋላ እኔ የማላስፈልገው ፤ የራቀኝ ዓይነት ስሜት ተሰማኝ። ይሄን ግን ለእርሱ ልነግረው አልፈለግኩም። ደስታው ትንሽ እንኳን እንዲደበዝዝበት አልፈልግም!! አቅፌው እንባዬን እየጠረግኩ ደስ እንዳለኝ ነግሬው መኪናዬን መንዳት ጀመርኩ። ሆቴሉ ደውለን ሪሴፕሽን እቃውን እንዲያስቀምጡልን አድርገን። የሚከፋፈለውን ከፍለን ሻንጣውን ወሰድን። ለአፍታም ቢሆን ከእኔ እይታ ዘወር እንዲል ስላልፈለግኩ ሆቴል ከመያዛችን በፊት ጎንጥን ለማየት ወደሆስፒታል ነዳሁ።

«የእኔ ኪዳን? አውቃለሁ ታጥበህ ልብስ ለመቀየር እንደቸኩልክ!! ለትንሽ ደቂቃ ሆስፒታል የሆነ ሰው ጠይቀን እንመለስ እና ደግሞም የምነግርህ ትልቅ ነገር አለ።» አልኩት በመንገዳችን።

«ምንድነው እሱ? የምነግርህ ትልቅ ነገር ስትዪ ሁሌም የሚከተለው ደስ የማይል ነው!! ምንድነው እሱ? ምን ልታደርጊ ነው? ደህና ነሽ አንቺኣ?»

«ኸረ ጭራሽ እንደሱ አይነት ነገር አይደለም!! እንደውም ደስ የሚል ነው መሰለኝ! ቢያንስ በግማሽ!»

ጎንጥ የተኛበት ክፍል ስንገባ ትንፋሹን ሰብስቦ የሆነ መርዶ እየጠበቀ ያለ ይመስል ነበር። ከሆዱ ድረስ ትንፋሹን ስቦ በረጅሙ የመገላገል ዓይነት ተነፈሰ እና ፈገግ አለ።

«ነፍሴን እኮ አወክሻት ዓለሜ? ከቤቱ ወጣች ካሉኝ ቆየ!! ስትዘገዪ ከመንገድ ምን አገኘሽ ብዬ ነፍሴ ከስጋዬ ልትለይ?» አለ የመጨረሻውን ዓረፍተ ነገር መልስ ባልጠበቀ ጥያቄ ዓይነት አስረዝሞ!! ማለት የፈለግኩት የነበረው <ልቤንኮ በረደኝ! እጄን ያዘኝ! ጦሽ ብዬ ላልቅስና! ኸረ በመድሃንያለም ነፍሴን አታስጨንቂያት! እያልክ አባብለኝ!> ነው። ያልኩት ግን «የኪዳንን ሻንጣ ልናመጣ በዛው ሄድን! ይቅርታ ቢያንስ መልዕክት እንኳን መላክ ነበረብኝ!»

ኪዳን አንዴ እኔን አንዴ እሱን <እየሆነ ያለውን ነገር አንዳችሁ ትነግሩኝ> በሚል አስተያየት ያየናል።

ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
1.3K viewsTsiyon Beyene, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 11:39:09 «ብዙ ጠበቅኩሽኮ ሜል! አንድም ሶሻል ሚዲያ አካውንትሽ አክቲቭ አይደለም!! ካንቺ ሳልሰማ ብዙ የቆየሁበት ቀን 12 ቀን ነው መጀመሪያ የታሰርሽ ጊዜ!! ቢያንስ እንዳላስብ በሰው ትልኪብኝ ነበርኮ!! ቢቸግረኝ መልዕክት ላኩልሽኮ (ትዝ አለኝ! ቁጥሩ ከማይታይ ላኪ ላመስግን ወይስ ልፀልይ? የሚል መልዕክት ስልኬ ነበረው! ስላልገባኝ እንጂ!! ምንም ቢፈጠር የምደውልለት እኔ ነኝ እንጂ እሱ እንዳይደውል ህግ አለን!! ስልኩን በቃሌ ነው የማውቀው እንጂ ሴቭ አላደርገውም!!)

…… በእኔ አስችሎሽ በጤናሽ ሁለት ወር እንደማትቆዪ አውቃለሁ። እኔስ አንቺን ባጣ ሰው እንደማልሆን አታውቂም? ከዛ በላይ መጠበቅ አልችልም ነበር ትኬቴን ቆርጬ መጣሁ!! የያዝኩትን ሻንጣ የያዝኩት ሆቴል ክፍል ወርውሬ ልብሴን እንኳን ሳልቀይር ማንን መጠየቅ እንደነበረብኝ እርግጠኛ ስላልነበርኩ እቤት መሄዱ አደገኛ ሊሆን ስለሚችል ብዬ ክለቡጋ ሄድኩ!! መምጣቴንም እዛ መሆኔንም ማን እንደነገራቸው አላውቅም!! ከዛ ወጥቼ ታክሲ ልይዝ ስጠብቅ መጥተው በመኪናቸው ከበቡኝ!!»

«ቆይ ቆይ ቆይ (ከእቅፉ ወጣሁ!) ክለብ ማንን አገኘህ? ማንን አናገርክ? ስንት ሰዓት ነው የሄድከውስ?»

«አመሻሽ ነገር 11 ወይ 12 ሰዓት ገደማ!! ብዙ ሰው ነበርኮ እኔእንጃ!» አለኝ ግራ እየገባው።

«ከበር ጀምሮ ያናገርከውን ሰው አንድ በአንድ ንገረኝ!! ለማስታወስ ሞክር!» እያልኩት መኪናውን አስነስቼ መንዳት ጀመርኩ።

«ጋርዶቹን? መግባት አይቻልም ሰዓት ገና ነው ብለው እንቢ አሉኝ መጀመሪያ እ ….. ከዛ አንቺን ፈልጌ እንደሆነ ከካናዳ የተላከ ዕቃ ላደርስ እንደሆነ ነገርኳቸው እና ከውስጥ የሆነ ሰው ጠርተው አገናኙኝ። ከዛ ለእነርሱ የነገርኳቸውን ስነግረው ሄደሽ እንደማታውቂ …. አንድ ቀን ብቅ ብለሽ እንደነበር ነገረኝ። የግድ ማድረስ ያለብኝ እቃ አለ ስለው እሱም ገብቶ ዳዊት የሚባል ሰው ጠራልኝ። ፍቅረኛሽ መሆኑን ነገረኝ (እዚህጋ የአይመስለኝም ሽርደዳ ያለበት ፈገግታ ፈገግ ብሎ በቁም ነገር የሚያወራውን እየተከታተልኩ እንደሆነ ሲያውቅ ወደ ቁምነገሩ ተመለሰ።) እሱ ወደ ውስጥ እንድገባ ጋበዘኝ እና ከዛ በቃ ያልታወቀ ሰው በሽጉጥ መትቶሽ እንደነበር ከዛም ድጋሚ ከሰዎች ጋር ተጣልተሽ እስከሆስፒታል የሚያደርስ ጉዳት ደርሶብሽ እንደነበር እና እቤት እንደማገኝሽ ነገረኝ።»

« ከኤርፖርት ሆቴልህ? ከሆቴልህ ክለብ? በመሃል የሄድክበት ቦታ አለ? አስታውስ? ያናገርከው ሰው? ሁለቴ የገጠመህ ሰው?»

«ሜል? እኔን ታውቂኝ የለ? ጀርባዬን እያየሁ የምሄድ ሰውኮ አይደለሁም!! ግን ማንንም አላገኘሁም!! ከዛ ውጪ የትም አልሄድኩም! ያናገረኝም ያናገርኩትም ሰው የለም ከሪሴፕሽኖቹ ውጪ!!» አለኝ ተጨንቆ

«ክለብ ውስጥ ሌላ ማን ነበር?»
«የሚሰሩ ሰዎች ነበሩ!! ቤቱን እያስተካከሉ ምናምን የነበሩ እኔ እንጃ በደንብ አላስተዋልኩም ግን ሴቶችም ነበሩ!!»

«ስምህን የነገርከው ወይም የእኔ ወንድም መሆንህን የነገርከው ሰው አለ?»
«ለዳዊት! ስሜን ነግሬዋለሁ ግን ያንቺ ወንድም መሆኔን አልነገርኩትም!! ዳዊት እባላለሁ ሲለኝ ኪዳን! ብዬዋለሁ!!»

«ምን ያህል ይሆናል ውስጥ የቆየኸው?»
«እኔ እንጃ አንድ ሰዓት!! የሚጠጣ ጋብዞኝ አንድ አንድ ብርጭቆ ይዘን ነው የሆነውን የነገረኝ!! ይኸው ጀመረሽ ነገር ስትቀምሪ መሃል ቤት እኔን የምታጦዥኝ ነገርሽ!»

«ጥርጣሬ እንጂ ያረጋገጥኩት ነገር ስለሌለ ልነግርህ አልችልምኮ ኪዳንዬ! መጠጡን የጋበዘህ እሱ ነው? አልጠጣም ብለኸው ነበር? እንድትጠጣ ወተዋተህ?»

«አይ እውነትም ፍቅረኛሽ ነበር በሚገባ ነው የምታውቂው!! አዎ አልጠጣም እቸኩላለሁ ስለው። <እዚህ ድረስ መጥተህ ሳላስተናግድህ መሄድህን ሜሉ ብትሰማ ትቀየመኛለች፤ አንድ ብርጭቆ ይዘን የሆነውን ላውራህ አለኝ!!»

«ይሄ የውሻ ልጅ!! እውነት ባይሆን ነው የሚሻለው እንጂ አልለቀውም! (ይሄ ጤነኛ ንዴት ይሆን አልገባኝም! ጭንቅላቴ ከውስጥ የተወጠረ አይነት ስሜት ነው የሚሰማኝ የሆነ ሊፈነዳ የቀረበ ነገር። ደረቴ ላይ እልህ እና ቁጣ ከትንፋሼ ጋር እኔ ልውጣ እኔ ልቅደም ግብ ግብ የገጠሙ አይነት ስሜት) ይሄ ሙት እሱም ሰው ሆኖ መሆኑ ነው?» ኪዳን እየሆነ ያለው ግራ ገብቶት

«ሜል? እሱ ደውሎላቸው ነው የመጡት ብለሽ ነው የምታስቢው? ከአጠገቤኮ ለአፍታም ዞር አላለም ነበር። ኸረ በፍፁም እንዲህ የሚያደርግ ሰው አይመስልም! ግማሹን ሰዓትኮ እንዴት እንደሚወድሽ ነው ሲነግረኝ የነበረው። ደግሞ ፍቅሩ አይኑ ላይ ያስታውቃል። ምንም ከማድረግሽ በፊት አጣሪ እህትዬ በእኔ ሞት? እ?»

«ሌባ አይኑ እና ቅቤ ምላሱ አይሸውድህ!! በእርግብ ላባ ያጌጠ እባብ ነው!! ታውቀኛለህ ደግሞ ባልተረጋገጠ ነገር ምንም አላደርግም!!» እያልኩት ስልኬን አውጥቼ ደወልኩ!!

«ሻለቃ! ሜላት ነኝ!!»
«ሜላት ሜላት?»
«አውቀኸኛል ባክህ! እንዴት አስታውሳ ደወለች ብለህ ከሆነ ግራ የተጋባኸው አዎ አስታውሼ ነው!! አደጋ የደረሰብኝ ቀን ለኤግዝቢትነት በሚል የወሰዳችሁትን ስልኬን መረጃውን ከውስጡ አፅድታችሁ እንደመለሳችሁልኝም ጭምር ነው ያስታወስኩት! ለሶስተኛ ወገን አሳልፋችሁ ሰጥታችሁ ማለቴ ሸጣችሁ የግሌን መረጃ እንደነገዳችሁበትም ጭምር!! ልቀጥል?»

«ምን እንደምታወሪ ታውቂዋለሽ? ወይስ ጥይቱ ሚሞሪሽን ብቻ ሳይሆን ማሰቢያሽንም ነው የወሰደው?»

«ምን እንደማወራ አሳምረህ ታውቃለህ!! ፌስቡኬ የእኔ መሆኑን ሰይጣን እንኳን አይደርስበትም። ድንገት እኔ በተመታሁ በነጋታው 10 ዓመት ሙሉ ማን መሆኔ ሳይታወቅ የተጠቀምኩበት አካውንት በአስማት ታወቀና ዘጉት ነው የምትለኝ ያለኸው? ኦው ለምን ስልኬን እንደሚፈልጉት አልነገሩህም ማለት ነው?» ዝም አለ ለአፍታ

«የውልህ! በጣም በተቻለኝ አቅም ጥሩ ሴት ልሆን እየሞከርኩ ያለሁበት ሰዓት ላይ በመሆኑ ፈጣሪህን አመስግን!! ከናንተ ጋር አውጫጭኝ የምጫወትበት ጊዜ የለኝም!! አንድ መረጃ ብቻ ነው የምፈልገው!! የመታኝን ሰው ማወቅ ነው የምፈልገው!! መሃል ከተማ ነው! አመለጠ ምናምን በሚል ተረት ተረት እኔን አትሸውደኝም!! ግማሽ መንገድ ላግዝህ?  ጥቁር ጃጓር መኪና የጎማው ቸርኬ ወርቅማ ፣ ከኋላው መስታወት በቀኝ በኩል ጠርዝ ላይ ትንሽዬ ቀይ ስቲከር ያለበት፣ ታርጋ ቁጥሩ የመጨረሻ ሁለት ቁጥር 52 ነው!! እኔ ሁለት ጥይት መትቶኝ ይሄን ሁሉ መረጃ ስቶር ማድረግ ከቻልኩ ምርመራውን የያዘው ወይም ይዞ የለቀቀው ባልደረባህ በአንድ ሰዓት ውስጥ ሙሉ መረጃውን ጠረጴዛህ ላይ ማኖር አይቸግረውም!! ሌላው ደግሞ ሴት ናት!! ወንድ ለመምሰል የሞከረች ሴት ናት!! መኪናው በማን ስም እንደተመዘገበ እና ሴትየዋ ማን እንደሆነች ብቻ ነው ማወቅ የምፈልገው። ከአንድ ሰዓት በኋላ እደውልልሃለሁ! ከዛ ቀድመህ አሁንም ቢሆን የምትነግረኝ ነገር ካለህ ግን ዝግጁ ነኝ!!» ዝም አለኝ። ስልኩን ዘጋሁት!! እና ወደኪዳን ዞሬ

«ያረፍክበት ሆቴል ደውል እና ሻንጣህን መውሰድ እንደምትችል አረጋግጥ!! የምታርፍበት ሌላ ቦታ እንፈልጋለን። ለጊዜው እኔም ወደቤት መሄድ ያለብኝ አይመስለኝም!!»


«በእንዲህ ዓይነት ሰዓትኮ ሌላ የማላውቃት ሴት ነው የምትሆኝብኝ!! ውስጥሽ ሁለት ሴት ያለች ነው የሚመስለኝ! የእኔ ሜል እና የሌላ ሰው ሜላት! የእኔዋ እናት፣ እህት፣ ስስ ፣ የምታለቅስ ፣ የምታቅፍ ፣ የምታባብል ፣ ቀድማኝ የምትሞትልኝ …….. ያችኛዋ አያድርስ ነው!! » አለ ኪዳን በመገረም ሲያየኝ ቆይቶ!!
996 viewsTsiyon Beyene, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 11:39:09 #የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ሀያ ሶስት)
(ሜሪ ፈለቀ)


ኪዳን የመጠጥ ውሃ የሞላው ብርጭቆ ይዞ ወደሳሎን ብቅ ሲል ልቤ ወደቦታዋ ተመለሰች። እዚህ ድረስ ያለውን በድል ተወጥቼዋለሁ!! ብርጭቆውን ተቀብዬው ለደሳለኝ ከወገቤ ጎንበስ ብዬ በሁለት እጄ ሳቀብለው ጭራሽ የሚያወራው ተወነባበደበት። ጋዜጠኛው በሚሆነው ትርምስ ትዕግስቱ ነው ያለቀው። ኪዳን እየሆነ ያለው ነገር ግር ብሎት አይኑን ከወድያ ወዲህ ያንቀዋልላል። ወደጆሮው ጠጋ ብዬ «አምላክን በልመና አታድክም!! » አልኩት እና ጠቀስኩት።  ፈገግ ብሎ ደረቱን እንደመንፋት አድርጎ ጎምለል እያየ ዙሪያውን መቃኘት ጀመረ። አተኩሮ ላየው የሆነ ቁራጭ የፊልም ትወና እየከወነ ነው የሚመስለው። ሁሌም እንዲህ ነው! ከልጅነታችን ጀምሮ ከልጆች ጋር ተደባድቤ እኔ ከሆንኩ ያሸነፍኩት የፀቡ መሃል ሜዳ ይገባና ደረቱን ነፍቶ ይንቀባረራል። «ማን መሰለችህ? የእኔ እህት እኮ ናት!!» ይላል እየተጀነነ።

•  * * * * * * * * * * * * *

ድሮ ልጅ እያለን አባቴ እናቴ ላይ ሙድ የሚይዝበት መላው ነበር አሁን እኔ እና ኪዳን የምንግባባበት ኮድ። እናቴ ብር እጇ ላይ ቢኖርም ባይኖርም አለኝ አትለውም!! ብር ጨርሰሻል ወይ ብሎ ቀጥታ ከጠየቃት መልሷ ሁሌም አዎን ነው። በአቋራጭ ነው የሚያጣራው

«አስካል እንደው ከአባወራዎቹ ልደብለቅበት እስኪ መቀነትሽን ፈትሽልኝ!» ይላታል

«አይ እንግዲህ እንኳን ላንተ አምቡላህን መጋቻ ለልጆቼም የሚቀምሱትን ማሰናዳበት አልሞላልኝ» ትለዋለች

«ውይ በሞትኩት እናቴን! አያ ተካን አበድረኝ ልበለው ይሆን? እንደው ቸሩ መድሃንያለም ለልጆቼ የምሰጠው አታሳጣኝ» ይላል ወደላይ እንደማንጋጠጥ ብሎ በአንድ አይኑ እሷን አጮልቆ እያየ እና እያስተዛዘነ (ልበደራቸው የሚላቸው ሰዎች ስም ይቀያየራል)

«አይ እንግዲህ አምላክን በልመና ማድከም ደግም አይደል!! የምንችለውን እናደራርግና በተረፈው ማመስገን ነው። ያመሰገንነው አምላክ የጎደለውን ይሞላል!» ትለዋለች ልትወጣ ነጠላዋን እላይዋ ላይ እያደረገች። አለኝም እንዳትለው ለእሱ መጠጫ መስጠት አትፈልግም። የለኝም እንዳትለው ባሏ የሰው ፊት ሊያይባት ሲሆን በዘዴ አድበስብሳ! አባቴ እሷ ዞር ስትል ጠብቆ እየሳቀ

«እም! መች አጣኋት እናታችሁን? አላት ማለት ነው! አሁን ዘንቢል ሙሉ ሸምታ ትመጣ የለ? ምንአለ በሉኝ!» ይላል። እንዳለውም ከገበያ መዓት ነገር ሸማምታ ስትመጣ አባቴ ያላትን አንነግራትም ተያይዘን እንስቃለን!!

የእውነትም እጇ ላይ ብር ከሌላት መልሷ ይለያል። የአባዬ ጥያቄ ስሞቹንና አጠያየቁን ቀይሮ ያው ነው። የመጨረሻው <ለልጆቼ የምሰጠው አታሳጣኝ> የሚልበት ጋር ሲደርስ

«እንግዲህ አንድዬ ያውቃል!! እርሱ የከፈተውን ጉሮሮ ሳይዘጋው አያድር!!» ካለች አባቴ አሁንም እሷ ዞር ስትል ጠብቆ

«አሁን የእውነቷን ነው የላትም ማለት ነው!!» ብሎ ከኛ ፊቱን አዙሮ ብር ይቆጥር እና « ገበያ ውረጅበት ብሎሻል! ብላችሁ ስጧት» ብሎ ለአንዳችን ያቀብለናል። ለምን እራሱ እንደማይሰጣት አሁንም ድረስ አይገባኝም!! ምናልባት ለእኛ ማስተማር የፈለገው ነገር ይኖር ይሆን ነበር። ሁሌም መልሷ እንዲሁ ነው። ሁሌም የእርሱ አጠያየቅ ተመሳሳይ ይዘት ያለው ነው። ገና እሱ ሲጠይቃት በተለይ እኔ ሳቄ ይመጣል። ለእማዬ <እየፈተነሽ ነው!> አልላትም!! ለትንሿ ልቤ የእነርሱ የፍቅር ቋንቋቸው መሆኑ ገብቷት ነው መሰለኝ በተለይ የሌላት ጊዜ እሱ ሲያዝንላት ልቤ በሙቀት ቅልጥ ትላለች።

ከኪዳን ጋር ልጆች ሆነን እናታችንን የምናስታውስበት አንዱ ጨዋታችን ነበር። አድገን የህይወት ውጥንቅጥ ውስጥ የተነከርን ጊዜ ደግሞ ምልክት መሰጣጫችን ሆነ። ያለንበት ሁኔታ ተስፋ ያለው፣ መውጫ ያለው ፣ ደህንነታችን ጥሩ ሁኔታ ላይ ከሆነ። «አምላክን በልመና አታድክሚ….. » የምትለዋ! ለምሳሌ ባለፈው ኪዳን እንዳለኝ « ደህና ነኝ አታስቢ! አልጎዱኝም!! ተረጋግተሽ መላውን ፈልጊ!»  እንደማለት ነው!! ወይም ደግሞ « አንድዬ ያውቃል» ብዬ መልዕክት ካደረስኩት «እንዳትደውልልኝ፣ በምንም መንገድ ልታገኘን አትሞክር! ያለሁበት ሁኔታ ሲሪየስ ነው!!» እንደማለት ነው። እንደገባንበት ማጥ መልእክቱ ይለያያል። እኔ እና እሱ እንግባባበታለን!! በደፈናው ያለንበትን ሁኔታ አስከፊነት የምንለዋወጥበት ነው።

•                   
•  * * * * * * * * *

ጋዜጠኛው ከዚህ በኋላ ላይቭ እንዳለ ሊቆይ የሚችለው ከ2 ደቂቃ አይበልጥም!! እንደየትም ብሎ ቢያራዝምልኝ ሊጨምርልኝ የሚችለው 1 ደቂቃ ነው። በዛ 2 ደቂቃ ደግሞ መኪናችን ጋር መድረስ አለብን። ለጋዜጠኛው ተጨማሪ ደቂቃ ማስረዘም ከቻለ ምልክት ሰጠሁት። ትከሻውን ሰበቀ። እሞክራለሁ እንደማለት ነገር።

«አንቺ እስከበሩ ትሸኝናለሽ እኮ!!» አልኳት ሚስትየውን። ባሏ አፉ እዛ ይለፍልፍ እንጂ አይኑም ቀልቡም እኛጋ ነው። ባይገባትም እየመራችን ወጣች። በፍጥነት ወደአጥሩ በር እየተጓዝኩ

«ልትከተሉኝ ብታስቡ! መንገዴ ላይ የሆነ ነገር ልትፈጥሩ ብትሞክሩ ውርድ ከራሴ!! ወጥተሽ ጋዜጠኞቹ መኪና ውስጥ ገብተሽ ማረጋገጥ ትችያለሽ!! አሁን ላይቭ እየተላለፈ ያለው የባልሽ ቃለመጠይቅ ብቻ ነው። አንዲት ዝንፍ ያለች ነገር አደርጋለሁ ብላችሁ ብትሞክሩ እዛ መኪና ውስጥ ያሉት ባለሞያዎች አንድ በተን ብቻ ነው መጫን የሚጠበቅባቸው። ቤትሽ እያንዳንዱ ክፍል ካሜራ አስቀምጫለሁ!! እየሆነ ያለው ነገር አሁን እኔና አንቺ የምናወራውም ምስል ሳይቀር ሪከርድድ ነው። መኪናዬ በስህተት ጎማዋ ቢቀንስ አልኩሽ ሁሉንም ምስል ገጣጥሞ ዜና ማዋቀር አይከብድምኣ? ቻው! መልካም እድል በይልኝ ባልሽን!! እም ጷ» በእጄ የመሳም ምልክት አሳይቻት ራሷ ለዘበኞቹ እንዲያሳልፉኝ ምልክት ሰጠቻቸው እና እኛ ስንወጣ

«ቱ » ብላ በንዴት እና በጥላቻ ምራቋን ስትተፋ እሰማታለሁ። እኔና ኪዳን በሩጫ መኪናችን ውስጥ ስንገባ ጋዜጠኛው የላይቭ ስርጭቱን ጨርሷል። ከአካባቢው እስክርቅ ድረስ በማይነዳ ፍጥነት እየነዳሁ ምንም ቃል ሳልተነፍስ ሸመጠጥኩት። ብዙ እርቀን እንኳን እንዳልተረጋጋሁ ያወቅኩት ኪዳን

«ሜል በፍፁም እዚህ ድረስ ሊከተሉሽ አይችሉምኮ!» ሲለኝ ነው።

«አይችሉም ብሎ ተዘናግቶ ወጥመዳቸው ውስጥ ከመውደቅ ሊሞክሩ ይችላሉ ብሎ መጠንቀቅ ነው የሚያዋጣው!! አታውቃቸውም እስከምን ጥግ መሄድ የሚያስችል ጭካኔ እንዳላቸው።» እጁን ሰዶ ትከሻዬን ዳሰስ ዳሰስ ሲያደርገኝ ዞሬ አየሁት። የናፍቆቴ መጠን እየሆኑ በነበሩት ክስተቶች ተከድኖ እንጂ ገደቡን የጣሰ እንደነበር የገባኝ ዓይኖቹን ሳያቸው ነው። መኪናዬን ጥጉን አስያዝኩት እና አቀፍኩት!!

«ለምን መጣህ? በዝህች ዓለም ያለኝ ብቸኛ ነገሬ አንተ መሆንህን አታውቅም? የሆነ ነገር ሆነህብኝስ ቢሆን? ሰው እንደማልሆን አታውቅም?» ቁጣም ፍቅርም እንባም ሳግም ያንቀረቅቡኝ ጀመር። ያውቀዋል ስስቴን!! ሁሌም እየተቆጣሁት ወይ እየጮህኩበት ሳለቅስ አይመልስልኝም። ስረጋጋ ነው ምክንያቱን የሚነግረኝ!!

«ይቅርታ ሜል! ይቅርታ እሺ!» አለኝ ከእኔ በላይ አጥብቆ አቅፎኝ እያባበለኝ!! መረጋጋቴን ሲያይ!!
1.1K viewsTsiyon Beyene, 08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 22:18:46 አምስት ጅራፌን ጀርባዬ ላይ ጠጥቼ ሌሊቱን ያሳለፍሁት በሆዴ ተኝቼ ሳቃስት ነው አንዲት ኢትዮጵያዊት በወለደች በሁለተኛ ቀኗ
“ኧረ ስለነፍስ! ወገቧ ያልጠና ትኩስ አራስ አትግረፏት የፍርዷ
ውሳኔ ለሌላ ጊዜ ይተላለፍላት ብንል የሚሰማን ጠፍቶ ከተፈረደባት ሃያ አምስት ጅራፍ ውስጥ አስራ ሰባቱ ብቻ አሰናበታት
ወንድዬ! በሷ ሞት ማንም ያዘነ የለም እሷም ለራሷ አላዘነችም ልጄን፥ልጄን … ብቻ እንዳለች ግልግል
ነው የሚባለውን ሞት ሞተች ልጅዋን አደራ ለማንም አልሰጠችም ሁላችንም አቅም የሌለን አደራ በላ ነን ጥሩ አደረገች  እንኳንም አደራ አላለችን አደራ ብትለን ኖሮ በመጨረሻዋ የመከራዋ መጀመሪያ ወይንም ማጠቃለያ አዝንባት ነበር
አብራን ኖራ እንዴት አቅማችንን ረሳችው' ብዬ እጠላት ነበር" ወንድማለም እምቦቀቅላዋ ከእኛ ከተገረፍነው ጋር ወህኒ ቤት ውስጥ ዐይኖቹ እንባ ተብሎ በጥቅል ስም  በሚጠራው ደም ተሞሉ" ዐይኑን ጨፍኖ: ደሙን አፍስሶ ንባቡን ቀጠለ።

ከተገረፍነው ጋር ስታለቅስ ዋለች ምርር ብለን ስናነባ
እሷም አብራን አነባች ከሁላችን ለቅሶ የዚያች ንፁህ ለቅሶ እንደ
ሬት መረረኝ እኛስ ባሳለፍነው ጥቂት ዓመታት የፈፀምነው ኃጢያት
ወይንም እርግማን ይኖርብን ይሆናል ይህች ሙጭቅላዋ ህፃን
ወንድዬ! እስኪ ምን አጠፋች? አንድ ጊዜ አንድ ፈረንሳዊ ደራሲ ያለው ትዝ አለኝ እግዜርን ማምለክና ካርታ ጨዋታ መጫወት
አንድ ነው ብሎ የፃፈው
እራስህን መድበህ ትጫወትና ከበላህ
እሰዬ ኪስህን በገንዘብ ትወጥራለህ ገንዘብ ደግሞ ኃይል ነው በራስህ እንድትተማመን እንድትኮፈስ ያደርግሃል እንደ ፅጌረዳ አበባ አይ ሲያምር ያሰኝሃል ሁሉ ወዳፍንጫው አስጠግቶ መዐዛህን ወደ ውስጥ እየሳበ ይረካብሃል ይክብሃል ይሽቆጠቆጥልሃል እንደ
በግ ገራም ሆኖ ይታከክሃል ጅራቱን እየቆላ ካንተ ያስቀድመኝ እያለ ይምልልሃል ሰው ብትበድል እንኳ የሳንቲም ሽርፍራፊ
ስለምትወረውር እሱ አፉ እንጂ ውስጡ የዋህ ነው እየተባልህ የሚማረርብህ የለም ከተበላህ ግን ያው ኪሎህ ስለሚቀንስ መሬቷ
እያንቀረቀበች ስታነፍስህ አንደበትህ ሁሉን ሲያበሳጭብህ
ሁሉ እንዳላዬ ፊቱን ሲያዞርብህ ውሾች ሊነክሱህ ሲጮሁ
በራስህ ከሌሎች ጋር ተባብረህ ኳስ አበደች እያልህ ስትጠልዘው
ህሊናህን እንደ ሽንኩርት እየላጥህ ስትጥለው ያንጊዜ እንደ አበቅ
የምትደፋበትን መፈለግ ነው እና! እግዚአብሔርን የምናመልከው
እንደ ካርታ ጨዋታው ብናተርፍ  ብለን ነው የገነትን ምቾት
ልንጎናፀፍ በለምለሙ መስክ ልንፈነጭ ካልሆነም ያው ሽ ቢታለብ በገሌ ለማለት እንጂ አንተ ወንድዬ እግዜር ካለ እውን
የረሃብና ጦርነት ምሳሌ እንዳደረገን ዘላለም ይኖራል? ዛሬ እንኳን
በቃችሁ አይለንም? ምሳሌው አይቀየርም?

"አንድ ጊዜ አዲሳባ እያለሁ አንተ አልነበርክም ብቸኝነት
እንደ ውርጭ ቤታችን ገብቶ
ገብቶ ሞላ.ውርጩ አጥንቴን ሲያኝከው ህቅ ብዬ አለቀስሁ በልጅነቴ ገነት ማለት የተዋበ
ልምላሜ የተሞላበት ይመስለኝ ነበር የኔ ጅል ከዚህ ውጭ ገነትን
የሚያስበው ማን አለ' አትበለኝ እንጂ" ገሃነም ግን አስጠሊታ ሆኖ ነበር የሚሰማኝ" ታዲያ የዛን ቀን ፀሐይ እንደ በዛበት ዋልካ መሬት ፊቴ የተሰነጣጠቀ እስኪመስለኝ ካለቀስሁ በሃዘን ኩምትርትሬ ከወጣ
በኋላ በኃሳቤ ወደ ሆነ ቦታ ተነጠቅሁ ገሃነም ውስጥ! ከማዶ ገነት አለ  እንዳሰብሁት ግን ሰፊ አልነበረም ጠባብ ነው ግን ያምራል እኔ ግን እንዲያ ዐይኔ እስኪፈርጥ  አልቅሼ: አልቅሼ የሄድሁት
ገሃነም ነው አይገርምም
ወንድማለም! ከዚያ የሚዘገንን ቆሻሻ ክምር ላይ በጭንቀት እንደቆምሁ ድንገት ትናንሽ አበቦች
ከትንሽነታቸው በስተቀር
ግን የሚያምሩ አየሁ
ወንድዬ! አሁን ሳስበው እነዚያ ትናንሽ አበቦች ተስፋ ናቸው ጥሩውን ብንመኝም
የምናገኘው ግን ያልተመኘነውን ነው ያልተመኘነው መጥፎ
ህይወት ላይ ግን ትንሽም ቢሆን የሚያምር ነገር አለ እና! እግዜርን ያን ትንሽ ነገር እንኳን አታሳጣኝ እያሉ መለመኑ አይሻልም ለዚህ
ለዚህ ወዲያ ውሰደው ብሎ ሐይሉ ዲካ የለውም ከሚባለው አምላክ ጋር
ከመጣላት ደግሞ
ነው!… ብሎ እንደ ጠረጴዛ
ኳስ ቢያድቦለቡለኝስ፣ መጫወቻ ሆኜ ተሰባብሬ  መቅረቴ አይደል!
ወንድማለም!- እግዜር ግን ምነው ዝምታው ይበዛል? እስኪ የእኛስ ይቅር ይህች
የዶሮ እግር የመሳሰሉ እግሮችዋን እጆችዋን
እያወናጨፈች እየተንቀጠቀጠች
በምታለቅሰው ጨቅላ ለምን
ጨከነባት? በናቷ ሃጢያት ይሆን? እሷማ አጠፋሽ” ለተባለችው ቅጣቷን ተቀብላ  አስራ ሰባት ጅራፏን ቀምሳ የለ! የቀራትን
ስምንት ጅራፍ በህፃኗ ላይ ለመጨረስ ካልሆነ? እዚህ የሚቀጣው እዛም ይቀጣ ይሆን! ወንድዬ ቢጨንቀኝ እኮ ነው መቀባጠሬ! ይልቅ
የሆነውን ልጨርስልህ

"ህፃኗ  ልቅሶዋ ሲቀጥል አንጀቴ አልችል  ብሎኝ  እኔም ከማለቅስበት እየተንፏቀኩ ሄጄ አቀፍኳት ትንሽ ናት ከአፍ የወደቀች ጥሬ የምታህል' እጅ እግር: ዐይን  ሁሉም የሰው ልጅ
ያለው አካል ሁሉ እጅግ ቢያንስም አላት ወደ ጡቴ አስጠግቼ እሹሩሩ
እያልሁ ልቅሶዬን ቀጠልሁ ትንሽዬ አፏን አሞጥሙጣ
የሚጠባ ነገር ፈለገች, እኔ ደግሞ ያለኝ ደም ነው የግርፋቱ" ካለነው
ውስጥ ካለደም ወተት ያለው ጡት አልነበረምህፃኗ እንደማልረዳት
ስታውቀው እሪታዋን ለቀቀችው ኣጀብናት
እኛም በር
በማይከፍተው ልቅሷችን ወተት በማይሆነው እንባችን: ክፍሉን
አጥለቀለቅነው በእንባ: በምሬት: ከዚያ ልረዳት ያልቻልኋትን
ህፃን ካነሳሁበት አንጋለልኋትና ተንፏቅቄ ራቅሁ ይኸውልህ! ከተኛሁበት ስነቃ ሁሉም የእስር ቤት ጓደኞቼ ተኝተዋል ወንድማለም!-
ሚሚም‥ ተስቤ ሄጄ አየኋት
እውነተኛውን እንቅልፍ አፏን
እንዳሞጠሞጠች
እንደ ራባት ...አንቀላፍታለች
ለምን ተፈጠረች?
ለምንስ እሷን ለመፍጠር ብዙ ተደከመ  ወንድዬ! ላትኖር ተሸክማ ዘጠኝ ወር ካለ አዛኝ: ካለ እረፍት
ስትማስን የኖረችው እናቷስ
ለምን በምጥ አቃሰተች? ለምን ደሟ ፈሰሰ: ለምንስ ነጭ ላብ አነባች?
አቤት የመከራችን ዓይነት ቢመዙት ቢመዙት መርዘሙ
እንደ ውቅያኖስ የተንጣለለው እንባችን ሐዘን በሸነቆረው አካላችን
ፈሶ ፈሶ አለማለቁ ... ወንድዬ! የጠዋት ቁርሴ በለቅሶ የተጣፈጠ ቅስም ሰባሪ ሀዘን ሆነ ..." አባቷ ስቅስቅ ብሎ አልቅሶ ማስታወሻዋን ከደነው" ከዚያ በላይ  ማንበብ አልቻለም ከዚያ በላይ
አልቻለም ከዚያ በላይ መቆም አልቻለም ከዚያ በላይ የመከራ ሬት መጠጣት አልቻለም! ዐይኖቹ ተጨፈኑ አካሉ ተጨመታተረ ደሙ ዐይኖቹን እንደ ቀይ ጃኖ እያለበሰ በጉንጮቹ ቁልቁል ተንኳለለ ግን ለምን? ልጆች እንዲህ
ከማይችሉት የመከራ
ውቅያኖስ በጮርቃ እድሜያቸው ይነከራሉ? እኮ ምን ጠፍቶ? ማነው የሚወቀሰው! የላይኛው ወይንስ የምድሮቹ ንጉሶች! የማይመለሰው ጥያቄ እንደ አቧራ እየተበተነ ከአየሩ ተደባለቀ!

ይቀጥላል
660 viewsአትሮኖስ, 19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 22:18:45 #የዘርሲዎች_ፍቅር


#ክፍል_አንድ


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ከእንቅልፉ ረፋዱ ላይ ነቃ ክፍሉ በብርሃን ተሞልቷል
እንደተጋደመ ማሰብ ጀመረ ተስፋ ያለው ነገር አልታየውም እዚች
አገር ከመኝታው ሲነቃ ፍንድቅድቅ የሚል የእናቱን ጡት የሚጠባ ህፃን ብቻ ነው" ሌላው ግን ህሊናውን እያከከ ምን ሰርቶ እንደሚበላ ያስባል፤ ምን ሰርቶ እንደሚኖር ያልማል ትንሹ በትልቁ ህሊና
ገብቶ መሞትን ይመኛል ሞት የሌለበትን አሸናፊነት ለማግኘት ይማስናል እና ከመኝታው ሲነሳ ጭንቀትንና ተስፋ መቁረጥን ያዛጋል

ምነው አገሬ ጭንጫ ምድር በሆነች ኖሮ ለፋን ለፋን
ምርት ግን ጠፋ ብለን እናመሃኝ ነበር ምነው ከርሰ-ምድሯ በደረቀ
ኖሮ ካለውሃ መቼስ ምን መስራት ይቻላል እንልም ነበር ካላት የከርሰ-ምድር ውሃ አስር ፐርሰንት እንኳ አለመጠቀሟን ባናውቅ
ምነው የሰው ኃይልስ ባልኖረ ምን ይደረግ
የአለንን ለመጠቀም
ሰው ያስፈልጋል እንልም ነበር የሰው ኃይል ባልኖረ ኖሮ ይህች አገር ግን ሁሉም  አላት  ልምላሜ ታሪክ ውበት እህ!.. የጭንቀታችን ምንጭ የሆነው ህምታ ከየት መጣ?" የእኛ ትውልድ የወሲብ  የጦርነት የዝርፊያ ፊልም ማየት በቃው? እኮ ምን አለፋን በፊልም የሌለንን እናያለን በፊልም የማንኖረውን እንኖራለን ..."  ብሎ ሲፈላሰፍ ቆይቶ
ከመኝታው አፈፍ ብሎ ተነሳና ወደ ተናኘ መኝታ ክፍል ሄደ  ተናኘ በጠዋቱ የለችም እሱ ግን ወደ አልጋዋ ተጠጋና ጠርዙ ላይ ቁጭ አለ ራስጌዋ ካለችው ትንሽ ኮመዲኖ ላይ የእለት ውሎዋን የምትፅፍበትን ማስታወሻ አየው" ላንሳው አላንሳው ከህሊናው ጋር
ተሟገተ እረፍ  እረፍና ተነስ! ህሊናው አዘዘው"

እንጃባህ! በልጄ …'

"ኦሆሆ! ጅል አትሁን  አንተ አባት ማስታወሻ ደግሞ
ምሥጢር ተቀባይና አስቀማጭ ነው" አንተን አያውቅም ለአንተም
አይታዘዝም ጌታው እሷ ናት ገላጯ ፀሐፊዋ  ልጅህ ናት
ለአንተ የሚሆነውን ከእሷ ጠይቅ ከእሷ ህሊና አንብብ

"ማንም ሰው ሊገልፀው የማይፈልግ የምሥጢር መቃብር ህሊናው ውስጥ አለ በሐዘን ብቻውን እንደ ጥጥ ተባዝቶ አስከፊ
መቃብሩን ተሸክሞ በፍርሃት እየራደ ከአፅም ጋር እየተፋጠጠ እጣ ፋንታው የሆነውን ዘግናኝ ህይወቱን የሚኖር አለ! ... የህሊና ውስጥ ሞት ሃዘንተኛ የማይጠይቅበት የመቃብር ሐውልት የማይታነፅበት
በየግላችን ያጣነውን መልካምም ሆነ መጥፎ የህይወት እጣ በሙሚ
ቀባብተን ሳይበሰብስ የምንቀብርበት ብቸኛው የመቃብር ሥፍራ
ህሊናችን ነው" ሁለተኛ የመቃብር ሥፍራ ደግሞ የግል ማስታወሻ
ነው" ማንም ሊያየው፥ ሊመራመርበት ሊጎበኘው ... አይችልም
ካለባለቤቱ በስተቀር ለሌላ ሰው ዝግ ነው  ስለዚህ ማስታወሻዋን
አትንካው ! በሃጢያት ደም ህሊናህን አትበክለው ...'
አያገባህም፤ ለልጄ ከኔ የበለጠ ምሥጢር ጠባቂ የላትም ይህን ሲያስብ ሰቀጠጠው፤

"እሽ ልጄ የራሷ የህይወት ምሥጢር ይኖራት ይሆናል
ማወቅም አይገባኝ ይሆናል ማስታወሻዋን ማንበቤም ትልቅ የህሊና ወቀሳ ያመጣል" ግን እሷን ደግሞ ማወቅ አለብኝ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ አስፈልጋታለሁ  አለሁልሽ የማልላትን ልጄን እውነተኛ
እሷነቷን በመጠየቅ አላገኘውም የማነበው ልቆጣጠራት አይደለም
ለዚያማ ህሊናዋ የት ሄዶ የምታነበው መጽሐፍ መች አንሷት እሳትና ውኃ
ለልጄ ማወቅ ያለባትን  ማሳወቅ የነበረብኝንም እሳትና ውኀ
አሳይቻታለሁ እንዴት እንደምትጠጣና እንደምታበስል ግን እያየች፥
እያነበበች እየሞከረች
ተማረች አባት ልጁን ዘለዓለም የሚያስተምር መምህር አይደለም ትምህርት አያቆምም አባትና የክፍል አስተማሪ ግን የማስተማሩ እድላቸው የሆነ ደረጃ ላይ ያቆማል ከዚያ መማማር በመጨረሻ ደግሞ ይማራሉ" እና!- ከልጄ የህይወት ፈተና ልማር ተወኝ" ብሎ ህሊናውን መንጭቆት
ማስታወሻዋን ከኮሞዲኖው ላይ አነሳው

ሰርቶ መብላት ምን ነውር አለው መሰደድስ ቢሆን
ወንድማለም! ከቸገረህ ምን ያሳፍራል? እውነቴን'ኮ ነው በሃብት ደልበዋል የተባሉትስ አሜሪካኖችና አውሮፓውያን ተሰደው ለአረብ አሽከር ሆነው ብራቸውን አፍሰው አገራቸው ይገቡ የለ ..." የሚለውን የራስ ማፅናኛ አባባል አንብቦ ሌላ ገፅ ገለጠ።

"ወንድማለም! ወገቤ እስኪቆረጥ ለሰዓታት ስማስን ቀኑ ነጉዶ
ለሊቱ ጭላጭ ሰዓት እየቀረው ነው ምስጋና የሌለበት ባዶ ህይወት!
“ለገንዘብሽ ነው ስትቆይ ያው መጥገብሽ አይቀርም ፀባይሽ ካላማረ ኮንትራትሽን ሰርዞ መተካት ነው ተሰልፎ ከሚለምነው አንዱን
እየተባልህ የዕቃ ክብር ተነፍጎህ በዘመናዊ ባርነት መኖር ወንድማለም ደከመኝ እባክህ ልተኛ! ልተኛ ማን አስተኝቶኝ ባለቤቷ እንቅልፍ ስታጣ የኔን መኝታ በር አንኳኩታ ቀስቅሳኝ
ተመልሳ መተኛት ልማዷ ነው" አንዳንዴ ሳስበው እኔ ሰራተኛዋ ብቻ ሳልሆን የእንቅልፍ ማስወሰጃ እንክብሏም ነኝ እላለሁ  በል
ለሁሉም ጎኔን ላሳርፈው ማለቱ ይሻለኛል የሚለውንም አንብቦ ሌላ
ገፅ ገለጠ።

"አይ ወንድማለም!  ይሄንስ እድሜ ልክህን ባታስበው
ይሻላል" ለአንተ እኔ ሁሌ ህፃን ነኝ አይደል?  ግንኮ ህፃን ከሆንኩ ሁለት አስርተ ዓመታት አለፉ ግን አንተ ስለጎረምሳነት ዘመንህ
ለምንድን ነው የማታወራው?  የምትወደድ ሰው ነበርህ?  ወይንስ
ጨካኝ: ዋሾ! ... ሁሉንም ሁን ለምን እንደሆንህ አላውቅምና ጭፍን
ያለ የተሳሳተ ፍርድ ሰጥቼ ልወቅስህ አልሻም ያ አይነት ፍርድ መስጠት ካቆምሁ ደግሞ ቀናት ተቆጠሩ።

"ወንድዬ! የጀመርሁትን ሳልነገርህ  ምን ዙሪያ ጥምጥም አዞረኝ? ማስታወሻዬን ነው አታነበው፤ግን ፈራሁህ ስፅፍ  እያሰብሁህ ነው" በዚህ ዓለም የምታምኝው?'
ብባል የለኝም
የምትቀርቢው? ከተባልሁ
ግን ወንድማለምን
ነው የምለው"ይከፋህ ይሆን? ይክፋህ እንጂ የምወድህ
ስለማላምንህ ስንት የደበቅሁህ ጉድ አለ መሰለህ አንተ መቼም እንደ
አባቴ ብትሆንም
ብዙ አባቶች ድፍን ፍቅርን የምትሻ ግብዝ አባት አትመስለኝም ሁሉም ልክ እንዳለው ታውቃለህ  አይደል?"

"ፍቅሬ አገረሼ ወንድዬ! አንድ ጊዜ በየሄድሁበት እያስነጠሰ የሚያሳጣ ፍቅር ይዞኝ ነበር" ያ የፍቅር ገጠመኝ አሁን ተረት ነው
የነ ጦጢትና አንበሳ ተረት የዓረብ ቤት እያፀዳሁ ግን ያ የተረት ስሜቴን ፏጨረው፤ አንዴ ይቆረጥመኛል ሌላ ጊዜ ይለበልበኛል እንደ ቁርጠት ቀስፎ አላስቆም አላስቀምጥ ይለኛል
ያንጠራራኛል እንደ ምጥ ገፍቶ ሲመጣ ደግሞ ሲቃ ነው፡ ውለጂው ነው
አንተ ወንድማለም! አሁን አሁን ሳስበው ከሱስ ነፃ ነኝ!' እያልሁ ስመፃደቅ ለካ ማፍረሻ የሌለው ሱስ ሱሰኛ ነኝ  እህህህ በሱስ መጠመድ ቢሉህ መጠመድ ነው ያውም በቅርብ ባላረከው
ወደፊትም በቅርቡ በማታገኘው ሱስ የሚፋጨው የስሜት ስለት
ህሊናህን ሲበሳሳው፤ እየወጠረ ሲያከረው ነፍስህ ረፍት አጣ ውጪ
ነፍስ ግቢ ነፍስ ብትሰቃይ ምን ይሰማህ ይሆን?" ፈገግ አለ ጥያቄዋ
አፈፍ አድርጎ ተሸክሞት ወደ ኋላው ከነፈ አልፎት ወደመጣው የወጣትነት ህይወት የልጁን ምስጢር ከዚያ በላይ አንብቦ ማወቅ
ግን አልፈለገም እሷ ግን ማስታወሻዋ ላይ ስሜቷን: ውጥረቷን ረሃቧን ጥማቷን ... ዘክዝካው ነበር"

"... ወንድማለም የአለሁት ወህኒ ቤት ነው ትናንት ሃያ
529 viewsአትሮኖስ, 19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 20:06:11 አቅራቢያው ስደርስ የጋዜጠኛው ቡድን እኩል ደረሰ። ስልኬ ላይ የማየውን እቤት ያሉት ካሜራዎች እይታ አቀበልኳቸው። እነርሱ በኮምፒውተር ፣ በተለያዩ ገመዶች ፣ ማይክራፎኖች  እና ሌሎች ነገሮች በሞላው የመኪናቸው ጀርባ የሚሰካካውን ሰካክተው ዝግጁ መሆናቸውን ሲነግሩኝ መኪናችንን የአጥር በሩጋ አስጠግተን አቁመን እኔ እና አንድ ማይክራፎን የያዘ ጋዜጠኛ እና ሌሎች ሁለት ካሜራ እና ካሜራ ረዳት ወርደን ስንጠጋ ጠባቂው የያዘውን መሳሪያ ወደፊት አስቀድሞ ወደእኛ ቀረበ።

«ጋዜጠኞች ነን!! ላይቭ ነው! አቶ ደሳለኝ ስለምርጫው ትንሽ እንዲሉልን ነው!» አለው አብሮኝ ያለው ጋዜጠኛ። ጠባቂው ምኑም አልተመቸውም። ለሌላኛው ጠባቂ መልዕክቱን ለአቶ ደሳለኝ እንዲያስተላልፍ ጮክ ብሎ ተናግሮ እኛን እንድንጠብቅ አዘዘን። ሌላኛው ጠባቂ ከደቂቃዎች በኋላ አቶ ደሳለኝን አስከትሎ ብቅ አለ።

«እኔ ከምንም ዓይነት ጋዜጠኛ ጋር ቀጠሮ አልያዝኩም!! ምን አይነት ጣጣ ነው! ሰው ማረፍ አይችልም? ደግሞ ይሄን ቤት ማን አሳያችሁ?» እያለ እየተነጫነጨ ቀና ሲል ከእኔ ጋር ተያየን። ሊቀየር ሲዳዳው አብሮኝ ያለው ጋዜጠኛ ለካሜራ ማኑ እንዲጀምር ምልክት ሰጠው። ቀጥሎም የቴሌቭዥን ጣቢያውን ፈቃድ እያቀበለው

« አቶ ደሳለኝ ላይቭ የኢትዮጵያ ህዝብ እየተከታተሎት ነው። በዚህ ምርጫ ለየት ባለ የምርጫ ቅስቀሳዎ የህዝብን ቀልብ የሳቡ ይመስላል። ወደ ውስጥ ገብተን አንድ ሁለት ነገር ቢሉን? » አለው። ግራ ተጋባ እና እየተወነባበደ ሳቅ አይሉት ስላቅ ያልለየለት ፈገግታ ፈገግ እያለ ወደውስጥ ጋበዘን። ይሄኔ ፅፌ አዘጋጅቼው የነበረውን መልዕክት ኪዳን ያለበትን ክፍል ጨምሮ ካሜራ የተገጠመባቸውን ክፍሎች ምስል ከሚያሳየው ምስልጋ ላኩለት። ስልኩ መልዕክት መቀበሉን ቢሰማም አላየውም።

«አቶ ደሳለኝ መልዕክቱ የሚያስፈልጎ መልዕክት ይመስለኛል።» አልኩት ጠጋ ብዬው። በጥፍሮቹ ቢቦጫጭረኝ ደስ እንደሚለው እያስታወቀበት የግዱን ፈገግ ብሎ ወደሳሎን እየመራን መልዕክቱን አነበበው።

« ቴሌቭዥንህን ክፈተው ካላመንከኝ ላይቭ ነህ!! ኪዳን ያለበት ክፍል ጨምሮ ኮሪደርህ እና ሳሎንህ በድብቅ ካሜራ እይታ ውስጥ ነው። የምስሉ መዳረሻ መቼም ይገባሃል የኢትዮጵያ ህዝብ አይን ነው። አርፈህ በቀጣፊ ምላስህ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያለህን ፍቅር እና ብትመረጥ የማታደርገውን የውሸት ቃልህን ላይቭ ዘብዝበህ የምርጫ ቅስቀሳህን ብታደርግ ይሻልሃል ወይስ ዜናውን ከምርጫ ቅስቀሳ ወደአፈና ወንጀል ብንቀይረው? ምርጫው ያንተ ነው!! ከጋዜጠኞቹ ጋር እያወራህ ወንድሜን ሳሎን አስመጣልኝ። ምንም ግርግር ሳንፈጥር ከጋዜጠኞቹ ቀደም ብዬ ውልቅ ብዬ እወጣልሃለሁ!! አይ ካልክ ግን እዚሁ ላይቭ ወንድሜን እንዳገትከው ከነምስሉ ለጋዜጠኛው ሹክ እለዋለሁ። እዛው ላይቭ ጮማ ዜና አይመስልህም? በዛ ላይ ያን የቪዲዮ ቅጂ እመርቅላቸዋለሁ።!!» እያነበበ ጋዜጠኛው ደጋግሞ ስሙን ይጠራዋል። አልሰማውም!! እንደመባነን ብሎ

«እ እ!! የሆነ ትንሽ አስቸኳይ መልዕክት ደርሶኝኮ እ!!» ተንተባተበ።
«አዝናለሁ መጥፎ ዜና ነው?» አለው ጋዜጠኛው።
«አይ እንደው ትንሽ ነገር ነው። እኔ የምልህ እና አሁን ይሄም ላይቭ እየተላለፈ ነው?» ብሎ የቴሌቭዥኑን ሪሞት አንስቶ እየከፈተ  የሆነች ተንኮል ያለበት አስተያየት ወደእኔ አየ። ልቤ በመጠኑም ቢሆን መደለቅ ጀመረ። ደቂቃ እንኳን ዝንፍ ያለ ክፍተት ከተፈጠረ ሰውየው እዛ ያለነውን በሙሉ ጭጭ አድርጎ የቀደመ እቅዱን ለማሳካት የጋዜጠኞቹ ብዛትም ማንነትም የሚያሳስበው ሰው አይደለም። ጋዜጠኛው ነውም አይደለምም ሳይለው (ምክንያቱም እስከዛ ደቂቃ ድረስ ላይቭ አልነበረም) ቀጠለ። በቴሌቭዥኑ ዜና የምታቀርበዋ ሴት ስለአቶ ደሳለኝ አውርታ ስታበቃ ባልደረባዋን ጋበዘችው። ጋዜጠኛው ጥያቄውን ቀጠለ። መልሱም መላ ቅጡ የጠፋበት ወሬ ከመሆኑ በተጨማሪ በተቀመጠበት ላብ ያጠምቀው ጀመር። እየተንተባተበ ጥቂት እንዳወራ ሚስትየው ብቅ እንዳለች እየሆነ ባለው ነገር ግራ ተጋብታ ፍሬን ያዘች። በሚቀባጥረው ወሬ መሃል ወደሚስቱ ዞሮ «እስቲ ኪዳንን የሚጠጣ ውሃ እንዲያመጣ አድርጊልኝ! ቡናም ሻይም ሳልላችሁ በሞቴ ለእናንተስ ምን ይምጣላችሁ?» አለው ጋዜጠኛውን! ጋዜጠኛው ቀጥታ በዜና መሃል እየተላለፈ ያለ ፕሮግራም ላይ መዘለባበዱ እያናደደው ግን በጨዋ ደንብ ቀጠለ።

«በእውነቱ አቶ ደሳለኝ በዚህ አጋጣሚ ሳይዘጋጁ የመጣንቦት ቢሆንም እንግዳ ተቀባይነትዎ እና ልግስናዎ አልተለየንም። ከልብ እናመሰግናለን!! ባልደረባዬ የቀሩትን ዜናዎች ለማቅረብ እየተጠባበቀች ስለሆነ ለህዝቤ ማለት አለብኝ የሚሉት መልዕክት ካለ እድሉን ልስጦት!! »

ጋዜጠኛውን በቅጡ የሰማው አይመስልም። ሚስቱ እንደጅብራ መገተሯ አሳስቦት በግንባሩ መልዕክት ሊያስተላልፍላት እየሞከረ ነው። እያመነታች ከሳሎኑ ስትወጣ ልቤ መደለቋን ቀጠለች። እሱም ለዚህ የፈረደበት የኢትዮጵያ ህዝብ ላቡንና ወሬውን በቲቪ ማስተላለፉን ቀጠለ። ኪዳን የመጠጥ ውሃ የሞላው ብርጭቆ ይዙ ወደሳሎን ብቅ ሲል ልቤ ወደቦታዋ ተመለሰች። እዚህ ድረስ ያለውን በድል ተወጥቼዋለሁ!!

.ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
1.4K viewsTsiyon Beyene, 17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ