Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163.71K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 39

2022-12-17 23:33:56
ፍቅር እስከ መቃብር

ዴርቶ ጋዳ

ዣንቶዣራ

ዝጎራ አንዲሁም የተለያዩ መጽሐፍትን በpdf ይፈልጋሉ? እንግዲያዉስ የፈለጉትን አማርጠዉ ያንብቡ

https://t.me/+UyfpV2SfvBJkNmVk
https://t.me/+UyfpV2SfvBJkNmVk
427 viewsENFALOT ° , 20:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 21:00:03 ዳመና ፈጥሮ ላይዋ ላይ እያዠ ዘላለም ልታነባ ነው በእሷ ያገኘውን ደስታ በእሷው መከራ ሊነጠቅ ነው"
ጋልታምቤ የጥጆችን በረት ሲከፍተው ጂናቸውን አቁመው እናታቸው ጉያ ገቡ እናቶቻቸው የልጆቻቸውን ሰውነት ላሱ፤ እሱ
ግን ለጎይቲ የሚያደርግላት የለም ከረሰሰው ስሜቱን … ራሱን ወደ ሰማይ ቀና ሲያደርግ ጎይቲን በጭጋጋማው ሰማይ አያት አንገቷን ደፍታ ስታነባ ከሰዎች በረት ወጥታ ወደ ጨለማ ስታዘግም ውበቷ
ውሃ አንዳጣ አበባ ሲጠወልግ አያት ያኔ ህይወቱ ጎመዘዘው
መኖሩ እንደእርጥብ ጌሾ መረረው፤ ልጁ አክ እንትፍ ተብላ ስትተፋ በእዝነ  ህሊናው አይቶ ተሸማቆ ዐይኖቹን ጨፈነ  ግን አልተኛም ግን አላንቀላፋም እረፍት አላገኘም ሳጉ ይሰማዋል … ምን ነበረበት ዐይንን መጨፈን ማለት መተኛት ሁሉንም መርሳት በሆነ!

ይቀጥላል
1.6K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 21:00:03 #የዘርሲዎች_ፍቅር


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


#ክፍል_አምስት


ካለወትሮው እያከታተለ የሚወርደው ዝናብ የሐመርን ምድር:
የወሮን መንደር የብርሃን ጥላ አልብሷታል" ሰማዩ ላይ በጨርቅ እንደተጠቀለለ ህፃን ዳመናው እየተገለባበጠ
ምርር ብሎ እየጮኸ
ብልጭታው በሁሉም አቅጣጫ ይፈነጣጠቃል

ከክቧ የሐመሮች ጎጆ የሚትጎለጎለው
ከሚጥመለመለው ጥቁር ዳመና ጋር እየተደባለቀ  ይጠፋል ፍየሎች በጎች ጥጆች ገና ከበረታቸው አልወጡም በከብቶች አንገት የተንጠለጠለው የኤሊ ድንጋይ ከብቶቹ በተንቀሳቀሱ ቁጥር
ቋቋ ቋቋ እያለ ይሰማል" መንደሯ ልብ ብለው ሲያዳምጧት ትንፋሽዋ እንደወትሮዋ ነው፤ ማነጠሱ፥ ጨዋታው፥ እንጉርጉሮው: ቀልዱ ወፍጮው፥ የወፎቹ ዝማሬ ሁሉም ከዘመናት በፊት
እንደተቃኘው ነው

የናት ጉያ ሙቀት የናፈቃቸው ሆዳቸውን የሞረሞራቸው ጥጆች ግን ከናታችን አራክቡን በሚል ሆድን በሚያላውስ ቅላፄ እ-
ም--ዋ … እም-ቡ-ዋ እያሉ የጌቶቻቸውን ጆሮና ቀልብ ለመሳብ ረሃብና ናፍቆታቸውን በለሆስታ ዜማ አለዝበው ያንጎራጉራሉ" ላሞች እንደሌሎች ከብቶች ማመንዠካቸውን አቁመው ፊታቸውን ወደ ጥጆቻቸው አዙረው ዐይናቸውን እያቁለጨለጩ: ሳጋቸውን እያሰሙ የጥጆችን ከለላ በአፍንጫቸው እያሸተቱና
እየነካኩ የናትነት አንጀታቸው ረፍት ነስቶ ያንሰፈስፋቸዋል አንተነህ ይመር ከምድጃው ጎን ካለችው ትንሽ መደብ ላይ
በቦርኮታው የቀኝ ጭኑን አስደግፎ፥ ጎኑን እሳቱን እያሞቀ እሱም
የማይሰማ ውስጡ ፈልቶ እዚያው ተኖ የሚቀረውን ሳጉን ራሱ ለራሱ ይሰማል
ባለቤቱ እሳቱን እየቆሰቆሰች ሻላው (ቆጡ) ላይ ባሰረችው ጠፍር የአንጠለጠለችውን እርጎ በቀኝ እጅዋ ወደ ፊትና ኋላ
ትንጣለች ቅቤ ለማውጣት ነጭና ጥቁር መልክ ያለው ቁርበት ከበስተ ኋላዋ ተነጥፏል ዳሚ ሰረቅ እያደረገች ስታየው ቆይታ

"ይእ! ምን ሆነሃል የኔ ጌታ?" አለችው
ቢጨንቃት" እሱ ግን ዝም አላት ዝም እየተነፈሰ ጭጭ

"ተቡኑ ልስጥህ?"
ጋልታምቤ መልስ ሳይሰጣት ውጭውን
አየው  በጠባቧ በር በግድግዳው ቀዳዳ አየሩ ክርስስ ያለ ነው  ቀዝቃዛ የሱም ልብ ቀዝቅዛለች
በሐመር ባህል የተጠየቀ ሁሉ ወዲያው የመመለስ ግዴታ የለበትም  አዋቂ አስተሳሰቡ የበሰለ ከመናገሩ በፊት ልቡን ዐይኑ ላይ ማውጣት አለበት በልቦናው የሚያይ ሐሳቡ ሚዛናዊ ሆነ ክፉና ደግ ለመለየት በቃ ሃላፊነት ለመቀበል ደረሰ ማለት ነው" ጋልታምቤም በዚህ መላ
የሚስቱን ጥያቄና ጭጋጋማውን ቀን በልቦናው አየው" ልቦናው ግን ምንም እንዲል አልፈቀደለትም
ዝምታ ደግሞ በራሱ ቋንቋ ነው ዝምታና ዐይን ዝምታና ጥርስ ዝምታና ዝም በአይነቱ የተለያዬ ትርጉም አላቸው በቢጫው በሬ ምድር  በሐመር።

ዳሚ የጋልታምቤን ዝምታና ዐይን አይታ የሚያሳስበው ነገር እንዳለ አውጥቶ ሊነግራት ግን እንዳልፈለገ ተረዳች ያን ጊዜ።

ይእ! ምን ሆነ? እንግዲ ተሱ ይምጣ'ንጂ እኔ ምናባቴ
ላርግለት ብላ እሷም ዝም አለች ዝም ተባባሉ እሱና እሷ እሱና እሱ: እሱና ተፈጥሮ ተዘጋጉ"

ጋልታምቤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሰረቅ አድርጎ አያት ልቧን ከንፈሯ ላይ ተቀምጦ አየው ፍርሃት ነፋ ልትት፤ ነፋ ልትት
ሲያደርገው ሲገፋፋው ሲያንቀጠቅጠው ሲያወዛውዘው ተመለከተው

ዳሚ ከበስተግራዋ ተሰካክተው ከተቀመጡት በጨሌ ያጌጠውን
ሾርቃ አንስታ ጠረግ ጠረግ በማድረግ ከተወዘተው እንስራ በቅል ጭልፋ ሸፈሮ ቡና ቀድታ አቀበለችው

ጋልታምቤ እግሩን አንፈራጦ ተቀበላትና ግራ ቀኝ ፊትና ኋላ ጎለል ጎለል አድርጎ አበረደው ከዚያ እፉት ብሎ ፕስስ አድርጎ አማተበ ሸፈሮ ቡና የቦርጆ ፍሬ ሽፋን ነው ደስታን ያመጣል ራስን ለማየት ከራስ ጋር ለመምከር የቆሸሸ ህሊናን
ፈውስን ለማጽዳት የሚፋጅ የሚያቃጥል ነገር ሲያጋጥም ነቅነቅ ወዝወዝ
እያደረጉ ለማብረድ ለማቀዝቀዝ ጥሩ ነው
ይህ ሐይል ያለው
ሸፈሮ የተወጠረውን ስሜት ሲያላላው፥ የታመቀ
የጋልታምቤን ትንፋሹን እያንቦለቦለ አስወጥቶ እሁ! አለ ዳሚ አየችው የደሙ
ዝውውር ተረጋግቶ ይሽከረከራል: ገፅታው ጠይቂኝ ይላል"

"ዛሬ ቀን ምን ሆነሃል?" ስትለው ትክ ብሎ አያትና ዐይኖቹን ከላይዋ ላይ አንስቶ  ከራሱ ጋር ሙግት ገጠመ" ይህች ሰው
ባትሰማው ይሻል ይሆን? ይህማ የማይቀር እዳዋ ነው ከሌላ ከምትሰማው እኔ ብነግራት አይሻልም አአይ ይቅርባት  ትጨነቃለች ችግሩ ደግሞ ወደሷ እየገሰገሰ ነው መከራዋን በቀስ እየደራረበች ብትሸከመው አይሻልም … ብሎ ፊቱን ወደ ዳሚ
መለሰው

"ዳሚ!"

"ዬ!" አለችው ዐይኖችዋን ከዐይኑ ነቅላ እሳት እሳቱን እያየች አይን አፋርነቷ
ትልቁ ውበቷ ነው" ሁሌም ሲጠራት ዐይኗ
ይንከራተትና የሆነ ቦታ ገብቶ ውሽቅ ይላል" የምታየው ግን እሱን ነው።

"ዳሚ!" አላት ደግሞ

"ዬ!" አለችው ድምጿን ከረር አድርጋ  እየሰማሁህ  ነው'
ለማለት።

"ያች ልጅ መንጠፏ ነው ይሆን?" አላት የሃሣብ ሸክሙን በጥሶ ላይዋ ላይ በትኖ ዳሚ ጥያቄውን  ስትሰማ ህሊናዋ አስደንጋጭ ነጎድጓድ ባረቀበት ክው ብላ ደነገጠች አልጮኸችም መልስም አልሰጠችም ውስጧ ግን ባንዴ ባዶ ሆነ ቀፎ ዐይኖችዋን እሳቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ተክላ ቆየች
ጥያቄው በቀፎው ሰውነቷ
እየተንጎዳጎደ ነዘራት አመማት እንደ ሚጥሚጣ ለበለባት ... እሳቱ
ላይ የተሰካው ዐይኗ ሙቀቱ እንዳቀለጠው ሁሉ በፈሳሽ ተሞላ በእንባ  በምሬት  የዐይኗ ኳስ ሲንቀሳቀስ ግን እንባዋ ፈሰሰ እንባዋን ንፍጧ ጠርቶት ቁልቁል ወረደ እንባዋ ንፍጧን ተከተለው አያት ጋልታምቤ እንደገና በዐይነ-ህሊናው ራሱን አየው፤ እንደ
ከስኬ ወንዝ ወደ ውስጡ የሚሰርገው እንባው ስለማይፈስ መውጫ
ስለሌለው የሰራ አካላቱ ላይ የእንባ ጎርፍ ተኝቶበታል"

"ሁለት ዓመት ሙሉ ይኸው ወልዳ ለመሳም አልታደለችም የሐመር ሽማግሎችም ተነጠፈች በሐመር ደንብ መሰረት ለከሎ ወይ ምትክ ይሰጠው ካለበለዚያም ጥሎሹ ይመለስ እያሉ ነው" አላትና
መሬቷን ተመለከታት ዳሚ የሚለውን አልሰማችውም  ከፊት ለፊቱ ተቀምጣ እሷ ግን የለችም አትንቀሳቀስም:

ጋልታምቤ  ከውስጥ የዳሚ ከውጭ የላሞች ሳግ ተሰማው የጥጆች ጥሪ የጎይቲ ሰቆቃ

መሀን ሴት በሐመር ልቧ እንደ አሮጌ ቅል የተጠረማመሰ ምስጥ እንዳነካከተው ግንድ ተስፋዋ ፍርክስክስ ያለ ከዚህ መከራዋ በተጨማሪም ቤተሰቧን የመጥፎ ቤተሰብ የምታሰኝ እሷ የመጣችበትን መንገድ ለሌላው ግን የምትከለክል
እርጉም ተብላ
ከማህበራዊው ቡድን ተነጥላ ተወርውራ የምትጣል የቤተሰቧን ጎጆ
በጨለማ የምትሸፍን ናት

"የፈራሁት ደረሰ! ብላ ዳሚ የእንባዋን ውታፍ ከፈተችው
ልቧን ነደለችው ሆን ብላ ያዳፈነችውን የጭንቀት እሳት እፍ አለችው የእንባ ፈሳሽ ያገኘው ስሜቷ እንደ ደረቀ ቅጠል በውስጧ
ሲንቀለቀል ናጣት አርገፈገፋት አስቃሰታት
ስለዚህ ጋልታምቤ ጭንቀቷን ተቀምጦ ማየት ሰቀጠጠው
ከተቀመጠበት ተነስቶ ጥጆችን ከእናታቸው ያራክባቸዋል ከጥቂት ደቂቃ በኋላ አንዱ ጠብቶ ሌላው
ሊያራክባቸው ወጣ ጥጆችን
አጥብቶ ጥጋብ ይሆንና የመለያየቱ ምልክት ድራሹ ጠፍቶ መላላስና
መቦረቅ ይመጣል አንተነህ ይመር ለጎይቲ ምኑን አጥብቶ ከጭንቀቷ
ይገላግላታል! አለኝታው፡ መስታዋቱ ደስታውን እንዳያይባት መከራ
1.4K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 20:48:50 «አዲስአበባ ከሄድን እዛ አንድ ቀን እንኳን እንድታድር አልፈልግም!! ሳይውል ሳያድር እንድትወጣልኝ ነው የምፈልገው ምን ያደርጉብኝ ይሆን ብዬ ማሰብ አልፈልም!!»

«አውቃለሁ!! ግን አንቺስ?»

«እኔ ምን? እኔ ራሴን መጠበቅ አያቅተኝም!!»

«ሜል ብዙ ነገር ተቀይሯል። ምን ያህል እንዳስተዋልሽው አላውቅም እንጂ አንቺም ራሱ ፍፁም ተቀይረሻል። ወደኋላ ተመልሰሽ ያለፈ ህይወትሽን መኖር የምትችዪ አይመስለኝም! እሱን ነው የምታስቢው? ምንድነው የምታስቢው?» አጠያየቁ የእኔ ኪዳን አይመስልም በጣም ተኮሳትሮ እንደታላቅ ነው የሚያወራው

«አላውቅም! ራሴ እንደተቀየርኩ አውቃለሁ ነገር ግን ያለፈውን ህይወቴን ሙሉ ለሙሉ ተፋትቼ መኖር እችል እንደሆነ አላውቅም! ምክንያቱም እኔ ብቻ እንጂ የተቀየርኩት በዙሪያዬ ያሉ ሰዎችም ሁኔታዎችም እንዳሉ ናቸው። የቱን ጥዬ የቱን ይዤ እንደምቀጥል አላውቅም!»

«ለምን ከሀገር መውጣትን አታስቢበትም? ሁሌ ጀርባሽን መጠበቅ ሳይኖርብሽ አዲስ ህይወት አዲስ ማንነት ትገነቢያለሽ!»

«እኔእንጃ የኔ ኪዳን!!»

«በጎንጥ ምክንያት ነው? የነገ አብሮነታችሁ ምን ሊሆን እንደሚችል ተነጋግራችኋል?»

«አይደለም! ስለነገም ያወራነው የለም! ስለምንም ያወራነው የለም!»

«ሜልዬ እስኪ ዛሬ እንደ ትንሹ ወንድምሽ ሳይሆን እንደ 31 ዓመት ትልቅ ሰው አውሪኝ! እንደምትዋደዱ ግልፅ ነው!! እኔ ሳውቅሽ ለማንም ሆነሽ የማታውቂውን ነው ለሱ እየሆንሽ ያለሽው! ማንንም ሰው ባላቀረብሽው ልክ ነው እሱን ያቀረብሽው! ወደፊትሽን ስታስቢ እሱ አለበት? ያወራችሁት አይኑር! አንቺ ምንድነው የምታስቢው?»

«እኔ እንጃ ኪዳንዬ የእውነቴን እኮ ነው እኔንጃ የምልህ!! ታውቃለህ እኔ ፍቅር አላውቅም!! ፀብ ቢሉኝ አውቃለሁ፣ በቀል ቢሉኝ አውቃለሁ ……. ፍቅር ግን አዲሴ ነው!! ስምጥ ብዬ ከዋኘሁ በኋላ ነውኮ እንደወደድኩት እንኳን የነቃሁት! ደግሞ እኔ ብቻ የማስበው ምን ይፈይዳል? እኔ ስላሰብኩህ ና ወደፊቴ ውስጥ ላካትህ ይባላል?»

«ጠይቂዋ!»

«ምን ብዬ?»

«ምንድነው ስለወደፊት የምታስበው? አብሮነታችን ምን ድረስ ነው የሚዘልቀው? ብለሽ ነዋ!»

«እህ እሱ አይደል እንዴ ወንዱ! ይሄን መጠየቅ ያለበት እሱ አይደለም? በግድ እየገፋፋሁት ቢመስልብኝስ?» ስለው ከቀናት በፊት ሲስቅ የሰማሁትን ሳቅ ሳቀ።

«አይመስልም ዓለሜ (ልክ ጎንጥ በሚልበት ለዛ) ዘመኑ ተቀይሯል!! ሴት ተንበርክካ አግባኝ የምትልበት ዘመን ላይ ነን!»

« ምንስ ፍቅር ብርቄ ቢሆን ጥንቅር ይላታል እንጂ ተንበርክኬማ አግባኝ አልለውም! ጭራሽ? ለተሸነፍኩትም መደበቅ ቢቻለኝ በዋጥኩት! እንቢ እያለኝ እያመለጠኝ እንጂ!!» ተሳሳቅን!!

በሚቀጥለው ቀን ኦንላይን ትኬቱን ቆርጦ አጎቴን ተሰናብተን (ስንብቱ በእንባ የታጀበ ነበር።) ወደ አዲስ አበባ መጣን!! የዛኑ ቀን በረራው ነበረ። ስንሰነባበት

«ሜል አስብበታለሁ በይኝ ከሀገር መውጣቱን?»

«አስብበታለሁ ሙት!!»

«ለዓለሜ እንደምትዪው <የእህቴን ልብ ብትሰብር ውርድ ከራሴ!! ጦርነት በራስህ ላይ እንዳወጅክ ቁጠረው አንላቀቅም!!> ብሎሃል በይልኝ። የምሬን ነው ንገሪው!»

«ሂድ አሁን አርፈህ!! እነግርልሃለሁ!!»

እሱን ሸኝቼው ስመለስ ህይወቴን ካቆምኩበት መቀጠል እንደማልችል ገባኝ። ቤቴ እንኳን ያለስጋት መሄድ እንደማልችል ሳውቅ መኪናውን መንገድ ዳር አቁሜ ውስጥ እንደተቀመጥኩ ብዙ ቆየሁ። የእውነት ምንድነው አሁን የማደርገው? እንደድሮው ባር ሄጄ ወገበ ቀጫጭን ሴቶች የቆመ ፖል ላይ ሲውረገረጉ ፣ ለፍዳዳ ሰካራሞች ለሀጫቸውን እያዝረከረኩ ብራቸውን ሲረጩ …. .፣ አቅላቸውን የሳቱ ሱሰኞች ሀሺሺን ከሺሻው እያደባለቁ ሲያጨሱ …… እያየሁ እየተዘዋወርኩ ብሉልኝ ፣ ጠጡልኝ ፣ አጭሱልኝ ፣ ተዝናኑልኝ እያልኩ ብሬን መምታት ይቻለኛል?

ከአንድ ሰዓት በላይ ከቆምኩ በኋላ የሆነኛው ገስት ሀውስ ይዤ ለዛሬ እርፍ ብዬ መተኛት ፈለግኩና ከዛ በፊት የጎንጥን ድምፅ መስማት ፈለግኩ። አንዱ ሱቅ ገብቼ ደወልኩ። ስልኩ ዝግ ነው። ገስትሀውስ ገብቼ ለማረፍ ሞከርኩ እና ተገላበጥኩ። ራሴን አሁንም ወጥቼ የሱቅ ስልክ ላይ ስደውል አገኘሁት። ዝግ ነው!! ተመልሼ ገብቼ ለጥ ብዬ አድራለሁ ያልኩትን ለሊት ስገላበጥ አደርኩ። ይሄኛው ስሜት ደስ አይልም!! ስልኩን ባይከፍተው የት ብዬ ነው የማገኘው? የድሮ ሚስቱ ቤት ሄጄ <እየገደልሽኝ ሳለ እግረመንገድሽን ጎኔ የት እንዳለ ብቻ ንገሪኝ> ነው የምላት? ደግሞ ለራሴ <ማታ አይደል ያዋራሁት? ይሄኔ ባትሪ ዘግቶበት ነው!> እላለሁ። ዛሬ እንደምመጣ እያወቀ ስልኩን የዘጋው ሊያገኘኝ ስላልፈለገ ቢሆንስ? ምን እየሆንኩ ነው ስንት ሀሳብ እያለብኝ ስለእርሱ ብቻ የማስበው? ……. ስወራጭ ቆይቼ ሊነጋ ሲቃረብ እንቅልፍ ወሰደኝ!!

እንደነቃሁ ተጣጥቤ ስልኩን ሞከርኩ። አሁንም ዝግ ነው። ወደሰፈሬ ነዳሁ እና ተናኜን ቅያሪ ልብሶች ተቀብያት ጎንጥ ብቅ ብሎ እንደው ስጠይቃት አለመምጣቱን ነገረችኝ። ልብሴን እዛው መኪና ውስጥ ቀይሬ ሻለቃው ቢሮ ሄድኩ። የሰዎቹን ፎቶ ከተገበያየሁ በኋላ እንደማላውቃቸው ሳውቅ መረጃ የሚያቀብለኝ ሰው ጋር ደወልኩ።

«ኢሜል የማደርግልህን ፎቶ ተመልከተውና መረጃ አቀብለኝ» ካልኩት በኋላ የሁለቱን ሰዎች ፎቶ እየላኩለት ልክ እንዳልሆነ የማውቀው ሀሳብ ጭንቅላቴን ወጠረኝ። ላለማድረግ ከራሴ ጋር ታገልኩ። ግን አቃተኝ!! ከስልኬ ውስጥ ጎንጥን ስቀጥረው ይዤው የነበረውን ፎቶ አብሬ ላኩለት። መልሶ ደወለልኝ እና

«ይሄን ሰውዬኮ ከዚህ በፊት ጠይቀሽኝ ነበር።»

«አውቃለሁ!! ተጨማሪ መረጃ ፈልግ!! በጓሮ ሂድ!» አልኩት (ሰውየው በግልፅ ከተመዘገበው መረጃ በላይ የተደበቀ መረጃ አለው ለማለት ነው በጓሮ ሂድ የምንባባለው)

ስልኩን ዘግቼው ኮምፒውተር ቤቱ ውስጥ ፍዝዝ ብዬ ቀረሁ!!!


ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
1.4K viewsTsiyon Beyene, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 20:48:50 #የመኖር አካፋይ ፣ የመሞት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ሀያ ስድስት)
(ሜሪ ፈለቀ)

የእማዬ ቀብር ላይ የአባቴ ገዳዮች ዘመድ አዝማድ እና ልጆች ሁሉ ሊቀብሯት ሲያጅቧት ፤ አንዳንዱም ሲያለቅሱላት እያየሁ የተሳከረ ስሜት ወረረኝ። የዛን እለት ከአቶ አያልነህ ጋር የነበሩት ሰውም አረፋፍደው ተቀላቀሉ። የኛም ወገን የእነሱም ወገን የተፈጠረውን እልቂት ይቅር ተባብለው ተሻግረውት እኔ ብቻ ነበርኩ በጥላቻ የሰከርኩት? አይደለም! እዚህ ያሉት ናቸው በይቅርታ የተሻገሩት!! ጥላቻ እና ቂማችንን ይዘን ከተማ የገባን እኔና መሰሎቼ በየሶሻል ሚዲያው በቃላት ተዋግተናል፣ ካለመንደራችን በተገናኘንበት ተጠማምደን ተጠላልፈናል፣ የደማችንን ምንጭ ተጠያይቀን ለአባቶቻችንን ፀብ እኛ ተሰነካክለናለን ተጫርሰናል፣ እኛ እንደአባቶቻችን በጥይት ተጫርሰን ባናሳያቸውም ለወለድናቸው ልጆቻችንን እና ታናናሾቻችን ጥላቻችንን አጋብተናል። እነርሱ ግን እረስተውትም እንኳን ባይሆን አልፈውት የአንዳቸውን ለቅሶ ይላቀሳሉ። እኔ ግን ከወራት በፊት እንኳን የእነእርሱን የልጅ ልጅ እንኳን ባገኝ በማያውቀው የአያቱ በደል ጥላቻዬ ውስጤ ይፈላ ነበር።

ከቀብር መልስ ሰው እየተሰናበተን ሲወጣ አቶ አያልነህ ከሚስታቸው ጋር ተሰናብተው ሊወጡ ሲሉ እጄን ያዝ አድርገው።

«እግዜሃር ያፅናሽ!» ሲሉኝ እጃቸውን በደንብ ጨብጬ ይዤ

«ዛሬ ነው የፈቱኝ!! እስከዛሬ የእርሶ እስረኛ ነበርኩ።» ስላቸው ቁጥብ ያለ ፈገግታ ፈገግ ብለው

«እኔ ይቅር ብያለሁ እርሱ ጨርሶ ይቅር ይበልሽ!! በርቱ!!» ብለውኝ ወጡ!!

በኋላ ላይም ወዳጃቸው የተቀመጡበት ሄጄ እጃቸውን ያዝ አድርጌ (በአካል ስላላገኘኋቸው ሁሌ ይከነክነኝ ነበር) «የማይገባኝን ይቅርታ ስለሰጡኝ አመሰግናለሁ!!» አልኳቸው። እሳቸው ከአቶ አያልነህ በላይ በተፈታ መንፈስ

«እግዜር ያፅናሽ ልጄ!! እቤቴ በተውሽው መልዕክት የልጆቼን ህይወት ነው የቀየርሽው!! ልብሽ ቀና ነው የእኔ ልጅ ቂምና ጥላቻ ለማንም አይበጅ! ለአባትሽም ለእኛም አልሆነን!! ልብሽን ከክፉ ጠብቂው!» ብለው ጭራሽ እኔኑ አበረቱኝ።

የቀብር ቀን ማታ ፍራሽ ላይ ተቀምጠን ሊያማሽ የመጣውን ለቀስተኛ እየተቀበልን ስንሸኝ በሚገባ እና በሚወጣው ሰው መሃል ጎንጥ በሞላ ሞገሱ ጎንበስ ብሎ ድንኳኑን ሲዘልቅ ሳየው የእማዬን መሞት አሁን የተረዳሁ ይመስል ድንኳኑን በለቅሶ ደበላለቅኩት። እስከአሁን ሲገባ ሲወጣ ከነበረው ሰው የበለጠ ፣ እስከአሁን ሊያፅናናኝ ከሞከረው ህዝብ በበለጠ ፣ እንደነፍሴ ከምወደው ኪዳኔ እንኳን የበለጠ ፣ ከአጎቴም የበለጠ ……. እሱ ብቻ የበለጠ ህመሜ የሚገባው ዓይነት ነው የመሰለኝ። ድንኳኑ እንደአዲስ በለቅሶ ተናጠ። ሌላ ሰው መኖሩን ረሳሁ!! ዘልዬ እቅፉ ውስጥ ገባሁ!! አላባበለኝም አብሮኝ አለቀሰ። ሽማግሌዎች <ከመሸ እንዲህ አይለቀስም> ብለው ሊያረጋጉ ሲሞክሩ አጎቴ ከውጭ ብቅ ሲል ጎንጥን ሲያየው ከእኔ ብሶ አረፈው። ልክ የሆነ ታናሽ ወንድሙን ያገኘ ወይ ታላቅ ልጁን አልያም የብዙ ጊዜ ወዳጁን ያገኘ ይመስል

«አመለጠችኝኮ! አትከብጅኝም ትንሽ ቆይ እያልኳት አሻፈረኝ ብላ ሄደች! እንብኝ አለች! ናፍቆቴ አልወጣልኝም እያልኳት ተሸነፍኩ አለች!» እያለ ሲያለቅስ ድንኳኑ ተተራመሰ። ጭራሽ ሁለቱ ተቃቅፈው ሲላቀሱ የተወሰኑ ቀናት አብረው ያሳለፉ ሳይሆን ሳይነጋገሩ የሚግባቡ ቤተሰቦች ነው የሚመስሉት። እኔስ ስለወደድኩት ወይ ይወደኛል ብዬ ስላሰብኩ ለልቤ አቅርቤው መሰለኝ ሳየው ሀዘኔ የፈነቀለኝ። አጎቴስ? ምናልባት እኔ ያልሰማኋቸውን ቅፅበት የልብ የልባቸውን አውግተውበት ተናበው ይሆን? ወይስ ለልብ ለመቅረብ የተለየ ነፍስ ያለው ሰው አለ?

ለቅሶው ሲበርድ አጠገቤ መጥቶ ፍራሽ ላይ ተቀመጠ። ለቀስተኛው ማን ስለመሆኑ ግራ እየተጋባ ሲጠያየቅ አጎቴ «ቤተሰብ ነው!» እያለ ይመልሳል። አንድ ዘመዳችን

«የአባትሽ ቤተሰብ ነው? የእነርሱ ደም ይመስላል!» ስትለኝ በደንብ አስተዋልኩት። በጭንቅላቴ ውስጥ ሊጠፋ የደበዘዘ የአባቴን መልክ ለማነፃፀር እየታገልኩ ….. ቁመቱ ፣ ትከሻው ፣ ግርማ ሞገሱ ፣ ጥይምናው ፣ ጅንንነቱ …… ከአባቴ ጋር ይመሳሰላል። ለአፍታ <የተሸነፍኩት ሳላውቀው አባቴን እሱ ውስጥ ስላገኘሁ ይሆን?> ብዬ አሰብኩ። ሳይታወቀኝ አፍጥጬ እያየሁት ስለነበር

«ምን አስፈልጎሽ ነው?» አለኝ

«ምንም! ስለመጣህ ደስ ብሎኛል።» አልኩት

«እንዴት ይቀራል ብለሽ አሰብሽ?» ብሎ ወደትከሻው አጥብቆ ከያዘኝ በኋላ የህመም ትንፋሽ ተነፈሰ። ከሆስፒታል የሚወጣበት ቀን ቀናት እንደሚቀሩት እያወቅኩ እሱን አለማሰቤ አሳፈረኝ። እሱ አጠገቤ መሆኑን እንጂ የእርሱን ቁስል አላሰብኩለትም።

«ውይ! ይቅርታ!» ብዬ ከትከሻው ቀና ስል መልሶ ከቅድሙ በላላ ሁኔታ ትከሻው ላይ አስደግፎኝ
«ደህና ነኝ!!» አለኝ

«ሆስፒታል መቆየት ነበረብሃ?»

«አንድ ሁለት ተጨማሪ ቀን ነበረብኝ! የእኔ ሀሳብ አይግባሽ!! ደህና ነኝ አልኩሽ እኮ ዓለሜ? አንች መድሃኒቴ አይደለሽ? ሆስፒታል ምናባቱ?» ብሎ ከደቂቃዎች በፊት ስንሰቀሰቅ የነበርኩትን ሴት ያሽኮረምመኛል? እያየኝ ያለ ሰው መኖሩን ለማረጋገጥ አይኔን የተቀመጠው ለቀስተኛ ላይ አንቀዋለልኩ።

እናቴ የሞተችብኝ እኔ ከዛ ደግሞ የተሽኮረመምኩትም እኔ …… ለሰው የሀዘኔን ጥልቀት አሳይቼ መሽኮርመሜን መደበቅ ያለብኝም እኔው!! ምክንያቱም ምንም እንኳን ሊያፅናኑ ቢመጡም ስፅናና እንደሚዳኙኝ አውቃለሁ። <የእናቷ ለቅሶ ላይ ተሽኮረመመች፣ የእናቷ ለቅሶ ላይ ስታስካካ ነበር ፣ ምን እሷ ምንም አልመሰላት ኸረ አላያችኋትም እንዴ እናቷን መቅበሯን ረስታ ከወንድ ጋር ስትለፋደድ?> እንደሚሉኝ አውቃለሁ። ግራ የሚገባኝ ሊያፅናኑኝ የሚሞክሩት የውሸት ነው ማለት ነው? ሀዘን ማብዛት ጥሩ አይደለም የሚሉት ስለሚባል ነው ማለት ነው? ስፅናና ወይ ስስቅ ታዲያ ለምን ይከፋቸዋል? <በደንብ አላለቀሰችም!> ሁሉ እንደሚባል አውቃለሁ!!

ስለዚህ ተሰብስቤ ተቀመጥኩ። እኔ ትቼው የምሄደው ህዝብ እና መንደር ቢሆንም ለአጎቴ ወሬ ትቼለት መሄድ አልፈለግኩም!! በሁለተኛው ቀን ጎንጥ የምጨራርሰው ጉዳይ አለኝ ብሎ ወደከተማ ተመለሰ።

ከእማዬ ቀብር በኋላ ቤቱ ውስጥ የሚተራመሰው ዘመድ አዝማድ እና ጎረቤት እየተመናመነ ሄዶ ድንኳኑ ከተነሳ በኋላም ኪዳን መሄድ የፈለገ አይመስልም። «ትንሽ ቀን እንቆይ!» ሲል ብዙ ቆየን። ሁሉም ወደቤቱ ገብቶ ሶስታችን ብቻ የቀረን ቀን ማታ ሀዘናችን በረታ እና እንደአዲስ መላቀስ ያዝን። ኪዳን ከሁለታችን ብሶ «ምናለ ትንሽ ቀን ብትሰጣት? ፣ ምናለ ትንሽ ቀን ብጠግባት? ፣» እያለ ከአምላኩ ጋር ሲሟገት አንጀቴ ልውስ ብሎብኝ ተንሰፈሰፍኩ። አጎቴ እንደልማዱ «እህቴ ፤ ክፋዬ ፣ አንድ ደሜ …. » እያለ እንዳልተነፋረቀ እንባውን በፎጣው አደራርቆ

«ተው ደግም አይደል። የፈጣሪን አይን አትውጉ! ሳናያት ሳናውቅ አልፋስ ቢሆን? የልጆቿን ዓይን ዓይታ ፤ ጠረናችሁን ስባ በትውልድ ቀዬዋ ሀገሬው ቤቱን ነቅሎ ወጥቶ በፍቅር የሸኛት እሰቡት አምላክ እንዴት ቸር እንደሆነ? ደግም አይደል?» ብሎ ተቆጥቶ አረጋጋን!! እንባችንን አቆምን እንጂ ለሚቀጥሉት ቀናት እንደተኳረፈ ሰው በመሃከላችን ብዙም የቃላት ልውውጥ አልነበረም። የሆነ ቀን ውጪ ሳሩ ላይ ተቀምጠን

«የኔ ኪዳን? አሁንም ከዚህ በላይ መቆየት ትፈልጋለህ?» አልኩት

«እኔ እንጃ ሜል! ወደ አዲስአበባ መመለስ ከፈለግሽ እንመለስ! እኔ አሁን ምን እንደምፈልግ ራሱ አላውቅም!!» አለኝ።
1.4K viewsTsiyon Beyene, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 18:00:11 ‹‹እሞክራለሁ አያቴ››

‹‹አዎ በደንብ ሞክር …ከኃላ ታሪክህ ካልታረቅክ የፊትህን ታሪክ ማሳመር አትችልም፡፡አውቀህም ቢሆን ሰታውቅ የብዙ ሰው ልብ ሰብረሀል…የብዙ ሰው ደስታ አክስመሀል፤ ለዚህ ደግሞ ያለምንም ማቅማማት ኃላፊነቱን መውሰድ አለብህ፡፡

‹‹ኸረ እወስዳለው…በደንብ ነው ምወስደው.. ሌላወ  ይቅር አክስቴን ያሳዘንኳት እራሱ ቀላል ነው.?.››

‹‹አዎ ገብቶሀል ማለት ነው…አክስትህ ለአንተ እናትህ ነች….በፍቅርና በርህራሄ ልክ ከማህፀኗ እንደወጣ ልጇ አድርጋ አሳድጋሀለች..የአንድ እናት የመጨረሻ ደግነት የሚለካው ከሌላ ሰው ማህፀን የወጣን ልጅ ከራስ ማህፀን ፈልቅቆ ከስጋዋ ቦጭቀውና ከአጥንቷ ቀንሰው ከተፈጠሩ ልጆች እኩል በማየት ነው….ያንተ አክስት በዛም አላበቃች፤ የአንተ ኃላፊነት የሆነችውን ልጅህን መልሳ እያሳደገች ነው…ይህ ለእሷ ምን ያህል በየቀኑ የሚንጠባጠብ የልብ ድማት እንደሚያስከትልባት ታውቃለህ….?ልጅህን ባቀፈች ቁጥር አንተን ሆነ እናቷን ታስታውሳለች….

እነዚህ ልጆች ሳሳድግ ምን ላይ ይሆን የተሳሳትኩት? እያለች አብዝታ እራሷን ትወቅሳለች…እንዲህ ባላደረኩ ኖሮ….እንዲህ ማድረግ ነበረብኝ…..መአት ነገር እያሰበች እራሷን ትቀጣለች፡፡››

‹‹ጋሼ ይሄም እውነት አይደለም…ለእኛ ሉጋም የለቀቀ ስህተት እሷ ቅንጣት  ኀላፊነት የለባትም …ሁሉም ጥፋት የእኛ ነው….፡፡››

‹‹በዛ እኔም አልከራከርህ….ጥፋቱ ሁሉ የሁለታችሁ ነው….፡፡ አክስትህ ግን እርግጠኛ ነኝ እንደዛ አታስብም፡፡ልጄ ምን አልባት አባት መሆንህን አውቃለሁ…በስም አባት መሆንና እና ልጅ ማሳደግ ግን ፍፅም የሚገናኝ ነገር አይደለም፡፡ለዘመናት አባይ የእኛ ነው እያልን ስንዘፍንና ስናቅራራ ኖረናል ግብፆችም እንደዛው አባይ የእኛ ነው ይላሉ፡፡አንድ ኢትዬጵያዊ መንገድ ላይ አቁመህ አባይ የማነው ብትለው አረገኝ ይሄ ምን የሚሉት ጥያቄ ነው አባይማ ከእኛው ጎጃም ምድር ከሰከላ መንጭቶ አያሌ ወንዞቻችንን እያስገበረ የሚንፎላፎል የገዛ ወንዛችን ነው ይልሀል፡፡››

አዎ በቲኦሪ ደረጃ ትክክል ነው…እውነታው ግን አባይ የግብጽች ነው፡፡ምክንያቱም እንሱ ተንከባከብውታል ….በላዩ ላይ ዘርተው ሙዝ ገምጠዋል፤ ብርቱካን ልጠው ውጠዋል፡፡፡ግድብ ገድበውበት ህዝባቸውን በሰው ሰራሽ ብርሀን እንድያሸበርቅ አድርገዋል፡፡ስንዴ በገፍ ዘርተውበት ህዝባቸውን መግበውበታል ፤ በየቀኑ ይበሉታለ  በየቀኑ ይጠጡታል፤ በየቀኑ ይንከባከቡታል፤ እና የእኛ ነውር ሲሉ ቃሉ ከከንፈራቸው በዘልማድ አይደለም የሚወጣው ከጥልቅ ልባቸው በፍቅርና በስስት ነው የሚፈሰው፡፡ ምን አልባት እኛም ከአሁን ወዲያ ልከ እንደነሱ  ወግ ይደርሰን ይሆናል…እና ልጅም ወልዶ ማሳደግ ቀላል አይደለም፡፡››
‹‹እሱማ በትንሹም ቢሆን ይገባኛል››

‹አዎ..አንድ ልጅ ወልዶ ለማሳደግ ትልቁ ጣጣ ልጁ ሚያስፈልገውን ምግብ፤ ልብስ የመሳሰሉትን ማሟላት አይደለም፡፡ከዛ ይልቅ የልጁን ማንነት መስራት ነው ከባዱ ጉዳይ፡ብዙው ወላጅ ሳያሳከው የሚቀረውና ፌል የሚያደርገውም  እዚህ ላይ ነው፡፡ልጅን በየትኛው  መንገድ መምራት ነው ተክክል ፡እያንዳንዱን አታካችና ድንበር አልባ የልጅ ጥያቄዎችንስ በምን አይነት ዘዴና ብቃት መመለስም ይቻላል?፡፡ልጅን ማቅረብ ነው ማራቅ ጥሩ?፡፡ሲያጠፋ መግረፍ ወይስ ዝም ብሎ ማየት? ወይስ ምከር መለገስ…?ምክሩ ማያርቀው ሆኖስ ሲገኝ?፡፡እነዚህ የመሳሰሉት አያሌ የህይወት  መንገዶች  ውጤታቸውም የራሱ የሆነ ጥሩና መጥፎ ጎን ያላቸውና በትክክልም አስቀድመው የማይተነበዩ ናቸው፡፡፡፡እና ቀድመን የራሳችን ህይወት መስመር ተቆጣጥረን  መምራት ያልቻልን በህይወት ኪሳራ ውስጥ ምንዳክር ወላጆች እንዴት ባለ ታአምር ነው ስኬታማ ልጅ የመቀረፅን እጅግ ረጅምና አታካች ፕሮጀክት በብቃት እና በስኬት ልንወጣ ምንችለው?፡፡በዛ ላይ የሀይማኖት ተቋማት ተፅዕኖ አለ፤ .የማህበረሰብ ተፅዕኖ አለ.፤የቴክኖሎጂ ተፅዕኖ አለ..የጓደኛ እና የትምህርት ቤት ተፅዕኖ አለ…ከነዚህ መካከል የአንዱ የተጣመመ ተፅዕኖ ለዕድሜያችንን እኩሌታ የለፋንበትን የልጃችንን ህልውና ድምጥማጡን ላለማጥፋቱስ ምን ዋስትና አለን?፡፡
‹‹አያቴ››

‹‹አቤት ልጄ››

‹‹እርሶ  ከጎኔ ባይኖሩልኝ ምን ይውጠኝ ነበር….?››

‹‹አንተ ቀልማዳ….በል ተነስ አሁን ወደስራ ሂድ ..ስትንቀሳቀሰ ቀለል ይልሀል……እዚህ ካበቃለት ሽማግሌ ጋ ነገር በመፍተል ጊዜህን አትፍጅ››

‹‹እሺ»
እሄዳለሁ..አመሰግናለሁ ብዬ ልብሴን ቀያየርኩና ወደሆቴል ሄድኩ፡፡

ይቀጥላል
2.2K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 18:00:10 #እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
:
:
#ክፍል_ስምንት
////

"ሠላም ነሽ ታአምር?"

"ሠላም ነኝ"

" አባዬ...ድምፅህን ስለሠማው ደስ ብሎኛል"

"እኔም ደስ ብሎኛል የእኔ ጣፋጭ...ግን ስልኬን እንዴት አገኘሽ?"

"የጓደኛዬ የቢጡ አባት ነው አባቴን ባገኝ ደስ ይለኛል እያልኩ ሳለቅስ አሳዘንኩትና ..ከፌስብክ ላይ ፈልጎ ባንተ ስም የሚመሳሰል ሶስት ቁጥር ሰጠኝና …ሞክሬ …ሞክሬ..  ከዛ አገኘውህ...እናም ደስ አለኝ"

"ውዴ..እስከዛሬ ፈልጌ ስላላገኘውሽ በጣም ይቅርታ...እቴቴን ስላስቀየምኳት ፈርቼ እኮ ነው"

ዕድሜ ልኬን ከብዙ ሰዎች ጋር በክፉም በደጉም ብዙ ንግግር ተነጋግሬያለሁ... እንደዛሬው ግን የምይዘው የምጨብጠው ጠፍቶኝ አያውቅም...ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ፊት ብቀርብ እራሱ እንዲህ አልርበተበትም።

"አባዬ"
አልተቀየምኩህም..እቴቴም ደግሞ ሰው ሳያያት ክፍሏ ውስጥ ትደበቅና ያንተን ፎቶ እና የእናትህን ፎቶ እያየች "የእህቴን አደራ በላሁ›› እያለች ታለቅሳለች ..፡፡

"እውነትሽን ነው..?"

"አዎ አባዬ እውነቴን ነው"

""ታአምሬ"

"ወዬ አባዬ"

"ስልኩ..ማለት የደወልሽልኝ በማን ስልክ ነው?"

"ስልኩ የራሴ ነው...እማዬ ከአሜሪካ ስትደውል በራሴ ስልክ እንዳናግራት ልካልኝ ነው"

"እና በዚህ ብደውል አገኝሻለሁ?"

"አዎ ግን..ማለቴ አንተን እንዳገኘሁህ እቴቴ ስለማታውቅ ፈርቼ ነው"

"ችግር የለም"

ሲመችሽ..እንዳወራሽ ስትፈልጊ ሚስኮል አድርጊልኝ"

"እሺ አባዬ"

"ቻው...እወድሀለሁ"

"እኔም በጣም ወድሻለሁ..ቻው"ስልኩ ተዘጋ፡፡

ስልኩን ከዘጋሁ በኃላ እንኳን እንባዬንም ስሜቴንም መቆጣጠር አልቻልኩም.፡፡ አልጋውን ለቅቄ በመውረድ ቤት ውስጥ ከላይ ወደ ታች እየተመላለስኩ   ወለሉ ላይ የተዝረከረከኩትን ዕቃዎች  እየረገጥኩ ዘለልኩ ..፡፡በቃ እብድ ነው የሆንኩት ። የማልረባ ነኝ...፡፡እኔ ሰው አይደለሁም፡፡መኖር ፈፅሞ አይገባኝም…

ከብዙ ቆይታና  መታገስ በኋላ ጋሽ ሙሉአለም ድምፅ አውጥተው ተናገሩ ...፡፡ ውስጤ መተራመሱ  ብሶ ቤቱን በማተራመሴ እሳቸውንም እየረበሸኩ መሆኑን እስከአሁን ልብ አላልኩም ነበር።

"ልጄ ምን ገጠመህ?"

‹‹አያቴ ጉድ ሆኜሎታለሁ? ..እኔ እኮ ሰው አይደለሁም?

‹‹ሠው አይደለሁም ስትል?

"በስህተት እና  ሀጥያት የተጨማለቅኩ እርኩስ ነኝ።

"እንደዛማ ከሆነማ እንደውም ኦርጅናሌ ሰው ነህ...››

‹‹አያቴ ትክክል ኖት ..ግን ይሄን ታሪክ ብነግሮት  ቀጥታ ይጠሉኛል...ዛሬውኑ ነው ቤቱን ለቀህ ውጣልኝ የሚሉኝ "

"ይበልጥ አጓጓኸኝ..‹.ምን ሰራው ቢለኝ ነው ይሄንን ልጅ የምጠላው?›እያልኩ ውስጤን እየጠየቅኩ ነው?...እስቲ ንገረኝና የትዕግስቴንና ይቅር የማለት ችሎታዬን  ልክ ልፈትሽበት።››

"ልጄ ደወለችልኝ"

"ልጄ ..?.›

‹‹አዩ አያቴ ገና ከመጀመሪያው ደነገጡ አይደል?"

"ሂድ ከዚህ…. ቀላማጅ፡፡ እኔ አልደነገጥኩም...ይልቅ ቅድምአያት ስላደረከኝ ተደስቼ ነው"

‹‹ይሁን እሺ….ልጅቷን የወለድኩት ካሳደገችኝ ከአክስቴ ልጅ መሆኑን ስነግሮትስ ምን ይሰማዎታል....? 40 ለሚሆን ደቂቃ ከመጀመሪያው አንስቼ አወራሁላቸው...በፅሞና አዳመጡኝ።

"የማልረባ ሰው ነኝ አይደል?"እንዲጮሁብኝ …እንዲረግሙኝ ፈልጌለሁ፡፡

.እሳቸው ግን ለስለስ ብለው ሀዘኔታ ባጠቃው አነጋገር"የማትረባም ብትሆንም ልጄ ያው ሰው ነህ… ዋናው እሱ ነው።ሰው ደግሞ በማንኛውም ጊዜና አጋጣሚ አውቆም ሆነ ሳያውቅ በሁኔታዎች አስገዳጅነት ስህተት ይሰራል!ምክንያቱም ሰው እንደዛ ስለሆነ?ልዩነቱ አንዳንድ የሰራውን ስህተት ለመሸፈን ሌላ ስህተት ሲጨምር አጠቃላይ ሁኔታውን ጭምልቅልቅ አድርጎ እስከወዲያኛው ያበላሸዋል..፡፡ሌላው ደግሞ ስህተቱን በማረምና ያስከፋቸውን ሰዎች በመካስ ቀሪ ህይወቱን ያስተካክላል..፡፡.ደግሞ ያንተ የሚገርም ነው..፡፡ልጅ አለችህ..ልጅቷ ደግሞ ስህተት ልትሆን አትችልም..፡፡.እሷ ንፁህ እውነት ነች...፡፡ስህተቱ እሷ የተገኘችበት መንገድ ነው...፡፡እሱም ቢሆን አንዴ የተዘረጋ መንገድ ነው... በመንገድ ዙሪያ ያለውን ገደል ማስተካከል  ነው የምትችለው፡፡ መንገድን ለሁለት በመክፈል የለያዩት ገደሎች ድልድይ መስራት ነው የምትችለው፤ድልድዩ ደግሞ በይቅርታ ብረትና በፍቅር አርማታ ነው የሚገነባው... ፡፡

‹‹እንደሚሉት ቀላል አይደለም››

‹‹አትሞኝ ልጄ ፤የሰው ልጅ ከባባድ ነገሮችን ለመስራት ብዙም አይቸግረውም …ብዙ ጊዜ እንዝላል የሚሆነው ጥቃቅን ነገሮችን ለመስራት ነው፡፡ያው ዞሮ ዞሮ ጥቃቅን ነገሮች ተደምረው ነው ከባድ ችግሮችን የሚፈጥሩት ፡፡አሁን የነገርከኝን ታሪክ ስትሰራ በአንድ ቅፅበትና በአንድ ቀን አይደለም..ቀስ በቀስ፣አንድን በአንዱ ላይ እየደረብክ….በአመታት ውስጥ ነው የሆነው፡፡ለማጥፋት እንደዛ ከሆነ ያንን የጠፋውንም ለማደስ እንደዛው ቀስ በቀስ ምን አልባት የአራት እና በአምስት አመታት ጥረትና ልፋት ይጠይቅ ይሆናል..ግን በየእለቱ የምትችለውን ስራ.››

‹‹እንዴት አድርጌ አያቴ?››

‹‹ይው እኮ አስበህበትም ባይሆን ዛሬ ጀመርክ፡፡››

‹‹አልገባኝም፡፡››

‹‹ያው ከልጅህ ጋር አወራህ፣ድምፆን ሰማህ፤ምን ያህል አንተን እየናፈቀች እንደሆነ እና በአንተም ምንም ቅሬታ እንደሌላት ከአንደበቷ አረጋገጥክ፡፡››

‹‹አዎ አያቴ እሱን እንኳን እውነቶትን ነው፡፡››

‹‹አዎ እውነቴን ነው፤ አሁን ማድረግ ያለብህ ከጭንቀትና ትካዜ እራስህን ሙሉ በሙሉ አላቅና ከልጅህ ጋር ያለህን ግንኙነት በጥበብ በጣም ሳታግለበልበው ፤በጣም ሳታደፋነው በሚገባው ልክ  ይዘህ አስቀጥለው››

‹‹ማግለብለብ ማለት?››

‹‹ለምሳሌ የሚቀጥለው እሁድ ብር ብለህ ደብረብርሀን ሄደህ ላግኝሽ ብትላት ቤተሰቦቾ ሳይዛጁበት ይሰሙና ልጃችንን ይዞብን ሊጠፋ ነው ብለው ፈፅሞ እንዳታያትና እንዳታናግራት በሊያደርጉ ይችላሉ.. ወይም እናቷ ጋ አሜሪክ ሊልኳት ይችላሉ….ስለዚህ መጀመሪያ በስልክ ግንኙነትህን በደንብ አጠንክር..ስለቤተሰቦችህ አሁናዊ ሁኔታ ቀስ በቀስ ከልጅህ እየጠየቅክ ተረዳ..፡፡ታዲያ ስትጠይቃት በጥበብ ማለቴ ድንገት በወሬ በወሬ ትዝ ብሎህ እንዳነሳህ እያስመሰልክ መሆን አለበት..፡፡የዛሬ ልጆች ቀላሎች አይደሉም…..እሷን ስለዘመዶችህ መረጃ ለማግኘት እየተጠቀምክባት እንደሆነ ከተሰማት ልትቀየምህ ትችላለች፡፡ከዛ አጠቃላይ ሁኔታውን ከተረዳ በኃላ ምን አይነት እርምጃዎችን መውሰድ እንዳለብህ ትወስናለህ…፡፡ችግሮችሀን በደረጃ ከፋፍላቸው…ከዛ እያንዳንዱን በተናጠል ስታየው  መፍትሄ ለማበጀት ያን ያህል ከባድ አይደለም…..፡፡

ለምሳሌ የልጅህን በአካል ማግኘት፤ከልጅህ እናት መታረቅ፤የአክስትህን ልጆች ይቅርታ መጠየቅ፤ የአክስትህን ባል ይቅር እንዲልህ መማፀን፤ የእራስህን ህይወት ለልጅህ በሚመጥን መልኩ ማስተካከል፡ እነዚህን ሁሉ ኮተት ችግሮች በአንድ ኩንታል ውስጥ ጠቅጥቀህ ካየሀቸው  ዘላለም በጫንቃህ ተሸክመህ ስታላዝን ትኖራለህ እንጂ መቼም አትፈታቸውም፤ግን እያንዳንዱን በፔስታል ለየብቻ አድርገህ ያዛቸው ቅደም ተከተል ስትሰጣቸው በአንድ ጊዜ አንዱ ፔስታል ብቻ ተሸክመህ መዞር ቀላል ስለሆነ ሳትጨናነቅ በተወሰነ ጥረትና መስዋዕትነት ትፈታዋለህ፡፡ እሱን መፍታትህ ለሁለተኛው ፔስታል ውስጥ ላለው ችግርህ መፍቻ መንደርደሪያ ይሆናል.እንደዛ ነው ልጄ››
2.3K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 07:04:38 ለ Pp የሚሆን ጥቅስ አጥተው ያውቃሉ? ወይስ ለፍቅረኛዎ የሚልኩት የፍቅር መልዕክት ይፈልጋሉ? ተቀላቀሉን
91 viewsENFALOT ° , 04:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 23:25:29 መንታ ልቦች :
አፍቃሪ ሆነክ ይሄ ቻናል ከሌለክ እመነኝ አንተ እውነተኛ አፍቃሪ አይደለህም
857 viewsENFALOT ° , 20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 23:13:30
እስቲ ይሄ የፍቅር ሳይኮሎጂ ነው የእናንተን ወይም የፍቅረኛዎትን #የመጀመሪያ ፊደል ይምረጡና ፈታ ይበሉ
444 viewsENFALOT ° , 20:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ