Get Mystery Box with random crypto!

አትሮኖስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronosee — አትሮኖስ
የሰርጥ አድራሻ: @atronosee
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163.71K
የሰርጥ መግለጫ

╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።
Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 38

2022-12-19 22:33:45 ቤቲንግ ለምትመድቡ ሁሉ ይህን ምርጥ ቻናል እናስተዋውቃቹ 

ብዙ ዓመት ልምድ ባላቸው ቀማሪዎች የተከፈተ ብችኛ ታማኝ ቻናል ነው ከኛጋ በመሆን ከሳምንት እስከ ሳምንት አሸናፊ ለመሆን ቻናሉን JOIN ያድርጉ
459 viewsENFALOT ° , 19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 22:14:31
#ድንግልናዬ_እና_መዘዙ

እጅግ ልብ አንጠልጣይ #የዳናዊት_መክብቡ የህይወት ታሪክ ድንግልናዋ እና ፈተናዎቿ

ብዙዎችን በእንባ ያራጨ አይረሴ የሕይወት ገጠመኝ

ተለቀቀባት ታሪኩን ከስር ተጭነው ይመልከቱት
https://t.me/joinchat/AAAAAEzGj1iAHLL8f6eqKw
973 viewsENFALOT ° , 19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 22:11:15
እስቲ ይሄ የፍቅር ሳይኮሎጂ ነው የእናንተን ወይም የፍቅረኛዎትን #የመጀመሪያ ፊደል ይምረጡና ፈታ ይበሉ
501 viewsENFALOT ° , 19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 21:00:04 "ይእ! እንግዲያ ምን ሆነ?" ብላ ጎይቲ ትንሽ አሰበችና

ውሃውን ጠጥቶ አልተረፈውም?"

"ተርፎት ነበር ምነው?"

"እህ! የተረፈውን ውሃ ምን አደረግሽው?"

"ደፋሁታ! ካርለት የጎይቲ ጥያቄ ገረማት

ደፋሁት! ምነው ካርለቴ  ምነው ፍቅረኛ አድርጎሽ
ቢመጣ ቀና ለቀን አሳዘንሽው?"

"ምን አድርጌ?" ካርለት ግንባሯን ክስክስ አደረገች

"ይእ! ጎይቲ አላስችላት ብሎ ከትከት ብላ ሳቀች

"ምነው"

ምን አጠፋሁ?"  አለቻት ካርለት " ጎይቲን ትንሽ
በስጨት ብላ።

"ይእ!ምነው የጀግና ትራፊ መድፋት ነውር ነው  እንኳን
ጀግና ማንም እንግዳ መወደድ መጠላቱን የሚያውቀው የተረፈውን
በፊቱ ስትጠጭው ነው፤ የተረፈውን ደፋሽ ማለት ግን ጠልተሽዋል ወይንም ንቀሽዋል ማለት ነው ብለን ስንት ጊዜ ነው የነገርንሽ?
ስትላት  ካርለት ክው ብላ አፏን ያዘች ጎይቲም እየሳቀች ሄዳ አቀፈቻት ካርለት ግን የሰማችውንና ማስታወሻዋ ላይ የፃፈችውን
በመዘንጋቷ በራሷ አፈረች።

ይቀጥላል
1.5K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 21:00:03 #የዘርሲዎች_ፍቅር


#ክፍል_ስድስት


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


ካርለት ድንኳናን ዘግታ ስትፅፍ የሰው ኮቴ የሰማች መሰላትና ጆሮዋን አቁማ አዳመጠች

"ካርለት?"

"የስ" ብላ ቶሎ በማስተካከል "ዬ! አለች - እንደ ሐመር ልጃገረዶችı ካርለት የጠራት ሰው ማን እንደሆነ አውቃዋለች
ደልቲ ነው ቀብራራው ጀግና የድንኳኗን ዚፕ ከፍታ ፈገግ ብላ አየችው" ሰውነቱ በአኖ (ከኦሞ ወንዝ ዳር በመጣ የተላቆጠ አፈር)
ተዥጎርጉሯል፥ ጴሮው (መሃል አናቱ ላይ ባለው ጌጥ) ላይ የተሰካው
የቀጭኔ ላባ በንፋስ ይርገበገባል ... እሱ ግን ፊቱን ዞሮ በርኮታው
ላይ ቁጭ ብሎ ጥርሱን በልምጭ ይፍቃል"

አንቺ ንብ አደለሽ
ምነው ቀፎሽን ዘጋግተሽ መቀመጥሽ

"ደልቲ ንፋሱ: ልጆችም
እንዳያስቸግሩኝ አለችው
ፈገግ ብላ እያየችው" እሱ ግን መልሷ አልተዋጠለትም ይህች ሰው! ነፋስና ልጅ የምትጠላ ምን ልትወድ ነው እህ! ብሎ ቆሽቱ
እያረረ ሃሣቡን ሳይናገር ከታጠቀው ዝናር አንድ ቀላህ አውጥቶ
ውታፏን ከፈተና በአውራ ጣቱ ጀርባ የትንባሆ ዱቄት ፈሰስ አድርጎ ጎንበስ ብሎ በአፍንጫው ቀዳዶች ሞዠቅ ሞዠቅ አድርጎ ሽቅብ ማገና በዐይኖቹ እንባ ፍጭጭ ብሎ ደጋግሞ ካስነጠሰው በኋላ
ትንባሆውን ለካርለት አቀበላት በሐመር ሴት ልጅ ትንባሆ መሳቧ ነውር የለውም! በፍቅረኞች መካከል ትንባሆ (ሱረት) መሰጣጣት ደግሞ አንዱ የመግባባታቸው ምልክት ነው።

"ሽማግሎች ለዛሬ ከብት ውጋ ብለውኝ ይኸው በሬዬን ይዠ መጣሁ" አላት ካርለት ትንባሆው ካስነጠሳት በኋላ ምክንያቱን የሰማች ቢሆንም ከእሱ አንደበት ለመስማት ብላ።

"ምነው  ምናጠፋህ?" ስትለው  መፋቂያውን አኘክ አኘክ አድርጎ ተፋና ረጋ ብሎ፣

"አንች ሰው ምነው ሥርዓት ቢኖርሽ ሴት በየት አገር ነው
የወንድን ጥፋት የምትጠይቀው?" አላት ደልቲ ካርለት እንዲህ
ስታጠፋ ጎንበስ ብላ እግሯን
እንድትይዝ አድርጎ ጡቷን
እንዳይመታ እየተጠነቀቀ ሁለት ሶስት ቀን በባራዛ አርጩሜ ደህና አድርጎ እየገረፈ ቢገራት ልክ እንደ ስልጡን አህያ ትሰግር እንደነበር አስታውሶ እህ! ሽማግሎች እንዳሉትስ በመታረሚያዋ ጊዜ
ስታጠፉ እኔ እንጂ ሌላ ማን ይታዘንበታል! ብሎ አዝኖ ጢቅ አድርጎ ምራቁን ተፋና ጥርሱን ይፍቅ ገባ።

"ጎይቲ ስታለቅስ ነው የምትውል አይተሃት ታውቃለህ?"አለችው ካርለት በጥያቄዋ ጎርጉራ አንድ አዲስ ነገር ባገኝ ብላ።

"ሰማሁ! እኔን እህቴን ምን የከፋ ችግር መጣባት! አዘነ
ደልቲ።

"ለዚህ ምን መፍትሔ አለው ታዲያ?" ስትል ካርለት ደልቲ
ሰረቅ አድርጎ አይቷት

"ምን መፍትሄ ይኖረዋል  ሽማግሌ ያለውን መቀበል ነው እንጂ።

"ጎይቲ ከከሎ ጋር ከተጋቡ ወዲህ እኮ ሌላ ወንድ አታውቅም "እንደገና ለዓመል ያህል ሰረቅ አድርጎ እንደዘበት አያት የለበሰችው
ቆዳ የፊተኛው ክፍል ጉያዋ ውስጥ ተሸጉጦ: የቀኝ ጭኗ ውስጥ ክፍል እንደ ጥጥ ንጥት ብሎ ታየው"

"ተታናናሽ ወንድሞቹ ጋርስ  አልቀበጠችም?"

"ከሎ ታናሽ ወንድም እኮ የለውም ሁሉም የእሱ ታላላቆች ናቸው"" ስትለው ታናሽ ወንድም እንደሌለው እያወቀ የረሳበት ምክንያት እየገረመው
"ተዘመዱ ወንዶችስ ጋር?" ካርለት የሰጎን ላባ የሰካበት ጴሮ  የተተለተለውን ሳንቃ ደረቱን እንደ አቦ ሸማኔ ቀጠን ያለ ወገቡን አይታ ምራቋን ከምላሷ ስር መጣ ዋጠችና,

"ከማንም ጋር አልቀበጠችም ካለ ከሎ በቀር" አለችው

"እህ!" ሲል ካርለት ቀጥሎ የሚለውን ለመስማት ጆሮዋን መዘዘች እሱ ግን ጭራሽ ያልጠበቀችውን ጥያቄ

"የምጠጣው ውሃ ትሰጭኝ?" አለ ከኮዳዋ በኩባያ ቀድታ ውሃ
ስትሰጠው ቀና ብሎ አይቷት

"እሱን አንች ጠጭው፤ ለኔ በሾርቃ ስጭኝ" አላት ካርለት ውሃ ለማምጣት ሄደች ደልቲ አረማመዷን÷ ዳሌዋን ወገቧን ከኋላዋ የሚወናወነውን ቆዳዋን ጥርሱን እየፋቀ አየና ምራቁን ጢቅ አድርጎ ተፋና የበረቱ ከብቶች ቀለማቸው የተለያዬ ነው  ቀይ፥
ዳልቻ: ነብርማ: ነጭ የካርለትም ቀለሟ ነጭ መሆኑ ሚስቶቹን
እንደ ከብቶቹ ቀለም ማሳመሩን ሲያስብ የደስታ ስሜት ተሰማው መልሶ ደግሞ የሐመር ልጃገረዶች እንዳለቁ ሁሉ ከዚች አግድም አደግ ጋር ቢቀርብኝስ ብሎ አሰበ አንዴ ግን አገባሻለሁ ብሏል1
ስለዚህ ቃሉን ማጠፍ አልፈለገም ግዴለም አገባታለሁ ድምጿ ግን
ምነው ተዛሬ ነገ ቃናው አይጣፍጥ?  ብልግናዋና ድምጿ እንጂ ሴትነቷስ  እያለ ሲያስብ ካርለት ውሃ በሾርቃ ይዛለት ብቅ አለች

ከርቀት እያያት  ደሞ ደህና ገብሮ የነበረው ሰውነቷ እንደ ምስጥ ንጉስ ተመልሶ ለሰለሰ እያለ ሲያስብ ካርለት ሰው ጠርቷት
ዘወር ስትል የጀርባዋ ሰንበር ታየው  ከሎ ከብት ሲዘል የተገረፈችው"
ደልቲ ትንሽ ፈርጠም ብሎ ሳቅ  አለ ካርለት
አላየችውም ትዝ አለው ስትገረፍ ሰውነቷ የተንቀጠቀጠው ወድቃ
የተዘረረችው

ባለጌ! ብሎ ተቆጨና መልሶ ደግሞ አዘነላት ጀርባዋ ላይ
ያሉት የግርፊያ ሰንበሮች ጥቂት ናቸው ለሐመር ልጃገረድ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበር ሌላው ውበቷ ሲሆን ዳንስ ቦታና ጫካ ውስጥ ወንዱ
እንደ አኮርዲዎን መጫወቻ ሰንበሮቹን በጣቱ እየነካካ የፍቅረኛውን የፍቅር ቅላፄ በማስተካከል የጋራ የፍቅር ስሜት የሚፈጥሩበት ነው
ሴቷና ወንዱ

በልጃገረድ ጀርባ ላይ ባለ የግርፊያ ሰንበር ላይ ሻካራ የእጅ ጣት ጫፎችን ማንቀሳቀስ ትናጋው በፍቅረኛው ምላስ የተነካ ያህል በስሜት ንዝረት መላ ሰውነቱ ያረግዳል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበሯ ጀርባዋ ላይ የበዛ ዘመደ ብዙ' ካነሰ ደግሞ ዘመደ ትንሽ ናት ይባላል ብዙ ጊዜ ልጃገረዶች እርስ በርስ
ስለዚህ ሲጨዋወቱ

ይእ! ይሄ ሁሉ ማን ሲዘል የተገረፍሽው  ነው? ተብላ
የተጠየቀች እንደሆነ እጅዋን አዙራ ጀርባዋን እየዳሰሰች

ይእ! ይሄ የባልዳምቤ
ይሄ የሸረምቤ ይሄ የላሎምቤ …እያለች ትዘረዝራለች ልጃገረዷ በእነዚህ ሁሉ ዘመዶችዋ ስትፎክርና ሳትፈራ ስትገረፍ ያያት ደግሞ ስንትና ስንቱ ወንድ ተመኝቷታል ከስንቱ ጋርስ ቀብጣለች ሊያገባት የፈለገውስ እንዴት እንደሚበዛ መገመቱ አይቸግርም አንድ
የሐመር ወንድ ደግሞ ሌላው የተመኛትን ያፈቀራትን የራሱ አድርጎ ከማግባት የበለጠ ትልቅ
ክብር የለም  በሐመር የጋብቻ አለም።

ካርለት ግን የተገረፈችው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፤ የዛን ቀንም  ግረፉኝ ብላ አልፎከረችም  ስትገረፍም ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ
ስታለቅስ በመጨረሻም ህሊናዋን ስታ ስትወድቅ ምድረ ጎረምሳ ተሳስቆባታል እንጂ ማንም ለፍቅር አልተመኛትም ደልቲ ይህን
አስታውሶ

ወዲህ ወዲያ ስትል እንደ ፍየል ጅራት ስትወናወን እንጂ እሷስ ብትሆን ስንትና ስንት ዘመዶችዋ ከብት ሲዘሉ ብትኖር ኖሮ
የመገረፉ እድል መች ያመልጣት ነበር! እያለ ሲትከነከን ካርለት
አጠገቡ ደርሳ ውሃ የያዘ ሾርቃውን አቀበለችው
እየተጉመጠመጠ ደጋግሞ ተፋና ስምጥጥ አድርጎ ጠጥቶ ባይሮ ኢሜ ብሎ
አመሰገናት እግዜር ይስጥልኝ ለማለት

ካርለት ሾርቃውን
ሾርቃውን ልትመልስ ሄደች ያን ጊዜ ደልቲ ደሙ ፈላ  ነደደው ተቀብላ ፈንጠቅ አድርጋ ደፋችውና
ይህች አሳሳች! ብሎ እራሱን ለማረጋጋት እየሞከረ ከመቀመጫው ተነሳ

"ይእ! እህ የታል አያ ደልቲ?  አለ አሁን ውሃ ብሎኝ
ሰጥቸው መጣሁ አላልሽኝ?" አለች ጎይቲ ከካርለት ጋር ወደ ድንኳኗ
እየተጠጉ
"ጎይቲ  አሁን እኮ እዚህ  ቁጭ ብሎ ስናወራ ቆይተን ውሃ ስጭኝ ብሎኝ ሰጥቸው ሾርቃውን መልሼ: አንችን ጠርቸሽ መጣን በዚህ ቅፅበት የት ሄደ?"

"ይእ! እኔን ትጠይቂያለሽ ደሞ ይልቅ አንች ምንሽ  ውስጥ ከተትሽው? አያ ደልቲ መቼም ካለ ነገር እንዲህ ሹልክ ብሎ እንደ
ሌባ አይጠፋም ተቀያየማችሁ?"

"ኧረ በጭራሽ"
1.5K viewsአትሮኖስ, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 18:00:14 እንተኛለን ወይም እኔ አልጋ ላይ ተኝተን እንገኛለን።ሁል ጊዜ አንደኛው አልጋ ባዶውን ነው የሚያድረው..በኃላ እማዬ ለምን ማትጠቀሙበት ከሆነ ክፍሉ ይጨናነቃል አለችና የሁለታችንንም አልጋ አውጥታ አንድ ባለሜትር ከሀያ አልጋ አስገባችልን።

አንብቤ ጨረስኩ….የሚነዝር የልጅነት ትዝታ ውስጥ ነው ወደኃላ ተስቤ እድዘፈቅ ያደረገችኝ…እንዴ ልጅቷ ይህን ያህል ሀሳብን አቀናብሮና አሳምሮ የመፃፍ ችሎታ ነበራት እንዴ…?እርግጠኛ ነኝ ይሄንን  ማስታወሻ መፃፍ የጀመረችው እኔ ከጠፋው በኃላ አሜሪካ ለመሄድ በዝግጅት ላይ በነበረችበት አጭር ጊዜ ውስጥ ሳይሆን አይቀርም….ግን እንደዛ ከሆነ ለምን ጥላው ሄደች…?.መልስ ላገኝለት ያልቻልኩት ጥየቄ ነው…ልጄ ቀጣዩን ክፍል መቼ ይሆን የምትልክልኝ…?የሚያስጨንቅ ጉጉት አደረብኝ፡፡

ይቀጥላል
2.2K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 18:00:14 #እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_አስር


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////

እራሴን አመም ስላደረገኝ አስፈቅጄ ወደቤት ስገባ ሶስት ሰዓትም አልሆነም።..ሹክክ ብዬ ገብቼ አልጋዬ ላይ "በመውጣት አረፍ እንዳልኩ ስልኬ ጠራ...አሁን ማንንም ቢሆን አንስቶ የማናገር ፍላጎት የለኝም የዜና ወርቅም ብትሆን እንኳን፡፡ስልኩ መጥራቱን ቀጥሏል ማንም ቢሆን ላለማንሳት ድምዳሜ ላይ ከደረስኩ ማንነቱንም ማየት አስፈላጊ አልነበረም ..እኔ ግን እጄን ሰድጄ ስልኬን አነሳሁ፡፡ እስክሪኑን ወደአይኔ አስጠጋሁ..ተፈናጥሬ ከመኝታዬ ተነሳሁና ቁጭ አልኩ..እንዳይዘጋብኝ እየተስገበገብኩ አነሳሁት..

‹‹ሄሎ የእኔ ውድ..?

"ሄሎ አባዬ እንዴት ነህ?

"አለሁልሽ ..በጣም ሰላም ነኝ..አልተኛሽም እንዴ?"

"አይ ገና ልተኛ እየተዘጋጀሁ ነው...አባዬ የእኔ ክላስ የትኛው እንደሆነ ታውቃለህ አይደል?"

በምናብ ወደ አደኩበት ቤት ፈረጠጥኩ..ሁሉንም ክፍሎች በሀሳቤ ቃኘሁ ከእነቴቴ መኝታ ቤት ቀጥሎ ያለችው ክፍል ነች አይደል?"ግምቴ መቼስ የቤቱ ትንሽዬ ህፃን ስለሆነች ለቁጥጥርም ለሊት ተነስቶ ደህንነቷን ለማየትም ቅርብ ያለው ክፍል ነው የሚመረጠው ብዬ ነው...፡፡

"አይደለም..እዛ ህፃን ሆኜ ነበር አሁን ትልቅ ስሆን የአንተና የእማዬ  የነበረውን ክፍል ወሰድኩት

ደነገጥኩ"በእውነት እሱ ክፍል መኖሩ ትዝ አላለኝም ነበር፡፡ እንደዛ ያልኩት ከዛ ሁሉ ዝብርቅርቅ ክስተት በኃላ እቴቴ ክፍሉን ምንቅርቅር አድርጋ የአንድን ሳይድ ግድግዳ በመደርመስ ከሌላው ጋር በመቀላቀል ክፍሉ ለታሪክነትም  እንዳይታወስ የምታደርገው ነበር የሚመስለኝ ..ለዛ ነው ያንን አይነት ጥያቄ የጠየቅኳት"

"ልጄ ሳይገኝ ያ ክፍል አይከፈትም ብላ ከእነዕቃው አሽጋበት ነበር...ከዛ እኔ አክስቴ ትልቋን ለመንኩና እሷ በሌለችበት አስከፈቼ ገባሁበት፡፡"

"ታዲያ አልተቆጣችሽም?"

"አይ  ምንም አላለቺኝም ግን አለቀሰች፡፡"

እኔም አሁን አለቀስኩ የሚቆጠቁጥ እምባ በቀኝ ጉንጬ ረገፈ"የእኔ ማር እናትሽ ለእቴቴ ትደውልላታለች አይደል?"ድንገት በእምሮዬ ብልጭ ያልኝን ጥያቄ ጠየቅኳት፡፡

"ትደውልላታለች...እቴቴ ግን ትሰማታለች እንጂ አታናግራትም፡፡"

"ለምን?"

‹‹"እኔ እንጃ አባዬ...የሙት እህቴን ቃል እንድበላ አደረጋኛለች..ልጄን ወይ በህይወት አልያም ሞቶ ከሆነ ሬሳውን አግኝቼ እርሜን ሳላወጣ ከእሷ  ጋር ባወራ እግዜር ይቀየመኛል ትላለች...ግን አባዬ እርም ማውጣት ማለት ምን ማለት ነው?።››

"ቁርጥ ማወቅ ማለት ነው የእኔ ልጅ"ቀላል ነው ብዬ ባልኩት ቃል ገለፅኩላት።

"አባዬ"

"ወዬ የእኔ ልጅ"

"እቃችሁን ስጎለጉል የእማዬ  ማስታወሻ ደብተር አገኘሁት..ሁል ጊዜ አነበዋለሁ.. ደስ ይላል..።"

"እናትሽ ማስታወሻ ደብተር ነበራት እንዴ? እኔ አላውቅም..."

"አዎ አላት ..ትልቅ ሰማያዊ ደብተር....እና ደግሞ ስላንተ ብቻ ነው የፃፈችው...ትንሽ ትንሽ አንብቤው ስላልገባኝ ተውኩት.. ››

የእውነትም በጣም ተገርሜ "በእውነት ይገርማል .!"አልኩ ፡፡

በድንገት ማስታወሻው ላይ ያለውን ሀሳብ ለማወቅ የሚቀስፍ አይነት የጉጉት  ስሜት ተሰማኝ..ልጄ የውስጤን እንዴት ማንበብ እንደቻለች አላውቅም"አባዬ ከፈለክ ትንሽ ትንሽ ፎቶ እያነሳው ልልክልህ እችላለሁ"ደ

ተነቃቃሁ"እንዴት  አድርገሽ?"

"ቴሌግላም መጠቀም እኮ በጣም እችላለሁ...ለእማዬ ፎቶዬንና የፈተና ውጤቴን እያነሳሁ ሁሌ ነው የምልክላት"

"በጣም ደስ ይለኛል የእኔ ማር...በይ አሁን ተኚ"
"እሺ አባቢ ..ደህና እደር...እወድሀለሁ"

"እኔም እወድሻለሁ"

ስልኩ ተዘጋ...እራስ ምታት የሚባል ነገር ከጭንቅላቴ ተጠራርጎ ወዴት ጥርግ እንዳለ እኔ እንጃ።ልጅ መድሀኒት ነው የሚባለው ለካ ዝም ብሎ አባባል አይደለም፡፡

ስልኬ ተንጣጣ...ሚሴጅ ነው..ከልጄ ነው ከፈትኩት

‹‹ልኬያለሁ›› ይላል ወዲያው ዳታ አበራሁና ቴሌግራም ከፈትኩ .ተአምር እዬብ  ሁለት ፋይል ልካልኛለች...የእኔ ቅመም ልጅ...፡፡ዳውን ሎድ አደረኩትና ከፈትኩት ፡፡ እውነትም ልምድ አላት ፡፡ፍይሉ በጥራት የሚነበብ በጥንቃቄ ተነስቶ የተላከ ነው።የእናቷን የእጅ ፅሁፍ ሳየው ሰውነቴን ነዘረኝ ፅሁፍና ምስሏ በአእምሮዬ እየተፈራረቀ  ትዝታ ውስጥ ጨመረኝ...ምን አለ እህቴ ባትሆኚ።ትራሴን አስተካክዬ አልጋዬ ላይ ጋደም አልኩና ማንበብ ጀመርኩ።

ግንቦት 5/2008 ከምሽቱ 5 ሰዓት

እቤታችን ሲመጣ 9 አመቱ ነበር ።የመጣበትን ቀን በደንብ ነው የማስታውሰው እማዬና አባዬ ለቅሷ ብለው ወደ አዲስአባ ከሄዱ ከሳምንት በሀላ ነው ጥቁር በጥቁር ለብሰው  ፊታቸው ጨልሞና ከፍቶቸው ሌላ የከፋው ፤ለንቦጩን የጣለና ግራ የገባው ልጅ ይዘው የመጡት፡፡ልጁን ቀድሞውንም አውቀዋለሁ፤ ያውቀኛል፡፡ አዲስአባ ያለችው የአክስቴ ልጅ ነው።የአሁኑ አመጣጡ ግን እንደከዚህ ቀደሙ ቦርቆና ፈንድቆ ከእኔና ከእህቶቼ ጋር ለአራት ለአምስት ቀን እቃ እቃ ተጫውቶ ለመመለስ እንዳልሆነ ገብቶኛል።

ትላልቅ ሰዎች አክስቴም ባሏም በድንገተኛ አደጋ ዘእንደሞቱ ሲያወሩ ሰምቼያለሁ ..ግን ይሄ ድንገተኛ አደጋ   የተባለው ሰውን የሚገድል አውሬ ምን አይነት ነው?ስል በወቅቱ በነበረኝ የልጅነት አዕምሮዬ  አሰብኩና በጣም ተበሳጨሁ። አክስቴን በተመለከተ ጣፋጭና የማይሳሳ አይነት ትዝታ ነው ያለኝ።በሶስት  ወር ሆነ በስድስት ወር ልትጠይቀን ስትመጣ ..ኬክ፤ቸኮሌት፤ እና ልብስ ቀሚስ፤ ቲሸርት ጫማ ብቻ አንድ ነገር ይዛልን ትመጣ ነበር።

ትምህርት ቤት ሲዘጋ ደግሞ አዲስአባ እንሄዳለን...ያንን ቢሄድ ማለቂያ የሌለውን ከተማ በፈንጠዝያ ስንዝናናበት ቆይተን ሽክ ብለን በአዳዲስ ልብስ አሸብርቀን እንመለሳለን..አመቱን ሙሉ ከደብረብርሀን ወጥተው ለማያውቁ ጓደኞቻችን ስለአዲስአባ ተረት መሰል ታሪኮችን እየተረክን ስንጎርርባቸው እንከርማለን ለእኔ የአክስቴ ሞት ትርጉም በዛ የጨቅላነት ዕድሜዬ እንኳን  በደንብ ነበር የገባኝ...ከአሁን በሀላ ከአዲስ አበባ የሚመጣልኝ ምንም ኬክ ሆነ ቸኮሌት እንደማይኖር ገባኝ..ዘናጭና ፍሽን ቀሚሶችም ከአክስቴ እንደማይበረከቱልኝ ከሁሉም በላይ ግን ክረምት መጥቶ ት/ቤት በተዘጋ ቁጥር አዲስአበባ ሄዶ መዝናናት የማይቻል መሆኑን ምን አልባትም ትልቅ ሰው እስክሆን አዲስአበባን እንደማላያት ተረዳሁ..
እና እዬቤን እማዬ ከሌሎች ሀዘንተኞች ጋር ይዛው ስትመጣ እላዩ ላይ ተጠምጥሜ አንገቱን አቅፌ አለቀስኩ..ቢያባብሉኝ እራሱ ላቆም አልቻልኩም... በወቅቱ እንደዛ ማለቀሴ  አክስቴን አስታውሼ ነበር. የምታመጣልኝ ኬክና ቸኮሌትም ስላማራኝ ነበር...እናም አዲስአባም መሄድ ስለፈለኩ ግን ደግሞ እንደማልችል ስለገባኝ ነበር.፡
.ታላላቆቼ በድርጊቴ ግራ ቢጋቡም እኔ ግን በጣም አዝኜ ነበር..እና ለእዬቤ የራሱ አልጋ ከአዲስአባ እስኪመጣለት አልጋዬን አጋራሁት..እርግጥ አብዛኛውን ጊዜ እማዬ እያለ ሲቃዠና ሲንፈራገጥ እማዬ እየመጣች ወደራሷ መኝታ ቤት ትወስደውና ከማዬና አባዬ መሀል ይተኛ ነበር...እንደዛ ሲያደርግ እኔም ምን አለ አብሬው ሄጄ መሀከላቸው በተኛሁ እላለሁ፡፡እኛ ልጆቻቸው እንደው ፍርጥ እንላታለን እንጂ ከእነሱ ጋር የመተኛት እድል አናገኝም።እና በዚህ አይነት ሁኔታ እዬቤ ወንድማችን ሆነ፡፡ እቃቸው ከአዲስአባ መጣና ከእኛ ቤት እቃ ጋር ተቀላቀለ..ቤታቸውም እንደተከራየ  እማዬ ስታወራ ሰምቼያለሁ። አልጋውም መጣለትና ከእኔ አልጋ ጎን ቦታ ተመቻቸለት።ግን ስንላፋና ስንጫወት ቆይተን ሳናስበው ወይ እሱ አልጋ ላይ ጥቅልል ብለን ተቃቅፈን
2.5K viewsአትሮኖስ, 15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-18 20:05:16 ‹‹ያው ገና ልጅ ነሽ ብዬ ነዋ››
‹‹አንዳንድ ነገሮችን እኛ በቀላል ስላደረግናቸውና ስላገኘናቸው ለሌላውም እንደዛው በቀላሉ ይገኛሉ ማለት አይደለም….ያሉን ነገሮች ዋጋ በመገመት  ላይ ቀሺሞች ምንሆነው ለዛ ነው…..በል አሁን እንተኛ አለችና ከነልብሶ አልጋ ላይ ወጥታ ከውስጥ ገልጣ ጥጓን ይዛ ጥቅል ብላ ተኛች፡፡እኔም ጃኬቴን አውልቄ ሱሪዬንና ቲሸርቴን እንዳለ በመተው ልክ እሷ እንዳደረገችው ከውስጥ ገባሁና ተቃራኒውን ጠርዝ ይዤ ተጠቅልዬ ተኛሁ…፡፡ቢያንስ ከዚህ ቀደሙ የሚለየው ብርድልብሱን ወርውረልኝ በአልጋ ልብስ ተጠቅልላ አልተኘችም፡፡አንድ አንሶላ ለሁለት አንድ ብርድልብስ ለሁለት ተጋርተናል..ይህ ጥሩ እድገት ነው፡፡ስለዚህ ተመስጌን ብዬ ተኛሁ…ተኛሁ ማለት እንቅልፍ ወሰደኝ ማለቴ አይደለም፡፡እንደውም የሀሳብ ትብታብ ውስጥ ነው የተሰነቀርኩት፡፡
ሄዳለሁ ብዬ አልነበረ እንዴ…?ለምን ታዲያ..? እንዳልሄድ እንኳን ያን ያህል ሳትለምነኝ ተከትያት ገባሁ……ምን ፈልጌ ነው…?.የምታፈቅረው ሰው እንዳለ በግልፅና በማያሻማ ቋንቋ ነግራኛለች፤ለዛውም ጄኔራል….አይደለም አራት ኮከብ የደረደረ ጅኔራል ይቅርና የቀበሌያችን ታጣቂዎች ኃላፊ ልጅ ስጀነጅን ብገኝ ሌላ ሰበብ ተፈጥሮልኝ ከርቸሌ ልወረወርበት በምችለበት ሀገር እንዴት ነው እንዲ ያቃለልኩት….?ነው ወይስ እሷ እንዳለችው ፍቅር መቼም ቀላል ሆኖ አያውቅም ይሆን? ..እሺ አባባሉ  እውነት ይሁን ግን እኔ እንዳዛ የሚያስብል አይነት ፍቅር ከእሷ ይዞኛል እንዴ…?አረ ቆይ እስኪ ከዚህ በፊት የጀመርኩትን እና ህይወቴን እንዲሀ  ብትትኑን ያወጣውንስ ፍቅር እልባት መች አበጀሁለት..?እንዴ እልባት ማለት ወደኃላም መመለስ ያምረኛል እንዴ?…በራሴ የእብደት ሀሳብ ተገረምኩ…፡፡ሴትዬዋ እኮ የገዛ ልጆቾን እራሱ ጥላ አሜሪካ ከገባች 6 አመት ሞላት…በዚህ ስድስት አመት ውስጥ አንድ ቃል አልተለዋወጥንም፤ስለእሷ ምንም  ሰምቼ አላውቅም፤ ስለእኔም እርግጠኛ ነኝ ምንም ሰምታ አታውቅም ፡፡ታዲያ ምንድነው የማወራው…?የመገለባበጥ ድምፅ ሰማሁና ሀሳቤን ለጊዜውም ቢሆን ገደብኩት…ወደእኔ ዞረችና ክፍተቱን አጠበበችው…መታ ተለጠፈችብኝና አቀፈችኝ…እኔም በፀጥታ አቀፍኳት፡፡

ይቀጥላል
2.1K viewsአትሮኖስ, 17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-18 20:05:16 #እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_ዘጠኝ

ከምሽቱ አምስት ሰዓት ነው፡፡የምሰራበት ሆቴል ቤርጎ ይዛለች፡፡ስራ እንደጨረስክ ና ብላኝ ስለነበረ ስራዬን ጨርሼ ወደእሷ ለመሄድ እየተዘጋጀው ነው፡፡ስደርስ በረንዳ ላይ ባለ ወንበር ላይ ኩርምት ብላ ቁጭ ብላለች አይኖቾን ሰማይ ላይ ሰክታ ፈዛለች፡፡ከጎኗ ቁጭ አልኩና‹‹ጨረቃን እያየኋት ነው እንዳትይኝ?››አልኳት፡፡

‹‹አልኩህ››

‹‹እራስሽን ምን አሳየሽ?››

‹‹ማለት? ››

‹‹ያው እንቺም ጨረቃ ነሽ ብዬ ነዋ...››

‹‹ጨረቃ ነሽ ስትል በቀጥታ ምን ለማለት ፈልገህ ነው?››

"ከዚህ ንግግሬ ምን የማይገባ ነገር አገኘሽበት... ጨረቃ ነሽ ስል አደንዛዥ የሆነ ውበት ባለቤት ነሽ ማለቴ ነዋ።"

‹‹ጨረቃ እውነትም እንደምትለው አደንዛዥ ውበት አላት ?››

" የላትም እንዴ?"

‹‹እኔ ምን አውቄ እንደዛ ስላልከኝ ነው..ይህቺን አባባል ሁሉም ሰው ይጠቀማታል …ግን በትክክል በምሽት ስራዬ ብሎ የቤቱን በራፍ ከፍቶ በረንዳ ላይ ወጥቶ አንገቱን ወደ ሰማይ አንጋጦ፤ አይኖቹን ጨረቃ ላይ ተክሎ፤ ውበቷን ያስተዋለ ድምቀቷን ያጣጣመ..  ከመቶ ሺ አንድ ሠው ይገኝ ይመስልኸል...ግን ዝም ብሎ ስለሚባል ብቻ ትክክል ይሁን አይሁን ሳያውቅ ሁሉም ይደሰኩራል....

"እና ማጠቃለያሽ ጨረቃ ቆንጆ አይደለችም ነው?›

"አይ ነችምም አይደለችምም..ለምሳሌ እኔ ቆንጆ ነኝ?"

"ግጥም አድርጎ ...በጣም ውብ ነሽ"

"ከዚህ በፊት ሁለት ሰዎች ቀጥታ አሁን አንተ እንደቆምከው ፊቴ ቆመው ምንሽም የማያምር አስቀያሚ ሴት ነሽ ብለውኝ ያውቃሉ።እንደውም እንደዛ አይደለም.አስቀያሚ ወንዳወንድ ነገር ነሽ ነው ያሉኝ፡፡››

"እና ማንኛችንን አመንሽ?"

"ሁለታችሁኑም"

"ሁለታችንንማ ልታምኚ አትችይም ..አንቺ ወይ ቆንጆ ወይ አስቀያማሚ ነሽ.."

"አይ እንደየሁኔታው ቆንጆም አስቀያሚም ልሆን እችላለሁ...ውበት እንደየተመልካቹ ነው በሚለው ንግግር አምናለሁ...ለዚህ ነው ቆንጇ ነሽ ሲሉኝ ብዙ የማልፈነጥዘው አሰቀያሚም ሲሉኝ አንገቴን የማልደፋው።"

‹‹እና ማየቴን ላቁም?››

‹‹እንዳሰኘህ…ግን ጨረቃ በትከክልም  ምን ግዜ ውብ እንደምትሆን ታውቃለህ?››
‹‹አላውቅም ንገሪኝ ››
ጦር ሜዳ ፊት ለፊት ግምባር ላይ እያለህ የሆነ ግዳጅ  ተሰጥቶህ ከጓደኞችህ ጋር ድቅድቅ ባለ ጨለማ እየተጓዝክ መንገድ ጠፍቶህ ከጠላት ምሽግ ሰተት ብዬ ገባሁ ወይስ የጠላት ደጋፊ ከሆኑ ህብረተሰብ እጅ ወደቅኩ እያልክ አቅጣጫህን እንዴት እደምታስተካክል ግራ ገብቶህ እያለ ድንገት ብልጭ ብላ ስትወጣ…ከዛ እየደመቀች ስትሄድ….በቃ ውብ መሆኗ የሚገባህ የዛን ጊዜ ነው፡፡ምክንያም ህይወትህ የምታድንበት ጭላንጭል እድል ሰጥታሀለችና፡፡
‹‹ወይም ደግሞ›› ብዬ እኔ ቀጠልኩላት
‹‹ወይ ደግሞ.. በጣም የምትወጃትን ማለቴ የምታፈቅሪያት ልጅ  አባትዬው ከእቅፍሽ ነጥቀው ለሌላ ሊድሩብሽ መሆኑን ስትሰሚ እሷን በጠፍ ጨረቃ ከቤት አስኮብልለሻት በየጫካው ይዘሻት ስትጠፊ በዛን አስደሳችና ጭንቀት በተቀላቀለበት ወሳኝ ሰዓት ለመንገድሽ ብርሀን ሆና ከፊት ለፊትሽ ቦግ ስትል .. በዛን በክፉና በደስታ ቀን የመንገድሽ አጃቢና መሪ ብሎም  ለፍቅርሽም ድምቀት ስትሆን…አዎ የዛን ቀን ነው ጨረቃ ከውብም ውብ መሆኗን በደንብ የሚገባሽ››
‹‹አየህ ጨረቃን እንደየልምዳችን ነው ለውበቷ ትርጉም የሰጠነው..››
‹‹እንደልምዳችን  ማለት?አንቺ ወታደር ነሽ እንዴ?››ግራ ገብቶኝ ጠየቅኳት፡፡
‹‹አይ ማለቴ ጓደኛዬ ወታደር ነው….ታውቃለህ አይደል?››
‹‹አዎ የበቀደምለታው ጄኔራል አይደል?››
‹‹አዎ ..እሱ ነው››
‹‹ግን…እንዲህ ከሌላ ሰው ጋር በምትሆኚበት ጊዜ ችግር አይፈጥርብሽም?››
አይኖቾ በንዴት ግልብጥብጥ አሉ….‹‹እንደዚህ ከማን ጋር ስሆን አይተኸኛል?›አፋጠጠችኝ፡፡
‹‹አረ አረጋጊው…ከእኔ ጋ ለማለት ፈልጌ ነው›
‹‹ካንተ ጋርስ ምን አድረግናል?››
‹የባሰ አለ ሀገርህን አትልቀቅ› ይላል የሀገሬ ሰው..ድንብርብሬ ወጣ…ምን ብዬ በንዴት ወደላይ የተመነጠቀ ስሜቷን  ልመልሰው?‹‹ምንም አለማድረጋችንን እኮ የምናውቀው እኔና አንቺ ብቻ ነን…ቢያንስ ሁለት ቀን አንድ ክፍል ውስጥ አንድ አልጋ ላይ አድረናል…››
‹እ..እሱስ እውነትን ነው….ግን ያ ምንም ችግር የለውም..እሱም አመቱን ሙሉ ከሚስቱ ጋ ሲተኛ እኔ ምንም ብዬው አላውቅም፡፡››
‹‹ሚስቱ?›
‹‹አዎ ሚስቱ….ሚስትና ሶስት ልጆች አሉት››
‹‹ከባድ ነው››
‹‹አዎ ፍቅር ምን ጊዜም ቀላል ሆኖ አያውቅም››
‹‹ግን ምንድነው ስራሽ..?››
‹‹እሱን ማፍቀር?››
‹‹አይ ስራ መትተዳደሪበትን  ነው የጠየቅኩሽ..?››
‹‹ነገርኩህ ስራዬ እሱን ማፍቀር ነው….ገንዘብ ማገኝበትን ከሆነ የጠየቅከኝ ሌላ ጊዜ ነግሀለሁ…ግን ለራሴ የሚበቃ በቂ ገቢ አለኝ፡፡››
‹‹አይ ጥሩ ነው‹‹
‹‹ጥሩ ባይሆንስ ምን ምርጫ አለኝ....በል አሁን ይብቃን ገብተን እንተኛ››
‹‹አዎ ተነሽ.. ግን እኔ ወደቤቴ ልሂድ››
ፈገግ አለች‹‹ምነው ምን አሳቀሽ?››
‹‹አይ ወደቤት ልሂድ አባባልህ እራሱ ያስቃል..ምነው የጄኔራሉ ሽጉጥ ፊትህ ላይ ሲደቀንብህ በምናብህ አየህ እንዴ ››
‹‹ቀላል…ትቀልጂያለሽ እንዴ…?ገና በቅጡ እንኳን ያላየኋት እና ያላሰደኳት ልጅ አለችኝ..ድፍት ቢያደርገኝ ምን እላለሁ፡?፡››
ከተቀመጠችበት ተነስታ እጄን ይዛ ወደክፍሏ እያመረን ነው.. በራፍ አካባቢ ስንደርስ ነው ስለልጄ የነገርኳትን …ስትሰማ በድንጋጤ እጄን ለቀቀችና ባለችበት በመቆም አፍጥጣ አየችኝ፡፡
‹‹አንተ የእውነትን እንዳይሆን?››
‹‹ግራ ገባኝ ..ስለፍቅረኛዬ እያወራኋት ቢሆን ልሸመጥጣት እችል ነበር ..የልጅ ነገር ግን እንዴት አድርጌ…?መጀመሪያ አዳልጦኝ የተናገርኩ ቢሆን ወደኃላ ልመልሰው ግን እልፈለኩም …ቀጠልኩበት፡፡
‹‹አዎ ልጅ..አለቺኝ..የ7 አመት ልጅ..ተአምር ትባላለች››
‹‹ከዚህ በፊት ግን ፍቅረኛም ሚስትም እንደሌለህ የነገርከኝ መሰለኝ››
ይሄን ደግሞ መች ይሆን የቀባጠርኩላት…ማስታወስ አልቻልኩም፡፡አሁን ወደፊት ተንቀሳቅሰን በራፍ ጋር ደርሰናል….በእጇ ያንጠለጠለችውን ቁልፍ በማስተካከል በራፉን እየከፈተች ነው‹‹አዎ አሁንም  ሚስትም ፍቅረኛም የለኝም ….እውነቴን ነው››
ወደውስጥ ገባች…ሄዳለሁ ያልኩት ሰውዬ ተከትያት ወደውስጥ ገባሁ ..መልሳ በራፉን ከውስጥ ቆለፈችው፡፡አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች፡፡ከጎኗ ተቀመጥኩና ወሬዬን ቀጠልኩ፡፡
‹‹ነገሩ ውስብስብ እና የድሮ ታሪክ ነው… ሀይስኩል ተማሪ እያለው ነው የልጅ አባት የሆንኩት››
‹‹ታድለህ….ምን አለ እኔም ከእናቴ ቤት ሳልወጣ አንድ ዲቃላም ቢሆን ወልጄ በሆነ››
‹‹እውነትሽን ነው?፡፡››
‹አዎ..እውነቴን ነው…..የህይወቴ አንዱ ህመም የልጅ እናት ካለመሆኔ ጋ የተያያዘ ነው…››አይኖቾ በእንባ ተሞሉ…አረ ዘረገፈችው፡፡
‹‹ታዲያ እኮ አሁንም  ይቻላል.. ገናነው አልረፈደም…ሶስትም አራትም ልጅ መውለድ ትችያለሽ››
ኩስትርትር ብላ‹‹መቻሌን በምን አወቅክ?››በሚል ጥያቄ አስበረገገችኝ፡፡
2.0K viewsአትሮኖስ, 17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-17 23:42:01 የስልክ ቁጥሮን መጨረሻ በመጫን እድሎን ይመልከቱ
342 viewsENFALOT ° , 20:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ