Get Mystery Box with random crypto!

ATC NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ atc_news — ATC NEWS
ርዕሶች ከሰርጥ:
Dambidollouniversity
Dv
Scamalert
Fastmereja
የሰርጥ አድራሻ: @atc_news
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 116.34K
የሰርጥ መግለጫ

#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2024-04-21 08:23:21
ይኼ ከወላይታ ዩኒቨርስቲ የተማሪ መመገቢያ አዳራሾች አንዱ ላይ የተለጠፈ ማስታወቂያ ነው።

"ዩኒቨርስቲው በጀት ስለጨረሰ የተሰጣችሁን ብሉ" ነው አንድምታው። ወላጅ/አሳዳጊ ልጁን ወደ ዩኒቨርስቲ ሲልክ መንግስትን አምኖ ነው። "ልጄ ቀለም ይቆጥርልኛል" ከሚለው ባሻገር "ቤት እንዳለውም ባይሆን ቢያንስ ልጄ አይራብም፣ ደህንነቱ ይጠበቃል" የሚል ያልተፃፈ የጋራ ውሉን ተማምኖ የአብራኩን ክፋይ ስስቱን ወደ ትምህርት ተቋማት ይሰዳል።

መንግስት ለነዚህ የትምህርት ተቋማት በጀት መድቦ አደራውን ለመወጣት እንደሚሞክር ቢጠበቅም፤ ለምግብ የተሰጠኝ ገንዘብ ከወራት በፊት አልቋል የሚል ዜና ያውም ለተማሪዎቹ ምጣኔ እና ኃብት አስተዳደርን ከሚያስተምር ተቋም ሲነገር ያስደነግጣል... ያሳፍራል... አይደለም ወላጅን ማንኛውንም ሰው ጭንቀት ላይ ይጥላል።


እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ እንጠይቃለን:

1. ለአመት የተበጀተ በጀት በምግብ ዋጋ ንረት ግማሽ ላይ የሚያልቀው ምግቡን የሚገዙት ከዚምባቡዌ እና ቬንዙዌላ ነው ወይ? በጀቱ ሲበጀት ይህን የገበያ ለውጥ ታሳቢ ማድረግ ለምን አልተቻለም?

2. ትምህርት እንዳይቋረጥ ባለው ጥሬ ዕቃ አገልግሎት እየሰጠሁ ነው ያለው ዩኒቨርስቲው የጠቀሳቸው ጥሬ ዕቃዎች መቼ የገቡ፣ በምን አይነት የንፅህና ይዞታ ላይ ያሉ፣ ምን ያህል ጊዜ የሚያቆዩ ናቸው?

3. በህክምና ምክንያት የተለየ ምግብ መብላት ያለባቸውን ተማሪዎችስ እንዴት ለማስተናገድ ታስቧል?

3. ወትሮም ሆድ ጠብ የማይለው ምግብ መጠን እና ጥራቱ ሲያንስ የተማሪዎች ጤና እና ንቃት የሚያሳርፈውን ጉዳት እንዴት ሊያካክሱት አሰቡ? የልጆቹ የትምህርት አቀባበል ላይ ተፅዕኖ አይኖረውም?

Surafel Dereje
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
15.7K viewsMuJa. M, 05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 19:11:02
" ለኤጀንሲዎች ፈቃድ መስጠትም ሆነ መቆጣጠር የሚመለከተው እኛ ነው " - የስራና ክህሎት ሚኒስቴር

ዜጎችን ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ፍቃድ ለስራና ክህሎት ሚኒስቴር ብቻ የተሰጠ ሃላፊነት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በዚህ ጉዳይ በሚኒስቴሩ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት የኤጀንሲዎች ፈቃድ መስጫ ዴስክ ሃላፊ አቶ ተክሌ ተስፉ ለመናኸሪያ ሬዲዮ 99.1 ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

" አሁን ላይ በተለያዩ ከተሞች በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ኤጀንሲዎች ሰዎችን ' ካናዳ እና ወደ ሌሎችም የውጭ ሀገራት ስራ እናስቀጥራችኃለን ' በሚል የሚያስተላለፉት ማስታወቂያ ፈጽሞ ፈቃድ የሌለው እና ህገ ወጥ ነው ' ብለዋል።

ይህን ስራ በሚሰሩት ላይ በጥቆማና በፍለጋ ሲደረስባቸው እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ገልጸዋል።

" ለኤጀንሲዎች ፈቃድ መስጠቱንም ሆነ መቆጣጠሩንም የሚመለከተው የመንግስት ተቋም ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በፌደራልም በክልልም ያሉ ኤጀንሲዎች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ፈቃድ ከተሰጣቸው ብቻ ስራው ላይ መሰማራት እንደሚችሉ አስገንዝበዋል።
                    
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እየተበራከቱ መጥተዋል ያሏቸው ህገ ወጥ ኤጀንሲዎችን በጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል።

ዜጎችን ያለ ፍቃድ " ወደ ውጭ እንልካለን " የሚሉ ህገ ወጦች ምንም አይነት እውቅና የሌላቸው መሆኑን ህብረተሰቡ እንዲረዳው ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው (መናኸሪያ 99.1 ኤፍ ኤም) በሰጡት ቃል አስገንዝበዋል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
16.7K viewsMuJa. M, 16:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 19:08:04
በሁለቱም ቅርንጫፎቻችን (ሜክሲኮና መገናኛ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች ከሁሉም ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

Graphics Design
Interior Design
Digital Marketing
Adobe photoshop
Website Design
Programming Language
Video Editing
Database
Basic Computer
Accounting Softwares (Peachtree/ Queeck books)
Engineering Softwares (Autocad,Etabs, Civil 3d,Reviet, solid work, bill of quantity, software engineering courses)
SPSS & STATA
MS-Project
  Foreign (English, Arebic, German, Chinese, French, Italy, swedish, Norway, Spanish, Turkish..) & Local (Amharic, Oromiffa, Tigrigna, Geez..) Languages

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

አድራሻ:-1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)
            2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት(ትንሹ ኬኬር)

0910317675/0991929303/0991929304
@Top_trainings

Join our telegram channel
https://t.me/topinstitutes
14.7K viewsMuJa. M, 16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 12:41:30
#Update

የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?

ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ በማሰባሰብ በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በኩል አረጋግጠው ባሳለፍነው ሳምንት ለትምህርት ሚኒስቴር መላካቸውን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
19.3K viewsMuJa. M, 09:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-19 19:40:32
#Update

የመውጫ ፈተና አገልግሎት ክፍያ

ከኢ...ዲ.ሪ.ት/ሚ/ር በቁጥር 8/342/562/16 በቀን 09/08/2016 ዓ.ም በተፃፈው ደብዳቤ መሰረት ከሰኔ 14-212016 ዓ.ም ድረስ ለሚስጠው የመውጫ ፈተና አገልግሎት ክፍያን አስመልከቶ ተፈታኝ ተማሪዎች #እያንዳንዳቸው 500.00 /አመስት መቶ ብር/ እስከ ሚያዝያ 15/2016 ዓ.ም ድረስ እንዲከፍሉ አሳውቋል።

በዚሁ መሰረት በተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ የዘንድሮ አመት ተመራቂ ተማሪዎች ክፍያውን ይከፍሉ ዘንድ ዩንቨርሲቲዎች እያሳሰቡ ይገኛል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
22.8K viewsMuJa. M, 16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 20:48:11
ለመጨረሻ ግዜ የወጣ ማስታወቂያ
#WachamoUniversity

መጋቢት 06/2016 ዓ/ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተፈጠረው የሲስተም ችግር ምክንያት የባንኩን ገንዘብ በማጭበርበር ገንዘብ ያወጣችሁ ወይንም ያዛወራችሁ ተማሪዎች እስከ 04/08/2016 ዓ/ም እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ገንዘቡን ለባንኩ እንድትመልሱ እና የመለሳችሁበትን ማረጋገጫ /ደረሰኝ/ ከባንኩ እንድታመጡ በቀን 03/08/2016 ዓ/ም ጥብቅ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡

ስለሆነም በማስታወቂያው መሠረት ገንዘቡን የመለሳችሁ ተማሪዎችን እያመሰገንን፤ እስከ አሁን ገንዘቡን ለባንኩ ያልመለሳችሁ ከዚህ በታች ከ1 እስከ 55 ድረስ ስም ዝርዝራችሁ የተገለጠው ተማሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ እስከ 11/08/2016 ዓ/ም ድረስ እንድትመልሱ እያሳሰብን ፤ ገንዘቡን የማትመልሱ ተማሪዎች እርምጃ ለመውሰድ የምንገደድ መሆኑን በጥብቅ እናስታውቃለን። (ዩንቨርስቲው )


ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
14.0K viewsMuJa. M, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 19:46:35
#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ከዚህ በታች በተገለፀው የትምህርት መስክ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ በመምህርነት በቋሚ ኮንትራት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ የሥራ መደብ፦ መምህርነት
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 16
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ በህክምና የመጀመሪያ ዲግሪ
➤ የሥራ ቦታ፦ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ
➤ የመመዝገቢያ ጊዜ፦ ከሚያዝያ 8/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ብቻ
➤ የምዝገባ ቦታ፡- አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ የሰው ሃብት አስተዳደር 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 5

Note:

አመልካቾች ለምዝገባ ስትሔዱ የ8ኛ እና 10ኛ/12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት፣ የመጀመሪያ ዲግሪ ማስረጃ ሰርቲፊኬት እንዲሁም የሙያ ፍቃድ ምዝገባ የታደሰ ዋናውና የማይመለስ አንድ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡

አመልካቾች የመጀመሪያ ዲግሪ ውጤታችሁ 3.00 እና ከዚያ በላይ ሊሆን ይገባል፡፡

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
13.8K viewsMuJa. M, 16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 10:18:36
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ እንዲገባ ተገቢው ድጋፍ ሊደረግለት እንደሚገባ ተገለጸ
***********

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ እንዲገባ ተገቢው ድጋፍ ሊደረግለት እንደሚገባ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመላክቷል።

ቋሚ ኮሚቴው በአካል በመገኘት የዩኒቨርሲቲውን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክቷል፤ የዩኒቨርሲቲውን ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራንን እና ሰራተኞችም አወያይቷል።

በውይይቱ ወቅት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ችግሮቹን በትዕግስት በመቋቋም የመማር ማስተማር ስራው እንዲጀመር በማድረጉ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል።

ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ መንግስት ተጨባጭ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው ያሉት ነገሪ (ዶ/ር)፤ አሁንም በዩኒቨርሲቲው እና ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በችግርነት የሚነሱ የበጀት፣ ውዝፍ የደመወዝ ክፍያዎችና ሌሎች መንግስት ደረጃ በደረጃ እየፈታቸው የሚሄዱ መሆኑን ጠቁመዋል።

#EBC
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
15.2K viewsMuJa. M, 07:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 20:58:43 የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
__

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Health Officer, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Technology, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatrics Nursing እና Emergency & Critical Care Nursing ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች በግንቦት 2016 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡
ስለሆነም አዲስም ሆነ ነባር፣ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የኦንላይን ምዝገባው ከሚያዚያ 7/2016 እስከ ሚያዚያ 21/2016 ዓ.ም ብቻ የሚቆይና ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦

- የግል ትምህርት ተቋማት ተመዛኞች ከምዝገባ በፊት የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) Authenticate ማስደረግና ስማችሁን ከባለስልጣኑ ወደ ጤና ሚኒስቴር ማስላክ ይጠበቅባችኋል፡፡

- ከጥር 1/2015 ዓ.ም በኋላ የተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የትምህርት ሚኒስቴር መውጫ ፈተና(Exit Exam) ማለፍ ይጠበቅባችኋል፡፡

- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ #MoH


ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
15.7K viewsMuJa. M, edited  17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 19:22:48 በቴሌብር ሱፐር አፕ መረጃ መለዋወጥ የሚያስችል ሥርዓት ተዋወቀ።

ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌብር ሱፐር አፕ መተግበሪያው ላይ የሚካተቱ ተጨማሪ አገልግሎቶችን በዛሬው ዕለት አስተዋውቋል።  በዛሬው ዕለት ካስተዋወቀው አገልግሎት አንዱ "ቴሌብር ኢንጌጅ" የተሰኘው አገልግሎት አንዱ ነው።

"ቴሌብር ኢንጌጅ" ሦስት መሰረታዊ ዓላማዎችን ለማሳካት የተጨመረ አገልግሎት መሆኑን የገለጹት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፥ ገንዘብ ማስተላለፍ፤ ማኅበራዊ ትስስር መፍጠርና ማጋራትን መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።

ይህ አዲስ አገልግሎት በግለሰብም ሆነ በቢዝነስ ደንበኞች መካከል የተናጠል ወይም የቡድን የቀጥታ ውይይቶችን (online chat) ለማድረግ የሚያስችል ሲሆን የድምጽ፤ የፎቶ፤ የቪዲዮ፤ የፋይል መልዕክቶችን መላላክ ያስችላል።

በተጨማሪም በውይይት ወቅት ገንዘብ ማስተላለፍ የአየር ሰዓት መግዛትና መላክን ያካትታል። ከዚህም በተጨማሪ የተገልጋይ አካውንት መክፈት(ማስተካከል)፤ የጓደኝነት ጥያቄ ማቅረብ መቀበል በአዲሱ አገልግሎት የተካተቱ ናቸው።

በግሩፕ ውስጥ ሥጦታ መላላክን የሚያበረታታው "ሻሞ" የተሰኘ አገልግሎትም የተካተተ ሲሆን ለሰዎች ቀጥታ መሸልም ወይም እድለኛ ለሆኑ ሰዎች ሽልማት ማቅረብ ያስችላል።

ቴሌብር ኢንጌጅ የማኅበራዊ ሚዲያ ይሆን?

ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ አገልግሎቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት "አዲሱ አገልግሎት ከሶሻል ሚዲያ ያልተናነሰ ፊቸር ያለው ነገር ግን ስሻል ሚዲያን ለመተካት ሳይሆን የመጣው ዲጂታል ህይወትን ለማቅለል [ነው] " ሲሉ አስረድተዋል።

ዛሬ የተዋወቀው ሌላኛው አገልግሎት "የዴቨሎፐርስ ፖርታል" ምንድን ነው?

ኩባንያው "የዴቨሎፐርስ ፖርታል" የተሰኘ ሲስተሞችን ከቴሌብር ሱፐርአፕ ጋር ለማስተሳሰር (integrate) ያግዛል የተባለውን ሥርዓት አስተዋውቋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ እንደገለጹት አሁን ላይ ወደ 237 የንግድ ተቋማት እንዲሁም 108 የሚሆኑ የመንግስት አገልግሎቶች የክፍያ ሥርዓታቸውን ከቴሌብር ጋር ማስተሳሰራቸውን ጠቅሰው ይህ ግን በቂ አለመሆኑን አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም ሲስተሞችን ከቴሌብር ጋር ለማገናኘት ከ2 እስከ 3 ወራት ይፈጅ የነበረ ሲሆን አሁን ይፋ በተደረገው ሥርዓት ግን ተቋማት በሁለት እና በሦስት ቀናት ውስጥ ሥርዓታቸውን ከቴሌብር ሥርዓት ጋር ማስተሳሰር ይችላሉ ተብሏል።

የቴሌብር ሱፐር አፕን ከኢንተርኔት ክፍያ ነጻ (offline) መጠቀም ይቻላል?

የቴሌብር ሱፐር አፕ ከዚህ ቀደም ደንበኞች ሲጠቀሙ የነበሩትን አገልግሎቶች ጨምሮ አዲስ የተዋወቀውን አገልግሎት ያለምንም የኢንተርኔት ክፍያ መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።

ይህም ኩባንያው ባለፉት ጊዜያት የራሱን የክላውድ መሰረተ ልማት በመዘርጋቱ "የራሳችንን ዳታ ራሳችን እንድንጠቀም አስችሎናል" ሲሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።

ይህም ሌሎች የኢንተርኔት አገልግሎቶች ቢቋረጡ እንኳን አገልግሎት መስጠት ያስችለዋል ተብሏል።

የቴሌብር ቁጥራዊ መረጃዎች ምን ይላሉ?

- በሦስት ዓመት ውስጥ 44.5 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራት ችሏል።

- በሦስት አመት ውስጥ 775 የገንዘብ ዝውውሮች የተደረጉ ሲሆን ከ2 ትሪሊየን ብር በላይ አንቀሳቅሷል።

- ዛሬ ላይ በቀን 5 ቢሊዮን ትራንዛክሽን ይፈጸምበታል።

#TikvahMagazine
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
14.7K viewsMuJa. M, 16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ