የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ እንዲገባ ተገቢው ድጋፍ ሊደረግለት እንደሚገባ ተገለጸ *********** የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ እንዲገባ ተገቢው ድጋፍ ሊደረግለት እንደሚገባ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመላክቷል። ቋሚ ኮሚቴው በአካል በመገኘት የዩኒቨርሲቲውን የስራ እንቅስቃሴ ተመልክቷል፤ የዩኒቨርሲቲውን ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራንን እና ሰራተኞችም አወያይቷል። በውይይቱ ወቅት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ችግሮቹን በትዕግስት በመቋቋም የመማር ማስተማር ስራው እንዲጀመር በማድረጉ ሊመሰገን ይገባል ብለዋል። ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ መንግስት ተጨባጭ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው ያሉት ነገሪ (ዶ/ር)፤ አሁንም በዩኒቨርሲቲው እና ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በችግርነት የሚነሱ የበጀት፣ ውዝፍ የደመወዝ ክፍያዎችና ሌሎች መንግስት ደረጃ በደረጃ እየፈታቸው የሚሄዱ መሆኑን ጠቁመዋል። #EBC ለጥቆማ @atc_newsbot https://t.me/atc_news 15.2K viewsMuJa. M, 07:18