Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.60K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-06-04 11:34:10
በአማራ ክልል ወልቃይት ጠቀዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በሁመራ፣ ዳንሻ እና ማይካድራ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው።

ከሰልፎቹ መካከል በፎቶ
11.3K views08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 17:23:25
"በመስኖ ከለማው ስንዴ 4 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ያህሉ ምርት ተሰብስቧል" የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ
ባሕር ዳር: ግንቦት 13/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል በ2015 ዓ.ም በበጋ መስኖ ከ213 ሺህ 232 ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል። ከዚህም 10 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል የስንዴ ምርት ለማምረት ታቅዷል፡፡ በሥራው ላይ ከአንድ ሚሊየን በላይ አርሶ አደሮች ተሳትፈውበታል፡፡

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የመስኖ ባለሙያ ተሻለ አይናለም በዘር ከተሸፈነው መሬት ውስጥ ከ75 በመቶ በላይ መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

እስካሁን 159 ሺህ 697 ሄክታር መሬት የታጨደ ሲኾን 136 ሺህ 664 ሄክታር መሬት ተወቅቶ ወደ ጎተራ ገብቷል ብለዋል፡፡ ከዚህም 4 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል የስንዴ ምርት መሰብሰቡንም ጠቁመዋል፡፡

አቶ ተሻለ አርሶ አደሮች የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ በመሠብሰብ በበልግ ዝናብ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያደርጉትን ርብርብ አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ትርንጎ ይፍሩ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO
አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport
አሚኮ እውነታ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck
4.5K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 15:15:21
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚመራው የሚኒስትሮች የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ዛሬ ተጠናቀቀ።

ባሕር ዳር: ግንቦት 12/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚመራው የሚኒስትሮች የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ዛሬ ተጠናቅቋል።

የሚኒስትሮች የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ 2ኛውን የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳን ዛሬ መመልከቱም ተገልጿል።

በመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀጣይ ተግባር አቅጣጫዎችን አስቀምጠው የ100 ቀን ግምገማው ዛሬ መጠናቀቁን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO
አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport
አሚኮ እውነታ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck
9.0K views12:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 15:45:17
ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት ጋር ብሔራዊ ሙዚየምን ጎበኙ

ባሕርዳር : ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ)ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ እና የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ብሔራዊ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡

በኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት የተመራው የልዑካን ቡድን ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፥ በነበራቸው የቆይታ ጊዜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምን ጨምሮ ሌሎች በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን ተዟዙረው ጎብኝተዋል፡፡

የጉብኝቱ መርሐ ግብር በቱሪዝም ሚኒስቴር እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጋራ ትብብር የተዘጋጀ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO
አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport
አሚኮ እውነታ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck
10.5K views12:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 13:00:50
ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በ 4 ክልሎችና በድሬዳዋ ከተማ የተሳታፊዎች ልየታ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ ።

አዲስ አበባ፡ ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ) መግለጫውን የሰጡት ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አረዓያ በጋምቤላ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ሀረሬ ክልሎች እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተሳታፊዎች ልየታ ተግባር እንደሚጀመር ገልፀዋል።

ጉዳዩ ሀገራዊ ቢሆንም ሁሉንም ዜጎች ማሳተፍ ስለማይችል ዜጎችን በውክልና ማሳተፍ የግድ መሆኑን የተናገሩት ዋና ኮሚሽነሩ፤ ወረዳዎች 50 ሰዎችን መርጠው ይልካሉ። በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንም በውክልና የሚሳተፉበትን አሠራር መዘርጋታቸውንም ነው የተናገሩት ።የሃይማኖት ተቋማት፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ መምህራን እና የንግድ ተቋማትም በልየታ ሥራው ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሏል ።

ሥራ በሚጀመርባቸው አካባቢዎች ህኅብሰተሰቡ ተባባሪ እንዲሆን ሚዲያዎች ስለ ሀገራዊ ምክክሩ መረጃ እንዲሰጡም ዋና ኮሚሽነሩ ጥሪ አስተላልፈዋል። መረጣው እጅግ አካታች እና ተአማኒነት የተሞላበት እንደሚሆንም ተገልጿል ።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO
አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport
አሚኮ እውነታ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck
9.5K views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 11:43:29
8.4K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 11:21:19
የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜ ተገለፀ።

ባሕር ዳር: ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ)በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ኹኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የኾኑ ተማሪዎች ፈተና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ እንዲጠናቀቅ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጿል።

ፈተናውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በተሰጠው ትምህርት መሠረት ከማዕከል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት መላክ እንዳለበት ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።

በዚህም መሰረት በሴሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት የተቋማት የውስጥ ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንዲሁም በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንደሚያዝ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ተማሪዎችም በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን ለመከታተል ብቁ ኾነው ለመገኘት የሁለቱ ድምር አማካይ 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋልም ተብሏል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ፈተናውን በማሥተዳደርና ውጤት በመግለጽ በ2016 የፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ የኾኑ ተማሪዎችን ለይተው እስከ ሰኔ 30/2015 ዓም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ሥራ በማጠናቀቅ የ2016 የትምህርት መርሐ ግብር የተስተካከለ እንዲኾን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
8.0K views08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 11:12:48
"በኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካ ፓርላማ መካከል ሲደረግ የነበረው የልምድ ልውውጥ ጠቃሚ ግብዓት የተገኘበት ነው" አቶ ተስፋዬ በልጅጌ

ባሕር ዳር: ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ)በኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካ ፓርላማ መካከል ሲደረግ የነበረው የልምድ ልውውጥ ለምክር ቤቱ ቀጣይ ሥራ ጠቃሚ ግብዓት የተገኘበት መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ ገለጹ፡፡

በሁለቱ ምክር ቤቶች መካከል ሲደረግ የነበረው የልምድ ልውውጥ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

በመድርኩ ላይ የተገኙት አቶ ተስፋዬ የደቡብ አፍሪካ ፓርላማ ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ኢትዮጵያን በመምረጣቸው አመስግነው ፤ በነበረው ጊዜም ያገኙት ልምድ ለቀጣይ ምክር ቤታዊ ሥራ አጋዥ የሚኾኑ ግንዛቤዎችን ስለመውሰዳቸው ጠቅሰዋል፡፡

የሁለቱ ሀገራት ወዳጅነት ዘመናትን የተሻገረ ታሪክ ያለው በመሆኑ ይህንን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደዚህ ዓይነት ልምድ ልውውጦች አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል።

የሀገራቱን ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ወደ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ማሸጋገር እንደሚያስፈልግም ነው ያስረዱት፡፡

የደቡብ አፍሪካ ፓርላማ አባላትም በነበራቸው ቆይታ እና በልምድ ልውውጡ መደሰታቸውንና ቀጣይነት እንዲኖር ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

ላለፉት ሶስት ቀናት በኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካ ፓርላማ መካከል የልምድ ልውውጥ ሲደረግ መቆየቱ ከምክር ቤቱ ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
7.1K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 11:11:14
ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን

የሚያግዝ መንገድ ለመገንባት ስምምነት ተፈራረሙ

ባሕር ዳር: ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የፓሎች - ማቲያንግ - ማይውት - ፓጋክ መንገድን ለመገንባት በጁባ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

መንገዱ ምዕራብ ኢትዮጵያን ከሰሜን ምሥራቅ ደቡብ ሱዳን ጋር የሚያገናኝ የፍጥነት መንገድ መኾኑ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።

በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማርዲያት የተገኙ ሲሆን÷ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ.ር) እና የደቡብ ሱዳን የገንዘብ ሚኒስትር ዴር ቶንግ ንጎር (ዶ.ር) መፈራረማቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ÷ "ተስፋችን እርስ በእርስ ለመረዳዳት በጋራ መንቀሳቀስ ነው፤ ሕዝባችን ማየት የሚፈልገው ይህንን ነው፤ ይህ ሕዝባችንን የሚያስተሳስርና ፍላጎቶቹን የሚያሟላ ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክት ነው ብለዋል"።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ.ር) እንደተናገሩት የዚህ መንገድ መገንባት የሀገራቱን የንግድ ትስስር ከማጠናከር ባለፈ ሰው ሠራሽ የድንበር መለያየትን በማስቀረት የእህትማማች ሀገር ሕዝቦችን ይበልጥ ያቀራርባል።

በፊርማ ሥነ ሥርአቱ ወቅት ሀገራቱ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያሳልጡ የኤሌክትሪክና የነዳጅ ማስተላለፊያን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን ለማጠናከር ሃሳብ ተለዋውጠዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
7.6K views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 19:16:32
ምሽት 1:00 ትዕይንተ ዜና ባሕር ዳር: ግንቦት 10/2015 ዓ.ም (አሚኮ)

https://www.youtube.com/live/rAF5rgB9g-A?feature=share
9.3K views16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ