2023-05-09 15:09:34
"ኢትዮጵያ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ የሚችል የማምረት አቅም አላት" የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
ባሕር ዳር: ግንቦት 01/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ የሚችል የማምረት አቅም እንዳላት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡
ጽሕፈት ቤቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው ፅሁፍ÷ ኅብረትን፣ ልማትን እና አንድነትን ገንዘብ ካደረግን ኢትዮጵያ ማምረት ትችላለች ብሏል፡፡
ኢትዮጵያ በቂ መሬት፣ በቂ ውኃ፣ አምራች ወጣት፣ ምርትን መደገፍ የሚችል ኢነርጂ፤ የተሻለ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲሁም አስቻይ የሆነ የማምረቻ አውድ ያላት ሀገር መሆኗን አንስቷል፡፡
በማዕድን ዘርፍ ግብዓት መሆን የሚችሉ ማዕድናት በኢትዮጵያ እንደሚገኙ የጠቆመው ፅህፈት ቤቱ÷ በማዕድን ዘርፍ የተጀመሩ ሥራዎች ለኢንዱስትሪው ማደግ ከፍተኛ አስተዋፆኦ እንዳላቸው አመላክቷል፡፡
በተመሳሳይ በግብርና ዘርፍ የተጀመሩ ሥራዎች በከፍተኛ ደረጃ ለኢንዱስትሪው ግብዐት መሆን ይችላሉ ያለው ፅህፈት ቤቱ በዚህም የምርት ልማትን ማረጋገጥ እንደሚቻል አረጋግጧል፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/336LQaS
ቲክቶክ https://bit.ly/32rKF5J
ዲስከቨር አማራ አሚኮ https://www.facebook.com/DiscoverAmharaAMECO
አሚኮ ስፖርት https://www.facebook.com/AMECOSport
አሚኮ እውነታ ማጣሪያ https://www.facebook.com/AMECOFactCheck
10.1K views12:09