Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-30 09:29:37
የአቶ ግርማ የሺጥላ የአስከሬን ሽኝት ሥነ-ሥርዓት በወዳጅነት ፓርክ እየተካሄደ ነው።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የአቶ ግርማ የሺጥላ ቤተሰብ አባላት እና ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
9.7K views06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 08:17:13
የአቶ ግርማ የሽጥላ የአስከሬን ሽኝት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡

በወዳጅነት ፓርክ በከፍተኛ ወታደራዊ ሽኝት በመከላከያ እና በፌደራል ፓሊስ ማርች ባንድ አጃቢነት የክብር ሽኝቱ እየተካሄደ ነው፡፡

የአስከሬን ሽኝቱ በወዳጅነት ፓርክ ከተካሄደ በኃላ በቤተሰቦቻቸው ጥያቄ መሰረት የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ጌራ መሃል ሜዳ ነገ ሰኞ ሚያዝያ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ይፈጸማል፡፡
10.0K views05:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 13:33:35
የተለያዩ ተቋማት ኀላፊዎችና ሠራተኞች የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሽጥላ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሐዘን እየገለጹ ነው።


የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሴቶች፣ህጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ፣ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ እንዲሁም የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሽጥላና በግል ጥበቃዎቻቸው ህልፈተ ህይዎት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።


በክልሉ ሰላም እንዲሰፍንና ልማት እንዲረጋገጥ ህይወታቸው እስካለፈችበት ሰዓት ድረስ ሳይታክቱ ሕዝባቸውን ሲያገለግሉ እንደነበረ በሐዘን መግለጫዎቹ ተመላክቷል። ታጋይ ይሞታል ትግሉ ግን አይሞትምና በፅናት በየዘርፋችን ውጤታማ በመኾን ህልማቸውን እናሳካለን ብለዋል።


ተቋማቱ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እና ለመላው የክልሉ ሕዝብም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
4.0K views10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 12:11:05
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከተሞችና መሠረተ ልማት ቢሮ ፣ የአብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ከፍተኛ የሥራ አመራሮችና ጠቅላላ ሠራተኞች በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሺጥላ ድንገተኛ ግድያ የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።


ለመላው የክልሉ ሕዝብ፣ ለቤተሰቦቻቸው ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል።


በተመሳሳይ፤ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት በላከው የሐዘን መግለጫ በአቶ ግርማ የሽጥላና በጥበቃዎቻቸው ላይ የተፈጸመውን ግድያ በጽኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል። ድርጊቱም ለሀገርም ለክልሉም የማይጠቅምና ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ ይህንን ድርጊት በጽናት እንታገለዋለን ብሏል።


የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በድርጊቱ የተሰማቸውን ሐዘን በመግለጽ የአቶ ግርማ የሽጥላ ነፍስ በሰላም እንድታርፍ ምኞታቸውን ገልጸዋል።
5.1K views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 20:29:30
የአቶ ግርማ የሺጥላ የአስከሬን ሽኝት እሑድ ሚያዝያ 22/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚከናወን የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው ገለጸ፡፡

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው ዛሬ በሰጠው መግለጫ የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈጸመው ድንገተኛ ግድያ እንዳሳዘነው በመግለጫው ገልጾ ድርጊቱ የሚወገዝ ነው ብሏል፡፡

የሰኔ 15 የልብ ስብራት ሳይጠገን ሌላ ስብራት መከሰቱ አሳዛኝ ነው ያለው የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው ወንድምን በመግደል አሸናፊ መኾን አይቻልም፤ የድል ባለቤትም አያደርግም ነው ያለው፡፡ የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው ድርጊቱ የሕዝቡን ባሕል እና ሥነልቦና የማይመጥን እንደኾነም ገልጿል፡፡

የአማራ ሕዝብ በባሕሉ መሪውን ይጠብቃል ይንከባከባል፤ አልመራኝም ብሎ ሲያስብም እንዳይመራው ያደርጋል እንጅ ሰው እንዲሞት አይፈቅድም ነው ያለው የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው፡፡ ድርጊቱ ሀገርንም ክልሉንም እንደሚጎዳ አብራርቷል።

ድርጊቱ ከተሰማ በኃላ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ከፍ ባለ ሁኔታ እንዲፈጸም የተለያዩ ኮሚቴዎች መዋቀራቸውን አስረድተዋል፡፡

ዋናው ኮሚቴ በክልል ደረጃ መዋቀሩን የገለጸው ኮሚቴው የቀብር ቦታው በወላጆቹ ፍላጎት እና ጥያቄ መሰረት በተወለደበት ሰሜን ሸዋ ዞን ማሀል ሜዳ እንዲኾን ፍላጎት በመኖሩ ሌላ ኮሚቴም እንዲዋቀር መደረጉ ነው የተገለጸው፡፡

ቀብሩ ወደ ትውልድ ቀየው ከመሄዱ በፊት በአዲስ አበባ የሽኝት ፕሮግራም እንደሚኖር የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው አስረድቷል፡፡

የሽኝት ፕሮግራሙም እሑድ ሚያዝያ 22/2015 ዓ.ም ጠዋት ከ1ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ገልጾ በፕሮግራሙ ላይ ወዳጅ ዘመዶቹ እንዲገኙ ጥሪ ቀርቧል፡፡


ዘጋቢ፡- ምሥጋናው ብርሃኔ
9.1K views17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:51:55
የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ መሬት ቢሮ እና የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በአቶ ግርማ የሺጥላ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገለጹ።

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና መሬት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች፤ በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ድንገተኛ ህልፈተ ሕይዎት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል። ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል።

በተመሳሳይ፤ የአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ሚያዝያ 19 ቀን 2013 ዓ.ም ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን ከተማ በጉዞ ላይ በነበሩት የአማራ ክልል ብልጽግና ፖርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላና አብረዋቸው በነበሩ ወንድሞች ላይ በደረሰው የሞት አደጋ ከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን እንደተሰማው ገልጿል።

ጉባዔው ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል። ለሟቾችም ዕረፍተ ነፍስን ተመኝቷል።
10.2K views12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:50:35
ወንድሜ ግርማ ፣ነፍስህ በአፀደ ገነት ትረፍ!!

እጅግ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ ታሪክ ነው። ወንድሜ ግርማ የሺጥላ ህይወቱ ያለፈበት መንገድ ያማል!! ድካሙን በቅርብ እንደሚያውቅ የሥራ ባልደረባ ግርማ የመርህ ሰው፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሙሉ ጊዜውን ህይወቱ አስካለፈች ሰዓት ያገለገለ፣ ልበ ሙሉ ጀግና፣ ታታሪ፣ ቅን እና ሰውን እኩል የሚያገለግል ተግባቢ ነበር፡፡

ለእናቱ ፣ ለባለቤቱ፣ ለልጆቹ፣ ለቤተሰቦቹና ለመላ ኢትዮጵያዊያን መጽናናትን እመኛለሁ።

ፋንቱ ተስፋዬ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈጉባዔ።

ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም.
ባሕር ዳር
9.3K views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:49:48
8.2K views12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:49:44
8.3K views12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 15:49:41
8.3K views12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ