Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.60K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 700

2021-02-01 08:44:20
በኩር ጋዜጣ ጥር 24/2013 ዓ/ም ዕትም
https://www.amharaweb.com/በኩር-ጋዜጣ-ጥር-24-2013-ዓ-ም-ዕትም/
በኩር ጋዜጣ ጥር 24/2013 ዓ/ም ዕትም Download
6.8K viewsAmmaOnlineBOT, 05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 20:51:38
በ38ኛዉ የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና አማራ ክልል ከተዘጋጁት አምስት ዋንጫዎች ሦስቱን በመዉሰድ የበላይ በመሆን አጠናቀቀ።
ባሕር ዳር ፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ)
38ኛዉ የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ዛሬ ሱሉልታ ላይ ተካሂዷል።
አማራ ክልል ከተዘጋጁት አምስት ዋንጫዎች ሦስቱን በመዉሰድ የበላይ ሆኖ አጠናቋል።
በስድስት ኪሎ ሜትር ወጣት ሴቶች፣ በስምንት ኪሎ ሜትር ወጣት ወንዶች፣ በአስር ኪሎ ሜትር አዋቂ የሴትና የወንድ እንዲሁም የድብልቅ ዱላ ቅብብል ዉድድሮች ተካሂደዋል።
በዉድድሩ ከኬኒያ ፣ሱዳንና ደቡብ ሱዳን የመጡ አትሌቶችን ጨምሮ ከ800 በላይ አትሌቶች ተሳታፊ ሆነዋል። አትሌቶቹ ዉድድሩ ጠንካራ ፉክክር የታየበት እንደነበር ገልጸዉ በፈረንጆቹ መጋቢት 6 እና 7 ቶጎ ሎሜ ላይ በሚካሄደዉ የአፍሪካ ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና የኢትዮጵያን ስም ከፍ ለማድረግ ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽንም ቶሎ ወደ ዝግጅት እንዲገባ አትሌቶችና አሰልጣኞች ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተሳትፎና ዉድድር ዳይሬክተር አቶ አስፋዉ ዳኘ ዉድድሩ ዓላማዉን ያሳካ እነደነበር ተናግረዋል። ፌደሬሽኑ የተመረጡ አትሌቶችን በቅርቡ ለዝግጅት ሆቴል ያስገባል ብለዋል።
በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ጃንሜዳን ቀድሞ ለዉድድር ማዘጋጀት ባለመቻሉ 38ኛዉ የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና በሱሉልታ እንዲካሄድ ተደርጓል።
ዳይሬክተሩ የሱሉልታ ሜዳ ሀገር አቋራጭ ውድድርን ለማካሄድ መስፈርቱን የሚያሟላ አንደሆነ ገልፀዋል።
አትሌቶች በሰጡት አስተያየትም ከጃንሜዳ አንፃር የሱሉልታ የዓየር ፀባይ ለዉድድር ከባድ ነበር ብለዋል።
ዘጋቢ:– ባዘዘው መኮንን
8.1K viewsማሜ, 17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 20:42:48
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አብሮነቱን ለማስቀጠልና ለማጠናከር የህዝብ ለህዝብ ምክክር እያካሄደ ነው።
ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የህዝብ ለህዝብ ምክክሩ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ማክሰኞ ገበያ ነው እየተደረገ የሚገኘው። በውይይቱ ከዳባት፣ ከታች አርማጭሆ፣ ከምዕራብ አርማጭሆ፣ ጠለምትና በሰቲት ሁመራ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች የተወጣጣ ህዝብ ተሳታፊ ነው።
የውይይቱ ዓለማ ከ1984 ዓ.ም በፊት ጀምሮ የነበረውን የአካባቢውን ባህልና ወግ ወደ ነበረበት መልሶ ለማስቀጠል ያለመ ነው።
የውይይቱ ተሳታፊዎች የህወሃት አገዛዝ ቡድን ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብን አንድነቱን በማዳከም ያለ ማንነቱ ማንነት፣ ያለ ባህሉ ባህል ሰጥቶ ታሪኩንና ወጉን እያጠፋ በደል ሲያደርስ እንደቆየ አንስተዋል።
አሁን ላይ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የተገኘውን ድል እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ አንድነቱን አጠናክሮ የልማት ተጠቃሚ ለመሆን ዝግጁ እንደሆነም በውይይቱ ተገልጿል።
የልማትና የመልካም አስተዳደር እንቅፋት ናቸው ያሏቸውን እንደ ግድያና ስርቆት መሰል ሕገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልም ተወያዮቹ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ዘጋቢ፡- ኀይሉ ማሞ - ከወልቃይት
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
8.0K viewsማሜ, 17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 16:24:51
ባለፉት 6 ወራት 9 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡
https://www.amharaweb.com/ባለፉት-6-ወራት-9-ነጥብ-5-ቢሊዮን-ብር-ገቢ-መሰ/
ባለፉት 6 ወራት 9 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡ ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2013 በጀት ዓመት የ6 ወራት የገቢ አሰባሰብና በሌሎች ተግባራት አፈጻጸም ዙሪያ በየደረጃው ከሚገኙ የተቋሙ ባለድርሻ አካላት ጋር በባሕር ዳር የግምገማና የክለሳ ፕሮግራም እያካሄደ ነው፡፡ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኀላፊ ወይዘሮ [...]
8.3K viewsAmmaOnlineBOT, 13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 15:51:51
የላይኛው ርብ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ በታቀደለት ፍጥነት እንዲጠናቀቅ በቅንጅት ሊሠራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
https://www.amharaweb.com/የላይኛው-ርብ-የመስኖ-ፕሮጀክት-ግንባታ-በ/
የላይኛው ርብ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ በታቀደለት ፍጥነት እንዲጠናቀቅ በቅንጅት ሊሠራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአሁኑ ወቅት 21 በመቶ መድረስ የነበረበት የላይኛው ርብ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸሙ 10 በመቶ ብቻ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ እተገነባ ያለው በደቡብ ጎንደር ዞን ከ12 ሺህ በላይ የሊቦ ከምከምና የፎገራ ወረዳ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ [...]
8.1K viewsAmmaOnlineBOT, 12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 14:27:00
“ባለፈው ዓመት የተተከሉ የተዳቀሉ የፍራፍሬ ምርቶች ለቀጣይ ዓመት ለውጪ ገበያ የመድረስ አቅም አሳይተዋል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) ባለፈው ዓመት የተተከሉ የተዳቀሉ የፍራፍሬ ምርቶች ለቀጣይ ዓመት ለውጪ ገበያ የመድረስ አቅም ማሳየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር) ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው "ባለፈው ዓመት የጀመርነው አቮካዶን እና ፓፓያን የማዳቀል ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተከወነ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን የማድረስ ትልቅ አቅም አሳይቷል" ብለዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
7.5K viewsማሜ, 11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 14:26:02
የሰሜን ወሎ ዞን 18ኛው ዙር የባህል ስፖርቶች ውድድር በዋድላ ወረዳ አስተናጋጅነት ሲካሄድ ቆይቶ ተጠናቋል።
በዘንድሮው ዞናዊ ውድድር 12 ወረዳዎች በ6 የስፖርት ዓይነቶች በሴትና ወንድ ተሳትፈዋል።
ገበጣ፣ ሻህ፣ ቡብ፣ ኩርቦ፣ ትግልና የገና ጨዋታ ውድድር የተካሄደባቸው የባህል ስፖርቶች ናቸው፡፡
በውድድሩም ሃብሩ ወረዳ አጠቃላይ የውድድሩ አሸናፊ ሲሆን ራያ ቆቦ ወረዳ ደግሞ የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ዘጋቢ፡- ዋሴ ባየ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.9K viewsማሜ, 11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 13:42:57
https://www.amharaweb.com/13048-2/
በየዓመቱ የሚከበረውን የአገው ፈረሰኞች ማኅበር በዓልን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን የብሔረሰብ አስተዳደሩ ዋና አስተዳዳሪ ተናገሩ፡፡ ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ ባይነሳኝ ዘሪሁን የአገው ፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ዋና አስተዳዳሪው በመልዕክታቸው ሀገርን ከመበተን ለማዳን በተደረገው ርብርብ ልክ በየቦታው የሚፈሰውን የአማራ [...]
6.9K viewsAmmaOnlineBOT, 10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 13:22:08
“ፍትሕን እናሰፍናለን፣ የሕግ የበላይነትን እናረጋግጣለን ለዚህ ደግሞ ጊዜው አጭር ነው” አቶ አገኘሁ ተሻገር
ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር በሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኀበር 81ኛ ዓመት በዓል ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ በንግግራቸው “ወንድሞቻችን በዘራቸው ምክንያት ሞት፣ መፈናቀልና ስደት እየደረሰባቸው ነው፤ ወንድሞቻችን የጠላቶቻችን ዋነኛ ዒላማ ሆነው የእጅ አዙር የጥቃት ሰለባ በመሆናቸው የክልላችን መንግሥት ሁሌም ያንገበግበዋል” ብለዋል፡፡
“ፍትሕን እናሰፍናለን፣ የሕግ የበላይነትን እናረጋግጣለን ለዚህ ደግሞ ጊዜው አጭር ነው” ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳደሩ፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ የዛሬውን በዓል ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ የዘላለም ጠላት የሆነው የትህነግ ቡድን ላይመለስ በተሸኘበት ማግስት መከበሩ ነው ብለዋል፡፡ ሕግ በማስከበር ዘመቻው ተሳትፈው ደማቸውን ላፈሰሱና ህይወታቸውን መስዋዕት ላደረጉ ጀግኖች ምስጋና ይገባቸዋልም ብለዋል፡፡
አቶ አገኘሁ ባለፉት ዓመታት በዘራቸው ምክንያት የተፈናቀሉ፣ የተሳደዱና መገፋት የደረሰባቸው ወንድሞቻችን ሰቆቃ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲወገድና ሕግ እንዲከበር እየተሠራ እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ትርንጎ ይፍሩ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
7.0K viewsማሜ, 10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 12:10:11 የአዲስ አበባ አማራ ወጣቶች ማኅበር 7ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
ባሕር ዳር፡ ጥር 23/2013 ዓ.ም (አብመድ) የማኅበሩ ሰብሳቢ ወጣት ዓባይነህ አስማረ በጉባዔው ላይ እንደገለጸው ማኅበሩ ባለፉት ዓመታት የነበሩበትን አግላይ እሳቤዎች ተቋቁሞ በርካታ ሥራዎችን ሠርቷል፤ የተሳሳቱ ትርክቶችን ሞግቷል፤ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖችም ድጋፍ በማድረግ አማራነትን በተግባር አሳይቷል።
ማኅበሩ የተዛቡ ትርክቶችን ለማረም እየሠራ ቢሆንም አሁንም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ዜጎች በአማራነታቸው እየተገደሉ መሆኑ በእጅጉ አሳዛኝ ነው ብሏል ወጣት ዓባይነህ፡፡ “መፍትሄ እንዲሰጠውም አጥብቀን እንሰራለን፤ በአማራነት ለአማራነት በከፍታና በተደራጀ መንገድ መቆም አለብን” ብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኀላፊ አቶ አብረሃም ታደሰ የአዲስ አበባ አማራ ወጣቶች ማኅበር በከተማዋ በጎ ፈቃድ ሥራዎችን በመምራትና የአማራ ወጣቶችን አደራጅቶ በማንቀሳቀስ የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ቢሮውም ለማኅበሩ ሥራዎች ውጤታማነት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። ማኅበሩ ለበለጠ ጥንካሬ መሥራት እንዳለበትም አሳስበዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ዣንጥራር ዓባይ የአማራ ወጣቶች ማኅበር ለተመሰረተበት ዓላማ ስኬት የሠራቸው ሥራዎች የሚደነቁ መሆናቸውን ተናግረዋል። አቶ ዣንጥራር ዓባይ ማኅበሩ በጎ ማድረግን እሴታቸው ያደረጉ ወጣቶች የተሰባሰቡበት ነው፤ በተደራጀና ጨዋነት በተሞላበት መንገድ በአዲስ አበባ ለሚሠሩት ሥራ ከተማ አስተዳደሩ ዕውቅና ይሰጣል ብለዋል።
ማኅበሩ ከየትኛው የፖለቲካ ፓርቲ ነፃ ሆኖ በምክንያታዊነት ላይ የቆመና ለፍትሐዊ ተጠቃሚነት የሚታገል መሆን እንዳለበት አቶ ዣንጥራር ዓባይ አሳስበዋል።
“በመርህ ሞጋች በመሆንም ትግል ማድረግ አለበት፤ ከቆመለት ዓላማ ሳይዛነፍ ለተመሰረተለት የሕዝብ ጥቅም መሥራት ይገባዋል፤ ከተማ አስተዳደሩም ከጎኑ ነው” ብለዋል። በመድረኩ የታሪክ ተመራማሪዎቹ መምህር ታየ ቦጋለና ጋዜጠኛ ታዲዮስ ታንቱን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካቢኔ አባላት ታድመዋል። https://www.facebook.com/AmharaMassMediaAgencyAMMA/photos/pcb.1469624993212490/1469623793212610/
ዘጋቢ፡- ዘመኑ ታደለ - ከአዲስ አበባ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
7.2K viewsማሜ, 09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ