Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 692

2021-02-18 12:11:20
የኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት መኪናዎች ተርሚናል ተመረቀ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) በፌዴራል መንገዶች ባለስልጣን የገንዘብ ድጋፍ የተገነባው የኢትዮጵያ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት መኪናዎች ተርሚናል ተመርቋል።
በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አወል ዋግሪስ፣ የጅቡቲ ትራንስፖርት ሚኒስትር ሙሳ መሃመድ፣ በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ እንዲሁም ከሁለቱም ወገኖች የተውጣጡ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ተገኝተዋል፡፡
የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አወል ዋግሪስ በመክፈቻ ንግግራቸው ለተርሚናሉ መከፈት የጅቡቲ መንግስት ለሰጠው ድጋፍ አመስግነዋል።
ተርሚናሉ በየጊዜው እየጨመረ ለመጣው ወጪ ገቢ ሸቀጦችን የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም የተርሚናሉ መከፈት የሁለቱ ወንድማማቾች ህዝብ ግንኙነት በኢኮኖሚ ትስስርም እየተጠናከረ መሄዱን እንሚያመላክት ተናግረዋል፡፡ መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ነው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
4.9K viewsማሜ, 09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 12:08:57
የዩኒቨርስቲዎችን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሥራ የሚያግዙ የማኅበረሰብ አቀፍ አማካሪ ምክር ቤቶች ተቋቁመው ወደ ሥራ መግባታቸው ተገለጸ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) የዩኒቨርስቲዎች ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሥራ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ የማኅበረሰብ አቀፍ አማካሪ ምክር ቤቶች መቋቋማቸውን የሳይንስ እና ከፍተኛ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ከሚገኙ 51 የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ተመልሰዋል።
የሳይንስና ከፍተኛ የትምህርት ሚኒስቴር የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አመለወርቅ ህዝቅኤል እንደተናገሩት፣ በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የፌዴራል የፀጥታ ኃይሎች ወደ ተቋማቱ ወርደው የተቀናጀ ሥራ መሥራታቸው ለሰላማዊ የመማር ማስተማሩ ውጤት እንዲገኝ አስችሏል።
በተቋማቱ አስተማማኝ እና ቀጣይነት ያለው ሰላማዊ የመማር ማስተማር አውድ ተጠናክሮ ኢንዲቀጥል ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ማኅበረሰብ አቀፍ አማካሪ ምክር ቤቶች በየዩኒቨርሲቲዎች መቋቋማቸውንም ኃላፊዋ ገልጸዋል።
በእያንዳንዱ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንቶች የሚመራው ይህ አማካሪ ምክር ቤት የተቋማቱን አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ በቅርብ በመከታተል ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሔ እየሰጥ የሚሄድ ነው ተብሏል።
"በትምህርት ተቋማቱ እያንዳንዱ የሚባክን ጊዜ ከተማሪዎች ሕይወት የሚቆረስ ጊዜ ነው" ያሉት ዳይሬክተሯ፣ በተቋማቱ ያለው ጤናማ ሁኔታ እንዲቀጥል ሁሉም ሊተጋ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ሀገርም ሆነ ሀገርን ገንቢ ትውልድ ማፍራት የሚችል ተቋም ሊኖር የሚችለው ሰላም ሲኖር መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዋ፣ እያንዳንዱ ተማሪ የሚፈፅመው ድርጊቱ ሁሉ ምክንያታዊ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። ኢብኮ እንደዘገበው
4.6K viewsማሜ, 09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 12:06:39
የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ የደራሮ በዓል በዲላ ከተማ እየተከበረ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ የደራሮ በዓል የተከፈተው በጌዴኦ አባገዳዎች ነው፡፡
በዓሉን ለማክበር ከዞኑ ከአራቱም ማዕዘናት የተውጣጡ ታዳሚዎች በዲላ ከተማ ልዩ ልዩ የአደባባይ ትርዒት በማሳየት ወደ ዲላ ሁለገብ ስታዲየም በማምራት ላይ ናቸው፡፡
በዓሉ የመቻቻል፣ የፍቅር እና የአንድነት በዓል ነው፡፡
ምንጭ፡- የደቡብ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
4.8K viewsማሜ, 09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 11:28:53
በኢትዮጵያ የሲዊዲን አምባሳደር ሀንስ ሄኒሪክ ላንድኩስት እና የዩኒሴፍ ተወካይ አዴሌ ክሆድር የመተከል ተፈናቃዮችን ጎበኙ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) በኢትዮጵያ የሲዊዲን አምባሳደር ሀንስ ሄኒሪክ ላንድኩስት እና የዩኒሴፍ ተወካይ አዴሌ ክሆድር ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የተፈናቀሉ እና በአማራ ክልል ቻግኒ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ጎብኝተዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የሕፃናት ፈንድ (ዩኒሴፍ) ከኢትዮጵያ መንግስትና ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በመሆን ለተፈናቃዮች የጤና አገልግሎት፣ አልሚ ምግብ፣ የውሃና የንጽሕና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
4.7K viewsማሜ, 08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 11:28:09
ኢትዮ- ቴሌኮም የ4ጂኤልቲኢ አድቫንሲድ አገልግሎት በደቡብ ምስራቅ ሪጂን ሊጀመር ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮ- ቴሌኮም ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ የ4ጂ የኢንተርኔት አገልግሎት በደቡብ ምስራቅ ሪጂን ሊጀመር ነው::
አገልግሎቱን የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የ4ጂ የኢንተርኔት አገልግሎት በአዳማ፣ በአዋሽ መልካሳ፣ በሞጆ፣ በቢሾፍቱ፣ ዱከም እና በገላን ከተሞች እንደሚያስጀምር ነው የተገለጸው፡፡ መረጃው ኢትዮ- ቴሌኮም ነው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
4.7K viewsማሜ, 08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 11:06:05
የምርት ብክነትንና የጥራት መጓደልን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉ አርሶ አደሮች ተናገሩ፡፡
https://www.amharaweb.com/የምርት-ብክነትንና-የጥራት-መጓደልን-የሚ/
የምርት ብክነትንና የጥራት መጓደልን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉ አርሶ አደሮች ተናገሩ፡፡ ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) የምርት ብክነትን የሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሠራ መሆኑን የሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን የኢትዮጵያ ፕሮግራም አስታውቋል። ግበረ ሰናይ ድርጅቱ ከግብርና ሚኒስቴርና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ላለፉት 28 ዓመታት የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጅዎችን በማቅረብ ለምርትና ምርታማነት [...]
4.7K viewsAmmaOnlineBOT, 08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 11:00:57
የተለያዩ የቅጥር ማስታዎቂያዎች ጐንደርና ደብረ ማርቆስ
https://www.amharaweb.com/የተለያዩ-የቅጥር-ማስታዎቂያዎች-ጐንደር/
የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት በቅርቡ የአማራ ኤፍ ኤም ጎንደር 105.1 እና የአማራ ኤፍ ኤም ደብረማርቆስ 95.1 አካባቢያዊ ስርጭት ይጀምራል። በመሆኑም በወጣው የቅጥር ማስታወቂያ አመልካቾች እንዲወዳደሩ የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ጥሪ ያቀርባል። ለሕብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን! የተለያዩ_የቅጥር_ጐንደርና_ደብረ_ማርቆስ_2ዐ13 Download
4.7K viewsAmmaOnlineBOT, 08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 10:57:29
የትራንስፖርት ሚኒስቴር እና የአፍሪካ ልማት ባንክ በትራንስፖርት መሪ ዕቅድ ተግባራዊነት ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢፌዴሪ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ኤክስኪውቲቭ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ።
ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ኤክስኪውቲቭ ዳይሬክተር ቼፕሮ አሞስ ኪፕሮኖህ ጋር በቀጣይ 10 ዓመታት በሚተገበረው የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ የልማት ዕቅድ ተግባራዊነት ላይ ተወያይተዋል።
የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋር ሆኖ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን የትራንስፖርት ሚኒስቴር ገልጿል።
በተለይም ባንኩ በኢትዮጵያ ለልማት ሥራ ከሚያዉለው 1 ነጥብ 65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዉስጥ 31% በትራንስፖርት ዘርፍ ላይ እንደሚዉል ይታወቃል።
በሌላ በኩል በልማት ባንኩ ድጋፍና ብድር በሚሰሩ የትራንስፖርት መሰረተ ልማቶች እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ተግባራዊነት ላይ በሚታዩ አንዳንድ የአፈፃፀም ችግሮች ዙሪያም ተወያይተዋል።
የልማት ባንኩም የተለመደውን አጋርነት አጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ከሚኒስትሯ ጋር ተወያይተዋል።
ቀጣይ በሚኖሩ የልማት ስራዎች በተለይም ብሔራዊ የትራንስፖርት ፖሊሲን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችለዉን የትራንስፖርት ዘርፍ የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድን ለማሳካት ከባንኩ ጋር በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። መረጃው የትራንስፖርት ሚኒስቴር ነው፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
2.7K viewsማሜ, 07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 10:56:13
ደረጃቸውን ያልጠበቁ ትምህርት ቤቶችን ለማደስ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በመቀረጽ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች ኤጀንሲ ገለጸ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) በሀገሪቱ የሚገኙ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና የዳስ ትምህርት ቤቶችን ለማደስና ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ዳያስፖራው በተደራጀ መልኩ አስተዋጽዖ እንዲያበረክት ፕሮጀክቶች እየተቀረፁ መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጄንሲው ዋና ዳይሬክተር ሠላማዊት ዳዊት እንደተናገሩት ኤጀንሲው ከሚመለከታቸው የክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ የልማት ድርጅቶች፣ የዳያስፖራ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቶች ጋር በመሆን ፕሮጀክቶች ተቀርፀው ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተሠራ ይገኛል።
ትምህርት ቤቶችን በማደስ እና በመገንባት እንዲሁም በሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮች በየአካባቢው ያሉ የልማት ድርጅቶች፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎችም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅተው ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ዳያስፖራው በፕሮጀክቶቹ አተገባበር ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
በተለያዩ የዓለም ክፍል የሚገኙ ዲያስፖራዎች በሀገሪቱ ልዩ ልዩ አካባቢዎች የሚሠሩ ትምህርት ቤቶችን መደገፍ እንዲችሉ እየተሠራ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ኢትዮፕረስ ዘግቧል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
2.7K viewsማሜ, 07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-18 10:55:41
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክርቤት መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ።
ባሕር ዳር፡ የካቲት 11/2013 ዓ.ም (አብመድ) የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር ስምንተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀምሯል። ለሁለት ቀናት የሚቆየው መደበኛ ጉባዔ አጀንዳዎች የምክር ቤቱን 20ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባዔ እና አስቸኳይ ጉባዔ ቃለጉባዔ ገምግሞ ያጸድቃል፡፡
ጉባኤው የከተማ አስተዳደሩን የ2013 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም፣ የ2012 ዓ.ም የኦዲት ሪፖርት፣ የከተማ አስተዳደሩን ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደረጃ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እና የባሕር ዳር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የ2013 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸምን ገምግሞ ያጸድቃል፡፡
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርን የመሬት ካሳ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴን መሰየም እና ሹመቶችም ይካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
3.5K viewsማሜ, 07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ