Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 695

2021-02-16 14:54:57
በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት የተገነባው 14ኛው ትምህርት ቤት በደቡብ ክልል ተመረቀ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በደቡብ ክልል ከተገነቡት ሦስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ ዛሬ ለምረቃ በቅቷል፡፡
ጽሕፈት ቤቱ በመጀመሪያ ዙር በሁሉም ክልሎች ካስገነባቸዉ 20 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በደቡብ ክልል ከተገነቡት ሦስት ትምህርት ቤቶች አንዱ የሆነዉንና በጌዲኦ ዞን ገደብ ወረዳ ባንቆ ዳዳቱ ቀበሌ የተገነባው ትምህርት ቤት ነው በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ የተመረቀው፡፡
የተገነቡት ትምህርት ቤቶች 30 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎባቸዋል፤ ትምህርት ቤቶቹ በጌዲኦ ዞን ገደብ ወረዳ በሽካ ዞን ማሻ ወረዳ እና ደቡብ ኦሞ ዞን ሀመር ወረዳ እንደሚገኙ ከቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
ዛሬ የተመረቀዉ ባንቆ ዳዳቱ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቤተ ሙከራ፣ ቤተ መጽሐፍትና የኮምፒውተር ላብራቶሪ ያካተተ ነዉ፡፡
የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በደቡብ ክልል በሸካ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ያስገነባቸዉን ቀሪ ሁለት ትምህርት ቤቶች በቅርቡ እንደሚያስመርቅ ተገልጿል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.9K viewsማሜ, 11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 12:37:27 “የጣና በለስ ቁጥር አንድ የስኳር ፋብሪካ ከሶስት ወራት በኋላ ወደ ሙከራ ምርት ሊሸጋገር ነው” ስኳር ኮሮፖሬሽን
ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) በግንባታ ሂደት ላይ የነበረው የጣና በለስ ቁጥር አንድ የስኳር ፋብሪካ ከሶስት ወራት በኋላ ወደ ሙከራ ምርት እምንደሚሸጋገር ስኳር ኮሮፖሬሽን አስታወቀ፡፡
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለአንድ ዓመት ግንባታው ተጓቷል የተባለለት የጣና በለስ ቁጥር አንድ የስኳር ፋብሪካ፣ በሚቀጥሉት ሶስት ወራት ቀሪ የግንባታ ሂደቶችን አልፎ የፊታችን ግንቦት ወደ ሙከራ ምርት እንደሚገባ ኮርፖሬሽኑ ይፋ አድርጓል፡፡
የኮርፖሬሽኑ ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ጋሻው አይችሉህም እንደገለፁት በኮርፖሬሽኑ የተካሄደውን የለውጥ ሥራ ተከትሎ የተጀመሩትን የስኳር ፋብሪካዎች ለመጨረስ ነባሮችን ደግሞ የማምረት አቅም ለማሳደግ ግብ ተጥሎ ሲሰራ ነበር ብለዋል፡፡
የስኳር አቅርቦትን ለማሳደግ በተደረገ ጥረት ሀገራዊ የስኳር ምርት በ2011 ዓ.ም ከነበረበት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል በ2012 ወደ 3 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል ማሳደግ መቻሉንም ተናግረዋል፡፡
ከሰም፤አርጆ ዴዴሳ፤ኦሞ ቁጥር ሁለትና ሶስት የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ ተጠናቆ ወደ ሥራ በመግባታቸው የስኳር አቅርቦት እጥረትን መቀነስ እንደተቻለም ነው አቶ ጋሻው የገለፁት፡፡
በግንባታ ላይ ያለው ኦሞ ቁጥር አንድ የስኳር ፕሮጀክት የግንባታ አፈጻጸሙ 83 በመቶ ፤ አሞ ቁጥር 5 ደግሞ ግንባታው 27 በመቶ መድረሱም ተመልክቷል፡፡
በፀጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው የዘገየው የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ 93 በመቶ፤ ምዕራፍ ሁለት ግንባታ ደግሞ 85 በመቶ ደርሷል ተብሏል፡፡
ኮርፖሬሽኑ የስኳር ምርትን ለማሳደግ በስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት፤ የነባር የስኳር አምራች ማሽኖችን ብልሽት በመጠገን፤ በቂ የሸንኮር አገዳ አቅርቦት እንዲሁም የመፍጨትና ስኳር የማምረት አቅማቸውን ማሳደግ መቻሉን የስኳር ኮርፖሬሽን ማስታወቁን የዘገበው ኢብኮ ነው፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.9K viewsማሜ, 09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 12:35:45
የኢትዮ ሱዳን ጉዳይ የእርሻ ወቅት ሳይደርስ መፈታት እንዳለበት የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡
https://www.amharaweb.com/የኢትዮ-ሱዳን-ጉዳይ-የእርሻ-ወቅት-ሳይደር/
የኢትዮ ሱዳን ጉዳይ የእርሻ ወቅት ሳይደርስ መፈታት እንዳለበት የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) መንግሥት ትኩረቱን በትግራይ ክልል ሕግ ማስከበር ላይ ባደረገበት ወቅት ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሳ መግባቷ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያና ሱዳን በሚዋሰኑባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የሁለቱ ሀገራት ዜጎች ለዘመናት የቆየ ጠንካራ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትሥሥር አላቸው፡፡ ሱዳናውያን ወደ ኢትዮጵያ ገብተው የፈለጉትን ይሸምታሉ፤ ኢትዮጵያውያንም ወደ [...]
6.7K viewsAmmaOnlineBOT, 09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 11:46:59 የሱዳን ጦር በወረራ ከያዘው የኢትዮጵያ መሬት ለቆ እንዲወጣ የኢትዮጵያ መንግስት ተጨማሪ ስራዎችን እንዲያከናዉን ተጠየቀ፡፤
በድንበር አካባቢ በእርሻ ስራ የተሰማሩት ግለሰቦች በበኩላቸው የሱዳን ጦር በፈጠረባቸዉ የጸጥታ ስጋት ምክንያት ለመስራት መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡
6.7K viewsማሜ, 08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 11:03:01 አብሮነታችን ከሚታይባቸዉ ነገሮች መካከል ማዕድ በአንድ ገበታ አብሮ መመገብ ይጠቀሳል፡፡
በጋራ መመገብ ቤተሰባዊ አብሮነትን ያጠናክራል፤ የቅርበት ማሳያም ተደርጎ እንደሚታይ ነዉ የማህበረሰብ ጥናት ምሁራን የሚናገሩት፡፡
ለመሆኑ አብሮ በአንድ ማዕድ የመመገብ ልምዳቸው በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ሜሮን ጌታቸው በዚህ ዙሪያ ወዳዘጋጀችው መረጃ እንለፍ፡፡
6.8K viewsማሜ, edited  08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 10:58:26
የኮምቦልቻ ከተማ እና አካባቢዋ ነዋሪዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና ለብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡
ባሕር ዳር: የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) በሰልፉ ላይ የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰይድ መሐመድ፣ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ከማል መሀመድ (ዶ.ር) ተገኝተዋል፡፡
በሰልፉ ላይ ፅንፈኝነት የሰላምና የአብሮነት እሴት ፀር ነው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከጎንዎ ነን፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን የሚያደናቅፉ የውስጥ ኃይሎችን እናወግዛለን የሚሉና ሌሎች መልዕክቶች ተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ:- ሀያት መኮነን - ኮምቦልቻ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.7K viewsማሜ, 07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 10:55:13 በባህር ዳር ከተማ በህጋዊ መንገድ የመኖሪያ ቤት ለማግኘት በማህበር ተደራጅተው አመታት ቢቆጠሩም የቤት መስሪያ ቦታ አለማግኘታቸውን አስተያየታቸውን የሰጡ የማህበር አባላት ተናግረዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ከአማራ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ በክልሉ የተደራጁ የቤት ፈላጊ ማህበራትን ጥያቄ ለመፍታት መሬትን ከ3ተኛ ወገን የማስለቀቅ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ነዉ የገለጹት፡፡
6.1K viewsማሜ, 07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 10:35:20
በደሴ ከተማ ለብልጽግና ፓርቲና ለዶክተር ዐቢይ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) ደጋፊዎቹ ከከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመነሣትና ሆጤ ስታዲየም በመሰባሰብ የተለያዩ የድጋፍ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ነው።
ለድጋፍ ሰልፉ የወጡ የከተማዋ ነዋሪዎችም “ከብልጽግና ጋር ወደፊት”፤ “የጁንታውን ኀይል ለመደምሠሥ የተደረገውን ፖለቲካዊ አመራር እናደንቃለን”፤ “የአማራ ልዩ ኀይል፣ ሚሊሻ እና መከላከያችን ያደረጉትን ጀግንነት እናደንቃለን”፤ “የህዳሴውን ግድብ ግንባታ የሚያደናቅፉ ሴራዎችን እናወግዛለን”፤ “ከፋፋይነትን እና ብሔርተኝነትን እንፀየፋለን” እና መሠል መልእክቶችን እያስተላለፉ ነው፡፡
ዘጋቢ፡- ተስፋ ሞላ- ከደሴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.2K viewsማሜ, 07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 10:33:32
በአማራ ክልል የቆላ ስንዴን ለማልማት ከታቀደው 24 በመቶው በዘር መሸፈኑን ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡
https://www.amharaweb.com/በአማራ-ክልል-የቆላ-ስንዴን-ለማልማት-ከታ/
በአማራ ክልል የቆላ ስንዴን ለማልማት ከታቀደው 24 በመቶው በዘር መሸፈኑን ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡ የዘር እጥረት ለዕቅዱ አለመሳካት እንደ አንድ ምክንያት ተቀምጧል፡፡ ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአማራ ክልል የቆላ ስንዴን በአንደኛ ዙር መስኖ ለማልማት ከታቀደው 50 ሺህ 200 ሄክታር መሬት በአሁኑ ወቅት ከ17 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት መታረሱን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል [...]
5.5K viewsAmmaOnlineBOT, 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 10:29:29
የዋግኽምራ ብሔረሰብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 8ኛ ዓመት 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።
ባሕር ዳር: የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) ምክር ቤቱ በ2013 በጀት ዓመት 6 ወራት በብሔረሰብ አስተዳደሩ በአስፈጻሚ አካላት የተከናወኑ የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን በመገምገም የቀጣይ ሥራዎችን አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለፉት 6 ወራት የሥራ እንቅስቃሴንም ገምግሞ ያጸድቃል።
ምክር ቤቱ ልዩ ልዩ ሹመቶችንም መርምሮ እንደሚያጸድቅ ለ2 ቀናት የሚካሄደው የብሔረሰቡ ምክር ቤት መርኃ ግብር ያሳያል።
ዘጋቢ:- ስማቸው እሸቴ - ከሰቆጣ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.5K viewsማሜ, 07:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ