Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 698

2021-02-13 21:48:35
ለሀገራዊ መግባባት በሕገ መንግሥቱ ላይ የሚነሱ የማሻሻያ ጥያቄዎችን መመለስ እንደሚገባ ከአማራ ክልል የተውጣጡ የወረዳና የዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኀላፊዎች ተናገሩ።
https://www.amharaweb.com/ለሀገራዊ-መግባባት-በሕገ-መንግሥቱ-ላይ-የ/
ለሀገራዊ መግባባት በሕገ መንግሥቱ ላይ የሚነሱ የማሻሻያ ጥያቄዎችን መመለስ እንደሚገባ ከአማራ ክልል የተውጣጡ የወረዳና የዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኀላፊዎች ተናገሩ። ባሕር ዳር: የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) ሠላም ሚኒስቴር ያዘጋጀው ከወረዳ፣ ከዞንና ከክልል ለተውጣጡ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኀላፊዎች በሀገራዊ ሠላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በባሕር ዳር ከተማ [...]
7.8K viewsAmmaOnlineBOT, 18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 16:37:57
በአዲስ አበባ በሕገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ ከ2 ሚሊዮን ጄሪካን በላይ ፓልም የምግብ ዘይት በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ጀሞ ሚካኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በልዩ ስሙ አንበሳ ጋራዥ በሚባለው ቦታ በሕገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ ከ2 ሚሊዮን ጄሪካን በላይ ፓልም የምግብ ዘይት ዛሬ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በሕገ ወጥ መንገድ የተከማቸው ዘይት ሊያዝ የቻለው ፌዴራል ፖሊስ እና የላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከኅብረተሰቡ የደረሳቸውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ለ2 ሳምንታት ባደረጉት ጥብቅ ክትትል መሆኑን ኢብኮ ዘግቧል፡፡
8.3K viewsማሜ, 13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 16:35:17
በክልሉ እየተገነቡ ያሉ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ።
https://www.amharaweb.com/በክልሉ-እየተገነቡ-ያሉ-የመስኖ-ልማት-ፕሮ/
በክልሉ እየተገነቡ ያሉ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ። ባሕር ዳር ፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአማራ ክልል የሚከናወኑ የከፍተኛና መካከለኛ መስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን ያሉበትን ደረጃ ለማወቅና እያጋጠማቸው ያሉትን ችግሮች ለይቶ መፍትሔ ለመስጠት ውይይት እየተደረገ ነው። የክልሉ የከፍተኛና መካከለኛ የመስኖ ፕሮጄክቶች አስተባባሪ ኮሚቴ ነው ውይይቱን [...]
7.1K viewsAmmaOnlineBOT, 13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 16:12:32 በሚሠማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ለመሆን እንደሚተጉ በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቁ የአማራ አመራር አካዳሚ ተማሪዎች ተናገሩ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአማራ አመራር አካዳሚ በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 37 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ አስመርቋል፡፡ በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልመዋል፡፡
ከተሸላሚዎች መካከል አሳበች አይተንፍሱ አንዷ ናት፡፡ አሳበች አይተንፍሱ በፐብሊክ ፖሊሲና ሊደርሽፕ በሁለተኛ ዲግሪ 3 ነጥብ 93 በማምጣት በማዕረግ ተመራቂ ናት፡፡ ለበርካታ ዓመታት በባለሙያነትና በሥራ ኀላፊነት አገልግላለች፡፡
ጥንካሬን፣ ትዕግስትንና ራዕይ መሰነቋ በተሰማራችበት የትምህርት መስክ በማዕረግ እንድታጠናቅቅ እንደረዳት ተናግራለች፡፡ በአካደሚው በቆየችባቸው ጊዜያት ጽንሰ ሃሳብን ከተግባር ጋር አጣምራ በመማሯ በምትሠማራበት የሥራ መስክ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚረዳት ነግራናለች፡፡
አካዳሚው ለትምህርት ምቹና ጥሩ ድጋፍ የሚደረግበት በመሆኑ በቀጣይ በርካቶች የመማር እድሉን እንዲያገኙ እንዲመቻች መሠራት እንዳለበት ገልጻለች፡፡ አካዳሚው ጀማሪ ቢሆንም ያሉበትን እጥረቶች በአፋጣኝ በመፍታት እኛን ለውጤት አብቅቷል ብላለች፡፡
እንደ አሳበች ገለጻ ሴቶች “አንችልም” የሚለውን የአመለካከት እስር ቤት ሰብረው መውጣት አለባቸው፡፡ ሁሉም ሰው በተሠማራበት የሥራ መስክ ውጤት ለማስመዝገብ ማንበብ፣ መጠየቅ፣ በየጊዜው ራስን ከአዳዲስ ነገሮች ጋር ማላመድ ተገቢ እንደሆነ መክራለች፡፡
መላኩ ባዬ በአካዳሚው 4 ነጥብ በማምጣት በማዕረግ ተመርቋል፡፡ መላኩ በአካዳሚው በነበረው ቆይታ አዳዲስ ነገሮችን መቅሰሙን ነግሮናል፡፡ አካዳሚው አመራሮችን በማፍራት እያበረከተው ያለው አስተዋጽኦ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብሏል፡፡
“ነገ በምንሠማራበት የሥራ መስክ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሌም ተማሪ መሆን አለብን” ብሏል፡፡ እያንዳንዱ ሰው ሊደርስበት የሚችል ራዕይ አስቀምጦ ከሠራ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚችል ተናግሯል፡፡
ዘጋቢ፡- ትርንጎ ይፍሩ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.4K viewsማሜ, 13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 15:48:09
በባሕር ዳር ከተማ በሰላም ግንባታና ብሔራዊ መግባባት ላይ ያተኮረ መድረክ እየተካሄደ ነው።
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) ከአማራ ክልል በየደረጃው ላሉ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች በሀገራዊ ሠላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
ሰላም ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከወረዳ እስከ ክልል የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.0K viewsማሜ, 12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 15:46:53 በአማራ ክልል እያደገ የመጣውን የከተሞች ቁጥር የሚመጥን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለጸ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአማራ ክልል የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ እና የተጠሪ መሥሪያ ቤቶች የ2013 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም በደብረታቦር ከተማ ተገምግሟል፡፡
የክልሉ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት እና የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ተግባራት ተካተው በተገመገሙበት በዚሁ መድረክ ከታዳጊ እስከ ሜትሮፖሊታንት የአማራ ክልል ከተሞች 660 መድረሳቸውና የሕዝቡም ቁጥር በፍጥነት እያደገ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ እያደገ የመጣውን የከተሞች ቁጥር የሚመጥን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባም ተገልጿል፡፡
ለከተሞች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ማቅረብና መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠር፣ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ማድረግ፣ የከተማ መሰረተ ልማት ማስፋፋትና ህገወጥ መሬት ወረራን መከላከል ዋና ዋናዎቹ ተግባራት ሆነው እንደተፈጸሙ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ በዘርፉ የሚታየውን ሌብነት ከመታገል አንፃር በየደረጃው ምንጮችን በመለየትና ወደ ሌብነት ተግባር የገቡ የሥራ ኀላፊዎችንም ሆነ ባለሙያዎችን ለማረም የሚደረገው ጥረት መሻሻሉ በስኬትነት ተነስቷል፡፡
በአንጻሩ የዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ የመልካም አስተዳደር ችግር ምንጭ መሆኑ፣ ተገልጋዮችም በተቋሙ ላይ ሙሉ እርካታና አመኔታ አለመፍጠራቸው፣ ባለድርሻ አካላትን አለማሳተፍና የራስን ችግር ወደሌላ አካል የማሻገር አመለካከት በእጥረትነት ተመላክቷል፡፡
በቀረበው ሪፖርት ሠራተኞች ውይይት አድርገውበታል፡፡ በአካባቢ ልማት ላይ የኅብረተሰብ ተሳትፎ፣ ከተሞች በማዘጋጃ ቤት የአገልግሎት ደረጃዎችን መተግበርና የመሬት ሃብት ቆጠራ መከናወን ጥሩ አፈጻጸም ከታየባቸው ተግባሮች ውስጥ መሆናቸው ተነስቷል፡፡
ህገወጥ ይዞታዎችን የመለየትና የማፍረስ፣ ለልማት ተነሺዎች ትክ ቦታ የመስጠትና ካሳ የመክፈል፣ የሊዝ አፈጻጸምን ኦዲት የማድረግ፣ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ የመስጠት፣ የመንግሥት ቤቶችን የኪራይ ዋጋ የማሻሻልና ሌሎች ተግባራት በግማሽ በጀት ዓመቱ ዝቅተኛ አፈጻጸም ከተስተዋለባቸው ተግባራት መካከል ተጠቅሰዋል፡፡
የበጀት፣ የቁሳቁስ፣ የባለሙያ እጥረትና ከአጋር አካላት ጋር ተናቦ በመሥራት የነበሩ እጥረቶች ለአፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆን ዋና ዋና ምክንያቶች ተብለዋል፡፡ በቀጣይም የከተማ ፕላን ሥራዎች ለዝርፊያ የሚጋልጡ ስለሆኑ በጥንቃቄ እንዲመሩና እንዲሠሩ፣ የከተሞችን አቅም ለማሳደግ ሲባል የሚጫን የተጋነነ የቤት ዋጋ ግመታ በስመ ንብረት ዝውውር ላይ እንቅፋት ስለሆነ ለማስተካከል ሊሠራ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
ለከተማ መኖሪያ ቤት ፈላጊዎች ከዚህ ቀደም 13 ሽህ የሚደርስ ቦታ የተሰጠ ቢሆንም አሁንም ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት ለመመለስ ጠንክሮ መሥራት እንደሚጠይቅ ተነስቷል፡፡
ሁሉም የዘርፉ ተቋማትና የሥራ ክፍሎች በቀሪ ጊዜያት እቅዶቻቸውን መርምረውና አሻሽለው የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲሠሩ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
የቢሮው የ10 ዓመት መሪ እቅድም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
ዘጋቢ፡- ዋሴ ባየ - ከደብረታቦር
ፎቶ፡- ከአማራ ክልል ከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.8K viewsማሜ, 12:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 15:18:47
አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበር ዩኒዬን ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባቸውን ሦስት ፋብሪዎች ነገ ያስመርቃል።
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የሚገኘው አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበራት ዩኒዬን ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባቸውን ባለ 4 ፎቅ ህንፃ ፣ የእንስሳት መኖ ፋብሪካ፣ የፒፒ የማዳበሪያ ከረጢት እና የምንጣፍ ፋብሪካ ነገ ያስመርቃል።
የአድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበር ዩኒዬን ሥራ አስኪያጅ አቶ መሠረት ወርቄ እንደተናገሩት ዩኒዬኑ 83 መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ ከ178 ሽህ በላይ አባል አርሶ አደሮች እና ከ104 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል በመያዝ እየሠራ ነው።
በተለይም ከሀገር ውስጥ ወደ ውጭና ከውጭ ወደ ሃገር ውስጥ ግብይት፣ በግብርና ምርት ማሣደጊያ ግብዓትና ቴክኖሎጂ አቅርቦት፣ በትራንስፖርት አገልግሎት፣ በሜካናይዜሽን ዘርፎች አርሶአደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በነገው የምረቃ ሥነ ሥርዓት የፌዴራል፣ የክልል ፣የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች፣ የክብር እንግዶችና መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበራት መሪዎችና ባለሙያዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡- አዳሙ ሽባባው - ከእንጅባራ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.8K viewsማሜ, 12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 14:04:41
“የራዲዮ ተደራሽነት ውስን መሆን ለተዛባ የመረጃ ስርጭት መበራከት ድርሻ አለው” ጀማል ሙሃመድ (ዶክተር)
https://www.amharaweb.com/የራዲዮ-ተደራሽነት-ውስን-መሆን-ለተዛባ-የ/
"የራዲዮ ተደራሽነት ውስን መሆን ለተዛባ የመረጃ ስርጭት መበራከት ድርሻ አለው" ጀማል ሙሃመድ (ዶክተር) ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) ዛሬ የዓለም የራዲዮ ቀን ነው፡፡ እንደ ዛሬው ምድራችን በረቀቁ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ከመጥለቅለቋ በፊት፣ ነገሮችን በአንድ ትንሽ የስልክ ቀፎ ማከናወን ከመቻላችን በፊት ያኔ አንድ እንደ ብርቅ የሚታይ ውድ እቃ ነበር- ራዲዮ፡፡ ዘነበ ወላ “ልጅነት” በተሰኘው ልብወለድ መጽሐፉ [...]
5.9K viewsAmmaOnlineBOT, 11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 13:58:38
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዕጩዎች ምዝገባ ማከናወን የተራዘመባቸው ክልሎችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
https://www.amharaweb.com/የኢትዮጵያ-ብሔራዊ-ምርጫ-ቦርድ-የዕጩዎች/
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዕጩዎች ምዝገባ ማከናወን የተራዘመባቸው ክልሎችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ለ6ተኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ እንደሆነ ይታወቃል። ቦርዱ በማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (1) እና የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 37 ንዑስ አንቀጽ [...]
5.7K viewsAmmaOnlineBOT, 10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-13 13:47:38
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርኃ ግብር ቀጣይነት እንዲኖረው እንደሚሠራ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኤልያስ ሽኩር ተናገሩ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ከደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የማኅበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በደብረብርሃን ከተማ ተካሂዷል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ጨርቆስ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርኃ ግብሩ በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ለማካሄድ ታቅዶ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ በላይ ደጀን እንዳሉት ጤናማ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ወሳኝ ነው፡፡ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርኃ ግብር የማኅበረሰብ ትስስር ለመፍጠር ጉልህ ድርሻ እንዳለውም ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ባዘዘው ጫኔ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርኃ ግብሩ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች እንዲካሄድ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርኃ ግብር ቀጣይነት እንዲኖረው እንደሚሠራ የተናገሩት ደግሞ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኤልያስ ሽኩር ናቸው፡፡
ስፖርት ለማኅበረሰብ ትስስር፣ ለሰላምና አንድነት ያለው ድርሻ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
በመርኃ ግብሩ የክልልና የፌደራል የሥራ ኃላፊዎች፣ አርቲስቶች፣ የቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ ማኅበር አባላትና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ሃብታሙ ዳኛቸው - ከደብረብርሃን
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
5.9K viewsማሜ, 10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ