Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 693

2021-02-17 21:16:48

6.5K viewsማሜ, 18:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 16:37:05 የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የወጣው አዋጅ ትግበራ ላይ ሊሠራ ይገባል ተባለ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) በኢትዮጵያ የማኅበራዊ ድረ ገጽ አጠቃቀም ላይ ሰዎችን በብሄራቸው፣ በቆዳ ቀለማቸው፣ በሃይማኖታቸው፣ በጾታቸው ፣ በፖለቲካ አመለካከታቸው በመለየት ከሰዋዊ ክብራቸው ዝቅ በማድረግ ጥቃት ሲፈጽሙ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡
በየዕለቱ ሆነ ተብሎ የፖለቲካ ወይም የገንዘብ ፍላጎትን ለማሟላት ሐሰተኛ ዜና በማሰራጨት የግል ጥቅማቸውን ማሳካት ግባቸውን ባደረጉ ሰዎች ሀገርም ሕዝብም ዋጋ መክፈላቸውን ቀጥለዋል፡፡እነዚህ ሐሰተኛ መረጃዎችም ለበርካታ ጥፋቶች መንስዔ ሆነዋል፡፡
የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ሆነ ብለው አልያም በስህተት የሚያሰሯጯቸው መረጃዎች በሌሎች ተጠቃሚዎች ላይ በተለያየ መንገድ ጉዳት ሊያስከትሉ ይችላሉ። ተጠቃሚዎችም ቢሆን መረጃዎችን ሚዛን ላይ አስቀምጦ ትክክለኛነቱን ፈትሾ መጠቀም ላይ አልተሠራም ሲሉ ከአብመድ ጋር ቆይታ የነበራቸው ወጣቶች ምልከታቸውን አንስተዋል፡፡
ወጣት ያለምወርቅ አየለ እንደምትለው የሚለቀቁ መረጃዎች መልከ ብዙ መሆናቸውን መገንዘብ ይጠይቃል ብላለች፡፡ የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የወጣው አዋጅ ትግበራ ላይ ሊሠራ እንደሚገባ አንስታለች፡፡
ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመጣው አሰፋ አለምነው ከእውነታ የራቁ የሐሰት መረጃ በመልቀቅ ሀገርና ሕዝብን አደጋ ላይ የሚጥሉ መልዕክቶችን መቆጣጠር ካልተቻል ውጤታቸው የከፋ ነው ብሏል፡፡
አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት እና የግል ተወዳጅነትን እና የራስን አስተሳሳብ በሌሎች ለይ ለመጫን የሚደረግ ጥረት ዋጋ እንዳያስከፍል ግንዛቤን ማሳደግ እና የሕግ ማዕቀፉን ሥራ ላይ ማዋል ይገባል ነው ያለው፡፡ በጎ ተጽእኖ የፈጠሩትን፣ መልካም የሠራን፣ ታሪክን እና እውነታን ያሳወቀን ማበረታትት ይገባል ብሏል፡፡
ወጣት ኤርሚያስ ወንድሙ በበኩሉ የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ተጠቃሚ እንዴትና ለምን መጠቀም እንዳለበት ካለው ግንዛቤ ማነስ የተነሳ የተለጠፉ መረጃዎችን ሁሉ እውነት ነው ብሎ መቀበል እና መልዕክቶችን ማጋራት አብዝቶ ይታያል፤ ይህም ግለሰቦችን ለልዩ ልዩ ችግሮች እየዳረገ ነው ብሏል፡፡ ለዚህ መፍትሄው ደግሞ ምክንያታዊ እና በሀሳብ የሚሞግት ትውልድ መፍጠር ላይ ሊሠራ እንደሚገባ ተናግሯል፡፡
የተማሩና ብዙ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ሲያጠፉ እና ሌሎችን ለአደጋ የሚጥሉ ሀሳቦችን ሲያራምዱ የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የወጣው አዋጅ ሥራ ላይ ሊውል ይገባል ብሏል፡፡
ወጣት ጽዮን ተሾመ በበኩሏ መረጃዎችን ከማጋራታችን እና ሀሳቦችን የራስ ከማድረጋችን በፊት የመረጃ ምንጮችን ትክክለኛነት ማረጋገጥ ቀዳሚው ተግባር ሊሆን ይገባል ብላለች፡፡
የአዲስ አበባ የወጣቶች በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ጋር በመተባበር "ወጣትነት በማኅበራዊ ሚዲያ ለመልካም ኢትዮጵያዊነት" በሚል መሪ መልዕክት በአዲስ አበባ 11ዱም ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ 200 ለሚደርሱ ወጣቶች የማኅበራዊ ትስስር ገጽ አጠቃቀምን በተመለከተ ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡
የአዲስ አበባ የወጣቶች በጎፍቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኀላፊ አቶ አብርሃም ታደሰ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች አጠቃቀም ዙሪያ የወጣቶች የሰለጠነ እይታን ማስቀደም በመረጃ ይዘትና በግንኙነት ምህዳሩ ላይ ትልቅ ቦታ አለው ብለዋል፡፡
በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሕዝቡን ለጉዳት እንደሚዳርጉ መገንዘብ ይጠይቃል ነው ያሉት፡፡
"የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በተለይ ከፊታችን ላለበትን ትልቅ ሀገራዊ ምርጫ በበጎ ዓላማ በመጠቀም፣ የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ለማሳደግ፣ በቅንነትንና ኢትዮጵያዊ ስብዕናን በተላበሰ መልኩ መጠቀም ከቻልን የነገዋን ኢትዮጵያ ዛሬ ሠርተን ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ ያግዛል" ብለዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ጋሻው ፈንታሁን - ከአዲስአበባ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
8.8K viewsማሜ, 13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 16:36:28
የኢንዱስትሪ ፓርኩ ለባለሀብቶች የሚውል ቦታን በማዘጋጀት አልሚ ባለሀብቶችን እየተጠባበቀ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) ቡሬ የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታው ተጠናቅቆ ጥር 30/2013 ዓ.ም በመመረቅ አምራች ባለሀብቶችን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ፓርኩ ለሥራዉ ስኬታማነት የሚውሉ መሠረተ ልማቶችን ማሟላቱንና ባለሀብቶች በሚያቀርቡት መነሻ ፕሮጀክት መሠረት 142 ሄክታር የተዘጋጀ መሆኑን የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የዕቅድ ዝግጅት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ በልስቲ ወርቁ ተናግረዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኩ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ባለሀብቶች ወደ ፓርኩ ገብተው እንዲያለሙ የትውውቅ ሥራ እየተሠራ መሆኑንም ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡
የቡሬ የኢንዱስትሪ ፓርክ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ ሰባት የገጠር ሽግግር ማዕከላት በመገንባት ላይ እንደሚገኙ የጠቀሱት አቶ በልስቲ ከእነዚህ ማዕከላት ውስጥ የሞጣ የሽግግር ማዕከል ግንባታ መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡ ቀሪዎቹ የገጠር ሽግግር ማዕከላትም በያዝነው ዓመት መጨረሻ አካባቢ ይጠናቀቃሉ ተብሎ እንደሚገመት ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
ከማኅበራት፣ ከአርሶ አደሮች፣ ከምርት ማሰባሰቢ ማዕከላትና ከዩኒዬኖች ለፓርኩ የሚውሉ ዋና ዋና ግብዓቶች (ምርት ማሰባሰብ) ሥራ በመሠራት ላይ እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ይህን ለማሳካት የግብርናና ሌሎች ተቋማት ከፓርኩ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ የተቀመጠ አቅጣጫ መኖሩን ነው አቶ በልስቲ ያስረዱት፡፡ በዚህ መሠረት ሪችላንድ ባዮ ኬሚካል ኀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ምርትን በማሰባሰብ ወደ ትግበራ ሙከራ መግባቱንም ጠቁመዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ብሩክ ተሾመ
6.3K viewsማሜ, 13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 16:35:38
የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ችግር ላለባቸው ሰዎች በነጻ ቀዶ ሕክምና ሊሰጥ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ሃረር ኢትዮጵያ እና ስማይል ትሬን ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከየካቲት 11/2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት በጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቀዶ ጥገና አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በቢሮው የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ንጋቱ የሻምበል እንደነገሩን እድሜያቸዉ 6 ወር እና ከዚያ በላይ የከንፈር መሰንጠቅ እንዲሁም ከ2 ዓመት እድሜ ጀምሮ የላንቃ መሰንጠቅ ችግር ያለባቸዉ ህጻናትና አዋቂዎች አገልግሎቱን በነፃ ያገኛሉ፡፡
በዘመቻው ከ80 በላይ ህጻናት እና አዋቂዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሕክምናውን ተደራሽ ለማድረግ ጤና ጥበቃ ቢሮ በየሩብ ዓመቱ በክልሉ የቀዶ ጥገና ሕክምና በሚሰጡ ሆስፒታሎች እየሰጠ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ ይሁን እንጅ በዘርፉ የሰለጠነ ባለሙያ ባለመኖሩ ሕክምናውን በመደበኛነት ለመስጠት አለመቻሉን አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡
ማኅበረሰቡ የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ በሕክምና የሚደን መሆኑን ተረድቶ ችግሩ ያለባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህፃናት ሲወለዱ ጀምሮ በተፈጥሮ የሚመጣ ነው፡፡
አቶ ንጋቱ እንደገለጹት የችግሩ ትክክለኛ መነሻ ባይታወቅም በዕርግዝና ወቅት በሚፈጠር የአመጋገብ ሥርዓት አለመስተካከል እና ደባል ሱስ በአጋላጭነት ይጠቀሳሉ፡፡
ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሠራ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
5.6K viewsማሜ, 13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 15:46:36
“እናንተ አንድ ልብ ከሆናችሁ፣ በምቀኝነት እርስ በራሳችሁ ተዋግታችሁ ታላለቃችሁ በቀር ሀገራችንን ለሌላ ለባዕድ አትሰጧትም” አጤ ምኒልክ
https://www.amharaweb.com/እናንተ-አንድ-ልብ-ከሆናችሁ፣-በምቀኝነ/
“እናንተ አንድ ልብ ከሆናችሁ፣ በምቀኝነት እርስ በራሳችሁ ተዋግታችሁ ታላለቃችሁ በቀር ሀገራችንን ለሌላ ለባዕድ አትሰጧትም” አጤ ምኒልክ ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) የአጤ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ከሚታወቅባቸው የሀገረ መንግሥት ባሕሪያት መካከል ሀገራዊ አንድነትና ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ስትራቴጂ ይጠቀሳሉ፡፡ ጥሩ የሀገር ውስጥ ግንኙነት እና የተሳካ የውጪ ዲፕሎማሲ መፈጠሩም ትልቅ ትሩፋት ተገኝቶበታል፡፡ ንጉሠ ነገሥት አጤ ምኒልክ ገና በጠዋቱ [...]
5.8K viewsAmmaOnlineBOT, 12:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 15:28:15
የኢትዮ-ህንድ ቢዝነስ ፎረም እየተካሄደ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራው ልዑካን የኢትዮ-ህንድ ቢዝነስ ፎረምን በህንድ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
ምንጭ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
4.9K viewsማሜ, 12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 14:52:18
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኔዘርላንድስ አቻቸው ማርክ ሩት ጋር የስልክ ውይይት አካሄዱ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከኔዘርላንድስ አቻቸው ማርክ ሩት ጋር በሀገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና አካባቢያዊ ሠላምና ፀጥታን በተመለከተ በስልክ ተወያይተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከኔዘርላንድስ ጋር በዲፕሎማሲ፣ በንግድ እና በኢንቨስትመንት ረገድ ያላት የቆየ ግንኙነት ለቀጣይ ትብብር ጠንካራ መሰረት እንደሚሆን ነው ዶክተር ዐቢይ የገለጹት፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር) በትዊተር ገጻቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩት ጋር ለነበራቸው መልካም ውይይት ምስጋና አቅርበውላቸዋል፡፡
በየማነብርሃን ጌታቸው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.1K viewsማሜ, 11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 14:50:34
የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት፣ ንግድና ቱሪዝም የሚያስተዋወቅ ፎረም በሩሲያ ቱሜን ክልል ተካሄደ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) ከሩሲያ ቱሜን ክልል ለተውጣጡ ባለሀብቶች፣ ነጋዴዎች እና ለከልሉ መንግሥት የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ኀላፊዎች ኢትዮጵያ ስላላት የኢንቨስትመንት፣ ንግድ እና ቱሪዝም ሃብቶች የማስተዋወቂያ ፎረም በበይነ መረብ ተካሄዷል፡፡
በሩሲያ ፌዴሬሽን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ ስለሀገሪቱ የንግድና የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡
ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከውኃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከንግድ እና ዘርፍ ማኅበራት መስሪያ ቤቶች የተወከሉ ተሳታፊዎች ስለሀገሪቱ የኢንቨስትመንት እና የንግድ አቅም በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል፡፡
ከተሳታፊዎቹ መካከል የቱሜን ክልል የኢንቨስትመንት ፖሊሲና ድጋፍ ጄነራል ዳይሬክተር ማሹኮቪ አንቶኒ አድንረቪች ፣የክልሉ የንግድና የኢንቨስትመንት አካላት እንዲሁም በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ ዲፕሎማት ስለሀገሪቱ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የቱሪዝም ሃብቶች ግንዛቤ እንዳስጨበጣቸውና ከኢትዮጵያ ጋር የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ለመመስረት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የአፍሪካ ሕብረት የንግድ እና የኢንዱስትሪ እንዲሁም የጤና ክፍል ተወካዮች እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ማብራሪያ መስጠታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.1K viewsማሜ, 11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 13:03:44
ኢትዮጵያውያን በጋራ በመቆም ለሀገራቸው የሚጠበቅባቸውን ኀላፊነት እንዲወጡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢፌድሪ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ጥሪ አቀረቡ፡፡
https://www.amharaweb.com/ኢትዮጵያውያን-በጋራ-በመቆም-ለሀገራቸው/
ኢትዮጵያውያን በጋራ በመቆም ለሀገራቸው የሚጠበቅባቸውን ኀላፊነት እንዲወጡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢፌድሪ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ በበይነ መረብ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይቱ በትግራይ ክልል የተወሰደውን ሕግ የማስከበር እርምጃ እና የተገኘው ውጤት፣ የሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነትና ኢትዮጵያዊያውያኑ ስለሚኖራቸው ተሳትፎ [...]
5.7K viewsAmmaOnlineBOT, 10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 13:00:20
በደቡብ ወሎ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድና ለብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) የድጋፍ ሰልፎቹ በጃማ፣ በመቅደላ፣ በአምባሰል፣ በደሴ ዙሪያ፣ በተሁለደሬ፣ በወረኢሉና በደላንታ ወረዳዎች እንዲሁም በሐይቅ ከተማ አስተዳደር ነው የተካሄደው፡፡
በጃማ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ክንድየ ወርቁ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና ለብልጽግና ፓርቲ ሕዝቡ ድጋፉን በመስጠቱ አመስግነዋል። አስተዳዳሪው ሀገራዊ ለውጥ ያመጣው የለውጥ አመራሩ ክብር ይገባዋል ብለዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን የብልጽግና ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ ኤርሚያስ መኮንን ብልጽግና ፓርቲ ከሕዝቡ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን የእድገት ጎዳናን ያበስራል ማለታቸውን የዘገበው ሃበሻ አንለይ ነው።
በየወረዳዎቹ በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍም
•የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን የሚያደናቅፉ የውስጥና የውጭ ኃይሎችን እናወግዛለን
•በትብብርና በድርድር መንፈስ የኢትዮጵያን አንድነት እናድስ
•ለውጡን የሚያደናቅፍ የሴራ ፖለቲካ እናወግዛለን
•ፈተናዎችን በጋራ እየመከትን የለውጡን ዘላቂነት እናረጋግጣለን የሚሉና ሌሎች መልዕክቶችም እንደተላለፉ ከደቡብ ወሎ ዞን ብልጽግና ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.4K viewsማሜ, 10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ