Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 696

2021-02-15 17:32:03 በአማራ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ449 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) የትራፊክ አደጋ በሀገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ እየተባባሰ መጥቷል፡፡ ለዚህ ምክንያት ከሆኑ ጉዳዩች መካከልም ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር ቀዳሚ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
አቶ ሙሉቀን ገዳሙ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪና በጥበቃ ሥራ ላይ ተሰማርተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኮሜርሻል የጥበቃ አገልግሎት ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፔዳ ቅርንጫፍ የጥበቃ ሥራ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ አቶ ሙሉቀን ከቀናት በፊት በመስሪያ ቤታቸው በር ላይ በደረሰው አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ እሳቸውና ባልደረባቸው ከሞት ተርፈዋል፡፡ በዕለቱ የሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት ባይኖርም የሥነ ልቦና ጫና እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡
ከደቡብ ክልል ዲላ ለትምህርት በመምጣት ላለፉት ሶስት ወራቶች በባሕር ዳር ከተማ ኑሮዋን እንዳደረገች የነገረችን ወጣት ሽቱ ከማል ደግሞ በከተማዋ ምቹና ሰፊ መንገዶች መኖራቸውን ጠቅሳለች፡፡ ይሁን እንጅ ከመንገዶች ምቹነት የተነሳ አሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከርን እንደ ልምድ መቁጠራቸው ለትራፊክ አደጋ ምክንያት ሆኗል ነው ያለችው፡፡
በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ትራፊክ ደኅንነት መምሪያ የትራፊክና ስታስቲክስ ባለሙያ ምክትል ኢንስፔክተር ሰጠኝ አለሙ የትራፊክ አደጋ አሳሳቢ እየሆነ መጥቷል ብለዋል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራትም አንድ ሺህ እንድ መቶ ሃያ አንድ የትራፊክ አደጋ መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡ በዚህም
• 449 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል
• 461 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት
• 487 ሰዎች ደግሞ ለቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል
• ከ28 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረትም ወድሟል፡፡
ለአደጋዎች መከሰትም ከ29 በላይ የትራፊክ አደጋ መንስኤዎች ተለይተዋል፡፡ ይሁን እንጅ በቀዳሚነት ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር ብቻ 234 አደጋ ደርሷል፡፡
ለእግረኞች ቅድሚያ ባለመስጠትም 206 አደጋዎች ደርሰዋል፡፡
ይህ ደግሞ ከምንም በላይ የአሽከርካሪዎችን የማሽከርከር ብቃትና ሥነ ባህሪ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተር ሰጠኝ አለሙ ገልፀዋል፡፡
አደጋውን ለመቀነስም ተደጋጋሚ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ቢከናወንም አጥጋቢ ውጤት አለመገኘቱን ነው ያስረዱት፡፡ አደጋው እየተባባሰ በመምጣቱም የጋራ መፍትሔ እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ብናየው ይርሳው (ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዲግሪ የጋዜጠኝነትና ሥነ ተግባቦት ትምህርት ክፍል ተማሪ)
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
9.1K viewsማሜ, 14:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 14:26:30
በቱርክ አንካራ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ተመረቀ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜቩሉት ካቩሶግሉ እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው አዲሱ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ግንባታ የተመረቀው፡፡
የኢትዮ-ቱርክ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው (እ.አ.አ) በ1896 በአፄ ምኒልክ እና በሱልጣን አብዱልሃሚድ ሁለተኛ መካከል ነበር፡፡
ፎቶ፡- (በቱርክ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና https://www.haberler.com)
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
8.6K viewsማሜ, 11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 14:24:41
አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር 18ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርት ውድድር አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ ከተማ አዘጋጅነት ከጥር 30/2013 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው 18ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርት ውድድርና 14ኛው የባህል ፌስቲቫል በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር አጠቃላይ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
ደቡብ ጎንደር ዞን 2ኛ ደረጃን ሲይዝ አዘጋጁ ደቡብ ወሎ ዞን 3ኛ ደረጃን ይዟል፡፡
ዛሬ በተደረጉ የፍፃሜ ውድድሮች በገና ስፖርት ምዕራብ ጎጃም ዞን ደቡብ ወሎን በመለያ ምት በማሸነፍ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ ለደረጃ በተደረገ ጨዋታ ደግሞ ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰሜን ሸዋን በማሸነፍ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል፡፡
በትግል ከ53 እስከ 57 ኪሎ ግራም በሴቶች ደቡብ ወሎ ምዕራብ ጎጃምን አሸንፏል፡፡
በወንዶች ከ68 እስከ 72 ኪሎ ግራም ሰሜን ሸዋ ሰሜን ወሎን በበቃኝ በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡
በዚህ ውድድር ላይ የታዩ ጥሩ ተወዳዳሪዎች በቀጣይ ድሬዳዋ ከተማ ላይ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የባህል ስፖርት ውድድር አማራ ክልልን እንደሚወክሉ የአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር በአማራ ክልል የባህል ስፖርት ውድድር ላይ የዘንድሮውን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት ዓመታት በአሸናፊነቱ ቀጥሏል፡፡
18ኛው የአማራ ክልል የባህል ስፖርት ውድድርና 14ኛው የባህል ፌስቲቫል በስፖርታዊ ጨዋነት እና ያለምንም የፀጥታ ችግር በሠላም ተጠናቋል፡፡
ውድድሩ በ11 የስፖርት አይነቶች ሲካሄድ ከምዕራብ ጎንደር በስተቀር ሁሉም የአማራ ክልል ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ተመስገን አሰፋ - ኮምቦልቻ
7.6K viewsማሜ, 11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 12:44:00

6.3K viewsማሜ, 09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 12:33:28
ከአዲስ ቅዳም ወደ እንጅባራ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ ተገልብጦ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደረሰ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) አደጋው በተለምዶ አድጓሚ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በመገልበጡ የደረሰ መሆኑን የአዊ ዞን ኮምዩኒኬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡
በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በአዲስ ቅዳም ጤና ጣቢያና በእንጂባራ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.2K viewsማሜ, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 12:32:14
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሥራ ጀምረዋል።
https://www.amharaweb.com/በወልቃይት-ጠገዴ-ሰቲት-ሑመራ-ዞን-የመንግ/
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሥራ ጀምረዋል። ባሕር ዳር፡ የካቲት 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን የሕግ ማስከበር ዘመቻው በስኬት ከተጠናቀቀበት ማግስት ጀምሮ ነዋሪዎች በነጻነት መደበኛ እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ዞኑ አስታውቋል። መንግሥትም ዞኑን መልሶ ለማደራጀት መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የዞኑ ብልጽግና ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አሸተ ደምለው ገልጸዋል። በዚህም አብዛኛው [...]
5.8K viewsAmmaOnlineBOT, 09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 11:51:16
ከ34 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የንጹህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት በአምደወርቅ ተመረቀ።
ባሕር ዳር: የካቲት 08/2013ዓ.ም (አብመድ) በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ድሃና ወረዳ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወርቅሰሞ ማሞና የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮን ጨምሮ የክልልና የብሔረሰብ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት ነው ዛሬ የተመረቀው።
የባርግባ የንጹሕ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት በድሃና ወረዳ አምደወርቅ ከተማን ጨምሮ ጭላ፣ጋኪው፣ ብርብራ እና ሽማምዳ የተሰኙ የገጠር ከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።
ከዋን ወሽ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በ120 ሚሊዮን ብር መነሻ የተጀመረ ሲሆን ተጨማሪ የትራንስፎርመር እና ሌሎች ወጭዎች ተጨምረውበት እስከ 150 ሚሊዮን ብር ወጭ ተደርጓል ተብሏል፡፡
ፕሮጀክቱ ከ34 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ፕሮጀክቱ ከድሃና ወረዳ ዋና ከተማ አምደወርቅ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባርግባ ወንዝን በመሳብ የተሠራ ነው፡፡
ዘጋቢ፦ ስማቸው እሸቴ - ከአምደወርቅ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.9K viewsማሜ, 08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 11:50:00 አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከሩሲያ እና ከስዊዘርላንድ አምባሳደሮች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ሰጡ።
ባሕር ዳር ፡ የካቲት 08/2013 ዓ.ም (አብመድ)
የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከሩሲያው አምባሳደር ቭላድሚር ዜልቶቭ እና ከስዊዘርላንድ አምባሳደር ክርስቲያን ዊንተር ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ማብራሪያ የሰጡት በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ፣ በኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግንብ የሶስትዮሽ ድርድር ዙሪያ ነው።
በውይይቱም አምባሳደር ይበልጣል ስለተጠቀሱት ጉዳዮች ወቅታዊ ሁኔታና ስለ ኢትዮጵያ አቋም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የሩሲያው አምባሳደር በበኩላቸው ስለተደረገላቸው ገለፃ አመስግነዋል።
አምባሳደር ቭላድሚር ሩሲያ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለባቸው፣የአገሮች ሉዓላዊነት መከበር አለበት እንዲሁም ጉዳዮች ፓለቲካዊ መደረግ የለባቸውም የሚል የፀና አቋም ያላት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የስዊዘርላንድ አምባሳደር በተመሳሳይ ሁኔታ በአምባሳደር ይበልጣል ስለተደረገላቸው ገለፃ አመስግነው፣ በገለፃው ስለተጠቀሱት ጉዳዮች ሰፊ ግንዛቤ እንዳገኙ ገልፀዋል። በሱዳን የኢትዮጵያን ኤምባሲ ጠቅሶ የዘገበው ኢዜአ ነው።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
5.9K viewsማሜ, 08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 10:54:01
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የተገነባው ጤና ጣቢያ ተመረቀ።
https://www.amharaweb.com/ማህበራዊ-ሚዲያን-በመጠቀም-የተገነባው-ጤ/
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የተገነባው ጤና ጣቢያ ተመረቀ። ባሕር ዳር ፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) በምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ ለ3 ዓመታት ተቋርጦ የቆየን ጤና ጣቢያ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያሉ የአካባቢው ተወላጆች ቴሌግራምን በመጠቀም 3 ብሎክ ያለው ጤና ጣቢያ አስገንብተው ለአገልግሎት ዝግጁ አድርገዋል። የድንጋይ በር ሀገረ ማርያም ጤና ጣቢያ በ2009 ዓ.ም በህብረተሰብ ተሳትፎ [...]
6.7K viewsAmmaOnlineBOT, 07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-15 09:41:05
በኩር ጋዜጣ የካቲት 08/2013 ዓ/ም ዕትም
https://www.amharaweb.com/በኩር-ጋዜጣ-የካቲት-08-2013-ዓ-ም-ዕትም/
በኩር ጋዜጣ የካቲት 08/2013 ዓ/ም ዕትም Download
7.5K viewsAmmaOnlineBOT, 06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ