Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 697

2021-02-14 14:00:43
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶክተር) የሻምቡ-ባኮን የአስፋልት ኮንክሪት መንገድን ሥራ አስጀመሩ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 60 ነጥብ 2 ኪሎሜትር ርዝመት ያለውን በሆሮ ጉዱሩ ዞን የሻምቡ ባኮን የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
የሻምቡ-አጋምሳ 95 ኪሎሜትር የአስፋልት መንገድም የመሠረት ድንጋይ ተጥሏል። መረጃው የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ነው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
9.5K viewsማሜ, 11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 13:59:46
የዓለም የሬድዮ ቀን በኢትዮጵያ ለ2ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ10ኛ ጊዜ እየተከበረ ነዉ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) የሬዲዮ ቀን በዓለም ለአስረኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ “ለአዲሱ ዓለም በአዳዲስ አማራጭ” በሚል ሃሳብ እየተከበረ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን እና ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጁት፡፡
የኢትዮጵያ ሬድዮ 85ኛ ዓመት ኤፍ ኤም 97.1 ሃያኛ ዓመት በዚሁ ቀን ታስቧል፡፡ በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ ንጉሴ ምትኩ (ዶክተር) እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ሬድዮ በብቸኛ የመረጃ ምንጭነት ለረዥም ዓመታት አገልግሏል፡፡ በቀጣይም ህዝብን በሚዛናዊነት ማገልገል እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ጌታቸዉ ድንቁ (ዶክተር) የሬድዮ ሞገድ የህዝብ ሃብት በመሆኑ በተጠያቂነት መስራት ይገባዋል ብለዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ በአሁኑ ጊዜም ሬድዮ ራሱን በማዘመን የበይነ መረብ ሬድዮ በመሆን ተደራሽነቱን ይበልጥ እያሰፋ ነዉ፤ ከመገናኛ ብዙኀን ዘርፍም በቀላሉና በስፋት ተደራሽም ነዉ ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያም 32 የሕዝብ፤13 የንግድ፤ 51 የማህበረሰብ ሬድዮ ጣቢያወች እንዳሉ ተጠቅሷል፡፡
ለዘርፉ ተግዳሮት የሆኑት የማስታወቂያ እጦትና የታክስ እፎይታ ሊታሰብበት እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል፡፡
የዘንድሮው የሬድዮ ቀን በመጀመሪያዋ ሴት ጋዜጠኛ ሮማንወርቅ ካሳሁን መታሰቢያነት ተሰይሟል፡፡
የዘንድሮ የሬድዮ ቀን የህይወት ዘመን ተሸላሚ ጋዜጠኞችም ደበላ ቱቲ፤ታደለ እንግዳወርቅ፤ሁሴን በዳሶ፤አባይነሽ ብሩ፤ ብርሃኑ ገብረ ማርያም፤ አበራ ለማ፤ መሀመድ አህመድ፤ ንጉሴ ተፈራ ናቸዉ፡፡
ዘጋቢ፡- ጺዮን አበበ- ከአዲስ አበባ
8.1K viewsማሜ, 10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 13:12:55
አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኀበራት ዩኒዬን ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ ነው።
https://www.amharaweb.com/አድማስ-ሁለገብ-የገበሬዎች-የኅብረት-ሥራ/
አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኀበራት ዩኒዬን ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ ነው። ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኀበራት ዩኒዬን ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና ማስልጠኛ ተቋማት በተለያዩ የሙያ መስኮች ለተመረቁ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አብመድ ከቦታው ተገኝቶ አረጋግጧል። ወጣት ፈለጉሽ የኔት በአድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኀበራት ዩኒዬን በሽመና ዘርፍ ተቀጥረው [...]
6.9K viewsAmmaOnlineBOT, 10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 12:33:45
አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበር ዩኒዬን ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን ፋብሪካዎች አስመረቀ።
ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የሚገኘው አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበር ዩኒዬን ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን ባለ 4 ፎቅ ህንፃ፣ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣ የፒፒ የማዳበሪያ ከረጢት እና የምንጣፍ ፋብሪካ አስመርቋል።
የአድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበር ዩኒዬን ሥራ አስኪያጅ አቶ መሠረት ወርቄ እንደተናገሩት ዩኒዬኑ 83 መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ ከ178 ሺህ በላይ አባል አርሶ አደሮች እና ከ104 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል በመያዝ እየሠራ ነው።
በምረቃ መርሃ ግብሩ የክልሉና የፌዴራል የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡- አዳሙ ሽባባው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.8K viewsማሜ, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 12:29:20
“ኢትዮጵያ እና ሱዳን ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን አስከብረው በትብብር ከመሄድ የተሻለ አማራጭ የላቸውም” ሱዳናዊ ፕሮፌሰር ሙሃመድ ሳላህ
https://www.amharaweb.com/ኢትዮጵያ-እና-ሱዳን-ብሔራዊ-ጥቅሞቻቸው/
“ኢትዮጵያ እና ሱዳን ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን አስከብረው በትብብር ከመሄድ የተሻለ አማራጭ የላቸውም” ሱዳናዊ ፕሮፌሰር ሙሃመድ ሳላህ ባሕር ዳር ፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮጵያ እና ሱዳን በሀገረ መንግሥት ግንባታ አያሌ የሚባል ዘመን ባለቤቶች ናቸው፡፡ የሁለቱ ሀገራት ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ፣ እና ማኅበራዊ ግንኙነታቸውም ከሀገረ መንግሥት ግንባታ ታሪካቸው ጋር በእድሜ የተቆራኘ ነው፡፡ ሁለቱ ሀገራት ረዥም ድንበርን የሚጋሩ፣ [...]
6.5K viewsAmmaOnlineBOT, 09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 10:37:07
‹‹በግፍ አይዘምቱም ከተዘመተባቸው አይረቱም››
https://www.amharaweb.com/በግፍ-አይዘምቱም-ከተዘመተባቸው-አይ/
‹‹በግፍ አይዘምቱም ከተዘመተባቸው አይረቱም›› ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) ‹‹ማስተማሪያም አታድርገኝ ማስተማሪያም አትንሳኝ›› የሚለው ድንቅ የኢትዮጵያዊያን አባባል ለኢትጵያ ጠላቶች አልተገለጠላቸውም፡፡ የኢትዮጵያ ጠላቶች ከተሸናፊዎቹ አይማሩም፤ እሳት እንደሚያቃጥል እያዩ ወደ እሳት ይወርዳሉ፣ በእሳት ተቃጥለው ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡ ኢትዮጵያ ለማሸነፍ ብቻ የተፈጠረች ነጻነት ያለው ሕዝብ ያለባት ነጻ ሀገር መሆኗን እያወቁ አሸናፊነቷን ማመን ይቸግራቸዋል፡፡ ለማሸነፍ ሌላ እድል ይሞክራሉ፣ የኢትዮጵያን [...]
6.9K viewsAmmaOnlineBOT, 07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 10:16:00
ማህበረሰቡ ጤንነቱን እንዲጠብቅ ዓላማ ያደረገው የጎንደር ከተማ የጋራ የአካል ብቃት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ዛሬ ተጀምሯል።
ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) የጋራ ስፖርታዊ እንቅስቃሴውን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ያስጀመሩት ሲሆን ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ከንቲባው ሞላ መልካሙ ማህበራዊ የስፖርት እንቅስቃሴው በአስተሳሰብ የተሻለ፣ በአካል ብቃት የዳበረ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንደሚያስችል አስረድተው የአካል ብቃት እንቅስቃሴው ቀጣይነት እንዲኖረው ትኩረት ተሰጥቶ የሚሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
የማያቋርጥ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ከተለያዩ በሽታዎች እራሳቸውን ለመከላከል በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉም አስተያየታቸውን ለአብመድ የሰጡ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።
በጎንደር ከተማ የተዘጋጀውን ህዝባዊ የስፖርት እንቅስቃሴ ያዘጋጀው የከተማ አስተዳደሩ ባህል ቱሪዝም ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ነው።
ዘጋቢ:- ሀይሉ ማሞ- ከጎንደር
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.5K viewsማሜ, 07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 10:13:36
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የልማት ሥራዎችን ለመመረቅ ደንቢዶሎ ገቡ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ሥራዎችን ለመመረቅ ደንቢዶሎ መግባታቸውን ኢብኮ ዘግቧል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንና ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው በልማት ሥራው ምረቃ ላይ ለመገኘት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ደንቢዶሎ ተገኝተዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.1K viewsማሜ, 07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 09:59:29
በገቢዎች ሚኒስቴር የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የሰጣቸው ስልጠና በታክስ አስተዳደሩ እየተፈጠሩ ያሉትን የወንጀል ድርጊቶች ለመከላከል እንደሚረዳቸው ሕግ አስከባሪዎች ተናገሩ።
https://www.amharaweb.com/በገቢዎች-ሚኒስቴር-የኮምቦልቻ-ቅርንጫፍ/
በገቢዎች ሚኒስቴር የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የሰጣቸው ስልጠና በታክስ አስተዳደሩ እየተፈጠሩ ያሉትን የወንጀል ድርጊቶች ለመከላከል እንደሚረዳቸው ሕግ አስከባሪዎች ተናገሩ። ባሕር ዳር ፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ) በገቢዎች ሚኒስቴር የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር በገቢ ግብር አዋጅ፣ በታክስ አስተዳደር አዋጅ፣ በታክስ ዙሪያ በሚፈጸሙ ወንጀሎች እንዲሁም በጉሙሩክ አዋጅና በሚፈጸሙ የኮንትሮባንድና የንግድ ማጭበርበር ዙሪያ ስልጠና አካሂዷል፡፡ [...]
6.3K viewsAmmaOnlineBOT, 06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-14 09:05:27
በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ጊዜ የሚከናወነው ማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በአዊ ብሔረስብ አስተዳደር ተጀመረ።
ባሕር ዳር ፡ የካቲት 07/2013 ዓ.ም (አብመድ)
በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ጊዜ የሚከናወነው ማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በሁሉም የክልሉ ወረዳዎችና ከተሞች እንዲጀመር የአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን ማሳወቁ ይታወሳል።
በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በተጀመረው ፕሮግራም የተገኙት የብሔረሰብ አስተዳደሩ ዋና አስተዳዳሪ ባይነሳኝ ዘሪሁን ህብረተሰቡ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝን ለመከላከልና ሙሉ ጤነኛ ለመሆን ማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አዘውትሮ መሥራት ይገባል ብለዋል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ የዕድሜ ባለፀጎችና ጎልማሶች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ የመሳተፍ ውስንነት እየታየ በመሆኑ በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
የብሔረሰብ አስተዳደሩ ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ቃለአብ ከሃሊ የአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን በአስተላለፈው ውሳኔ መሠረት በብሔረሰብ አስተዳደሩ በሚገኙ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተጀምረዋል ነው ያሉት።
ማህብረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከአካል ብቃት እንቅስቃሴ በተጨማሪ ማህበራዊ መስተጋብር ስለሚያስተሳስር ሁሉም ሰው በትኩረት ሊሠራው ይገባል ብለዋል። መምሪያ ኃላፊው በቀጣይ ሁሉም የሥራ ኃላፊዎችና ነዋሪው በሳምንት ሶስትና አራት ቀን እንዲሰራ ይደረጋልም ብለዋል።
ተሳታፊዎችም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጤና ያለውን ጠቀሜታ ግምት ውስጥ በማስገባት በተከታታይ ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ : -አዳሙ ሽባባው -ከእንጅባራ
6.8K viewsማሜ, 06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ