Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 694

2021-02-17 12:07:31
5 ሺህ የሦስተኛ ዲግሪ ምሩቃንን ለማፍራት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሀገር ውስጥ ትብብርና ትስሰርን በማጠናከር በመጪዎቹ 5 ዓመታት 5 ሺህ መምህራንን በሦስተኛ ዲግሪ ለማሰልጠን የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ሁርቃቶ የከፍተኛ ትምህርት መምህራንን ሁለንተናዊ ልማት ለማሳደግ ፕሮጀክቱን ወደሥራ ማስገባት አስፈልጓል ነው ያሉት፡፡
ዶክተር ሳሙኤል እንደተናገሩት በትብብርና ትስስር ተግባራዊ የሚሆነው “Home Grown Collaborative PhD Programs” በሁሉም መስክ ብቁ የሆኑ መምህራንን በማቅረብ የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ወሳኝ ሚና አለው፡፡ "እንደ ሀገር የምናስበውን የልማትና ብልጽግና ጉዞ ለማሳከት ብቃት ያላቸው መምህራን፣ ሳይንቲስቶችና ተመራማሪዎችን ማፍራት ወሳኝ " ነው ብለዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ሀገሪቱ ያላትን ሃብትና አቅም በማስተባበርና በሚገባ በመጠቀም እውቀትና ክህሎት ያለው ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሀገር ውሰጥና አለም አቀፍ ትብብርና ትስስሮችን በማጠናከር ለፕሮግራሙ መሳካት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የሦስተኛ ዲግሪ ሥርዓተ ትምህርት ክለሳና ቀረጻ፣ የሀገር ውሰጥና የውጭ ሀገራት ፐሮፌሰሮችን ማሰማራትና የምርምር፣ የቤተ ሙከራ ግብዓቶችን አጠናክሮ ማሰቀጠል ፕሮግራሙ ከሚያተኩርባቸው ጉዳዮች መካከል እንደሆኑ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
5.8K viewsማሜ, 09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 11:40:11
ኢትዮጵያኒዝም የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ጉልላት!
https://www.amharaweb.com/ኢትዮጵያኒዝም-የጥቁር-ሕዝቦች-የነፃነት/
ኢትዮጵያኒዝም የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ጉልላት! ባሕር ዳር ፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሃገራት የእኩልነት ተምሳሌት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ዓርማ ናት፡፡ ጭቆና ያንገሸገሻቸው እና ባርነት ያጎበጣቸው ጥቁሮች በዚያ የጨለማ ዘመን ለነፃነት ተስፋ አድርገው ፊታቸውን ያዞሩት ወደ ኢትዮጵያ ነበር፡፡ በባርነት የተቀፈደዱ እና በማኅበራዊ ብዝበዛ የተሸማቀቁ ጥቁር ሕዝቦች ማንነታቸውን የሚገልጹት በኢትዮጵያኒዝም ጥላ ስር ሆነው ነበር፡፡ ኢትዮጵያን [...]
5.6K viewsAmmaOnlineBOT, 08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-17 11:36:19
በጋምቤላ ክልል 125ኛው የአድዋ ድል በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) በጋምቤላ ክልል 125ኛው የአድዋ ድል በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡
በዓሉ በስፖርታዊ ውድድር፣ በሥራ ጉብኝት እና በፓናል ውይይት እየተከበረ ይገኛል፡፡
የኢፌዴሪ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው እና የጋምቤላ ክልል ርእሰ መሥተዳደር አቶ ኡሞድ ኡጁሉን ጨምሮ የተለያዩ የክልሉ እና የፌደራል መንግሥት የሥራ ኀላፊዎች እንዲሁም የአካባቢዉ ነዋሪዎች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት የክልሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ተጎብኝተዋል፤ የአድዋ መታሰቢያ ፓርክም ተሰይሟል፡፡
አዲሱ ትውልድ ከቅድመ አያቶቹ የወረሰውን የጀግንነት እና የመተባበር ባህል ዳግም በማደስ ለሀገሪቱ ሰላም እና ልማት በጋራ መረባረብ እንዳለበትም በክብረ በዓሉ ላይ ተገልጿል፡፡
የአድዋ ታሪክ በኢትዮጵያውያን የጋራ ተጋድሎ መላዉ ጥቁር ህዝቦች ድል የተጎናጸፉበት መሆኑም በመድረኩ ላይ መገለጹን ኢብኮ ዘግቧል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.6K viewsማሜ, 08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 18:12:30
የጎንደርና የካርቱም ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራን በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ለማስቀጠል እየሠሩ ነው።
ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) የሁለቱ ሀገራት ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የሀገራቱን የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት በመጠቀም እየታየ ያለውን ችግር በሰላማዊ ውይይት መፍታት በሚቻልበት ዙሪያ ተወያይተዋል።
ውይይቱ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ ሲሆን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምሁራንን ጨምሮ በሱዳን የካርቱም ዩኒቨርሲቲ የታሪክና የህብረተሰብ እድገት ምሁሩ ዶክተር ኡመር አል አሚን ተገኝተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ባደረጉት ንግግር ምንም እንኳን ኢትዮጵያና ሱዳን የጠበቀ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው መሆኑ ቢታወቅም ሱዳን የኢትዮጵያን ደንበር አልፋ ወረራ መፈጸሟን አስረድተዋል።
ይህ ድርጊትም የሁለቱን ሀገራት የቆየ መልካም ግንኙነት የሚያሻክር በመሆኑ ሱዳናውያን ምሁራን ቸግሩ መፍትሔ እንዲያገኝ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በሱዳን የካርቱም ዩኒቨርሲቲ የታሪክና የህብረተሰብ እድገት ምሁሩ ዶክተር ኡመር አል አሚን በበኩላቸው ሁለቱ ሀገራት ብሄራዊ ጥቅማቸውን በማይነካ መልኩ የጋራ ችግሮቻቸውን በውይይት መፍታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲም ከሱዳን አቻ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ለማስቀጠል እየሰሩ እንደሚገኙ ታውቋል።
ዘጋቢ፡- ኃይሉ ማሞ - ከጎንደር
9.3K viewsማሜ, 15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 18:11:41
የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ካሳው 125ኛውን የአድዋ ድል በዓል ለማክበር ጋምቤላ ገቡ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ካሳው ነገ በጋምቤላ ክልል የሚከበረውን 125ኛውን የአድዋ ድል በዓል ለማክበር ጋምቤላ ከተማ ገብተዋል።
የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትፘ ዶክተር ሂሩት ካሳው ጋምቤላ ሲደርሱ በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ኡሞድ ኡጁሉና በክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች አቀባባል ተደርጎላቸዋል።
ሚኒስትሯ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ የሚገኙ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን ይጎበኛሉ ተብሏል። ዘገባው የኢብኮ ነው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
7.8K viewsማሜ, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 18:10:40
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ ለአካል ጉዳተኞች የዊልቸር ስጦታዎችን አበረከቱ፡፡
ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከሚሠራቸው ሥራዎች አንዱ ተጋላጭ ለሆኑ ወገኖች እንክብካቤ ማድረግ ነዉ፡፡
ጽሕፈት ቤቱ ካሁን ቀደም በተለያዩ ከተሞች እንዳደረገዉ የዊልቸር ድጋፍ ሁሉ በደቡብ እና በሲዳማ ክልሎች ለሚገኙ 28 አካል ጉዳተኞች ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸዉ በሃዋሳ ክተማ ተገኝተው የዊልቸር ስጦታ አበርክተዋል፡፡
ዊልቸሮቹ የተገኙት ሞቢሊቲ ወርልድ ዋይድ ከተባለ የውጭ ሀገር ግብረ ሰናይ ድርጅት መገኘታቸውን ከቀዳማዊት ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
6.9K viewsማሜ, 15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 17:23:47
“የክትባት አቅርቦት እና የተጎጅዎች ቁጥር አለመመጣጠን ውሻን የሚያሳብድ በሽታ ለመከላከል ፈታኝ አድርጎታል” የአማራ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
https://www.amharaweb.com/የክትባት-አቅርቦት-እና-የተጎጅዎች-ቁጥር/
"የክትባት አቅርቦት እና የተጎጅዎች ቁጥር አለመመጣጠን ውሻን የሚያሳብድ በሽታ ለመከላከል ፈታኝ አድርጎታል" የአማራ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) ውሻን የሚያሳብድ በሽታ በውሻ፣ በድመት እና በሌሎች እንስሳት ንክሻ አማካይነት ወደ ጤናማ ሰው ሊተላለፍ የሚችል አደገኛ በሽታ እንደሆነ ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡ በሽታው በቫይረስ አማካኝነት ይመጣል፤ በዋናነት ደግሞ አንጎልን ያጠቃል። ማንኛውንም አጥቢ እንስሳትን የሚያጠቃ [...]
6.7K viewsAmmaOnlineBOT, 14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 17:20:41
ጊዜ ቆጣቢ እና ምርትን ከብክነት ሊታደጉ የሚችሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን እያስተዋወቀ መሆኑን “ሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን” የተባለ ግብረሰናይ ድርጅት አስታወቀ፡፡
https://www.amharaweb.com/ጊዜ-ቆጣቢ-እና-ምርትን-ከብክነት-ሊታደጉ-የ/
ጊዜ ቆጣቢ እና ምርትን ከብክነት ሊታደጉ የሚችሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን እያስተዋወቀ መሆኑን “ሳሳካዋ አፍሪካ አሶሴሽን” የተባለ ግብረሰናይ ድርጅት አስታወቀ፡፡ ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) እንደ ድርጅቱ መረጃ በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነት በዓለም ላይ ዝቅተኛ ከሆኑት ሀገራት መካከል ሲሆን የግብርና ቴክኖሎጂ አለመስፋፋት መሠረታዊ ምክንያቱ ነው፡፡ አብዛኛው አርሶ አደር ዘርፉን ለማዘመን የቴክኖሎጂ እውቀት የሌለው መሆኑ፣ በገንዘብ እጥረት እና [...]
6.9K viewsAmmaOnlineBOT, 14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 15:31:39
‹‹እነሆ ቤተመቅደሱን ይጠብቁ ዘንድ ነብሮች ታዘዙ››
https://www.amharaweb.com/እነሆ-ቤተመቅደሱን-ይጠብቁ-ዘንድ-ነብ/
‹‹እነሆ ቤተመቅደሱን ይጠብቁ ዘንድ ነብሮች ታዘዙ›› ባሕር ዳር፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) ምድር ጨለማ ለብሳ ተኝታለች። የሰው ልጅ ሁሉ ወደ ጎጆው ገብቷል። በውጭ ላይ ያሉ ጥቂት ሰዎችም ድምፅ አያሰሙም። ምድርን የሚያደነቁሯት ድምፆች ሁሉ ፀጥ ረጭ ብለዋል። መቼም የፈጣሪ ሥራ እፁብ ነው። ቀን ሰጥቶ በጎዳና የሚያመላልሰውን ሕዝብ ሌሊት ሰጥቶ ያሳርፈዋል። እርሱ አይተኛም ፍጡር ግን ይተኛል። ግሩም [...]
7.4K viewsAmmaOnlineBOT, 12:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 15:01:09
የጃፓን መንግሥት ለኢትዮጵያ አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ የመፀዳጃ መገልገያ ገንዳዎችን ድጋፍ አደረገ።
https://www.amharaweb.com/የጃፓን-መንግሥት-ለኢትዮጵያ-አንድ-ሚሊዮ/
የጃፓን መንግሥት ለኢትዮጵያ አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ የመፀዳጃ መገልገያ ገንዳዎችን ድጋፍ አደረገ። ባሕር ዳር ፡ የካቲት 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) የጃፓን መንግሥት የከተማ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 1 ሚሊዮን ዶላር ወጭ የተደረገባቸው የመፀዳጃ መገልገያ ገንዳዎችን በዩኒሴፍ በኩል ለኢትዮጵያ አስረክቧል፡፡ በጃፓን መንግስት በኩል የተበረከቱት 165 ሺህ የመጸዳጃ ገንዳዎች (ሶቶ ፓን) ናቸው፡፡ ገንዳዎቹ የአዲስ አበባ ከተማ ተወካይ በሆኑት ወይዘሮ [...]
7.2K viewsAmmaOnlineBOT, 12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ