Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Media Corporation

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharamassmedia — Amhara Media Corporation
የሰርጥ አድራሻ: @amharamassmedia
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 64.80K
የሰርጥ መግለጫ

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-04-28 12:45:53
9.0K views09:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 11:03:17
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በግርማ የሺጥላ ግድያ የተሰማውን ሐዘን ገለጸ።

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግርማ የሺጥላ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል፡፡

እኩልነትና ማኅበራዊ ፍትሕ የነገሰባት ጠንካራ ኅብረብሔራዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ርብርብ አቶ ግርማ የተሰጣቸው ታላቅ ሕዝባዊ፣ ደርጅታዊና መንግስታዊ ኃላፊነት በልበሙሉነት፣ በትጋትና በኃላፊነት ስሜት የተወጡ ናቸው ብሏል ምክር ቤቱ፡፡

አቶ ግርማ የሺጥላ ሀገር ወዳድ፣ ብልህ ቁርጠኛ የፖለቲካ አመራር እንደነበሩ ገልጾ ለሀገርና ለወገን ሲሉ ሙሉ ጊዜያቸውን በመጨረሻም የማይተካውን ውድ ሕይወታቸውን ሰውተዋል ብሏል፡፡

የአቶ ግርማ ጉልህ ሀገራዊና መንግሥታዊ አበርክቶ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ማኅደር ፈፅሞ የሚዘነጋ አይሆንም ነው ያለው ምክር ቤቱ በሐዘን መግለጫው፡፡

ምክር ቤቱ በአቶ ግርማ የሺጥላና በግል ጠባቂዎቻቸው ላይ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ሀዘን ገልጾ ለወገኖቻችን ሞት ምክንያት የሆነውንም አሳፋሪ ፅንፈኛ ድርጊትና ጥቃት በፅኑ አውግዟል፡፡

ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸውም መፅናናትን ተመኝቷል፡፡
9.7K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 09:54:34
ከአማራ ክልል ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

የተከበሩ አቶ ግርማ የሺጥላ ሚያዚያ 19/2015 ዓ.ም የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በሰሜን ሸዋ ዞን ሠርተው ከመሀል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን ሲመለሱ ልዩ ቦታው መንዝ ጓሳ አካባቢ በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን ባሶና ወረና ወረዳ ቀይት ምርጫ ክልልን ወክለው የተመረጡት የክልል ምክር ቤት አባል፣ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በተከበሩ አቶ ግርማ የሺጥላ እና የግል ጥበቃዎቻቸው ላይ በታጠቁ ፅንፈኛ ኀይሎች በደረሰባቸው ጥቃት የተሰማን ሐዘን መራራ ነው።

የአማራ ክልል ምክር ቤት ለሟቾች ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ እና መላው ሕዝብ መጽናናትን ይመኛል።

የአማራ ክልል ምክር ቤት

ባሕር ዳር
9.8K views06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 09:53:30
በአማራ ክልል የምሁራን መማክርት ጉባዔ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ በታጠቁ ኃይሎች የተፈፀመውን ግድያ በፅኑ በማውገዝ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል።

የሐሳብም ሆነ የፖለቲካ ልዩነቶችን በኀይልና በመግደል ለመፍታት መሞከር ለሕዝባችን እና ሀገራችን ዘለቄታዊ ሰላም አያመጣም።

የምሁራን መማክርቱ ለቤተሰቦች እና ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና ሕዝብ መፅናናትን ተመኝቷል።
9.4K views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 23:49:31
ከኢፌዴሪ ም/ጠ ሚኒስቴር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ ደመቀ መኮንን የተላለፈ የሀዘን መግለጫ
በዛሬው እለት ወንድማችን አቶ ግርማ የሺጥላ በስራ ላይ እያሉ በታጠቁ ሃይሎች በተፈጸመባቸው ጥቃት መገደላቸውን ስሰማ ከፍተኛ እና ጥልቅ የሆነ ሀዘን ተሰምቶኛል።
አቶ ግርማ እና የግል ጠባቂዎቻቸው ላይ የተፈጸመው ድርጊት ፍጹም ተቀባይነት የሌለው፣የህዝባችንን እሴት የማይመጥን ነውር እና ህገወጥ ድርጊት ነው።
አቶ ግርማ የህዝብ ህይወት እንዲሻሻል የተሰጠውን ህዝባዊ ኃላፊነት እየተወጣ የሚገኝ መሪ ሲሆን በህልፈቱ ለመላው ለክልላችን እና ሀገራችን ህዝቦች ከፍተኛ ጉዳት ነው።
መንግስት ይህን ድርጊት የፈጸሙ አካላትን ለህግ በማቅረብ ተጠያቂ እንዲሆኑ ይሰራል።
ለወንድማችን ግርማ ፈጣሪ ነፍሱን በገነት እንዲያኖርው፥ ለብቤተሰቦች፣ለወዳጅ ዘመዶቹ እና መላው ህዝባችንም መጽናናትን እንዲሰጥልን እመኛለሁ።
11.1K views20:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 22:38:16
በዛሬው እለት ወንድማችን አቶ ግርማ የሺጥላ በስራ ላይ በነበረበት በታጠቁ ኃይሎች ግድያ ተፈጽሞበታል። እንዲህ አይነት እብሪተኝነት ውድቀትን እንጅ ድልን አያጎናጽፍም። ጥፋትን እንጅ ሰላምን አይሰጥም።
የህዝባችን የቆየ መገለጫው ስርዓታዊነት፣ ፍትሃዊነትና እኩልነት ነው። ከዚህ ታሪኩና ስነልቦናው ጋር የሚቃረኑ ተግባሮች በሙሉ ስርዓት አልበኝነት የወለዳቸው ናቸው።
በህግና ስርዓት እንጅ በደቦ ፍርድ የግልም ሆነ የቡድን፤ እንዲሁም የህዝብም ሆነ የአገር ጥቅምና ፍላጎት ማሳካት አይቻልም። ምክንያቱም የስርዓት አልበኝነት የመጨረሻ መዳረሻው ጥፋትና መጠፋፋት ነው።
ስለሆነም የክልላችን ህዝብ ዘላቂ ሰላሙን ለማረጋገጥ አንዲህ አይነት ስርዓት አልበኝነትንና ህገወጥ ተግባሮችን ከመንግሥት ጎን ቆሞ ሊያወግዝና ሊታገል ይገባል።
በወንድማችን አቶ ግርማ የሺጥላ ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በክልሉ መንግስትና በራሴ ስም እየገለጽኩ፤ ለክልላችን ህዝብ፤ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ በሙሉ መጽናናትን እመኛለሁ።
ዶር ይልቃል ከፍለ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
11.2K views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 20:44:02
የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በአቶ ግርማ የሺጥላ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልጻል።
የጋራ ምክርቤቱ በብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ እና የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ እና የግል ጠባቂዎቻቸው ላይ የተፈጸመው ድርጊት በጽኑ የሚወገዝ መሆኑን የጋራ ምክርቤቱ እየገለጸ ወንጀሉ የፈጸሙ አካላት መንግሥት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እንዲያደርግ እንጠይቃለን።
ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለስራ አጋሮቹ እና ለመላው ሕዝባችን መስጽናናትን እንመኛለን።
የአማራ ክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
ባሕር ዳር
11.5K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 20:23:47
"የጽንፈኝነትን ሰይጣናዊነት ያሳየ የግፍ ግድያ" የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ጽንፈኝነት ብዙዎችን ሕዝብ ልጆች አሳጥቶናል። ጽንፈኞች ሰው ሆንን ይጠፋሉ።
ዛሬ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ግርማ የሺጥላ ባደገበት ቀየ በጽፈኞች በግፍ ተገድሏል። ይህም የጽንፈኛው ኃይል የመርዝ ፖለቲካ በቀየ የማይወሰን፣ ከጓዳ ጭምር ገብቶ ቤተሰብን የሚበትን ሆኑን አሳይቶናል።
ውዱ የኢትዮጵያ ሕዝብ!
አጀንዳ አልባ የጥላቻ ፖለቲካ ዘርተው ጽንፈኝነት በማብቀል ልጆችህን በአደባባዩ የሚቀጥፉ የደም ነጋዴዎችን ማስቆም ካልቻልክ፣ የግፍ በትራቸውን የብዙኃኑን ቤት ማንኳኳቱ አይቀሬ ነው።
ዓላማቸው ማተራመስና ሀገራችንን ዕረፍት መንሣት የሆኑ አካላት አሉ። የእነዚህ አካላት አርአያዎቻቸው ዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ናቸው። የእነርሱን ተግባር በኢትዮጵያ ለመድገምና ኢትዮጵያን ለማጥፋት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ያልተፈጸሙ ዘግናኝ ተግባራትን ሁሉ ይፈጽማሉ።
ኢትዮጵያን ለማጽናትና ለማበልጸግ የጀመርነውን ትግል ጽንፈኞች አያስቆሙትም። ይሄንን ነውረኛ ዘግናኝ ተግባር የፈጸሙት የትም ቢገቡ ለሕግ ይቀርባሉ። ሌሎች በእነርሱ መንገድመ ጓዝ የጀመሩ በሕግ ማስከበር እዲቆሙ ይደረጋል።
ነብስህ በሰላም ትረፍ!
ሚያዝያ19/2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
11.7K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 20:21:10

10.4K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 18:44:13
ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት የወንድማችንን የግርማ የሺጥላን ነፍስ ነጥቀዋል።
ባሕር ዳር: ሚያዝያ 19/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ልዩነትን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ባሕል በሆነበት ክፍለ ዘመን፣ በሐሳብ የተለየንን ሁሉ በጠመንጃ ለማሳመን መነሣት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው።
ተወልዶ ባደገበት አካባቢ ፣ ከእኛ የተለየ ሐሳብ ማሰብ አልነበረበትም ብለው የሚያምኑ ነውጠኛ ጽንፈኞች የፈጸሙት አስነዋሪና አሰቃቂ ተግባር፣ ጽንፈኝነትን በጊዜ ታግለን ካላስወገድነው ወደ መጨራረስ እንደሚወስደን ጉልሕ ማሳያ ነው።
ነፍስህ በሰላም ትረፍ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
11.4K views15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ