Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Freeseminar
Cloudbridge
Traininginstitute
Cryptocurrency
Аирдроп
Tikvahtechteam
Techdailly
Attention
Cbdc
Cryptocurrencies
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.51K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 257

2022-05-24 17:47:33
የሊንኮቹን ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+Zhm6yWqPh7U0N2E0
17.7K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 17:47:26
ARE YOU LOOKING FOR LOGISTICS RELATED SHORT TERM
TRAINING PROGRAMS?

Our Association, Ethiopian Freight Forwarders and Shipping Agents Association (EFFSAA) has a good news!!!
We arranged continuous short term training programs on various topics of Logistics.

INTERESTED TO KNOW MORE?
Please call us at +251 903 182525 or +251 115 589045
OR
Visit our telegram channel
https://t.me/EFFSAAOfficial
19.5K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 22:42:18 #የዛሬ (ግንቦት 15/2014)

የአማራ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ፤ በክልሉ ከ4 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስታውቋል። የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳሳለኝ ጣሰው እንደገለጹት በቁጥጥር ሥር ከዋሉት 40 የሚሆኑት ከዚህ ቀደም በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው ፍርድ የተላለፈባቸው መሆናቸውን የጠቀሱ ሲሆን 210 የሚሆኑት ደግሞ በነፍስ ግድያ የተጠረጠሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ከትላትን በስቲያ፤ በጋምቤላ ክልል ዲማ ወረዳ በሚገኘው ስደተኛ መጠለያ ጣቢያና በመርከስ ቀበሌ ለጊዜው ማንነታቸው አልታወቀም በተባሉ ግለሰቦች የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

"በዓለማችን ያለው ቀውስ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ብቻ አይደለም። በዓለም ዙሪያ ያሉ ባልደረቦቻችን በዲሞክራቲክ ኮንጎ ለኢቦላ ወረርሽኝ፣ በአፍጋኒስታን፣ በኢትዮጵያ፣ በሶማሊያ፣ በደቡብ ሱዳን፣ በሶሪያ፣ በዩክሬንና በየመን ደግሞ ውስብስብ ለሆነ ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት እየሰሩ ነው" | ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደባህሬን አቋርጦ የነበረውን በረራ በሳምንት 3 ጊዜ ከግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የሚጀምር መሆኑን ገልጿል።

"እንደማንኛውም ሀገር እኛም በቫይረሱ [Mokeypox] ስርጭት ስጋት አለን። በኢትዮጵያ የመግቢያ እና መውጫ በሮች ላይ የተለመደው ክትትል እየተደረገ ይገኛል። በሀገሪቱ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት መግቢያ እና መውጫ ላይ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እና ወደ ሌሎች ሀገራት እንዳይሄድ የተላላፊ በሽታዎች ክትትል እየተደረገ ነው።'' | አቶ ዘውዱ አሰፋ በኢ/ህ/ጤ/ኢ የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና መረጃ ስርዓት አስተዳደር ዳይሬክተር

የቻን የአፍሪካ ዋንጫ በአስራ ስምንት ብሄራዊ ቡድኖች መካከል እንዲካሄድ ከውሳኔ ላይ መድረሱ ተገልጿል። ካፍ የተሳታፊ ሀገሮችን ብዛት በሁለት ማሳደጉ የተገለፀ ሲሆን ከቀናት በኋላ ግንቦት 18 የቻን የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች የእጣ ድልድል እንደሚወጣ ተነግሯል። የቻን የአፍሪካ ዋንጫ በሰሜን አፍሪካዋ ሀገር አልጄሪያ ከታህሳስ 30 እስከ ጥር 23 ድረስ 2015 ድረስ እንደሚካሄድ ተዘግቧል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
9.1K viewsedited  19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 19:04:33
ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌኮም ማጭበርበር ድርጊቶችን #በ9090 አሳውቁኝ ብሏል።

ከቴሌኮም አገልግሎት ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ጥቆማ ለመስጠት ኢትዮ ቴሌኮም የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ቁጥር ይፋ አድርጓል።

ደንበኞች ከታች ያሉትን ቁጥሮች በማስቀደም የደረስዎትን መልእክት ወደ 9090 #በነፃ በመላክ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ ትብብር ያደርጉ ዘንድም ጠይቋል።

በዚህም፦

- ከውጭ ሀገር የሚደወሉ ጥሪዎች በሀገር ውስጥ ቁጥር ሲቀበሉ 1ን በማስቀደም፤

- የማያውቁት የውጭ ሀገር ጥሪ ምልክት (Missed Calls) ሲያገኙ 2ን በማስቀደም፤

- የማያውቁት ሰው ገንዘብ፣ ካርድ ወይም የሞባይል ጥቅል እንዲልኩለት ካግባባዎት 3ን በማስቀደም፤

- የማጭበርበር መልእክት ከደረስዎ 4ን በማስቀደም፤

- የማያውቁት ሰው የቴሌብር ቁጥር እና የይለፍ ቃሎን ከጠየቅዎት 5ን በማስቀደም፤

- ለሌሎች የማጭበርበር ጥቆማዎች 6ን በማስቀደም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ጥቆማዎችን አድርሱኝ ሲል ጠይቋል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
22.0K viewsedited  16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 18:37:29
'የአፍሪካ ተምች' በጅማ ዞን መከሰቱ ተገልጿል።

'የአፍሪካ ተምች' በጅማ ዞን በሸቤ ሰምቦ ወረዳ መከሰቱን የጅማ እፅዋት ክሊኒክ ማዕከል አስታውቋል፡፡ የማዕከሉ ሀላፊ አቶ ቦና ሂርጳ ፥ ተምቹ በወረዳው በሚገኙ አራት ቀበሌዎች መከሰቱን መግለጻቸውን ፋብኮ ዘግቧል።

በዚህም በ400 ሄክታር መሬት ላይ በሚገኝ የበቆሎ፣ጤፍ፣ማሽላ፣ ዳጉሳ እና የግጦሽ ሳር ላይ ጉዳት አድርሷል ነው ያሉት፡፡

አሁን ላይ ተባዮችና የዕፅዋት በሽታዎች እየተስፋፉ በመሆኑ አርሶ አደሩ ማሳውን በመፈተሽ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው አሳስበዋል ሲል ዘገባው አመላክቷል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
20.9K viewsedited  15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:29:07
#ጥቆማ

አዋሽ ባንክ ታታሪዎቹ የተሰኘ የስራ ፈጠራ ውድድር በቅርቡ እንደሚጀምር አስታውቋል። የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው የውድድሩ ተሳታፊዎች የሙያዊ ክህሎት ስልጠና እንዲሁም በየደረጃው የገንዘብ ሽልማት ከማግኘታቸውም በተጨማሪ ከ1ኛ እሰከ 5ኛ የሚወጡ የመጨረሻዎቹ የውደድሩ አሸናፊዎችም ከብር 200 ሺህ እስከ አንድ ሚሊዮን የገንዘብ ሽልማትና የፈጠራ ሀሳባቸውን ተግባራዊ የሚያደርጉበት እስከ ብር አምስት ሚሊዮን የሚደርስ ከዋስትና ነፃ የብድር አገልግሎት ይመቻችላቸዋል ብሏል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
24.3K viewsedited  13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:23:45
የኢትዮጵያ ቡና በአልጄሪያ ገበያ ስለሚቀርብበት ሁኔታ ምክክር ተካሄደ

በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው የኢትዮጵያ ቡና በአልጄሪያ ገበያ ስለሚቀርብበት ሁኔታ በሀገሪቱ እውቅ ከሆነው የቡና አቅራቢ ፌኔክ ኮፊ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።

አምባሳደር ነቢያት በውይያታቸው የኢትዮጵያ ባለ ልዩ ጣዕም ቡና ቀጥታ ወደ አልጄሪያ ገበያ ስለሚቀርብበት ሁኔታ መምከራቸውን አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት 10 ወራት በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ውጭ ከተላከ ቡና አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንዳገኘች መገለጹ ይታወሳል። (ENA)

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
20.5K viewsedited  13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:22:47
የቤቶች መረጃ አስተዳደር ስርዓት በኦሮሚያ ዘጠኝ ከተሞች ሊተገበር ነው ተባለ።

ከቤቶች መረጃ አያያዝና አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚስተዋለውን ሰፊ ክፍተት ለመሙላት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የታመነበት የቤቶች መረጃ አስተዳደር ሶፍትዌር ትግበራ በኦሮሚያ ዘጠኝ ከተሞች ዛሬ በይፋ ተጀምሯል ተብሏል።

በክልሉ ከ122ሺህ በላይ የሚገኙ የቀበሌ ቤቶችን ለመመዝገብ፣ ጥገናና እድሳት ለማድረግ፣የኪራይ ውልን ለማከናወን፣ በተከራዮች የሚነሱ የተለያዩ ጉዳዮችንና ቅሬታዎችን ለመከታተልና መፍትሔ በወቅቱ ለመስጠት የመረጃ ስርዓቱ እጅግ ጠቃሚ ነው ተብሏል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
18.4K viewsedited  13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:15:58
በሐረርና ጅግጅጋ አካባቢ የተተከሉት ትራንስፎርመሮች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ ተባለ።

የሐረርና የጅግጅጋ ከተሞችና አካባቢያቸውን ችግር እንዲፈቱ የተተከሉት ፓወር ትራንስፎርመሮች ተከላ እና የፍተሻ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለሙከራ ዝግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል፡፡

የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንዳስታወቁት÷ በሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር የፓወር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራ እና ፍተሻው በመጠናቀቁ ኃይል መስጠት የሚችልበት የሙከራ ሥራ የሚሰራበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

አዲሱ የፓወር ትራንስፎርመር መሉ በሙሉ ወደ ስራ ሲገባ በሐረር፣ በአወዳይ፣ በኮምቦልቻ ከተሞችና የገጠር መንደሮች በማከፋፈያ ጣቢያው በሚስተዋለው ከአቅም በላይ ጭነት ምክንያት ያጋጥም የነበረውን የኃይል እጥረት ሙሉ በሙሉ ይቀርፋል ብለዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም እስከ ሐሮማያ ከተማ እንደ አስፈላጊነቱ መመገብ የሚችል አቅም የተፈጠረለት ሲሆን÷ አዲሱ ትራንስፎርመር ከነባሩ ትራንስፎርመር አቅም ጋር ሲነጻጸር በ5 እጥፍ የሚበልጥ አቅም እንዳለው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በጅግጅጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የፓወር ትራንስፎርመር ተከላ ሥራ እየተከናወነ ሲሆን÷ አፈጻጸሙም ከሐረር ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር ተቀራራቢ በሆነ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የሪጅኑ የሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከድር አብደላ ገልጸዋል።

አቶ ከድር አክለውም÷ ሪጅኑ ከሑርሶ እስከ ሐረር ድረስ ባለው የ132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ አስራ ሁለት የ132ኪሎ ቮልት 400/800/1 አምፐር ከረንት ትራንስፎርመሮችን በመትከል የምስራቅ ኢትዮጵያን የግሪድ ሲስተም የሚያስተካክል ሥራ ሰርቷል ብለዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
17.7K viewsedited  13:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:15:49
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+Zhm6yWqPh7U0N2E0
16.3K views13:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ