Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Choleraupdate
مور
Tikvahfamily
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.46K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-05-01 13:15:34
እንኳን አደረሳችሁ!

ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ!

ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን!

ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764

ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ t.me/bluebellgiftstore

#ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል https://t.me/bluebellgiftstore/627
22.5K views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 13:48:29
ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ ዓሳ እየተገኘ ነው ተባለ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከዚህ ቀደም ታጥቀው ይንቀሳቀሱ የነበሩና ሌሎች ወጣቶች በ2 ማኅበር ተደራጅተው በጀመሩት የዓሳ ማስገር ስራ ከህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ ዓሳ እየተገኘ መሆኑ ተገለፀ።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሐይቅ ግድቡ ውሀ መያዝ ከጀመረ ወዲህ በተለይም ለዓሳ ምርት ምቹ መሆኑ ሲገር በ8 ወራት ውስጥ 1729 ቶን ዓሳ ምርት ከህዳሴ ግድብ መገኘቱን ዶይቼ ቨለ በዘገባው አመልክቷል።

ወጣቶቹ የተደራጁበት ማህበርም 56 የሚደርሱ ወጣቶችን ያቀፈ ሲሆን በግደቡ ዳርቻ በሚሰሩት የዓሳ ማስገር ስራ በቀን ከ2 እስከ 3 ኩንታል ዓሳ እንደሚኝና በአካባቢው የዓሳ ማስገር ስራውን በማህበሰረብ አቀም ለማድረግና ለማሻሻል ዘመናዊ ጅልባዎች ያስፈልጋሉ ተብሏል።

@TikvahethMagazine
31.1K viewsedited  10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 12:25:30
#CholeraUpdate

በኢትዮጵያ ባለፈው ወር ከአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የኮሌራ ታማሚዎች ቁጥር እንደተመዘገበ ተነገረ

በአፍሪካ ባለፈው መጋቢት ወር በኮሌራ በሽታ ከተያዙ 14,441 አዲስ የኮሌራ ታማሚዎች መሃከል ከአህጉሪቱ ከፍተኛ ታማሚዎች የተመዘገቡባት ኢትዮጵያ መሆኗን የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት አመልክቷል።

በተጠቀሰው ወር በኢትዮጵያ 4009 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው ተነግሯል። በኮሌራ ከተያዙት ሰዎች ውስጥም 24 ሰዎች መሞታቸው ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ባለፉት 3 ወራት 9,429 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 111 ሰዎች መሞታቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል።

በአፍሪካ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2023 እስከ ማርች 31 ቀን 2024 በጠቅላላው በ18 ሀገራት 271,119 ሰዎች በኮሌራ በሽታ ሲያዙ በተጠቀሰው ጊዜ በኢትዮጵያ 39,892 ሰዎች በበሽታው ተይዘው 524 ሰዎች መሞታቸውም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
29.7K viewsedited  09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 12:17:49
#እንድታውቁት

ነገ ረቡዕ ሚያዚያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በአለም አቀፍ ደረጃ የሠራተኞች ቀን የሚከበርበት ቢሆንም፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዋናው መስሪያ ቤት እስከ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቹ ድረስ በሚገኙ ሁሉም ቢሮዎች ሁሉንም አገልግሎቶቹን እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

@TikvahethMagazine
26.7K viewsedited  09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 12:01:08
በ2023 አምስት ምርጥ እንግሊዝኛ ተናጋሪ የአፍሪካ ሀገራት የትኞቹ ናቸው?

"ኢዱኬሽን ፈርስት" የተባለ ዓለማቀፍ የትምህርት ተቋም እድሜአቸው ከ 18 - 20 የሆኑ 2.1 ሚሊዮን ወጣቶችን ከ113 ሀገራት የእንጊሊዘኛ ቋንቋ ችሎታቸውን በመገምገም የሀገራትን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ተናጋሪ ብቃት ደረጃ አውጥቷል።

ተቋሙ የቋንቋውን ተናጋሪዎች ብቃት በጣም የላቀ፣ ከፍተኛ፣ መካከለኛ፣ ዝቅተኛ እና በጣም ዝቅተኛ በሚሉ አምስት የብቃት ደረጃዎች በመክፈል ነው ሪፖርቱን ይፋ ያደረገው።

በሪፖርቱ መሰረትም ከ1ኛ እስከ 5ኛ የተቀመጡ የአፍሪካ ሀገራት በቅደም ተከተል፦

ደቡብ አፍሪካ
ኬንያ
ናይጄሪያ
ጋና
ኡዳንዳ መሆን ችለዋል።

ከአፍሪካ በቋንቋ ተናጋሪነት ብቃት የመጀመሪያ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ደቡብ አፍሪካ  "#በጣም_የላቀ" በተባለው ከፍተኛ የእንግሊዘኛ ብቃት ያላችው ሀገራት ምድብ ውስጥ ተካትታለች።

2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኬንያ እንዲሁም 3ኛዋ ናይጄሪያ "#ከፍተኛ" በተባለው እንዲሁም  ዩጋንዳ እና ጋና "#መካከለኛ" በተባለው የቋንቋ ተናጋሪነት ምድብ ተመድበዋል።

ሀገራችን #ኢትዮጵያ #ዝቅተኛ የእንጊሊዝኛ ቋንቋ ተናጋሪነት ምድብ ውስጥ ከታንዛኒያ፣ ሞሮኮ፣ አልጄሪያ፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ግብፅ ጋር መመደቧ በሪፖርቱ ተመላክቷል።

ኔዘርላንድስ፣ ሲንጋፖር፣ ኦስትሪያ፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ከአለም ከ1 እስከ 5 ያለውን የኢንግሊዝኛ ቋንቋ ተናጋሪነት ብቃት ደረጃ መያዝ ችለዋል።

@TikvahethMagazine
25.7K viewsedited  09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-30 12:00:33
እንኳን አደረሳችሁ!

ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ!

ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን!

ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764

ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ t.me/bluebellgiftstore

#ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል https://t.me/bluebellgiftstore/627
26.7K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 15:59:31
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በቤሩት አል ሃሪሪ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ምን ገጠመው?

የሊባኖስ አቬዬሽን ባለስልጣን “ቴል አቪቭ” የተሰኘ መለያ ያለበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቤይሩት ሲደርስ ተቃውሞ ማሰማቱን የሀገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የሀገሪቱ ሲቪል አቬዬሽን ባለስልጣን ቤይሩት ያረፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ 787-9 አውሮፕላን ወደ አዲስ አበባ ከመመለሱ በፊት ምልክቱን እንዲሸፍን አድርጓል።

በተጨማሪም፥ አውሮፕላኖች በቤይሩት ከመድረሳቸው በፊት ሊባኖስ "ጠላቴ ናት" ከምትላት እስራኤል ጋር የተያያዘ ምንም አርማ እንደሌለ ማረጋገጥ እንዳለበት አሳስቧል።

ሊባኖስ ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ኖሯት የማያውቅ ሲሆን እንደ ጠላት ሀገር የሚተያዩ ናቸው።

ሁለቱ ሀገራት በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመሀከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭትና የሊባኖስ ታጣቂ ቡድን የሆነው 'ሒዝቦላ' ጋር በሚያደርጉት ውጊያ ቀጠናው እና ሁለቱ ሀገራት የተካረረ ውጥረት ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል።

አየር መንገዱ አዳዲስ አውሮፕላን ሲያስገባ አውሮፕላኖቹ የመጀመሪያ በረራ ያደረጉበት የመጀመሪያው ከተማ ስም በውጨኛው ክፍል ላይ ይጻፋል። ይህም የአየር መንገዱ ልምድ ነው።

በዚህ መሰረትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ4 አመት በፊት ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኑን ወደ መስመር ሲያስገባ ቅድሚያ የበረረበትን የከተማ ስያሜ ' ቴል አቪቭ ' የሚል የሚል ስያሜ ሰጥቶት ነበር።

@TikvahethMagazine
35.3K viewsedited  12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 13:29:05
#ጥንቃቄ: በቦሌ ክ/ከተማ የጣለዉን ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ

በዛሬው ዕለት ንጋት ላይ በቦሌ ክ/ከተማ በወረዳ 11 ወረገኑ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የጣለዉን ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የክረምት ወር መግባቱን ተከትሎ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች 32 ሺሕ አባወራዎች ለጎርፍ አደጋ የተጋለጡ መሆናቸው ሲገለፅ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ ልደታ፣ ቂርቆስና አራዳ ክፍለ ከተሞች በተደጋጋሚ ጎርፍ የሚያጠቃቸውና በከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎች መሆናቸው በጥናት ተለይተው ታውቀዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸዉን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ህብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት የለየ ሲሆን ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ከከተማ አስተዳደሩና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልእክቶችን ተግባራዊ እንዲያደርግ መልእክቱን አሰተላልፏል፡፡

@TikvahethMagazine
36.6K views10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 12:50:23
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት የኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ገደብ ማስቀመጡን አሳወቀ

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በኅብረቱ አባል ሀገራት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ገደብ ማስቀመጡን ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

በዚህም የህብረቱ ለአባል ሃገራት ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን ቪዛ አመልካቾች ቪዛ ሲፈልጉ

- አስፈላጊ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ እና በአውሮፓ ህብረት ህግ የተቀመጠውን መደበኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ እንደሚገደዱ ተጠቁሟል።

- አባል ሀገራት ከአሁን በኋላ ከሁለት ጊዜ በላይ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ለመግባት የሚያስችለውን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን መስጠት እንደማይችሉም ተገልጿል።

- የዲፕሎማቲክ ወይም የሰርቪስ ፓስፖርት የያዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ ሲፈልጉ መደበኛውን የቪዛ ክፍያ ለመክፈል እንደሚገደዱም ተነግሯል።

በተጨማሪም፣ መደበኛው ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን ተቀይሯል።

ይህ ውሳኔ የተወሰነው የህብረቱ ምክር ቤት ባደረገው ግምገማ መሰረት ኢትዮጵያ በህገ-ወጥ መንገድ በአውሮፓ ህብረት የሚቆዩ ዜጎቿን በማስመለስ ረገድ የምታደርገው ጥረት በቂ ባለመሆኑ እንደሆነ ተነግሯል።

@TikvahethMagazine
34.1K viewsedited  09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 12:49:56
ኢትዮጵያ የፓኪስታን ባንኮች በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቻቸውን እንዲከፍቱ ጥሪ አቀረበች

የኢፌዲሪ አምባሳደር ጀማል በከር አብዱላ የፓኪስታን ባንኮች ከንግድ ጋር የተያያዙ ግብይቶችን ለማካሄድ ቅርንጫፎቻቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ መጠየቃቸውን የሀገሪቱ የዜና ምንጭ ዘግቧል።

አምባሳደሩ ጥሪውን ያቀረቡት በፋይሳላባድ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት (FCCI) ጋር በነበራቸው ንግግር ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስትም የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለማደላደል እና የሁለትዮሽ ንግድን ለማቀላጠፍ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የባንክ ቅርንጫፎችን መክፈት ትልቅ ፈተና እንዳለው የተናገሩት አምባሳደሩ ከተሳካ ግን የሁለትዮሽ ንግድን ለማጠናከር እና የፓኪስታን ላኪዎች ሰፊውን የአፍሪካ ገበያ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ብለዋል።

@TikvahethMagazine
29.5K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ