Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Choleraupdate
مور
Tikvahfamily
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.46K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-04-18 12:00:41
የውጭ ባለሀብቶች በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቀደ

ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ መደረጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቀዋል።

በዚህም መሰረት የውጭ ባለሀብቶች በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላክ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሟሉ የውጭ ባለሃብቶች ከማዳበሪያ እና ነዳጅ በስተቀር በሁሉም የገቢ ንግድ ኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ ተብሏል።

የጅምላ ንግድን በተመለከተ ከማዳበሪያ ጅምላ ንግድ በስተቀር በሁሉም አይነት የጅምላ ንግድ መስኮች መሰማራት ይቻላል ሲባል በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች ቅድመ ሁኔታዎችን ሲያሟሉ ለአገር ውስጥ ባለሃብት በተከለሉ ሁሉም የችርቻሮ ንግድ ስራዎች መሳተፍ እንዲችሉ መፈቀዱንም ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

@TikvahethMagazine
20.7K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 12:00:10
ከዘመኑ ጋር ይዘምኑ!

      ራሰዎን በአንድ ቋንቋ አይገድቡ! የተለያዩ ቋንቋዎችን ይማሩ! የስራ ፣ የትምህርት እና የህይወት አማራጭዎን ያስፉ !
    ስልክዎን ተጠቅመው የፈለጉትን ቋንቋ በታላላቅ ዩንቨርቲዎች እና ኮሌጆች በሚያስተምሩ  ብቁ መምህራኖቻችን ተምረው በራስ መተማመንዎን ያዳብሩ!
   
እንግሊዘኛ
አረብኛ
አፋን ኦሮሞ
አማርኛ  ቋንቋዎችን የትም ሀገር ቢሆን አያሳስበዎት  በኦንላይን እናስተምረዎታለን!

ብራይት የስልጠና ማዕከል
    ለብርሀናማ ሕይወት ትክክለኛ ቦታ
0970828287
0932878889
https://t.me/brighttraining90
18.4K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 12:00:10
MESTURAH STORE

ማንኛውንም አይነት እቃ ከ SHEIN እና ከ ALI EXPRESS ትእዛዝ መቀበል ጀምረናል ከታች ባሉት Website የፈለጋቹትን መርጣቹ በቴሌግራም ሊንካችን ይላኩልን

የቴሌግራም ሊንካችን https://t.me/mesturahstore

የቲክቶክ ገፃችን https://www.tiktok.com/@mesturahstore?_t=8lYRHxeLhfp&_r=1

በተጨማሪም 0911267699

የ SHEIN website: https://www.shein.com/

የ ALI EXPRESS website: https://www.aliexpress.com/
19.5K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 19:00:47
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ለ658 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው እንደገለጹት የኢድ አል ፈጥር እና መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ658 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ እንደተደረገላቸው ተናግረዋል።

በዚህም፦

በሙሉ ይቅርታ ወንድ 637 ፤ሴት 11 ፤

በልዩ ሁኔታ ወንድ 3 ሴት 3

በጠቅላላው 654 ታራሚዎች ሲሆኑ ለ 4 ወንዶች ደግሞ የእስራት ቅናሽ ተደርጎላቸዋል።

በክልሉ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን ስር ባሉ #ሰባት ማረሚያ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች በ2016 በጀት ዓመት ይቅርታ ሲደረግ ይህ ለ2ኛ ዙር ነው።

@TikvahethMagazine
27.1K viewsedited  16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 18:52:44
በአለም ተወዳጁ የአረቢካ ቡና ዝርያ ከ600ሺ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ መገኘቱ በጥናት ተረጋገጠ

በአለም ተወዳጅነትን ያተረፈው የአረቢካ ቡና ዝርያ ከ600,000 ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ደኖች ውስጥ በሁለት ሌሎች የቡና ዝርያዎች ተፈጥሯዊ ውህደት ስለመፈጠሩ ዓለማቀፍ የሳይንስ ተመራማሪዎች ቡድን በጥናት ማረጋገጣቸውን በኔቸር ጄኔቲክስ ላይ የወጣው የምርምር ውጤት ያመላክታል።

ይህ የአረቢካ ቡና ተክል መነሻው ኢትዮጵያ ሲሆን ተመራማሪዎች የዚህን የቡና ተክል የጂኖሚክ መረጃን በመጠቀም የቡናውን የረዥም ጊዜ ታሪክ ለማጥናት እና በዘመናዊ መንገድ ከሚመረቱ  ሌሎች የቡና ተክሎች ጋር ያለውን ግንኙነት ለመለየት ጥናት ማድረጋቸው ተገልጿል።

በዚህም የአረቢካ ቡና ከ "Coffea canephora" እና " Coffea eugenioides "  ከተባሉ የቡና ዝርያዎች ከእያንዳንዳቸው ሁለት ክሮሞዞሞችን በመውሰድ ከ600ሺ አመታት በፊት ስለመፈጠሩ የሳይንስ ተመራማሪዎቹ በተጠቀሙት የጊዜ ስሌት ቀመር ማረጋገጣቸውን ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine
24.9K viewsedited  15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 18:52:20
በወር 15,000 ብር ማግኘት ይፈልጋሉ?

እንግዲያውስ
ብስክሌት
ሞተር
E-bike ካልዎት ምን ይጠብቃሉ ከ ቢዩ ዴሊቨሪይ ጋር መስራት ይችላሉ።

ቢዩ ዴሊቨሪይ የምግብ አድራሽ ድርጅት ሲሆን ብስክሌት ፥ ሞተረ እና E-bike ካለው ግለሰብ ጋር አብሮ መስራት ይፈልጋል።

የስራ አድራሻ ፥ አዲስ አበባ

ለመመዝገብ:-


ከታች ባለው ( Telegram Bot ) በመጠቀም የቀረባልችሁን ጥያቄ በመሙላት

https://t.me/DriversRegistration_bot

ወይም

9533 ላይ በመደወል መመዝገብ ይችላሉ።
23.5K views15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 14:45:42
በግብርና ምርቶች ብክነት በዓመት ከ474 ቢሊዮን ብር በላይ እየታጣ መሆኑ ተነገረ

የግብርና ሚኒስቴር አዲስ ያስተዋወቀው የግብርና ምርቶች አስተዳደርና አመራር ስትራቴጂ፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ 474.67 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የምርቶች ብክነት መኖሩን አመልክቷል በማለት ሪፖርተር አስነብቧል።

እያጋጠመ ያለው ብክነት የምርት ሒደት የሚያቀላጥፉ ምርጥ ዘር፣ ውኃ፣ የአፈር ማዳበሪያ፣ የግብርና ኬሚካሎች፣ መሬት፣ የእንስሳት መኖ፣ እንዲሁም የእንስሳት መድኃኒቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል ካለመቻል እንደሆነ ተጠቅሷል። 

በመሆኑም በየዓመቱ 161.74 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ የሥጋና ወተት ምርቶች እንዲሁም 312.93 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ የቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬዎች፣ ፍራፍሬዎችና አትክልቶች እየባከኑ መሆኑም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
25.6K viewsedited  11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:20:12
በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ባለ የቁጠባ ዘመቻ በርካታ ጥሬ ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው።

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አከባቢዎች ቁጠባን ለማበረታታት በተደረጉ ዘመቻዎች ነዋሪዎች በርካታ ጥሬ ገንዘብ በስንቄ ባንክ በኩል በቁጠባ መልክ ማስቀመጥ መቻላቸው ተገልጿል።

ለአብነትም በጅማ ዞን ሊሙ ወረዳ በነበረ የአንድ ቀን ዘመቻ ብቻ 252 ሚሊዮን ብር በስንቄ ባንክ በኩል ገቢ መሆን ችሏል። የወረዳው አስተዳዳሪ አንደገለጹት በዚህ ዓመት 2.4 ቢሊዮን ብር በቁጠባ መልክ ወደ ባንኩ እንዲገባ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ በአጋሮ ከተማ በአንድ ቀን በተደረገ የቁጠባ ዘመቻ 21.8 ሚሊየን ብር በስንቄ ባንክ በቁጠባ ሂሳብ ገቢ ሆኗል ተብሏል።

@TikvahethMagazine
28.5K viewsedited  07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:19:34
#Update: በጄኔቫ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ለማሰባሰብ በተደረገው ስነ ስርዓት ሀገራት ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደሚሰጡ አስታወቁ

በኢትዮጵያ ለተከሰተው የሰብዓዊ ቀውስ አስቸኳይ 1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማሰባሰብ በስዊትዘርላንድ ጄኔቫ በተካሄደው ሥነ ሥርዓት ሀገራት 630 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለኢትዮጵያ እንደሚሰጡ አስታወቁ።

በዚህም አሜሪካ 253 ሚሊዮን ዶላር እንደምትሰት ቃል ስትገባ ዩናይትድ ኪንግደም 125 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድምሩ ከ139 ሚሊየን ዶላር በላይ ለመስጠት ቃል ገብተዋል።

የመንግስታቱ ድርጅት በሚቀጥሉት 3 ወራት ብቻ ለኢትዮጵያ እርዳታ ለማቅረብ 1 ቢሊዮን ዶላር  እንዲሁም በሀገሪቱ በ2024 እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ድጋፍ ለማድረግ 3.24 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል ማለቱ ይታወሳል።

@TikvahethMagazine
24.1K viewsedited  07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:19:01
MESTURAH STORE

ማንኛውንም አይነት እቃ ከ SHEIN እና ከ ALI EXPRESS ትእዛዝ መቀበል ጀምረናል ከታች ባሉት Website የፈለጋቹትን መርጣቹ በቴሌግራም ሊንካችን ይላኩልን

የቴሌግራም ሊንካችን https://t.me/mesturahstore

የቲክቶክ ገፃችን https://www.tiktok.com/@mesturahstore?_t=8lYRHxeLhfp&_r=1

በተጨማሪም 0911267699

የ SHEIN website: https://www.shein.com/

የ ALI EXPRESS website: https://www.aliexpress.com/
21.7K views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ