Get Mystery Box with random crypto!

የቤቶች መረጃ አስተዳደር ስርዓት በኦሮሚያ ዘጠኝ ከተሞች ሊተገበር ነው ተባለ። ከቤቶች መረጃ አያ | TIKVAH-MAGAZINE

የቤቶች መረጃ አስተዳደር ስርዓት በኦሮሚያ ዘጠኝ ከተሞች ሊተገበር ነው ተባለ።

ከቤቶች መረጃ አያያዝና አስተዳደር ጋር በተያያዘ የሚስተዋለውን ሰፊ ክፍተት ለመሙላት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የታመነበት የቤቶች መረጃ አስተዳደር ሶፍትዌር ትግበራ በኦሮሚያ ዘጠኝ ከተሞች ዛሬ በይፋ ተጀምሯል ተብሏል።

በክልሉ ከ122ሺህ በላይ የሚገኙ የቀበሌ ቤቶችን ለመመዝገብ፣ ጥገናና እድሳት ለማድረግ፣የኪራይ ውልን ለማከናወን፣ በተከራዮች የሚነሱ የተለያዩ ጉዳዮችንና ቅሬታዎችን ለመከታተልና መፍትሔ በወቅቱ ለመስጠት የመረጃ ስርዓቱ እጅግ ጠቃሚ ነው ተብሏል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot