Get Mystery Box with random crypto!

የስብዕና ልህቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የሰርጥ አድራሻ: @human_intelligence
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 89.08K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-06 13:28:02 እረፉ!!!!
“ዘመመ!” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ
እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ።

እረፍ!!!!
“ቆሜያለሁ!” ለማለት አጥሬን አትደገፍ
ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ።

እረፍ!!!!
በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም
በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም።

እረፊ!!!
በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ
በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ።


ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ
ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ።
ምክንያት ታመመ መፍትሄ ታመመ
ከጥያቄው በፊት መልሱ እየቀደመ።

ሌብነት ገነነ
ግርግር ገነነ
ብልጭልጭ ገነነ
ድንግርግር ገነነ
ኪሳራ ገነነ
ደላሎች ገነኑ፣ ደላሎች ጀገኑ
ባልዋለ ገበያ ዋጋ እየተመኑ!!!!!

ምክንያት ታመመ መፍትሔ ታመመ
ከጥያቄ በፊት መልስ እየቀደመ ::

እያዩ ፈንገስ
በረከት በላይነህ

@Human_Intelligence
4.1K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 22:51:43 በምንም ነገር አልገደብም !!!

ገና በ19 ወሯ በደረሰባት የትኩሳት በሽታ ራሷን የሳተችው ሄለን ኬለር፣ ወዲያውኑ የማየቷንና የመስማቷን ብቃት ተነጠቀች፡፡ ስለሄለን ስናስብ የሚያስገርመን ማየትና መስማት የተሳናት ሴት መሆኗ አይደለም፡፡ በሁኔታዋ ሳትበገር የመጀመሪያዋ ማየትም መስማትም የማትችል የዲግሪ ተመራቂ፣ የዩኒቨርሲቲ አስተማሪ፣ ጸሃፊ . . . ለመሆን መብቃቷ ያስገርመናል!!! ለዚህ ያበቃትን አመለካከቷ በአጭር ቃል ስታስቀምጠው፣ “ውስንነቴ ላይ አተኩሬ አላውቅም፣ ልቤንም በኃዘን አይሞሉትም፡፡ አልፎ አልፎ አንዳንድ ናፍቆቶች ቢመጡብኝም . . . እጅግ በጣም ስስ ስሜቶች ናቸው”፡፡

ሄለን ኬለር በውስንነታቸውና በገደባቸው ላይ ለሚያተኩሩ ሰዎች ካስተላለፈችው ብዙ መልእክቶች መካከል . . .  

“የራስን ሁኔታ እያዩ ሲያዝኑና ከንፈር ሲመጥጡ መኖር ክፉ የተባለው ጠላታችን ነው፡፡ ለዚህ ጠላት ራሳችንን አሳልፈን ከሰጠነው በዚህ ዓለም ውስጥ ምንም ጥበብ የሞላው ነገር ማድረግ አንችልም” – Hellen Keller
አንተ “ጎዶሎዬ ይህ ነው” ብለህ ከምታስበው ሁኔታህ እጅግ የባሰ ሁኔታ ውስጥ እያለ የተሟላ ሕይወት የሚኖር ሰው እንዳለ ላስታውስህ፡፡ በአንጻሩም፣ ሙሉ፣ ስኬታማና ደስተኛ ሆኜ ለመኖር ይህኛውና ያኛው ያስፈልኛል ብለህ የምታስባቸውን ነገሮችና ከዚያም በላይ እያላቸው በጣም አሳዛኝና ያልተሟላ ሕይወት የሚኖሩም ሰዎች እንዳሉም ላስታውስህ፡፡

“አንገትህን በፍጹም አታቀርቅር፡፡ ሁል ጊዜ ቀና በል፡፡ ይህችን አለም አይን አይኗን ተመልክተሃት በድፍረት ኑር”
– Hellen Keller

ያለህ ነገር ወይም ሁኔታህ ሌላው ሰው ካለው ነገርና ሁኔታ ቢያንስም እንኳ፣ ሰው መሆንህ ግን ከማንም አያንስም፡፡ ክብርህ ያለው ሰው የመሆንህ ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ፣ የገጠሙህን ሁኔታዎች ተጋፈጣቸው፣ ቀና ብለህ ለመኖርም ወስን፡፡ በዚህች ምድር ላይ ያለ ጀግና እስካሁን ምንም ክፉ ያልገጠመው ወይም ጎዶሎ ነገር የሌለው ሰው አይደለም፣ ጀግናው ከገጠመኞቹ አልፎ የሚሄደው ሰው ነው፡፡

“የእኛን ሁኔታ ከእኛ የተሻለ ነገር አላቸው ከምንላቸው ሰዎች ጋር ከማወዳደር ይልቅ፣ በተግዳሮት ውስጥ ካሉት ከብዙሃኑ ጋር ብናወዳድረው ምን ያህል ከታደሉት መካከል እንዳለን ይገለጥልናል”– Hellen Keller


የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
2.6K views19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 14:59:47 #ለጨረቃዋ_አልም!!!

ለጊዜው የማይደረስባቸው ቢመስሉህ እንኳ የሚያነሳሱህን ግቦች አስቀምጥ፡፡ በቀላሉ ልታሳካው የምትችለውን ግብ ካስቀመጥክ ከአቅምህ በታች የሆነን ነገር የማሳካት እድልህ ከፍተኛ ነው፡፡ ሌስ ብራውን በጥልቀት እንዳስቀመጠው “ለጨረቃዋ ዓልም፣ ጨረቃዋን ብትስት እንኳ ከከዋክብቶቹ መሀል አንዷ ላይ ትቆማለህ፡፡” 

ስራን ከመስራት ውጭ ወደ ስኬት፣ ወደ ደስታ ወይም ወደ ጤና የሚያደርስ ሌላ ምንም ምስጢር የለም፡፡ ትርጉም ያለው ግብን ለመከተል ስላለህ ፍላጎት ፍቃድንም ሆነ ይቅርታን አትጠይቅ - ዝም ብለህ ግብህን ተከትለህ ተጓዝ፡፡ በችሎታዎችህ ላይ ተመካ፤ እንዲሁም ውድቀት አማራጭ ይሆናል ስለሚለው ሀሳብ ፍንጭ አይኑርህ፡፡ እየሄድክ ተማር፡፡ ከወደቅክም ወደፊት ውደቅ፡፡

በርታ ለጨረቃዋ አልመህ ተጓዝ… ባይሳካልህ እንኳን ከዋክብቱ ላይ ታርፋለህና!
 
#የስኬት_አቡጊዳ መጽሐፍ

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
1.7K views11:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:56:15 በዕውቀት ዘመን በህዝብ ፈቃድ መተዳደር እንጂ መገዛት የለም!

ድሮ ድሮ አብዛኛውን የዓለም ሐገራት ይመሩ የነበሩት በጎበዝ አለቆች ነበር፡፡ ያኔ መሪ ማለት ባለመሣሪያና በስልጣኑ ላይ የሚቀናቀነውንና የሚጠላውን የሚገድል ነበር፡፡ በዛ ዘመን ጊዜ ያጀገናቸውና ዕድልና አጋጣሚ የፈጠረላቸው ጉልበታቸው ሃይላቸው የሆኑ ሠዎች ሐገርና ሕዝብን ከጉልበታቸው ስር አንበርክከው ለዘመናት በክርናቸው ገዝተዋል፡፡

ተገዢው የዓለም ህዝብ ለብዙ ዘመናት ከእንደዚህ ዓይነት አንባገነን ጭቆና ለመላቀቅና ነፃነቱን ለመጎናፀፍ በተለያየ የጭቆና አገዛዝ ቀንበር ውስጥ ሆኖ ትግሉን አላቋረጠም ነበር፡፡ በትግሉም ስንቱ አጥንት ከስክሷል፣ ደሙንም አፍሷል፣ ስንቱ ሕይወቱን፣ ልጁን፣ አባቱን፣ እናቱን፣ ዘመዱን፣ ንብረቱን፣ ጥሪቱን ወዘተ ገብሯል፡፡

ያ ቅስም ሠባሪ፣ ተስፋ አስቆራጭ፣ አድካሚና ስቃይ የተሞላው ትግል የስንቱን ህይወት ቀጥፎ ዛሬ ፍሬ አፍርቷል፡፡ ብዙዎቹ የዓለማችን ሐገራት ከጉልበት ብዝበዛ፣ ከአንባገነን አገዛዝ ተላቀዋል፤ እየተላቀቁም ይገኛሉ፡፡

ዛሬ መሪ ማለት በእውቀት ከፊት የሚቀድም እንጂ ከኋላ ሆኖ በጭቃ ጅራፍ የሚገርፍ አይደለም፡፡ መሪነት በእውቀት መሻል፣ በሐገር ፍቅርና በቅንነት መርቀቅ፣ ለፍትህና እና ለነፃነት ዘብ መቆም እንጂ ለራስ ጥቅም ብቻ አርበኛ መሆን አይደለም፡፡ ይሄ ዘመን ህዝብን በእውቀት አሳምኖ እንጂ በማስፈራራት ለሚገዛው መሪ ቦታ የለውም፡፡ የአሁኑ ትውልድ በፍትህና በነፃነት፤ በእኩልነትና በክብር፤ በምክንያትና በዕውቀት እንድታስተዳድረው እንጂ ቀጥቅጠህ #በአድሎና #በነሲብ እንድትገዛው አይፈልግም፡፡

አሁን በመሪህ መገዛት የለም መተዳደር እንጂ፡፡ በስልጣን ላይ ያሉ የሐገር መሪዎች ህዝብን ሊያገለግሉ እንጂ ሊገለገሉበት እንዳልሆነ የተረዱበት ዘመን ቢኖር አሁን ብቻ ነው፡፡ ማንም መጥቶ የሕዝብ አናት ላይ ወጥቶ እንዳሻው ሊዘውረው የማይችልበት ዘመን ላይ ደርሠናል፡፡ ጊዜ ዳኛ! አጃኢብ ጊዜ!

ለዚህም ነው ማሕተመ ጋንዲ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ዋዜማ ላይ ሆኖ ለሐገሩ ሕንድ ዘመኑን የቀደመ ንግግር የተናገረው፡፡ አባባሉም እንዲህ የሚል ነበር፡-

.......‹‹ከዕለታት አንድ ቀን ሕዝብን መምራት ማለት በጡንቻ መጠቀም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሕዝብን መምራት ማለት ከሕዝብ ጋር አብሮ ለመሄድ መቻል መሆኑ ታይቶኛል፡፡››....... ነው ያለው፡፡ ድንቅ ንግግር!

በዕውቀት ዘመን በህዝብ ፈቃድ መተዳደር እንጂ መገዛት የለም!

እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)

የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
1.9K viewsedited  14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 04:23:12 ብቃትን ፍለጋ!

አንድ ጊዜ ፈጣሪ ሰውን ያላካተተ ስብሰባን ጠራና ፍጥረትን ሁሉ ሰብስቦ አንድን ጥያቄ ጠየቃቸው፣ ይላል አንድ ምንጩ ያልታወቀ አፈ-ታሪክ፡፡

ጥያቄው እንዲህ የሚል ነበር፡-

“ለነገሩ ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ አንድን ነገር ከሰው ልጆች ልሰውርባቸው እፈልጋለሁ፡፡ ስለሆነም ያንን ከሰዎች ለመሰወር የምፈልገውን ነገር የት ባስቀምጠው ሰዎች ላያገኙት የሚችሉ ይመስላችኋል?” አላቸው፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት ብዙም የደፈረ እንስሳ ማግኘት ከባድ የነበረ ቢሆንም አራት እንስሶች የየግል ሃሳባቸውን ሰነዘሩ፡፡

ንስር እንዲህ አለ፡-

“ከሰዎች ለመሰወር የፈለከውን ነገር ለእኔ ስጠኝና ከፍ ብዬ መብረር ስለምችል ጨረቃ ድረስ ይዤው እወጣና እዚያ አስቀምጠዋለሁ”፡፡ ፈጣሪም መልሶ፣ “አንድ ቀን የሰው ዘር ጨረቃ ላይ የመውጣት ብቃት ስለሚኖረው ማግኘታቸው አይቀርም” አለው፡፡

አሳ እንዲህ አለ፡-

“እንደ ውቂያኖስ ጥልቅ ነገር እንደሌለለና ሰዎች እዚያ ጥልቀት ድረስ እንደማይሄዱ አውቃለሁና እኔ በዋና እዚያ ድረስ መጥለቅ ስለምችል ይዤው ልግባና እዚያ አስቀምጠዋለሁ”፡፡ ፈጣሪም መልሶ፣ የሰው ልጅ ወደጠለቀው ባህር የመግባት አቅም ለማዳበር ብዙ ጊዜ ስከማይፈጅበት ማግኘቱ አይቀርም” ብሎ መለሰ፡፡

አንበሳ በተራው እንዲህ አለ፡-

“እንኳን ሰው አብዛኛዎቹ የዱር እንስሶች እንኳ የሚፈሩት ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ የምደፍር እኔ ነኝ፡፡ እዚያ ወስጄ ባስቀምጠው ስለማያገኙት ለእኔ ስጠኝ”፡፡ ፈጣሪም፣ “ሰዎች ጫካን መመንጠር ብዙም ስለማይከብዳቸው ቀስ በቀስ ይደርሱበታል” አለ፡፡

ጦጣ በመጨረሻ እንዲህ አለች፡-

“ፈጣሪ ሆይ፣ ከእነዚህ ሁሉ ሃሳብ ሰጪዎች በበለጠ ሁኔታ ከሰው ጋር ቀረብ ብዬ የምኖረው እኔ ስለሆንኩኝ ባህሪያቸው በደንብ አውቀዋለሁ፡፡ ሰዎች አብዛኛውን ነገር ፍለጋ ውጪ ውጪውን ነው የሚሉት፡፡ ውስጣቸው ያለው ነገር ትዝም አይላቸው፡፡ ስለዚህ ውስጣቸው ብታስቀምጠው በቀላሉ አያገኙትም” አለችው፡፡

የጦጣ መልስ ተቀባይነት ስላገኘ ፈጣሪ ለመደበቅ ያሰበውን ነገር በሰው ውስጥ አስቀመጠው ይባላል፡፡ ይህ የተደበቀው ነገር የራሳቸው የሰዎቹ እምቅ ብቃት ነው፡፡ ብዙ ሰዎች በውስጣቸው ፈጣሪ ያስቀመጠው አስገራሚና የታመቀ ብቃት እያላቸው ምንም እንደሌላቸው በከንቱ ጊዜያቸውን ያባክናሉ፡፡

በውስጣችሁ ተዝቆ የማያልቅ እምቅ ብቃት እንዳለ ታውቃላችሁ? ፈልጋችሁ አግኙት! አውጡት! አዳብሩት! ተጠቀሙበት!


ዶ/ር እዮብ ማሞ
የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
3.9K viewsedited  01:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 21:26:56 መመሰጥ-ግስታልት ቴራፒ

የብዙዎቻችን ሕይወት በተግባራት የተጨናነቀ እና ፋታ አልባ ነው፡፡ ጸጥ ማሰኘት የማንችለው ብዙ ጫጫታ አለ፤ መተንፈስ እስከሚያዳግተን ድረስ እንጨነቃለን፡፡ እንቅልፍ ርቆናል፡፡ ሕይወታችን አሁንም ድፍርስ ነው፤ መስከን አንችልም፡፡ ለብቻችን የምንሆንበት ጸጥ ያለ ቦታ ያስፈልገናል።ይህ ነው የግስታልት ቴራፒ ተብሎ የሚጠራው።

ግስታልት ቴራፒ መነሻውን ያደረገው “አሁንን ብቻ ኑር” ከሚል የህላዊነት እሳቤ ነው፡፡ ዓለምን ያለምንም ጣልቃ ገብ ሃሳብ ቅመሳት። ያለፈ ታሪክ፣ የነገ ስጋትህን ሁሉ ለአፍታ ዘንጋቸው፡፡ ሸክምህን ሁሉ አራግፍ᎓᎓ አሁንን ብቻ በጸጥታ ውስጥ ሆነህ ኑረው፡፡ አሁን ላይ ብቻ አተኩር። ይህ ሳይኮሎጂስቶች የሚጠቀሙበት ቴራፒ (ህክምና) ነው ለጥቂት ደቂቃዎች ራስህን ከዓለም ለይተህ ጸጥ ባለ ስፍራ ሁን ምንም አታስብ ... ምንም አትስራ፡፡

ከዚህ ቀደም የነበረህ ማንነትህ አሁንህን ይጫነዋልና እርሳው᎓᎓ ሆነ ጭምትነትህ ያለፉ ድህነትህ፣ ኃብትህ... ተጫዋችነትህም ማንነቶች ናቸው፡፡ ወደ ኋላ መመለስ የለብህም። እኔ እንዲህ ነኝ ብለህ የምታስበውን ሁሉ እርሳ።

ይህ የባዶነት ስፍራ Fertile void ይሰኛል። ልክ ዘርን እንደሚሰጥ እርሻ ያልታረሰ ባዶ ስፍራ፡፡ በዚህ ስፍራ ያለኸው እንዲደብርህ ወይም ከራስህ ጋር እንድታወራ አይደለም። ልክ እንደማብሪያ ማጥፊያ መብራት እንደሚያጠፋ፣ ልክ በር ከውጪኛው ዓለም እንደሚለይህ ወይም ሰው ሲረብሽህ “እሽሽ” እንደምትልበት አይነት ... ይህም የጨለማ እና የባዶነት ስፍራ ነው። ሁሉንም ነገር ታጠፋለህ፣ ትዘጋለህ።

ሃሳቦችህ ባንተ ታዘው ሳይሆን በራሳቸው ይፈሳሉ፡፡ ላንተ ማሰብ አልተፈቀደምና የሃሳብ ወንዙን ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ መሟገት አልያም ከወንዙ ጋር ትግል መግጠም አትችልም።

ይህ የባዶነት ስፍራ አዳዲስ እና ያላስተዋልካቸው ሃሳቦች ከህቡዕ ህሊናህ ወደ ውጭ የሚፈሱበት ስፍራ ነው፡፡ ይህ ስፍራ ልክ እንደ ለም መሬት ፍሬን ያፈራል፡፡
በባዶነት ስፍራ ውስጥ መሆን በእጅጉ ይከብዳል፡፡ ልክ አለቃ ስራ ሲያዝህ አልሰራም የማለትን ያህል ይከብዳል፡፡ ከዚህ ቀደም አልለመድከውምና አዙሪትህን መስበር ቀላል አይሆንልህም:: ሆኖም ራስህን በባዶነት ስፍራ መሆንን አላምደው፡፡ ምንም አለማሰብ፣ ምንም
አለማድረግ፣ ከማንም ጋር አለመሆን... ባዶነት

ፍሉይ አለም

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.6K views18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 09:28:04 ሶሪያዊዉ ጋዜጠኛ በአገሩ ፍርስራሽ ለይ ቆሞ አገራቸውን ከማፍረሳቸው በፊት  የነበረውን ሁኔታ መለስ ብሎ በምሬት እያስታወሰ  እንዲህ በእንባው ጻፈ :-"

" ተከፋፍለን ነበር። እንጨቃጨቅ ፤ እንከራከር ፤ እንጣላ  ነበር።  መንፈሳዊ እሴቶች ወድቀው ነበር። ማናችንም ለማናችንም ግድ አልነበረነም።

"ሌሎች ደግሞ  ራሳቸውን ገለልተኛ አድርገው በሩቅ ቆመው ያዩን   ነበር።  ሌሎችም በእለት ሕይወታቸው ለይ ተጠምደው ነበር። ማንም እያስተዋለ አልነበረም።

" ይኸ ሂደት እያደረ ጠነከረና ቀዳዳ ሲያገኝ ድንገት ፈነዳና አገራችንን በሁላችንም ለይ አፈረሳት። አገራችን አይናችን እያየ ሳናስበው ድንገት  ፊታችን  ለይ  ነደደች።

"ያኔ ታዲያ ማናችንም በሰአቱ አገራችንን በማፍረስ ሂደት ለይ  እንደነበርን አላስተዋልንም ነበር። አገራችን መፍረሷን ያወቅነው አገራችን በሁላችንም ለይ ፈርሳ ሲጨልምብን ነበር.........።

"በወቅቱ አለን አለን ሲሉ የነበሩ የየቡድኑን መሪዎችን ጨምሮ ሕጻናትና እናቶችን ሳይምር በወቅቱ  ገለልተኞች የነበሩትን ሳይለይ አገራችን ሁላችንንም በፍረስራሿ ለይ ቀበረችን። ። " እያለ ይቀጥላል።

ዛሬ ሶሪያውያኑ አገራቸውን ዳግም ማግኘት ይፈልጋሉ። አላገኟትም ። የለችምና !!

ልብ ያለው ልብ ይበል

via-Wondwosen seifu

የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
5.2K views06:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-29 07:18:51 ጀልባዎቻችሁን አቃጥሉ!

እ.ኤ.አ. በ 1519 #Hernan Cortes  የሚባል አንድ አሳሽ  (explorer) ስድስት መቶ ከሚጠጉ ሰዎቹ ጋር አስራ አንድ መርከቦችን በመምራት በዚያን ጊዜ የታወቀና እጅግ የበለፀጉ ሀብቶች በብዛት የሚገኙበት መሬት ለመቆጣጠር ወደ ሜክሲኮ አቀና።  

ምኞቱ ከሠራዊቱ ቁጥር እጅግ የላቀ ነበር።  85,000 ስኩዌር ማይል የሚሸፍነውን ከ5 ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች ያለውን የአዝቴክ ኢምፓየር ግዛት በሙሉ ለመቆጣጠር ነበር። 

ነገር ግን አንድ ችግር ነበር -  ሌሎች በተመሳሳይ ሁኔታ ብዙ ቢሞክሩም ማንም ሊያሸንፈው ያልቻለ አንድ ጠንካራ ሰራዊት ይህን ሀብት ይጠብቅ ነበር።

ነገር ግን ይህ ሰራዊት በሜክሲኮ ድንበር ላይ ሲያርፍ ኮርቴስ ለሰዎቹ አንድ ነገር አዘዘ - “ጀልባዎቻችሁን አቃጥሉ!”  የሚል ቆፍጠን ያለ ትእዛዝ። 

ሰራዊቱም ትእዛዙን ተቀበለ።  

የእሱ ሰዎች ሁለት ምርጫዎች ብቻ ነበራቸው:-  ‘ጦርነቱን ማሸነፍ’ - ወይም ‘መሞት’!

ለማፈግፈግ ወይም ለማምለጥ ምንም እድል ስላልነበራቸው በሕይወታቸው ውስጥ በጣም ትልቅ ድፍረት የሚጠይቀውን ውጊያ ተዋጉ - እናም አሸነፉ።   

ድል አድራጊዎቹ ኮርቴስና የእሱ ሰዎች ነበሩ። በህይወት ዘመናቸው ተጠቅመው ሊጨርሱት የማይችሉትን ሀብትም ማግኘት ቻሉ። 


ይህ ታሪክ መመለስ የማትችልበትን ነጥብ፣ ወደ ኋላ የማትሻገርበትን መስመር እንዳቋረጥክ የምታውቅበት የስነ-ልቦና ቁርጠኝነትን ይወክላል። በዚህ መስመር ምንም አጥር የለም፣ ትከሻህን ማየት የሚባል ነገር የለም።  አሁን ሁሉም ነገር በዚህ አዲስ እውነታ ውስጥ ስኬታማ መሆን ላይ ብቻ ማተኮር ነው። 

በህይወት ውስጥ ወደኋላ ማፈግፈግ አማራጭ ባይሆን ኖሮ በየቀኑ ምን ያህል ማደግና ወደህልምህ መቅረብ ትችል ነበር? 

‘ጀልባዎችህ እየተቃጠሉ መሆናቸውን’ ብታውቅ፤ ምን ያህል ከፍታ ላይ ትደርሳለህ፣ ምን ያህል ትደፍራለህ፣ ምን ያህል በታታሪነት ትሰራ ነበር፣ ምን ያህል ህልምህን እውን ለማድረግ ቁርጠኛ ትሆን ነበር?

ብዙ ጊዜ፣ አዲስ እና አስፈሪ ነገርን ለመሞከር ስናስብ በ"ህይወት አድኖቻችን" ላይ የሙጥኝ እንላለን። ለምሳሌ:- የራሳችንን የግል ንግድ ለመገንባት እየፈለግን ነገር ግን በቅጥረኝነት ህይወት ላይ ልንቆይ እንችላለን ወይም የዕለት ተዕለት ተግባራችንን ሁልጊዜ በህይወታችን ለማድረግ የምንፈልጋቸውን ታላላቅ ነገሮች ላለመሞከር እንደ ሰበብ ልንጠቀም እንችላለን።  

ከፊታችን ያለው መንገድ ግልጽ ባይሆንም እንኳ በሕይወታችን ውስጥ ወሳኝ የሆነውን ውሳኔ መወሰን የሚያስፈልገን ጊዜ አለ።  የምትችለውን  ያህል መረጃዎችን  ሰብስቡ፣ ስጋቶችህን  ለያቸው/ለካቸው። ከዚያም ራስህን ወደፊት ለማራመድ የራስህን ምርጥ ውሳኔ ወስን።   ለአንድ ነገር ቃል ከገባህ በኋላ ከእሱ ጋር ለመጣበቅ ፍቃደኛ ሁን። 

ፍርሃትህ ማሳካት የምትፈልገውን ትልቁን የህይወትህን ህልም እንዲያሳጣህ አትፍቀድ። ‘እንዲህ ቢፈጠረስ? እንዲህ ቢሆንስ፣ እንዲህ ባይሆንስ.....?’’ ... እያልክ ራስህን ሽባ አታድርግ።  በትልቁ የሕይወት ግብህና ስኬታማ ለመሆን በሚያስፈልጉህ እርምጃዎች ላይ ብቻ አተኩር። 

እርግጥ ነው! የደህንነት መረቦች እና የማምለጫ መንገዶች ከህመም እና ጉዳት ይጠብቁናል። ነገር ግን ወደ ትልቁ የህይወት ግባችን ለመድረስ የምናደርገውን ጥረት፣ ትኩረት እና ቁርጠኝነት ይቀንሱታል ወይም ያጠፉታል። 

ለማድረግ ያሰብከው ወይም ‘አንድ ቀን አደርገዋለሁ’ እያልክ ማሳካት የምትፈልገው፤ ነገር ግን ረጅም ጊዜ በውስጥህ ተዳፍኖ የተቀመጠ ህልም  አለ?  ውስጣዊ ድምጽህን እመነው!  ህልምህን ተከታተል! 
ጀልባዎችህን አቃጥል! 
ወደኋላ አትመልከት!
ወደፊት ብቻ!!!

የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
6.2K viewsedited  04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 21:47:43 ለጊዜ ተዋቸው!

(Samuel Geda)

በአንድ ትንሽ መንደር ውስጥ የሚኖር አንድ ሰው ነበር። ታዲያ ይህ ሰው፣ በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በኑሮው ከሚገጥመው ችግር የተነሳ፣ ሁልጊዜም በህይወቱ ደስተኛ አልነበረም። አንድ ቀን ግን ከሚኖርበት ሥፍራ በቅርብ ርቀት የምትገኝ ከተማ ዘንድ፣ አንድ ታላቅ የኃይማኖት አባት ከአጃቢዎቻቸው ጋር እንደመጡ ይሰማል። ይህን ጊዜም እኚህን አባት ማግኘት አለብኝ ብሎ ይወስናል።

በመሸም ጊዜ እኚህ አባት ያሉበት ሥፍራ ይደርስና፡ እሳቸውን ለማግኘት ቁጭ ብሎ መጠባበቁን ይይዛል። ከረጅም ቆይታ በኋላም እኒያን አባት ያገኝና ጥያቄውን ይጀምራል። "አባቴ ሆይ፥ በህይወቴ ፍፁም ደስተኛ አይደለሁም፤ በቃ ሁሌም በችግር የተከበብኩኝ ሰው ነኝ... በዚህ በኩል የሥራ ጭንቀት፣ በዚህ ደግሞ የጤና ቀውስ፣ በዛላይ የቤቴ ውስጥ ችግር... ብቻ ተደማምሮ እረፍት ነስቶኛል፣ ደስታም ርቆኛል፤ እባክዎትን አንዳች የመፍትሄ ሀሳብ ይስጡኝና፡ ደስተኛና የሰላም ኑሮ እንድኖር ይርዱኝ!"

ሽማግሌውም ፈገግ ብለው፤ "ልጄ፥ ለችግርህ ነገ ጠዋት ላይ መፍትሄ እሰጥሃለሁ፤ ነገር ግን አሁን ባዝህ፣ ጥቂት የኔን ሥራ ልትሠራልኝ ትችላለህን?፤ ሰውዬውም በዚህ ይስማማል። እሳቸውም ቀጥለው፦ "በጉዞአችን የያዝናቸው መቶ ግመሎች በዚህ ይገኛሉ፤ እናም ዛሬ ምሽት የነርሱን ነገር፡ አደራውን ላንተ ሰጥቻለሁ፤ ሁሉንም ግመሎች እመሬት ላይ ካስቀመጥክ በኋላ ወደ መኝታ መሄድ ትችላለህ"። ይህንንም ብለው ወደ ድንኳናቸው ሲያቀኑ፣ ሰውዬውም የታዘዘውን ሊያደርግ ምሽቱን ግመሎቹ ዘንድ አመራ።

በቀጣይ ቀንም ሽማግሌው ማልደው ወደ ሰውዬው በማቅናት "ልጄ፥ ሌሊቱን ጥሩ ተኝተህ አደርክ?" ብለው ይጠይቁታል። ሰውዬው ግን ኅዘን በተሞላበት ስሜት ሆኖ "አባቴ፥ ለዐፍታ እንኳን እንቅልፍ ሳይወስደኝ ነው ሌሊቱ የነጋው። ብዙ ለፋሁ፣ ብዙም ጣርኩኝ፡ ይሁንና በአንድ ጊዜ ሁሉንም ግመሎች እንዲቀመጡ ማድረግ አልቻልኩም። አንዳንዶቹ ራሳቸው ይቀመጣሉ፤ አንዳንዶቹ ግን ላስቀምጣቸው ብሞክርም እንኳን አይቀመጡም፤ አንዱ በዚህ በኩል ሲቀመጥ፡ በሌላ በኩል ያሉት ይነሣሉ"።

ይህን ጊዜ ሽማግሌው ፈገግ እያሉ እንዲህ አሉ፦ "ካልተሳሳትኩኝ፡ ይህ የሆነው ትላንት ማታ ነው አይደል?"

- ራሳቸውን በራሳቸው ያስቀመጡ ብዙ ግመሎች ነበሩ!?

- ብዙዎቹ ደግሞ በአንተ ጥረት ሊቀመጡ ችለዋል!?

- ቀሪዎቹ ልታስቀምጣቸው ሞክረህ እንኳን አልተቀመጡም፤ ከቆይታ በኋላ ግን በጊዜ ውስጥ ራሳቸውን አስቀምጠው አግኝተሃቸዋል!?

ሰውዬውም፦ "አዎ! አዎ!...ትክክል!" ብሎ መለሰ።

ሽማግሌውም ቀጠሉና፦ "ስለዚህ አሁን አንድ ነገር ተረዳህን?፤ በህይወት ያሉም ችግሮች እንዲሁ ናቸው...

- አንዳንዶቹ በራሳቸው መፍትሄ ያገኛሉ።

- አንዳንዶቹ በአንተ ጥረት መፍትሄ ያገኛሉ።

- አንዳንዶቹ ደግሞ በአንተ ጥረት እንኳን አይፈቱም፤ እነዚህን ችግሮች ለጊዜ ተዋቸው። ትክክለኛው ጊዜ ሲደርስ በራሳቸው ይፈታሉና/መፍትሄ ያገኛሉና/።

ትላንት ማታ፣ ምን ያህል ብትሞክር በአንድ ጊዜ ሁሉንም ግመሎች ማስቀመጥ እንዳልቻልክ ትምህርት ወስደሃል። አንዱን ግመል በዚህ ጋር ስታስቀምጥ በሌላ በኩል ያሉት ይነሣሉ። ልክ እንዲሁ፤ እዚህ ጋር አንዱን ችግር ፈታሁ/ተፈታ ስትል እዛ ደግሞ ሌላ ችግር ተነስቶ ይጠብቅሃል። ህይወት እንዲህ ነውና!። ችግሮች የህይወት አካል ናቸው፤ አንዳንድ ጊዜ ጥቂት፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ በርካታ ችግሮች ይኖራሉ። ይሄ ማለት ግን ስለነሱ ሁሌ ማሰብ አለብህ ማለት አይደለም። እነሱን ለጊዜ እየተወክ ወደፊት ተጓዝ። በእያንዳንዱ እርምጃም ወደ ዓላማ-ህይወት (Purpose of life/self- realization/) ማደግን ተማር።

ልብ በል፤

• አንዳንድ ጊዜ፤ ደስታን ለማወቅ በኅዘን፣ ዝምታን ለማድነቅ በጩኸት፣ የመኖርን ዋጋ ለማወቅ ባለመኖር መንገድ ልታልፍ ግድ ነው።

ይኸውልህ፤ ህይወት በተቃርኖ የተሞላች ነች። እያንዳንዱ ስኬት ከሸክም ጋር ነው የሚመጣው። ትልቅ ቤት ማግኘት ስኬት ሲሆን፣ ብዙ የሚጸዳ መኖሩ ሸክም ነው። ልጅ መውለድ ስኬት ሲሆን፣ በእኩለ ሌሊት መነሳቱ ሸክም ነው። ባለስልጣን መሆን ስኬት ሲሆን፣ የህዝብን ጩኸት ማስተናገዱ ሸክም ነው።

ብዙ ጊዜ የምንሠራው ስህተት- ስኬቱን ያለ ሸክም ከመፈለግ የሚመጣ ነው። ይህ ግን እውነታው አይደለም። የሚመጡት በጥቅል (package) ነው። ዋናው ነገር፣ ሸክሙም እያለ በስኬቱ/በበረከቱ መደሰትን መማሩ ላይ ነው!!

ሰናይ ምሽት

የስብዕና ልህቀት
@Human_Intelligence
9.9K views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 20:07:50 ማንነት-ፍሮይድ

በተለያዩ ቀናት፣ በተለያዩ ሳምንታት ወይም በተለያዩ አመታት ውስጥ የተለያዩ ማንነቶች እንዳሉህ ተሰምቶህ አያውቅም? በአንደኛው ቀን ጨዋታ ወዳድ ተጫዋች ትሆንና በሌላኛው ቀን ቁጥጥርን የሚያበዛ ቁጡ ሰው ትሆናለህ፡፡ ሲግመንድ ፍሮይድ ስለ ባህሪ መለዋወጥ የሚለን ነገር አለ፡፡
ከእርሱ በፊት ስለ ሰው ልጆች ስነ-ልቦና ያጠና የለም ባንልም ፍሮይድ ግን በእጅጉ በተለየ ሁኔታ ተመራምሯል እና ዛሬም ድረስ የምንከተላቸውን የሳይኮሎጂ አስተምህሮዎችን ፈልስፏል።
ፍሮይድ የእኛ ማንነት በሶስት ይከፈላል ይለናል፡፡

#ኢጎ; ይህ አሳቢውና ምክንያታዊው ማንነታችን ነው፡፡ ይህን መጽሐፍ የሚያነበውና በአእምሮህ ውስጥ የሚተርክልህም ይህ የማንነት ክፍልህ ነው፡፡ ከሶስቱ ማንነቶችህም በመሃል ላይ ይገኛል።


#ኢድ; ይሄኛው የእንስሳነት ባህሪህን ያጎላዋል፡፡ ወሲባዊ ፍላጎቶችህ፣ በስሜትህ የምትመራባቸው ውሳኔዎችህ እና ሌሎችም ግልፍተኛ ድርጊቶችህ በዚህ የማንነት ክፍልህ ይመራሉ። ልክም እንደ ሰይጣን ሆኖ ውሳኔዎችን እንድትወስን ያጣድፍሃል። የሰደበህን ሰው እንድትደበድብ ወይም ድንጋይ እንድትወረውርበት ያበረታታሃል። ልክ ህጻን ልጅ ሲርበው እንደሚያለቅሰው ይህ ማንነትህ ድርጊቶችህ ስለሚያስከትሉት ውጤት
ሳይጨነቅ ምሱን እንድታመጣለት
ያለቅሳል።

#ሱፐር_ኢጎ; ይህ በአእምሮህ የተቀመጠ ዳኛ ነው፡፡ እንዲህ አታድርግ ነውር ነው፤ ይህን ማድረግህ አንተን እንድትዋረድ ያደርግሃል እያለ ሃሳቦችህ እና ድርጊቶችህ ላይ ሂስ ይሰጣል፡፡ ስለ ማህበረሰቡ ህግ እና ከድርጊትህ በኋላ ስለሚከሰት መጥፎ ነገር አበክሮ ይጨነቃል። ይህ ልክ ነው፤ ይህ ልክ አይደለም እያለ ይመክርሃል።

ለምሳሌ ለፈተና ልታጠና ተቀመጥክ፡፡ ኢድ መጨናነቅ አይወድም፤ እናም በቀስታ ፈታ በል አትጨናነቅ ይልሃል። ወይ ስልክህን አንድታነሳና ፌስቡክ እንድትጠቀም አልያም ከጓደኞችህ ጋር ሄደህ እንድትዝናና ይመክርሃል።

ሱፐር ኢጎ፤ ከኢድ በተቃራኒ፣ ነገሮችን አጋኖ እና መጥፎ አድርጎ ያቀርብልሃል። ዛሬ ካላጠናህ ፈተና ትወድቃለህ፤ ፈተናንም ከወደቅክ ይህን አመት ትደግማለህ... እያለ ያስፈራራሃል።

በመሃል ወይም ምክንያታዊ ማንነትህ ለማስታረቅ ይመጣል፡፡ ራሴን እስክጥል ድረስ መጨናነቅ የለብኝም፤ ሆኖም ግን ለአንድ ሰዓት ያህል አጥንቼ ወደ ጫወታ እሄዳለሁ ይላል፡፡

ፍሮይድ የማንነት ቀውስ የሚመጣው ሶስቱን አጣጥመን ሳንሄድ ስንቀር ነው ይለናል። ሰካራም፣ ሴሰኛ ሰው አይተህ ታውቃለህ ይሄ ሰው የኢድ (የእንስሳነት) ማንነቱ በርትቶበታል፡፡ በተቃራኒው ስለ ሁሉም ነገር የሚጨነቅ እና ፍጹም ለመሆን የሚጥር ሰው ያውቃል? ቋጣሪ፣ ጥንቁቅ አልያም አብዝቶ የሚጨነቅ ይሆናል ... ይህ ሰው የሱፐር ኢጎ (የዳኛው) ማንነት በርትቶበታል፡፡

ሁሌም ቢሆን በሁለቱ ማንነቶቻችን ውስጥ እንዳንዋጥ ራሳችንን ልንቆጣጠረው ይገባል፡፡ ነገር ሁሉ በጊዜው እና በአግባቡ ሲሆን ያማረ ይሆናል። ጠቢቡ ሰለሞን እንዳለው፡-
“ለማልቀስ ጊዜ አለው፥
ለመሳቅም ጊዜ አለው፤
ዋይ ለማለት ጊዜ አለው፥
ለመዝፈንም ጊዜ አለው።“

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
8.4K viewsedited  17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ