Get Mystery Box with random crypto!

የስብዕና ልህቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የሰርጥ አድራሻ: @human_intelligence
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 89.04K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-28 18:30:25 የታዋቂው ቢሊየነር ዋረን ቡፌት ምክሮች

ጓደኝነትህን ከፍ ያለ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ጋር አድርግ፡፡ ካንተ የተሻሉ ሰዎችጋ የምትውል ከሆነ እንደ እነሱ መሆን ትጀምራለህ፡፡ ተራ የሆነ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ጋር ስትሆን ተቃራኒውን ትሆናለህ፡፡

እድገትህ ያለው ከፊትህ እንጂ ከኋላህ (ካለፈው) አይደለም፣ የፊትህ ላይ አተኩር፡፡

ከምንም በላይ ራስህን አሳድግ፡፡ በፅሁፍም ሆነ በንግግር ሃሳብህን በሚገባ ለመግለፅ ተማር፣ ስልጠና ውሰድ፡፡ ይሄ ብቻ ተፈላጊነትህን በ50% ይጨምራል፡፡

በተቻለ መጠን ውስጥህ መሆን የሚፈልገውን ሁን፤ የሚያስደስትህን ስራ፡፡ 
ትሁት ሁን፡፡ ትሁት ሰው እኔ ብቻ ነኝ አዋቂ አይልም፡፡ ከሌሎች ይማራል፤ ያለማቀረጥ ያነባል፣ ሎሎችን ይሰማል፣ ይማራል፡፡

አካልህን እና አእምሮህን በሚገባ ተንከባከብ፡፡ በምድር ላይ ስትኖር የሚኖርህ አንድ አካል እና አንድ አእምሮ ስለሆነ በትጋት ጠብቀው ተንከባከበው፡፡
3.1K viewsedited  15:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 13:56:27 ሀገር ያጣ ሞት
ደራሲ -ሄኖክ በቀለ

"አንዳንድ ታሪኮች ርእስ የላቸውም ተነግረው እንዳልተነገሩ ይረሳሉ። አንዳንድ ሰዎች አስታዋሽ የላቸውም —ኖረው እንዳልኖሩ ይቆጠራሉ። አንዳንድ ገድሎች አልተዘከሩም የባከኑ መሥዋዕትነቶች ይባላሉ። አንዳንድ ቅሌቶች ሰው ፊት አልታዩም እንዳልተፈጸሙ ሁሉ በጨለማ ውስጥ ይቀራሉ። አንዳንድ አወዳደቆች ከትዝብት ልብሳችንን አራግፈን እንቀጥላለን። አንዳንድ ሕዝቦች በወል ተረስተዋል ተጋርደዋል —ዙሪያውን ለመታሰቢያነት የቀረላቸው ምንም የለም። አንዳንድ ኮቴዎች በመረሳት ተጠቅተዋል —አንዳንድ ወኔዎች ለሞት ዳርገዋል። "

"ታሪክ የአሸናፊዎች መዋዕል ነው። ነገሥታት ከአፍ ከአፍ እየተቀለቡ ዘመን ሲሻገሩ ሕዝብ ግን ተረስቶ ባለበት ይቀራል። የሱሲንዮስ ጋሻ ጃግሬ ማን ይባላል? የሰሎሞን እቁባት ለሕይወቷ ምን አደረገች? ስሟ እንኳ አልተጻፈም። ሰሎሞን ሰባት መቶ እቁባት ቢኖረው የሰሎሞን ታሪክ ብቻ ነው —እነርሱ የታሪኩ ሟሟያ ብቻ ናቸው  ...እንደጊዜና ቦታ ያሉ የመተረኪያ አጥቆች። ዛሬ የቆምንበት ምድር ላይ ትላንት ማን ነበረ? ለነገሥታት “ዘራፍ!” ካለው ስንቱ ተረፈ?  ታሪክ መርጦ ያስታውሳል። አሸናፊ መሆን ያልቻሉት ለአጉል አሟሟት ይሯሯጣሉ። ምንም ያልሠሩት በጀግና ሰይፍ ላይ በመውደቅ ብቻ የሚታወሱ ሰማዕት ይሆናሉ። ሲኖሩ ሳይሆን ሲሞቱ ያወቅናቸው ለቁጥር ይታክታሉ። ለሞቱ ግድ የሌለው ሕዝብ “ከሞቴ አሟሟቴን” ይተርታል። “ወይ ግደልላት ወይ ሙትላት፣ የፈሪ ወዳጅ አታሰኛት!”ን ያንቋርራል —የምትወደው ሰው ከሞተባት በኋላ “የጀግና ወዳጅ” መባል ምን ይፈይድላታል?ይህ ሲደመር የምንኖርለት ዓላማ “ወይ መግደል፣ ወይ መሞት” ይሆናል። እናም ያስጨንቃል!!

መሪዎች በክፉም፣ በደጉም ከሰው አፍ ይውላሉ። “ከሕይወቴ የገዘፈ ዓላማ አለ” ብሎ የሚያስብ ነዋሪ በደምፍላትና በእልህ ተነሥቶ  ሁሉ የማይታወስ አጽም ለመሆን ይፈጥናል።"

ሀገር ያጣ ሞት
ገፅ 132

ይህን የመፅሀፍ ገፅ እያነበብኩ የሀገራችን ወቅታዊ ፓለቲካ ታወሰኝ ደራሲው የሚተርከው በሁለት መሳፍንቶች መካከል በተደረገ ጦርነት ህይወቱን ስላለፈ  የአንድ ወጣት ታሪክ ነው።

የዚህ ድርሰት አስገራሚው ታሪክ በሁለቱ መሳፍንት(ራስ አሊና ደጃፍ ውቤ) ጥጋብ ምክንያት በተደረገው ጦርነት ብዙ ህዝብ ካለቀ በኋላ በዛው እለት ሁለቱ መሳፍንቶች 
ፊት ለፊት ሲገናኙ ያደረጉት ንግግር ነው።

ገፅ 139

"ራስ ዐሊም፣ ደጃች ውቤም ቁጭ ብለው ማዘዝና የመኳንንትን ሕይወት መግፋት እንጂ መግቢያ፣ መውጫውን አብጠርጥረው የሚያውቁ ጎበዞች አልነበሩም። የፍርሃታቸውን ባመጣላቸው በኩል ሲፈረጥጡ አንድ ጠባብ መንገድ ፊት ለፊት ተጋጠሙ። መንገዷ ከአንድ ሰው ውጪ የማታሳልፍ ሆና ወይ መመለስ ወይ ገድሎ ማለፍ ግድ ሆነ። ሁለቱም ሲያምታቱና ሲያስመስሉ ኖሩ እንጂ የውጊያ ዕውቀትም ጀግንነትም የሌላቸው ስለነበሩ ጦርና ጋሻቸውን እንደሰበቁ ተፋጠው ቀሩ።

ቆይቶም ደጃች ውቤ
“ዐሊ እንደው ጥጋባችን እንጂ እኔና አንተ ደም መቃባት ነበረብን?” አሉ።

“ውቤ አንተ እምቢ! አልክ እንጂ እኔ መች ፈለግሁት? ባንዋለድም ዘመድ ነን። ወንድሜ ነህ!”

“ግዛት እንደሁ እኔም የእኔን፣ አንተም የአንተን እንደያዝን ጦራችንን አጠንክረን ካሣን መውጋት ሲገባን...”

“ሰይጣን ሰውሮብን እንጂ ሐሳብህ ሐሳቤ ነው!”

“በል አሁን በጀ በል! ሄደን ጦርነቱን እንፍታ።”

“እንዲያ” .....ሁለት ታሪኮች ተቃቅፈው ተሳሳሙ። እንደ ወዳጅ ተያይዘው ወደ ጦርነቱ ቦታ ጋለቡ።

ሽምጥ ጋልበው ሲደርሱ፤ ጦርነቱ አልቆ፤ ቦታው በሰው ሬሳ ተሞልቶ፤ አንዳንዱም ወድቆ ሲያጣጥር ደረሱ። ለሞቱ ወታደሮቻቸው በማዘንና በማልቀስ ፈንታም በሬሳው ላይ ወዲህና ወዲያ እየተመላለሱ ይስቁና ይቀላለዱ ገቡ።

“ይሄስ አንዴም የተኮሰ አይመስልም። ታቅፎት ተኝቷል።”

“ዐሊ ና እስቲ ወደዚህ ...ይህቺማ ሁለት እጇም፣ ሁለት እግሯም የለ! ባለጓጉንቸር ሳጥን መስላልሃለች።”

ሳጥን የመሰለው፤  ያ ጎበዝ ወጣት ደጃች ውቤን ከልቡ ይወደው የነበረ... የደጃች ውቤ መሰደብ ያንገበገበው የነበረ  ...ደሙ ተንዠቅዥቆ ያልሞተ ...የደጃች ውቤን ንግግር ሰምቶ ጸጥ ጭጭ አለ።

ምናልባትም ከመጨረሻው ህቅታ ጋር ነገሥታት ለሥልጣናቸው እንጂ ለሕዝቡ ግድ እንደሌላቸው እያሰበ፤ ከረፈደም ቢሆን እያብከነከነው ሄደ። “የት?” እንዳትሉ! ሰው ከሞተ ወዲህ መኖሪያውን ማን ያውቃል? ምናልባትም አብረውት የተከመሩት ብዙ ሺህ ሬሳዎች ካልሆኑ በቀር።

የእናቶች ለቅሶና ዋይታ ምድሩን አደበላለቀው። አንዳንድ ታሪኮች ርእስ የላቸውም የሞትህ ትንፋሽ በአንገትህ ሥር በሞቀህ ሰዓት የተገለጠልህን ስሕተት መቼ ታርመዋለህ? አንዳንድ ሰዎች ስም የላቸውም —ይህ ወጣት የጦርነት ታሪኩ አጥቅ ነው፤ የመተረኪያ አማሃይ፤ በምድር ፊት ስለፈሰሰው ደሙ ማን ግድ አለው? ....አንዳንድ ገድሎች አልተዘከሩም። አንዳንድ ቅሌቶች ሰው ፊት አልታዩም። ታሪክ የአሸናፊዎች መዋዕል ነው። በአሸናፊ ስም የሚወድቀውን ነፍስ ከእንስፍስፍ የእናት አንጀት በቀር ማንም አያስታውሰውም። ማንም!!"

.............

በኢትዮጵያ መንግስት እና በወያኔ መካከል የተደረገው ጦርነት ከብዙ ደም አፋሳሽ ግጭት በኋላ ጦርነቱ በሰላም ስምምነቱ መጠናቀቁ ይታወሳል። በሁለቱም ወገን ያሉ መሪዎች በየቦታው ተቃቅፈው ፎቶ መነሳት ላይ ይገኛሉ። በዚህ ጦርነት ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ የነዚህ ሰዎች ታሪክ ግን ተረስቷል ፤ ሞታቸው ቁጥር ሆኖ አልፏል። ህይወታቸው ትርጉም ላለው ነገር እንዳለፈ ለመናገር እንኳን ያድግታል። የባከኑ መስዋዕቶች ሆኗል።ታሪክ የሚፅፈው የአሸናፊዎችን ገድል ብቻ ይሆናል።

“የጠገበ ሲያገሳው
ተግ ሲል ቀልቡን የነሳው
በመጨረሻ ጦርነት ያበቃል
ወታደሩ ያልቃል ንጉሥ ይታረቃል”

.......

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በአንዱ ፁሁፉ ላይ እንዲህ ይላል

"ለጊዜያዊ ይሁን ለዘለቄታ የፖለቲካ ጥቅም ሲባል በፖለቲካ ውስጥ ብዙ አይነት ኢ-ሞራል የሆኑ ነገሮች እንደሚሰሩ ቢታውቅም፣ ባሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየታየ ያለው በየትኛውም መመዘኛ ዝቅጠቱን ማሳነስ የማንችለውን የመሰለ የፖለቲካ አመለካካትና ድርጊት ይታያል።

ጦርነት በሰላም እንዲቆም ለማድረግ ስምምነት ላይ መድረስ አንድ ነገር ሆኖ ሳለ   ይህ ሰላም ከኋላው የተሸከመውን  ከባድ የህዝብ ሰቆቃ የማይመጥን የፊት ገጽታ የሰውነት ቋንቋ እያሳዩ፣ ከወያኔ ሰዎች ጋር የነበረው ግጭት በአንድ ምሽት በስካር መንፈስ ዳንስ ቤት ውስጥ የተፈጠረ ችግር በሚመስል መልኩ፣ በሳቅና በፈገግታ የተሞላ ግንኙነት ምን ያህል በጦርነቱ የተጎዳውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ህዝብ ሊያስከፋ እንደሚችል ዞሮ ማሰብ አለመቻል የሰላም ስምምነቱ  ስሜት አልባ፣ ሃላፊነት በማይሰማቸው ግለሰቦች የተደረገ እንደነበር ማሳያ ነው።"

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
4.7K viewsedited  10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 11:02:01 አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?

እሱባለው አበራ

እንደትላንት ተወልደን ዛሬ ላይ እድሜያችን ስንት ደረሰ? ወጣትነታችን ወደ ፊት የሚያራምደን መስሎን ተሞኘን። ዕቃቃችንን ስንጥል፥ ጨዋታችንን አልጠገብንም ነበር። ድክ፥ ድክ ያልነው በወጉ ዳዴ ሳንል ነው። ልባችን ላይ የሚነደው የጉርምስና እሳት ደረታችንን ሲፋጅ ሰፊ መንገድ ያለ መስሎን ነበር።


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


ከአባታችን ወገብ የተከፈለው ዘር፥ በእናታችን ማኅጸን እንቁላል ሳይመታ፤ ፅንስ ሳንሆን፥ ሥጋችን ሳይቦካ፥  አጥንታችን ሥር ሳይሰድ፥ ጅማታችን ሳይዘረጋ፥ ሽል ሳንሆን በፊት. . . ክፉ ዕጣ ቀድሞናል። አንዳችን ለአንዳችን ጠላት ተደርገናል። ለሞትም ታጭተናል። ሳንመርጥ ወግነናል። ደርሰን ባልበደልነው፥ ባልሠራነው ታሪክ. . . አክ እንትፍ ተብለናል።


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


እኔና አንተ ምንም እንኳ ወደ ፊት መጓዝ ብንፈልግም፤ ይሄ ሀገር የሚሄደው ወደ ኋላ ነው። ዳገቱን ወጣን፥ አቀበቱን አሸነፍን፥ ተራራውን ረታን ስንል. . . እየተንሸራተተ መቀመቅ ይዞን ይወርዳል። በየቀኑ ትርጉም አልባነትን እንድናንከባልል ተፈርዶብናል።


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


አናምንም። ግን ዕውቀት የማይዘልቀው የድንቁርና እና የአረመኔነት ዘረመል ሥጋ ለብሶ ያለው እዚህ ሀገር ነው። ኅዘንተኞች ሳለን መጽናኛ የለንም። ፍርፋሪ እሴት ሳይቀር ነጠቁን። ረክሰው አረከሱን። የሤራ ፖለቲካው ጉንጉን ፈጣሪ ዓለምን ከፈጠረበት ጥበብ በላይ ሳይረቅቅ አይቀርም። እግዚዖ!


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


ከተወለድን ጀምሮ አላስተኙንም። ታዲያ  ሕይወታችን ስለምን ቅዠት በቅዠት ሆነ? ማለት  መቼ አስተኝተውን? መቼስ ተደላድለን? እስከ መች እንደምንኖር አናውቅም። ሕይወት አጭር ናት፤ እዚህ ሀገር ደግሞ እጅግ በጣም አጭር ናት። ሕልውናችን ከእኛ ቁጥጥር ውጪ ነው። ብንነቃም፥ ብናንቀላፋም ሕይወት ጭራቅ መልኳን ለአፍታ አትቀይርም። የቸገረ ነገር!


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


እንዴት እንደሆነ ባናውቅም እንደ ትውልድ አምክነውናል። ሳንወለድ ገድለውናል። የእናት ጡት ሳንጠባ አስረጅተውናል። ቆምረውብናል። ቅያሜውን ሳናውቅ፥ ጦርም ሳንገጥማቸው፥ ያለ ወግ ድል አድርገውናል። ያረፈብን የጀግናም አይደለ፥ የፈሪ ዱላ ነው!


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?

ዳሩ ምርጫ አልነበረንም።

@EsubalewAberaN
@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
2.6K viewsedited  08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 22:54:24 ዓለም ቆንጮ
ድርሰት - ወንድሙ ሀይሉ

@Human_Intelligence
3.3K viewsedited  19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 13:33:56 ስለመፅሐፍ የተነገሩ አባባሎች!


ወዳጆች ዛሬ የንባብ ባህላችን እንዲዳብር ሊያነሳሱን የሚችሉ ስለመፃሕፍት የተነገሩ የተለያዩ ሠዎችን አባባል ዛሬ ልንዘክር ብዕራችንን ከወረቀቱ አገናኝተናል፡፡
መፅሐፍ የሚሠጡት ጥቅም የታወቀ ቢሆንም በማንበብ ብቻ ግን አዋቂ መሆን አይቻልም ባይ ነኝ፡፡ ምክንያቱም መፃሕፍትን ከማንበብ ባሻገር በንባብ ያገኘናቸውን ሃሳቦች ከሃሳባችን ጋር በማስተያየትና በማሻሻል፣ በማሠላሠልና በማስተዋል አዲስ ሃሳብ ካልፈጠርንበት መፅሐፍ ማንበብ ሳይሆን መፅሐፍ መቁጠር ነው የሚሆነው፡፡ ባነበብነው ሃሳብ ተገዝተንና አዲስ የባህሪ ለውጥ ወይም አዲስ ነገር ካልፈጠርንበት ማንበባችን ዕውቀት አይሆንም፡፡ ምክንያቱም ዕውቀት ስንል በተጨባጭ በተግባር የሚገለፅ ነውና፡፡
ለማንኛውም አባባሎቹን እነሆ እላለሁ..! ሃሳብና አስተያየታችሁ የተጠበቀ ነው፡፡ መልካም ንባብ!

‹‹መፅሐፍ አንድ ቁምነገር አለው፡፡ ይሄም እግርህን ከቤትህ ሳታነሳ ዓለምን እንድትዞር ያደርግሃል›› (ጁምባ ራሂሪ)

‹‹አንባቢ ከመሞቱ በፊት አንድ ሺ ኑሮ ይኖራል፡፡›› (ጆርጅ ማርቲን)

‹‹መፅሐፍት ተንቀሳቃሽ አስማቶች ናቸው›› (ስቴፈን ኪንግ)

‹‹እንደመፅሐፍ ያለ ታማኝ ጓደኛ የለም፡፡›› (ኸርነስት ኸርሚንግወይ)

‹‹ አንድ ነገር አንርሳ! አንድ መፅሐፍ፣ አንድ እስኪብርቶ፣ አንድ ሕፃን፣ አንድ መምህር ዓለምን መለወጥ ይችላሉ፡፡›› (ማላላ ዮሶፍዜ)

‹‹ዓለም መፅሐፍ ናት፡፡ ዓለምን ተጉዘው ያላዩ መፅሐፍ ይግለጡ፡፡›› (ቅዱስ አውግስጦስ)

‹‹መፅሐፍ በየዕለቱ የሚያጋጥመንን የህይወት ጉድፍ የሚያስወግድልን የነፍሳችን ማጠቢያ ነው፡፡›› (ያልታወቀ ሠው)

‹‹ማንበብ ለአዕምሮ ሲሆን አዕምሮም አካላችን ምን ማድረግ እንዳለበት ያቀናጃል›› (ያልታወቀ ሠው)

‹‹መፅሐፍ ከባድ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ዓለሙ ሁሉ በእርሱ ታጭቋልና፡፡›› (ኮሜሊያ ፈንክ)

‹‹ዛሬ አንባቢ የሆነ ነገ መሪ ይሆናል፡፡›› (ማርጋሬት ፉለር)

‹‹ዛሬ ልታነበው የምትችለውን መፅሐፍ ለነገ አታቆየው፡፡›› (ያልታወቀ ሠው)

‹‹ካነበብኩ መላው ዓለም ለእኔ ክፍት ነው፡፡›› (ሜሪ ማክሎድ ቤቱን)

‹‹አንዳንድ መፅሐፍት ነፃ ይተዉናል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ነፃ አድርገው ይሠሩናል፡፡›› (ራልፍ ዋልዶ ኤመርሠን)

‹‹መፅሐፍ ወደፊት ልንሆን የምንፈልገውን የያዘ ህልማችን ነው፡፡›› (ኔል ጌማን)

‹‹ቤተ-መፃሕፍቶች ልክ እንደጥሩ ትዝታ መዓዛቸው ያውደኛል፡፡›› (ጃኩሊን ውድሰን)

‹‹መፅሀፍ አስተሳሰባችንን የሚያቀጣጥል መሣሪያ ነው፡፡›› (አላን ቤኔት)

‹‹እኔ በቀላሉ የመፅሐፍ ጠጪ ነኝ›› (ኤል ኤም ሞንቶጎሞሪ)

‹‹ሌላ ሠው ያነበበውን ብቻ እያነበብክ ከሆነ ሌላ ሠው የሚያስበውን ብቻ ነው እያሠብክ ያለኸው፡፡›› (ሐሩኪ ሙራካሚ)

‹‹ቤት ያለመፅሐፍት ማለት አካል ያለነፍስ ማለት ነው፡፡›› (ሲስሮ)

‹‹ተራ ሠዎች ትላልቅ ቲቪ አላቸው፡፡ ብልህ ሠዎች ግን ቤተመፃሕፍት ናቸው፡፡›› (ያልታወቀ ሠው)
5.0K views10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 14:44:45 “Books are the mirrors of the soul.”―Virginia Woolf

<<ያም ያም እየተነሳ ፀሐፊ ነኝ ይላል፡፡ የሚታተመው መጽሐፍ ቢበዛ የሚረባው ግን ጥቂት ነው፡፡>> ዛሬ ዛሬ ከሀገሬ አንባቢዎች የምሰማው ቅሬታ ነው፡፡ በዚህ አባባል ውስጥ ድብቅ 'ጽሑፍና ጸሐፊ'ን ማግነን አለች፡፡ 'ያም ያም' ፀሐፊ መሆን ካልቻለ 'ፀሐፊ' መሆን ያለበት ምን አይነት ሰው ነው? የታተመው ሁሉ ጥሩ መጽሐፍ ካልሆነ 'ጥሩ መጽሐፍ' ምን አይነት ነው?
ሀገራችን በጽሑፍ ቀደምት ነን የሚሉ ሊቆች ቢኖሯትም፤ ጸሐፊ የሚከበርባት ሀገር ግን አይደለችም፡፡ በተለይ የፈጠራ ፀሐፍት እንደ ወፈፌና ጸረ-ሀገር ነው የሚታዩባት፡፡ ሥለዚህም የፈጠራ ጽሑፍ ይዘው ወደ መጽሐፍ ገበያ ከሚወጡት ውስጥ ሥሟን ያገነኑ፣ ቅዱስነቷን የመሰከሩ እንጅ ጉድፏን የነቀሱ፣ እንከኗን ያወሱ፣ አውስተውም ይታረም ያሉ አይነበቡም፡፡

ስሻ ወደ መጽሐፍ ገበያ ዘወር ዘወር እላለሁ፡፡ ሻጭ ወዳጆቼ ጋርም ተቀምጨ የገዥውን የንባብ ትኩረት ለማየት እሞክራለሁ፡፡ በብዛት የሚጠየቁና የሚሸጡትን እያሰብኩ 'እነዚህ መጻሕፍት አንባቢው ላይ የሚጨምሩለት ምን ነገር አላቸው?' ብዬ ራሴን እጠይቃለሁ፡፡ አብዛኞቹ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተሻለ መረጃ የማይሰጡ ናቸው፡፡ ጥቂቶቹ ቢያንስ መንፈሳዊ አገልግሎት አላቸው፡፡ ለማሰብ የሚሆኑት ወይም ምናብን የሚያነቁት ግን በቀን ውስጥ ላይጠየቁ ይችላሉ፡፡ ይህን እያሰብ መልሼ ሌላ ጥያቅ እጠይቃለሁ 'ሰው የሚያነበው ለምንድን ነው?' ብዬ፡፡ ምክንያታችን ልዩ ልዩ ሊሆን ይችላል፡፡ የተሻለው መልስ ግን 'የተሻለ ሰው' ለመሆን የሚለው ይመስለኛል፡፡ ያላወቁትን ማወቅ፣ ያልደረሱበት ላይ መድረስ፡፡ 'ማንበብ ጎደሎ ያደርጋል' ማለትም ለተሻለ ንባብና እውቀት ፍለጋ ያነሳሳል ማለት ይመስለኛል፡፡ ጥያቄው 'አውቀን ለምን?' የሚለው ነው፡፡ ሰው ነንና ኹልጊዜም በመሰራት ሂደት ላይ ነንና፤ ድክመታችንን ለመለየት፣ ያነሰንን ለማወቅ፣ ያላሰብነውን ለማሰብ ከሁሉም አስቀድሞ ደግሞ 'ማሰብ'ን ለማወቅ የተደራጀ፣ የተሰደረ ነገር ያስፈልገናል፡፡ በእኔ ቤት ይህ ነገር መጽሐፍ ነው፡፡ ማሰብ የሚያስለምድ መጽሐፍ፡፡ ማሰብ የሚያስለምድ እንጅ በእሱ መንገድ የሚያሳስብ አላልኩም፡፡
“Come to the book as you would come to an unexplored land. Come without a map. Explore it and draw your own map.” – እንዲል Stephen King

ማሰብ ሰው የመሆን ሂደትን የማወቅ ሂደት ነው፡፡ ሰው መሆን ዲበአካላዊና ህላዌያዊ ጥያቄዎች የሚነሱበት ነው፡፡ ከየት መጣሁ ወዴት እሄዳለሁ? ለምንና እንዴት ነው የምኖረው? መኖሬ የመወለድ ጣጣ ነው ወይስ ዓላማና ትርጉም አለው? ሕይወት ምንድን ናት? ፍቅር፣ ሐዘን፣ ደስታ፣ናፍቆት፣ ጥላቻ፣ ወሲብ ምንድን ናቸው? የሰው ልጅ ምናብና የፈጠራ አቅም እስከ የት ነው? ተፈጥሮ ምንድን ናት፣ እንዴትስ ነው የምትሰራው? እኔን ከተቀረው ተፈጥሮ ጋር ምን ያገናኝ፣ያስተሳስረኛል? ግለሰብ እና ማኅበረሰብ ምንድን ናቸው፣ ምንና ምን ናቸው? ኃይማኖት ምንድን ናት? መንፈስ እና ነፍስ የሚባሉ ነገሮች አሉ የሉም? እውነት ምንድን ናት? ሀሰትስ? ተፈጥሮ ፈጣሪ አላት? እንዴትና በምን ሁኔታ ወደ ህላዌ መጣን?
የሰው ልጅ የህልውና ታሪክ ምን ይመስላል? ከየት ተነስቶ የት ደረሰ? መድረሻውስ የት ነው?
እኒህና መሰል ጥያቄዎች የማሰብ ሂደትን የሚፈልጉ ናቸው፡፡ በማሰብና በማሰቢያ አካላችን መካከልም አንዳች ተኣምራዊ መስተጋብር መኖሩም ይገባናል፡፡ በርግጥ እነዚህ ነገሮች እያሰብኳቸው ያለሁት ማሰቢያ አካሉ ሥላለኝ ነው ወይስ ቀድሞ ታስቦና ታቅዶበት የተዘጋጀልን ነው? ብለው እንዲጠይቁም ይረዳል፡፡

እዚህ ለመድረስ ደግሞ ግብዓት ያስፈልገናል፡፡ ግብዓቶቹ ከሥሜት አካላትና ከህይወት ልምድ የሚገኙ ናቸው፡፡ እንደ ኤምፔሪስስቶች ገለፃ፤ እኛም በኑሮ እንደሚገባን፡፡ መጻሕፍት ደግሞ ላቅ ያሉት የግብዓት ምንጭ፡፡ መጻሕፍት የሰው ልጅ የማሰብ ጉዞ (Evolution of mind) ሰነድም ናቸው፡፡ ከየት ተነስቶ የት ደረሰ የሚነግሩን፡፡ መጻሕፍታችንን አይተን እንደ ሀገር የማሰብ ጉዟችንን መገምገም እንችላለን፡፡ ምናልባት ጥንታዊ የኃይማኖት መዛግብትን ጠቅሰን እንፎክር ካላልን የእኛ የሚያኮራ አይደለም፡፡ ስለማያኮራም መሸሸጊያ ፍለጋ ታሪክ እንጠቅሳለን፡፡ መጻሕፍት የነፍስ መስታዎት ናቸው እንዳለች ውልፍ፡፡ የእኛ የአሁን የገበያ ላይ መጻሕፍትም የነፍሳችን መስታዎቶች ናቸው፡፡ እነሱን አይተን ራሳችንን ማወቅ እንችላለን፡፡ አንዳች ረብ ከሌላቸው እኛም እንዲያ ብንሆን ነው፡፡ 

“Reading furnishes the mind only with materials of knowledge; it is thinking that makes what we read ours.” – ይላልና ሊቁ John Locke
[... ናትናኤል ዳኛው...]
5.6K viewsedited  11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 21:39:44
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን ኢድ ሙባረክ
3.2K viewsedited  18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 09:24:12 ለክርስትና እምነት ተከታይ የስብዕና ልህቀት ቻናል ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።

በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እንመኛለን።
2.0K views06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 21:57:44 ከራስህ አትሽሽ! ከእውነትህ ተፋጠጥ፤ የሰቀልከውን እውነት አውርድ!
(Face the reality!)
(እ.ብ.ይ.)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ በየዓመቱ የሚፆመው የአብይ ፆም ሊገባደድ የአንድ ቀን ዕድሜ ነው የቀረው፡፡ ፆሙ የጌታችንንና የመድሐኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የአርባ ቀንና የአርባ ሌሊት ፆም መታሰቢያ የሚያደርግ ዓመታዊ ፆም ነው፡፡ በተለይ ይሄ ሊያልቅ ያለው ሳምንት የክርስቶስን ህማማቱን፣ ግርፋቱን፣ አንግልቱን፣ ስቃዩን የምናስብበት ሳምንት ነው፡፡ አዎ ጌታችን የሰቀሉትን ‹‹የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው›› ብሎ ነፍሱን ቢሰጥም በሶሰትኛው ቀን በመለኮታዊ ሃይሉ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል፡፡ ሞትን አሸንፏል፡፡ ፍቅሩ ምድርን ሁሉ ገዝቷል፡፡

የሚያሳዝነው ጉዳይ ግን ዓለማችን አሁንም እውነትን እንደሰቀለች መሆኗ ነው፡፡ በዚህ በኛ ዘመንና ትውልድ አሁንም ሐቅ እንደተሰቀለ ነው፡፡ በእውነት የሚነግድ ነጋዴ ጠፍቷል፡፡ በታማኝነት ሐገሩን የሚያገለግል ባለስልጣን ህልም እየሆነ ነው፡፡ ዛሬም እውነት በምድራችን ላይ የለችም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሳለች፡፡ እውነት ያለው ፍቅር፣ እውነት ያለው እምነት፣ ሐቅ ያለው ንግድ፣ እውነት ያለው ወዳጅነት፣ እውነት ያለው ዝምድና፣ እውነት የሞላው ትዳር፤ እውነት ያለው ዕውቀት፤ ለእውነት የሚወግን ህግ፣ ለእውነት የቆመ መንግስት፣ በሀቅ የሚመራ የሰው ልጅ እየጠፋ ነው፡፡ በድብብቆሽ የጦፈ የሴሰኝነት ፍቅር፤ በወረት የሞቀ ወዳጅነት፣ በመከዳዳት የሚገባደድ ስምምነት፤ በመሰለቻቸት፣ በመጠላላትና በመጠፋፋት የሚያልቅ ወዳጅነት፤ በውክቢያና በችኮላ ተጀምሮ ግለቱን ቶሎ በሚጨርስ የወረት ፍቅረኝነት ዓለም እየታመሰች ነው፡፡ ሰው በገዛ የምኞት ገመዱ ተጠፍንጓል፡፡ ልቅ ፍላጎቱ መረን ለቅቆታል፡፡ ስሜቱ አዋክቦ ከሕሊናው አርቆታል፡፡ ደመነፍሱ ከራሱ ጋር አጣልቶታል፡፡ ስጋውና ነፍሱ፤ ስሜቱና መንፈሱ አልተዋሃደም፡፡ ለመብላት ብቻ የሚኖር ሆዳም ትውልድ ሆኗል፡፡ ለገዛ ጥቅሙ ብቻ ሲል የሌሎችን መብትና ጥቅም የሚጋፋ ስግብግብ ፍጥረት በዝቷል፡፡ ብልጠት እንጂ ብልህነት የሌለው ትውልድ በገፍ እያመረትን ነው፡፡

በዚህ ዘመን እውነቱንና እምነቱን በአፉ ብቻ የሚናገር ነው ምድሪቱን የሞላው፡፡ ለመናገር የፈጠነ፣ ለመስማትና ረጋ ብሎ ለማስተዋል የዘገየ ነው ዓለሙን ያጥለቀለቀው፡፡ በኑሮውና በሕይወቱ እውነቱንና እምነቱን በተግባር አጥብቆ የያዘ እምብዛም ነው፡፡ ሰውነቱን አሽቀንጥሮ የጣለ፣ ስብዕናው የተቃወሰ እልፍ ነው፡፡ ይሄ ሰልጥኛለሁ የሚለው ዘመነኛው ትውልድ ከህሊናው የተጣላ፤ ፍቃደ-ልቦናውን የዘነጋ፣ እፍረት የሌለው ፈጣጣ ትውልድ ስለመሆኑ ብዙ ማሳያዎቹን መዘርዘር ይቻላል፡፡ አዎ የዛሬው ሰው በገዛ ፍቃዱ በላዩ ላይ የባርነት ቀንበሩን አክብዷል፤ የሎሌነት ሸክሙን አብዝቷል፡፡ የሰለጠነ መስሎት ሠይጥኗል፡፡ ገንዘብ ገንዘብ ሲል ግንዛቤውን ጥሏል፣ ማስተዋሉን አጥቷል፡፡ ሰውነቱን ላይደርስበት አርቆ ሰቅሏል፡፡

ሰው እውነትን ሰቅሎ ኑሮውን አስወድዷል፡፡ የዋጋ ንረቱን ጭንቅላቱን አዙሮታል፡፡ ዘንድሮ ያልተሰቀለ ምን አለ? እውነት ተሰቅሏል፤ እምነት ተሰቅሏል፤ ኑሮ ተሰቅሏል፣ የእህልና የቁስ ዋጋ ተሰቅሏል፣ ሰውነት ላይደረስበት ተሰቅሏል፤ ደግነት ተወድዷል፤ ታማኝነት እንደብርቅዬ እንስሳ የሚታይ ሆኗል፡፡ አጃኢብ ነው መቼስ!

ወዳጄ ሆይ..... ያንተስ የአንተነትህ ፋሲካ መቼ ነው?? ያንተስ የሰውነት ትንሳኤህ ወዴት አለ?? ከቶ መቼ ይሆን ከሃሳብ ህመምህ፣ አስተሳሰብ ስቃይህ የምትገላገለው?? የሰው ልጆችስ ከወደቅንበት ስብዕናችን የምንነሳው መቼ ይሆን??

አዎ ወዳጄ! ከመንጋው ጋር አትጋፋ! በስሜት ከሚነጉደው ጋር አትንጎድ፡፡ የበዓሉን ምሳሌነት ተረዳ፡፡ የምታየውን፣ የምትሰማውን ሁሉ ከሕይወትህ ጋር እያገናኘህ አስበው፣ ተንትነው፣ አብሰልስለው፡፡ ከዛም የሚጠቅምህን ውሰድ፡፡ በጎ ነገርን ተለማመድ፡፡ በሚጠቅም አዲስ ሃሳብ ትለወጥ ዘንድ በርታ፡፡ በስቅለቱ በዓል የተሰቀለውን ክርስቶስ ህማሙን እያስታወስክ ዛሬም አንተን እያሰቃየህ ያለው የምኞት ዓለም እየመረመርክ፤ ራስህ አርቀህ የሰቀልከውን እውነት አውርድና ለእውነትና በእውነት ኑሮህን ጀምር፡፡ የትንሳኤውን በዓል ስታከብር አንተን የጣለህንና የአሸነፈህን ቀሽም አስተሳሰብ ድል ነስተህ በአዲስና በቀና አስተሳሰብ ተነስተህ ሕይወትህን አቅናው፡፡

ከራስህ አትሽሽ! ከእውነትህ ተፋጠጥ፤ የሰቀልከውን እውነት አውርድ - Face the reality!

‹‹ጥንት የተሠቀለችው እውነት
ለልብ አብነት ነች፣
ለሰው ምሣሌ ነች፤
በደምና በአጥንት፤ ታስራ የተገመደች፡፡
ውስጠኛዋን እውነት መላልሶ ለመስራት፣
የተሠቀለችውንም እውነት፤ ያሻል አለመርሳት፡፡››

....የትንሳኤውን በዓል ስታከብር አንተን የጣለህንና የአሸነፈህን ቀሽም አስተሳሰብ ድል ነስተህ በአዲስና በቀና አስተሳሰብ ተነስተህ ሕይወትህን አቅናው፡፡...

መልካም የትንሳኤ በዓል!

____
እሸቱ ብሩ
ይትባረክ

@EshetuBirruYitebarek
@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.0K views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 20:36:40 እንተዋወቃለን ወይ?
የአመቱ ድንቅ ወግ
በተስፋሁን ከበደ

@Human_Intelligence
4.1K views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ