Get Mystery Box with random crypto!

የስብዕና ልህቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የሰርጥ አድራሻ: @human_intelligence
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 89.04K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-01-07 12:14:34
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የቻናላችን ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።
መልካም በዓል ይሁንላችሁ ዘንድ እንመኛለን።
13.3K viewsedited  09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-04 06:08:41 የልማድ ምስጢር!

“ደጋግመን የምናደርገውን ነገር ነን፡፡ ስለሆነም፣ ልቀትና ምርጥነት የአንድ ጊዜ ተግባር ጉዳይ ሳይሆን የልማድ ጉዳይ ነው” - Aristotle

“እኔ የአንተ የዘወትር አጋርህ ነኝ፡፡ ታላቅ የሆንኩ ረዳትህ ነኝ ወይም ደግሞ ከባድ የምባል ሸክምህ፡፡ ወደ ስኬት ልገፋህ እችላለሁ፣ ወይም ደግሞ ወደ ውድቀት ልጎትትህ ብቃት አለኝ፡፡ ሁል ጊዜ እንዳዘዝከኝ ለመሆን ዝግጁ ነኝ፡፡ በየእለቱ ከምታደርጋቸው ነገሮች ገሚሶቹን ለእኔ አሳልፈህ ብትሰጠኝ ባፋጣኝና በትክክለኛው መንገድ አከናውናቸዋለሁ፡፡ ጠንከርና ጨከን ካልክብኝ፣ በቀላሉ ልትገራኝና ልታስተዳደረኝ ትችላለሀ፡፡ አንድ ነገር በምን መልኩ መደረግ እንዳለበት አሳየኝና ትንሽ ካለማመድከኝ በኋላ በፈለከው ጊዜ ሁሉ በፍጥነት አከናውንልሃለሁ፡፡ ታላላቅ የተሰኙ ሰዎች አገልጋይ ነኝ፤ ሆኖም የውድቀትና ያለመሳካትም ምክንያት እኔው ነኝ፡፡ ታላላቅ የሆኑን ሰዎች ታላቅ ወደ መሆን ያመጣኋቸው፤ የወደቁና ያልተሳካላቸውንም ሰዎች ለዚያ ያበቃኋቸው እኔ ነኝ፡፡ ማሽን አይደለሁም፤ ነገር ግን ልክ እንደ ማሽን የተሰጠኝን ሁሉ ሳላዛባ፣ ልክ እንደሰው ደግሞ በብልህነት እሰራለሁ፡፡ ከፈለክ ለትርፍ ተጠቀምብኝ ካለዚያም ለክስረት ተጠቀምብኝ፣ በእኔ በኩል እንደሆነ ምንም ልዩነት አያመጣም፡፡ ውሰደኝ፣ የራስህ አድርገኝ፣ አሰልጥነኝ፣ ጠንከርና ጨከን በልብኝ እኔም በተራየ አለምን አስገዛልሃለሁ፡፡ ቀለል በልልኝና ችላ በለኝ፣ አጠፋሃለሁ፡፡ ማን ነኝ? እኔ ልማድ እባላለሁ!” – Anonymous

ልማድ ማለት በአንድ ነገር አቅጣጫ ራሳችንን ከማስለመዳችን የተነሳ ያንን ነገር በቀላሉ ማድረግ ስንጀምርና እንደውም ማቆም ሲሳነን ማለት ነው፡፡ ይህ እውነታ ደግሞ ለጤናማውም ሆነ ለጤና ቢሱ ልማድ የሚሰራ እውነታ ነው፡፡ ልማድ ማለት ካለምንም የውጭ ግፊትና ጉትጎታ ማድረግ የጀመርነውና “የማንነታችን” ክፍል ወደ መሆን የመጣ ጉዳይ ነው፡፡ ከመልካም ልማድ ውጪ ማንም ሰው ምንም ነገር ማድረግ አይችልም፡፡ በሌላ አባባል ወደ ልማድ ባልመጣ መልካም ነገር ወደ ስኬት መምጣት አንችልም፡፡

ብቃትና ጥራት ማለት የተለመደን ነገር ባልተለመደ መልኩ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ደግሞ መልካምን ልማድ ማዳበር የግድ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ በአንድ ስፖርት ኦሎምፒክ ላይ የሚወዳደሩ ሰዎች በአማካኝ ካለማቋረጥ ለስድስት ዓመታት ሙሉ በአመት ለ310 ቀናት፣ በየቀኑ ለአራት ሰዓታት ልምምድ ያደርጋሉ፡፡ ሌሎች ሰዎች ቀኑን ሙሉ የማይሰሩትን ስራ እነዚህ ስፖርተኞች ጠዋት አንድ ሰዓት ከመሆኑ በፊት ሰርተው ይጨርሳሉ፡፡ 

አሁን ምንም አይነት የላቀ ደረጃ ላይ የደረሰን ሰው ተመልከትና ጀርባውን አጥና፤ ለረጅም ጊዜ ደጋግሞ ያደረገውንና የገነባውን አንድ ነገር ታገኛለህ፡፡ በሌላ አባባል፣ አሁን የደረሰበት የላቀ ደረጃ የደረሰው በአጋጣሚ ሳይሆን አንድን መልካም ልማድ አዳብሮና በዚያ ልማድ ዙሪያ ደጋግሞ በመስራትና በመሻሻል ነው፡፡

የንጽህና ልማድ ቤትን፣ አካባቢንና አገርን በንጽህና ልቀው እንዲገኙ ያደርጋቸዋል፡፡ የስራ ልማድ በብልጽግና ልቀን እንድንገኝ ያደርገናል፡፡ የጥናት ልማድ በእውቀት እንድንልቅ መንገዱን ይጠርጋል፡፡ ከማንኛውም ውብ ነገር ጀርባ መልካም ልማድ አለ፡፡ በእኔና በአንተም ኑሮ ስሌቱ ያው ነው፡፡

አንድ ቀን ከእንቅልፋችን ስንነሳ በአንድ ነገር ልቀን አንገኝም፡፡ ከአንድ ግብ አንጻር በየእለቱ የገነባናቸው ልማዶቻችን ናቸው የነገን ልቀታችንን የሚወስኑት፡፡ ልማድ የሕወታችንን አብዛኞዎቹን (ምናልባት ሁሉንም) ነገሮች አቅጣጫ ወሳኝ የሆነ ጉዳይ ነው፡፡ ጤንነታችንን፣ ኢኮኖሚያችንን፣ ወዳጅነታችንን የኑሮአችንን ጥራትና ሌሎችም ዋና ዋና ነገሮችን ስለሚወስን፤ ልማድ ሲጨመቅ ማንነት ይሆናል፡፡  

ዶ/ር እዮብ ማሞ
@Human_Intelligence
13.4K views03:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-31 20:51:11 አያ ጅቦ አለህ ? አለሁ ምን እየሰራህ ነው?....
እናንተን ልበላ

እናቴ የአምስተኛ እና የስድስተኛ ክፍል ጂኦግራፊ አስተማሪ ነበረች፤ ጡረታ ከመውጣቷ በፊት፡፡ የምታስተምርበት ትምህርት ቤት ብማርም እሷ የምታስተምርበት ክፍል አልተማርኩም። ልጆች ስለምትወድ፣ እንደ ልጆቿ ስለምትቀርባቸው እንደሚወዷት በርካታ ጊዜ ምስክርነት ሰምቻለሁ፡፡ አሁን እንኳን ጡረታ ወጥታ መንገድ ላይ ያስተማረቻቸው ተማሪዎች ፍቅር እና አክብሮታቸውን ሲገልጹላት ብዙ ጊዜ አይቻለሁ።

እናቴ የላላ፣ የተቆጠበ ማኅበራዊ ግንኙነት ያላት፣ ረጋ ያለች፣ ፈገግታ የማይለያት ደርባባ ሴት ናት። ሙሉ ጸጉሯ ሃጫ በረዶ መስሎ ጥቁር ነበረው ቢባል ለማመን ይቸግራል። ብቻዋን ነው ያሳደገችኝ፡፡

ልጅ ሳለሁ እቴቴ አባቴ የት ነው ያለው? እላታለሁ፡፡

“ይመጣል ሰላም ለማስፈን ነው የሄደው” ትለኝ ነበር!! በስንት ተረት ሰላም ምን ማለት እንደሆነ ከገባኝ በኋላ ሁከት እና ግርግር ሳይ አባቴ አልደረሰም ማለት ነው እያልኩ፣ ሲደርስ አባቴ ሁሉን ያስተካክላል እያልኩ አደግሁ።
ሲደርስ ሰላም ይሆናል።

"ትንሽ ነፍስ ሳውቅ አባቴ ጦርነት እንደሄደ፣ እናት ሀገሬ ብሎ ሸልሎ ወጥቶ አድሮ ወጥቶ መቅረቱ ተገለጸልኝ። አባቴ እንዴት ነበር? እለዋለሁ ከእኔ በዕድሜ በልጦ ተወልዶ በጥቂትም ቢሆን አባቴን የሚያውቀው ወንድሜን።

“አባታችን ተጫዋች፣ እናታችንን የሚንከባከብ፣ ደ'ሞ ደ'ሞ ከሥራ ማታ ሲመጣ ሁሌም በፌስታል ለእኛ አንድ ነገር ሳይዝ የማይመጣ፤ ከሥራ ደክሞት እንኳን መጥቶ ሳያጫውተን የማያድር ነበር” እያለ ይተርክልኛል።

በትንሹም በትልቁም አባቴ ቢኖር እላለሁ፤ ጉድለቱ ሲሰማኝ... አባት እና ልጅ ሲሄዱ የልጁ ዕድለኝነት ሲታየኝ የአባት ፍቅር ጉድለት ስሜት እየጠዘጠዘኝ፣ እኔም እንደ ማደግ ወንድሜም ለአቅመ አዳም ደረሰ።
ወንድሜ ሥልጣን ላይ ያሉትን የአባቴን ገዳዮች ለመታገል ፖለቲካን ማደሪያው አደረገ። ተቃዋሚ ነን ካሉት ጋር ሁሉ ቀድሞ ይሰለፋል፡፡ ሁሌም የተቃዋሚዎች ባንዲራ ያዥ እሱ ነው፡፡ ደፋር ነው ይሉታል።

አንድ ቀን ማታ እናቴ “ወንድሜ ቤት አላደረም” ብላ ሀገር ይያዝ አለች... ፈለገች፣ አስፈለገች... እሱን የበላ ጅብ አልጮህ አለ። ከጥቂት ቀን በኋላ ግን መታሰሩን ሰማን... እናቴ አነባች፣ ተንገበገበች! ያኔ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍቶኝ ስቅስቅ ብዬ ያለቀስኩት። ንፍጤን እና እንባዬን እየጠረግኩ አይመጣም እኮ እሱም እንደ አባዬ አይመጣም በኋላ ማንም የሚያግዝልኝ፣ ወንድሜ አይመጣም
የሚያስጠናኝ አይኖርም... እያልኩ አለቀስኩ!

በወንድሜ መታሰር ድብርት ይሆን ብቸኝነት የሆነ ውሉ የማላውቀው መንፈስ ወረረኝ። ደፋር እኮ ነው እያሉ ከፊት ሲያሰልፉት የነበሩት ሰዎች አንድ ቀን እንኳን ለመጠየቅ አልደፈሩም፡፡ የታሰረበትን የሚነግረን አጥተን ስንከራተት ያውቁ እንደሆን ስንጠይቃቸው እሱን ራሱ አናውቀውም አሉን፡፡

እናቴ የተነሳውን ርእስ ወደ ወንድሜ ስባ አምጥታ “አሄሄሄሄ ያልታደልኩ” ትላለች። በሰልኩ መሰለኝ ድሮ ስለ አባቴ እያወራችኝ ስታለቅስ፣ ሕመሟ ስለማይገባኝ ጀመራት የምል የነበርኩ ልጅ ዛሬ እኔ አለሁልሽ እያልኩ አጽናናት ጀመር።

ወንድሜ በታሰረ በሁለተኛ ወሩ እስር ቤት ውስጥ በተፈጠረ ጠብ መሞቱን ፖሊሶች ቤታችን መጥተው ሦስት መሥመር በማትሞላ ደብዳቤ አረዱን። እርማችንን ተንሰቅስቀን፣ ተንቀጥቅጠን አወጣን።

አባቴ እና ወንድሜ ሞቱ። ነገር ግን ለሞታቸው መታሰብያ የሞቱለት ጨለማን የማውደምም ሆነ ብርሃን የማፈንጠቅ ሂደት አልተከናወነም።

የቤታችን ሁለት የሙቀት ምስሶዎች ተገንድሰው ያለ ሙቀት፣ ያለ ምሰሶ እንኖራለን!
እኔ ስሜ ብርሃኑ ቢሆንም እናቴ ብርሃኔ ነው የምትለኝ፡፡ “ብርሃኔ” ስትለኝ 'ኔ' ን እርግጥ ጫን አድርጋ ስለምትጠራኝ የሆነ ማያዬ፣ እይኔ፣ ጧሪዬ የምትለኝ ነው የሚመስለኝ።

እንደ መርፌ ቀዳዳ አንድ ሆኜባት የኑሮ ፍልስፍናዋ በእኔ እና በኔ ዙሪያ ያጠነጥናል። ትንሽ ካመሸሁ ሰቀቀኗ ልክ የለውም። ሁሉም ነገር በሷ ሐሳብ ልክ ብቻ መሆን አለበት። አስራ ሁለት ሰዓት ቤት መግባት አለብኝ። አንድ ደቂቃ ካለፈ ስልኬ ይጮሃል። ቤት ገብቼ የማወራቸው ወሬዎች ከሀገር፣ ከመንግሥት፣ ከፖለቲካ የራቁ መሆን አለባቸው። በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለፖለቲካ ቀረበ፣ ለሀገር መቆርቆር ስሜት ያለው ወሬ ማውራት አልችልም።

“ብርሃኔ አደራህን አታምሽ፣ በማያገባህ አትግባ፣ በፖለቲካም ቢሆን፤ ደ'ሞ ደ'ሞ ፖለቲካ ሽንፍላ ነው አይጸዳም፤ የራስ ወዳዶች መጠቀሚያ ቃታ ነው፤ የግል ችግሩን እኛ እያለ እየቸረቸረ ዝና እና ፍራንክ የሚለቅም ብቻ ነው ያለው፡፡"

ሐሳብ ከሐሳብ አይፋጭም። እኔ ልብላው፣ እኔ ካልበላሁት በሚል ይናጫሉ እንጂ ትግሉ የሐሳብ፣ ለሕዝብ ጥቅም የቆመ አይደለም፡፡ ሕዝብ ሕዝብ የሚሉት ለቲፎዞ ነው። አየህ ልጄ በፖለቲካ ጥሩ የደደበው ያሸንፍና ሥልጣን ይይዛል። ትዕቢት የወጠረው ደግሞ ይወድቃል፤ እኔ የማውቀው እና ያየሁት ፖለቲካችን ይሄ ነው፤ እንዳትበላብኝ አበባዬ።

ይሄውልህ ብርሃኔ ብሔር፣ ጎሳ፣ ዝምድና የፖለቲካችን መሠረት ነው። በእሱ ትሰባሰባለህ፣ ሴራ፣ ውሸት፣ ሆድ፣ ክሕደት፣ ድድብና አለው፡፡ ዓለሜ የታላቅነት እውነተኛ ሕልም፣ እውቀትህ ያስበላሃል። እውነተኛ ከሆንከ ያሴሩብሃል፣ ያድሙብሃል፣ ስምህን ያጠለሹታል። የማያውቅህ ወታደር ጥንካሬውን ይፈትሽብሃል ወይ ደግሞ እንዳባትህ እና ወንድምህ ግንባርህን ይልሃል።”

"ፖለቲካችን ሞት አለው፤ ካልጨከንክ፣ ካልደደብክ መከራ ይጥልብሃል፣ ያሻህን ተናግረህ አትኖርም፣ አትወጣም፣ አትገባም፣ ሚስትህን ባል አልባ፣ ልጅህን አባት ታስናፍቀዋለህ። ቂመኛ ነው ቀን ይጠብቅልሃል። እንደኔ ባል እና ልጅ እንዳንተ አባት እና ወንድም ደቼ ትበላለህ።

ብርሃኔ እኔ ልሙት እልሃለሁ ፖለቲካችን ውስብስብ አይደለም። ለመጉላት ደደብ እና ራስ ወዳድ መሆን መስፈርቱ ነው። የሚወደድ ነገር የለውም፡፡

አበባዬ የሚፈልጉትን የሚያጎሉት እና የሚያፈዙት እነርሱ ራሳቸው ናቸው። ይሄውልህ ብርሃኔ በዚህ ጸድቶ በማይጸዳ ፖለቲካ ብትሞትብኝ ለአንድ ሳምንት ብሶቴ፣ እንባዬ፣ ለቅሶዬ በየሰፈሩ በየካሜራው ይንከባለላል። ከዛ... ይረሳል፤ ሐዘኑ እና ስብራቱ እኔ ጋ ብቻ ይቀራል።


ብርሃኔ የተበላሸ ሂደት ውስጥ ትክክል መሆን ስሕትት ነው!!
ልጄ የዚህ ሀገር ፖለቲካ ይቅርብህ፤ ትበላብኛለህ። አንዲት ጣት ማጣት ለማይገባው ዓላማ ባል እና ልጄን ገብሬያለሁ። ይበቃኛል።

ዜናው፣ ትግሉ፣ ፕሮፖጋንዳው፣ ጽንፈኝነቱ ከሰውነት ማማ ላይ ያወርዳል።
አደራህን ዓለሜ ግርግር ስታይ ለማጣራትም ብለህ ቢሆን እንኳን አትገተር። አትቀላቀል፤ ፖለቲከኞች ለግል ጥቅም ነው ተናጭተው የሚያናጩት። ሕዝብ ጥቅም ማግኛ ቃታቸው ነው። ችግሩ ወደ አንተ ካልመጣ አንተ ወደ ችግሩ አትሂድ።”
ከእናቴ የተለየ ሐሳብ ባይኖረኝም ያጣችውንም ስለማውቅ ስትናገር ጣልቃ ሳልገባ እሰማታለሁ፡፡
ዛሬም አባቴን እና ወንድሜን የበሉት ጅቦች ይጮኻሉ። ፕሮፖጋንዳቸውን ይነዛሉ። አንዱ ጎራ “ተነስ ከእኔ ጋ ብርሃን፣ ሰላም፣ ብልጽግናን በጋራ እናምጣ” ሲል አንዱ ጎራ “ሁሉም ሰላም ነው ተኛ! ዋ!” ይለኛል። ሁለቱም ጎራ እያንዳንዱን ክስተት ሥልጣን ማቆያ እና ሥልጣን መጨበጫ እንድትሆን አድርገው ይቀነብቧታል። ለሁሉም ና ከእኛ ጋ ሁን ጥሪዎቻቸው መልሴ ግን አንድ ነው፡፡

ወንድሜን እና አባቴን መልሱልኝ እና!!!

መፅሀፍ- አዎ እሱጋ ያመኛል
ደራሲ - አድሀኖም ምትኩ
share& Join
@Human_Intelligence
12.8K views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-15 07:16:21 እያንዳንዱን ችግር እንደ መሰላል ከተወጣጣህበት ከስኬት ጫፍ ትደርሳለህ!!

በአንድ ወቅት አንድ ገበሬ አህያው ጉድጉድ ወስጥ ትገባበታለች፡፡ ጉድጓዱ ሩቅ ከመሆኑ የተነሳ አህያዋ ለመውጣት በእጅጉ ተቸገረች፡፡ በጣም መጮህ ጀመረች፡፡ ባለቤቱም እሷን ለማውጣት ብርቱ ሙከራ አደረገ አልተሳካለትም ፤ አህያዋ አርጅታለችና ጉድጓድ ውስጥ ሊቀብራት አሰበ።

ጎረቤቶቹንም ጠራና ጉድጓዱን በአፈር መሙላት ጀመረ፡፡ አህያዋ ይህንን ስተመለከት እየቀበራት መሆኑን ተረዳችና እጅጉን  አዘነች፡፡

ይሁን እንጂ አፈር በተደፋባት ቁጥር አህያዋ አንድ ነገር ታደርግ ነበር። አፈሩን እያራገፈች ከአፈሩ ውስጥ ብቅ ትል ነበር። በተደጋጋሚ ከዚያም በተደፋው አፈር ላይ መቆም ትጀምራለች። በሒደት ውስጥ በአፈሩ ላይ በቆመች ቁጥር ከነበረችበት ጉድጓድ ከፍ እያለች በመጨረሻም ከጉድጓዱ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መውጣት ቻለች፡፡ በሚገርም ሁኔታ አህያዋን ሊቀብሯት የሞከሩት ስዎች ሁሉ በአህያዋ አወጣጥ በእጅጉ ተደነቁ፡፡

ውድ አንባቢያን እንደሚታወቀው የአህያዋ ታሪክ ሁላችንንም ይመለከተናል። የሚጫንብን አፈር ደግሞ በየጊዜው የሚያጋጥሙንና ዝም ብንላቸው በመጨረሻ ሊቀብሩን የሚችሉ ችግሮች ወይም መሠናክሎች ናቸው፡፡ አፈሩን የሚጭኑት ሰዎች በዙሪያችን ያሉ ሰዎች፣ ነገሮች፣ በህይወታችን ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥሩብን አዳዲስ ለውጦች እንዲሁም የራሳችን አፍራሽ ስሜቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ጉድጓዱ ደግሞ አሁን ያለንበት ግራ የተጋባንበት! ተስፋ ቢስ የሆንበት፡ መላ ያጣንበት ህይወት ወይም ገጠመኝ ሊሆን ይችላል፡፡

በእርግጥም እኛ ሰዎች በጤናችን! በኢኮኖሚ ህይወታችን፤ በትዳርና ፍቅር ህይወታችን በተለያየ አጋጣሚ ልክ እንደ አህያዋ ጉድጓድ ውስጥ የመግባት ዕድላችን ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ጠንካሮች እንደ ጠንካራዋ አህያ ከገቡበት ጉድጓድ ውስጥ መውጣት ሲችሉ አንዳንዶቹ በዚያው ተቀብረው ቀርተዋል፡፡

ውድ አንባቢያን በህይወታችን ውስጥ ያለው አማራጭ! ወደ ላይ መውጣት አልያም ደግሞ ወደ ታች ወርዶ ከጥልቅ ጉዳጓድ ውስጥ ተቀብሮ መቅረት ብቻ ነው! በየጊዜው ሊገጥመን የሚችለውን ችግር ልክ እንደ አህያዋ የሚጫንባትን አፈር እየረገጠች ወደ ላይ ከፍ እንዳለችው ሁሉ አንተም/አንቺም በየጊዜው የሚገጥማችሁን ችግሮች እንደ ድጋፍ እየተጠቀማችሁ በጥንካሬ ወደ ላይ መነሳት ያስፈልጋል፡፡ ከጥልቁ ጉድጓድ ውስጥ ለመውጣት የምንችለው ለመውጣት የምናደርገውን ጥረት ባለማቆም ብቻ ነው።
በመሆኑም ምንጊዜም በጠንካራ ውስጣዊ ቁርጠኝነትና እምነት ችግሮችን እንደ መወጣጫ ደረጃ በመጠቀም ከታች ወደ ላይ ተጓዙ ለማለት እወዳለሁ።

#share
Join: @Human_Intelligence
12.8K views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-22 21:06:42 የጠፋውን የሰው ልጅ ፍለጋ (Search for the lost human soul)

ዘመኑ 1950ዎቹ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ... ከሁለቱ የዓለም ጦርነቶች ስካር የባነነው ዓለም ለሌላ ዓይነት ባርነት ራሱን ሲያዘጋጅ ተገኘ፡፡ ሥልጣኔውም አገዘው፡፡ የሥልጣኔ ቀዳሚው ተልዕኮ የሰውን ልጅ እንሰሳዊ ደመነፍስ ማላመድ (taming human animalistic aggresion) ቢመስልም ውጤቱ ግን የተገላቢጦሽ ሆነ፡፡ ለኤሮፓዊ ፋውስታዊ የዛገ መዳዳቱ ስምረት ቴከኖሎጂው ረዳት ሆነለት፡፡

ዘመኑ ሰው ወደ አሻንጉሊትነት የሚያደርገውን የመምዘግዘግ ጉዞ አሀዱ ያለበት ሆነ፡፡ በአዲሱ ፈጠራ ቴሌቪዥን በመታገዝ "ፖፕ ከልቸር" ሰለጠነ፡፡ ሁሉም አብረቅራቂው ዘመን አመጣሽ ሳጥን ጋር ፍቅር ወድቆ ለአዲሱ ጊዜ ባርነት ራሱን አዘጋጀ፡፡ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ ቴክኖሎጂው በቀኝም በግራም እኩል ይመነደጋል፡፡ ቫይረሱ እና አንቲቫይረሱ፣ ሚሳኤሉና ጸረሚሳኤሉ እኩል ይበለጽጋሉ፡፡

ዛሬ ከሰባ ዓመታት በኋላ በዓለምአቀፍ ደረጃ ወደ ሁለት ቢሊዮን የሚጠጉ የቴሌቪዥኖች ዝግጅቶች ፣ ከ5 ቢሊዮን በላይ የሞባይል ስልኮች በሰው ልጆች እጆች ላይ ይገኛሉ። በአንጻሩ በሰው ልጆች የንባብ አትሮኖሶች ላይ እንደተዘረጉ የሚገመቱት መጻሕፍት ዓይነት ከ150 ሚሊዮን አይበልጥም፡፡

እነሆ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሞታችን ረክሶ ‹ላይቭ ስናየው ስንኳ ማስደንገጡ ቀንሷል፡፡ እንበላለን፤ ግን አናጣጥምም፡፡ እንዋሰባለን፤ ግን ፍቅርን ረስተናል፡፡ አብረን ሆነን ለብቻችንን ነን፡፡ አብረን እየኖረን አንዳችን ለሌላችን በዓድ፣ ሩቅ ነን፡፡ ወዳጅነት፣ ሣቅ፣ ፈገግታ፣ መታመን፣ ፍቅር፣ ፍትወት... ሸቀጥ ሆነው በገበያ ዋጋ ይቸበቸባሉ፡፡

ሰብዓዊት የማይቀለበስበት አስፈሪ ውጥንቅጥ ውስጥ ገብቷል፡፡ አንዳንዶች ይህ አረዳድ ጭፍንነት ሊመስላቸው ይችላል፡፡ አንዳንዶች ሀዘኑ ቤታቸው እስኪገባ ድረስ የመቃብር ደወሉ በየዕለቱ ለእነርሱ እንደሚደወል ይረሱታል፡፡

እናስ ኤሪክ ፍሮም እንዳስጠነቀቀው የሚቀጥለው ዘመን ሮቦቶች ለመሆን ምን ያክል ይቀረናል? በዚያ ዘመን (በ195oዎቹ አጋማሽ) የተነሱት እንደ ኤሪክ ፍሮም ዓይነት የሰው ልጅ ዕጣ ያስጨነቃቸው አሰላሳዮች ሰው ስለመዳረሻው እንዲጠነቀቅ አብዝተው ቢወተውቱም ሁሉም ከአጥበርባሪ ሳጥኗ ጋር ሲወዛወዝ ሰሚ አልነበራቸውም፡፡ ኤሪክ ፈሮም በ1955 እ.ኤአ በታተመ The Sane Society› በተሰኘ መጽሐፉ ላይ እንዲህ አለ፡፡

‹የ19ኛው ክፍለዘመን ጥያቄ፣ ትርክት ‹‹እግዚአብሔር ሞቷል›› ነበር፡፡ የሀያኛው ክፍለዘመን ፈተና ግን የሰው ልጅ ሞቷል› ሆነ፡፡ በ19ኛው ክፍለዘመን ኢ-ሰብዓዊነት ማለት ጭካኔ ነበር፡፡ በ20ኛው ክፍለዘመን ግን ኢሰብዓዊነት ማለት መደንዘዝ፣ ስሜት ማጣትና መነጠል ሆነ፡፡ የትናንት ስጋታችን የሰውን ልጅ ወደ ባርነት እንዳይገባ ነበር፡፡ የነገ ስጋታችን ግን የሰውን ልጅ ከሮቦትነት የመታደግ ሆኗል፡፡››

‹‹ሁላችንም በዘመናዊው የምዕራብ ዓለም የምንኖር ሰዎች እብደት ውስጥ ነን፡፡ ራሳችን እያታለልን ላለመሆናችን ምን ዋስትና አለን?››

ዓለም መልክ የሌለው መገማሸር ውስጥ ገብታለች፡፡ ልክ አንደ ሁልጊዜው!... በዚህ ሂደት ሰው የመሆናችን ቀለም አጥተናል፡፡ ሰው የመሆናችን ውሉ በምን ይረጋገጥ? ከቅድመ አያቶቻችን የሚያስተሳስረን ፈትለነገር ከተቋረጠ ሺህ ዘመናት አልፈዋል፡፡ በሕንጻ ሰንሰለቶች መካከል እየተመላለስን ስንኳ ሕልማችን የተራራ፣ የሸንተረር፣ የአደን፣ የለቀማ ነው፤ እንደ ግዞተኛ ነን፤ ፊሊፒናዊ፣ ቼካዊ፣ ቱርካዊ... መሆናችን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የቅዱስ ቁርዓን፣ ወይም የማናቸውም ቅኝት ሥሪት መሆናችን እውነታውን አይቀይረውም፡፡

እኔ ግን የዓይኑ ቀለም ያላማራቸውን በጅምላ ኮንነው ሰልፊ እየተነሱ ዘቅዝቀው የሚሰቅሉ ሕዝቦች ሀገር ዜጋ ነኝ፡፡ ያ ሁሉ የሺህ ዘመናት ወንጌል፣ ሥነምግባር፣ ሀፊዝ፣ ሥርዓት፣ ትምህርት፣ ግብረገብነት በቅፅበት ውኃ በልቶት መቅላት፣ እስከነፍስ ማቃጠል፣ መደፍጠጥ፣ ማሳደድ... ሁሉም በሚያስደነግጥ ፍጥነት ሲከናወን አቅመቢስ ስዱድ፣ ዲዳ ሆኘ ተመልከቻለሁ፡፡ ታምሜያለሁ፡፡ ብዙ ኢፍትሃዊነት ባለበት ምንም ማድረግ ካለመቻል በላይ የሚያም ምንስ ነገር ይኖራል?

ለነገሩ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሰብዓዊነት፣ በአጠቃላይ በስነፍጥረት ላይ የሚቃጣ በደል ካላመመኝ የስካሩ አካል ሆኛለሁ ማለትም አይደል? አንዳንዶች ለዚህ መድኃኒቱ ዜግነትን ማስረጽ፣ ሕገመንግስት መቀየር... ዓይነት _ ጨዋ ሐሳቦችን ሲሰነዝሩ እሰማለሁ፡፡ ምንኛ የዋሆች ሆነዋል ጃል! የታመመው በአጠቃላይ የሰው ልጅ (ሰብዓዊነት) መሆኑን ማየትስ እንዴት ይሳናቸዋል? ይህ የሰብዓዊነት ማሽቆልቆል፣ ስርዓት በመቀየር፣ ደንደሳም ዴሞክራሲ በማስረጽ፣ በአዋጅ በማስነገር፣ ኢትዮጵያን እንደ አሜሪካ በማበልጸግ ብቻ ሊሻሻል አይችልም፡፡ እንዲውም ሁላችንም ከጫፍ እስከ ጫፍ እንደ ሰው ካላሰብን አንተርፍም፡፡


ዘመናዊው የሰው ልጅ ከቅድመ አያቶቻችን አንጻር የሁሉም ነገር ውስጥ መትረፍረፍ ውስጥ ነው፡፡ ዛሬ የአንድ አሜሪካዊ ቤተሰብ አማካይ የመገልገያ ቁሳቁሶች ብዛት እስከ 300,000 ይገመታል፡፡ ከመቶ ዓመታት በፊት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር 5000% እጥፍ ተመንድጓል፡፡ ዘመኑ በሁሉም ነገር የመትረፍረፍ (Abundance) ቅዠት ውስጥ የሚዳክር ይመስላል፡፡ ነገርግን መትረፍረፍ መቅሰፍት ሆኖብን ምኞታችን፣ እውነታችን፣ የሕይወት ትርጉማችን አሳክሮብናል፡፡ ምንም የማይፈይድልን የመረጃ ናዳ ያጥለቀልቀናል፡፡ በተሳከረ የመረጃ ቱማታ ተዋክበን እውነታችን ራሱ ዋጋ አጥቷል፡፡

ዘመኑ እንደየትኛውም ግልብ ዘመን ነበርና ኤሪክ ፍሮምና መሰሎቻቸው አድማጭ አላገኙም፡፡ እንደየትኛውም ዘመን... ዛሬ ለስሙ እንሰዋለን የሚሉ ቢሊዮናት ተከታዮች ያሉት መሲሁ በቁርጡ ቀን ከመስቀሉ ፊት ለፊት ለብቻው እንደነበረበት ዘመን፡፡ የሚያሳዝነው ዘመን ልብ መግዛት ሲጀምር ዕድሎች ቁጭት ሆነው ከተፍ ማለታቸው እኮ ነው፡፡

የሰው ልጅ የለየለት ዕብደት ውስጥ ገብቷል፡፡ ነጠል ብሎ ለሚታዘብ ተመልካች የሚታየው የሚሰማው  ሁሉ  አጃኢብ ነው፡፡ ሥልጣኔው ሁሉ በየዕለቱ የሚያስመዘግበው መካን፣ መራቀቅ የአውዳሚነት መሆኑ ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ ከጦር መሣሪያ ጋር ያልተነካካው ቴክኖሎጂያዊ ፈጠራ ስንኳ በየዕለቱ ሰብዓዊነትን የሚያኮሰምን የመሆኑ ነገር ያስደነግጣል፡፡

ተመራማሪዎች በቅርቡ ሰው በማይደርስባቸው አስፈሪ የአርክቲክ አካባቢዎች ሳይቀር ብዙ ሺህ ቶን የሚመዝን የማይበሰብስ ቆሻሻ አግኝተዋል፡፡ የሰው ልጅ አሁን በተያያዘው ግዴለሽ ጎዳና ከቀጠለ ሩቅ በማይባል ዘመን ሕይወት ከውቅያኖሶችና ባህራት ተጠቃልሎ ሊጠፋ ይችላል፡፡


በፍም እሳት መቃመስ
ያዕቆብ ብርሀኑ

ይቀጥላል
@Zephilosophy
13.0K views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-13 19:30:37 ቢታነፅ ቢወቀር!
(በእውቀቱ ስዩም)

እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!

ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ

ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!

ለካስ...

ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!

#share
Join: @Human_Intelligence
12.6K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-09 19:53:19 ከ400 ዓመት በፊት የተነገሩ አምስት ጠቃሚ የሕይወት ምክሮች


ራስን ለመለወጥ የሚረዱ ምክሮችን ስናስብ ምናልባት ገበያውን የሞሉት አዳዲሶቹ መጽሐፍት ጠቃሚ ሊመስሉን ይችላሉ። ሁሌም ቢሆን ማንም ሰው ዘመናዊና አዲስ የሆኑ ነገሮችን በመጠቀም ራሱን መቀየር ይፈልጋል።

ነገር ግን ከብዙ ዘመናት በፊት የተጻፉ መጻሕፍት አሁን ላለንበት ዓለም ተግባራዊ መሆን ይችላሉ። 'ዘ አናቶሚ ኦፈ ሜላንኮሊ' የተባለው መጽሐፍ በአውሮፓውያኑ 1621 እንደተጻፈ ይነገራል። የዘመናዊውን ሰው አኗኗርና አስተሳሰብ ከዚህ መጽሀፍ በላይ የሚገልጽ ግን አልተገኝም።

በርተን እንግሊዛዊ ቄስና ምሁር ሲሆን ከ2 ሺ ዓመታት በላይ ግሪክ ውስጥ ጥቅም ላይ ይውሉ የነበሩ ሕክምናዎችና እና ፍልስፍናዎችን አጠናቅሯል።

ይህ እንግሊዛዊ ምሁርና ቄስ ከፍተኛ ድብርትን ያውቀዋል። በዚህ ጉዳይ ዙሪያም በርካታ ሃሳቦችን አስቀምጧል። ነገር ግን የበርተን የሕይወት ስራዎች በዘመናዊው ሰው ሕይወት ውስጥ ድብርትና ሀዘንን እንዴት ይረዱታል?

ስኮትላንዳዊቷ ጋዜጠኛ ኤሚ ሎፕትሮት የበርተንን ስራዎች አጠናቅራ በድጋሚ በማዘጋጀት ለ21ኛው ክፍለዘመን ሰው በሚመች መልኩ አቅርባዋለች።

እሷ እንደምትለው በ1620ዎቹ ሰዎች ከድብርትና ሀዘን ለመላቀቅ ይወስዷቸው የነበሩ የመፍትሄ እርምጃዎች አሁንም ድረስ ጥቅም ላይ መዋል የሚችሉ ናቸው።

1. የራሳችንን የስሜት መለዋወጥ በአንክሮ መከታተል

በድብርት አልያም በሀዘን ለሚሰቃይ ሰው የሚሰሙት ስሜቶች ምናልባት ያለምንም ምክንያት የሚሆኑ መስለው ሊታዩ ይችላሉ። ነገር ግን የሚሰሙን ስሜቶች የራሳቸው አካሄድ አላቸው።

ድብርት ተላላፊ በሽታ እንደሆነና ምልክቶቹም ሆነ የሚያሳርፉት ጫና ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተወረስ እንደሚሄድ በርተን ያስብ ነበር።

ምናልባት ነገሮችን የተመለከተበት መንገድ የተለየ ሊመስል ቢችልም በዘመናዊው ህክምናም ብቸኛው ምክንያት ባይሆንም ድብርት ከቤተሰብ የሚተላለፍ እንደሆነ ተረጋግጧል።

"አንድ የቤተሰብ አባል በከባድ የድብርት በሽታ የሚሰቃይ ከሆነ መላው ቤተሰብ አብሮት ህክምናውን አብረውት እንዲከታተሉና ለራሳቸውም ነገሮችን እንዲያስተውሉ እፈልጋለሁ'' ይላሉ በቤተሰብ ጉዳዮች ላይ የሚሰሩት ዶክተር ፍራንሲስ ራይስ።

ነገር ግን ድብርት ከቤተሰብ ብቻ የሚመጣ ጉዳይ አይደለም። የተለያዩ ውጪያዊ ምክንያቶችም የራሳቸው አስተወዋጽኦ አላቸው። በርተን መጽሐፉን በሚያዘጋጅበት ወቅት ራሱ ላይ ያስተዋላቸውን ነገሮች ከግምት ውስጥ አስገብቷል።

በየጊዜው የሚቀያየር የደስታና ሀዘን ስሜቶች በዘመናዊው የህክምና ዓለም 'ባይፖላር ዲስኦርደር' የሚባል ሲሆን በርካቶችን የሚያጠቃ ነው።

በአሁኑ ጊዜ ሰዎች የሚሰሟቸውን ስሜቶች በአግባቡ መከታተልና ለምን እንደሚለዋወጡ ማወቅ ለድብርት ፍቱን መድሀኒት ተደርጎ ይወሰዳል። ምን ሲገጥመን የስሜት መለዋወጥ ውስጥ እንደምንገባ ማወቅ ከቻልን እነዚያን ነገሮች ማስወገድ ቀላል ነው።


2. የቀዝቃዛ ውሃ ጥቅም

በርተን በመጽሐፉ ላይ ከብዙ ዓመታት በፊት በሌሎች ሰዎች የተጻፉ የተለያዩ ሀሳቦችን አስፍሯል።

ንጹህ በሆነ ቀዝቃዛ ወንዝ ውስጥ ገላችንን መታጠብ ደግሞ በርተን ካስቀመጣቸው መፍትሄዎች መካከል አንደኛው ነው። ማንኛውም ሰው ረጅም ህይወት መኖር ከፈለገ በጣም በሚያምር ተፈጥሮአዊ ቦታ ላይ ገላን መታጠብ አንደኛው መንገድ ነው ይላል።

'' በቀዝቃዛ ውሀ ምክንያት ሰውነታችን የሚሰማውን ጭንቀት መቋቋም ካስለመድነው ሌሎች አስጨናቂ ነገሮችንም መቋቋም ይማራል'' ይላሉ በዩናይትድ ኪንግደም በሚገኘው ፖርትስማውዝ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ማይክ ቲፕተን።

3. ከተፈጥሮ አለመራቅ

ተፈጥሮ ለበርተን ከፍተኛ ድብርትን ለማባረር ቁልፍ ሚና የሚጫወት ነገር ነበር።

በተለይ ደግሞ በተፈጥሮአዊ ጫካ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ አይነት እጽዋት ጭንቅላታችን ዘና እንዲል እና የሚያስጨንቁትን ነገሮች እንዲረሳ የማድረግ ከፍተኛ አቅም አላቸው።

በኦክስፎርድ ቦታኒክ ጋርደን ዳይሬክተር የሆኑት ፕሮፌሰር ሳይመን ሂሰኮክ እንደሚሉ አንዳንድ ተክሎች ድብርትን ለማከም ጭምር ጥቅም ላይ ይውላሉ።

በርተን ደግሞ አንዳንድ ተክሎች ስንመገባቸው ጭምር ድብርትና የማባረር አቅም ያላቸው ቢሆንም ተክሎቹን መመልከት በራሱ ድብርትን እና ጭንቀትን የማባረር አቅም አለው ይላል።

እንግሊዛዊው የእጽዋት ተንከባካቢ ሞንቲ ዶን እንደሚለው በከፍተኛ ሁኔታ በድብርትና ጭንቀት ተሰቃይቶ ነበር። ነገር ግን እጽዋትን መትከልና መንከባከብ ከጀመረ በኋላ ግን ነገሮች እየቀለሉ መምጣታቸውን ያስታውሳል።

''አንድ ተክል ከተተከለበት ጊዜ ጀምሮ እድገቱን መመልከትና መንከባከብ ለጭንቅላት የሚሰጠው ትልቅ እረፍት አለ'' ይላል።

4. ችግራችንን ለሌሎች ማጋራት

''በውስጣችን የሚሰማንን ጭንቀትና ድብርት ለራሳችን ብቻ ይዘነውና ተሸክመነው ከመቆየት ይልቅ ለሌሎች ማጋራትና አብሮ መፍትሄ መፈለግን የመሰለ ነገር የለም'' ብሎ ነበር በርተን ከ400 ዓመታት በፊት።

ጭንቀትና ድብርት የሚያጋጥማቸው ሰዎች ሁሌም ቢሆን ራሳቸውን ከሰዎች ለይተው መቀመጥ ይመርጣሉ። ነገር ግን መሰል ነገሮች እንደውም ጭራሽ ስቃዩን ያበዙታል።

በቤተሰብ ጉዳዮች ላይ የሚሰሩት ዶክተር ፍራንሲስ ራይስ እንደሚሉት ጭንቀት ሲገባን ከምንወዳቸውና ከሚወዱን ሰዎች ጋር ዘና የሚያደርግ ነገር ማድረግና ችግራችን በዚያው ለእነርሱ ማጋራት በጣም ወሳኝ ነው።

''ምናልባት ከሰዎች ጋር ብዙም ማውራት የማንወድ እንኳን ቢሆን ከሰዎች ጋር ለየት ያለ ነገር ማድረግ ጭንቅላታችን ትኩረቱን ወደ ሌሎች ነገሮች እንዲያደርግ ያግዘዋል''

ጭንቀትና ድብርት አሰቃየኝ ብሎ አንድ ሰው ሐኪም ጋር ቢሄድ ምናልባት ድብርትን የሚያስወግዱ በርካታ አይነት መድሀኒቶች ሊታዘዙ ይችል ይሆናል። ነገር ግን በአሁኑ ሰአት እንደ ዴንማርክ፣ ካናዳ እና ዩኬ ባሉ አገራት መሰል ችግር የሚያጋጥማቸው ሰዎች ከመድሀኒት ይልቅ ከሰዎች ጋር እንዲገናኙ፣ አዲስ ክህሎቶችን እንዲማሩ አልያም ተፈጥሮአዊ ቦታዎችን እንዲጎበኙ ነው የሚታዘዝላቸው።

5. ስራችንን እና ሕይወታችንን ማጣጣም

ምናልባት በርተን ቃል በቃል ስራችንን እና ሕይወታችንን ማጣጣም ብሎ ላይሆን ይችላል። ነገር ግን አዲስ ነገር የመማር ፍቅር በሚል ገልጾታል። እንደውም ይህ የመማር ፍቅር በራሱ ከበዛ ችግር ሊሆን እንደሚችልም አስቀምጧል።

በርተን እንደሚለው ሕይወታችንን የምንመራበት ስራን ለማሳካት አልያም ምርምር ለማድረግ ይሁን ሙሉ ትኩረታችንን እና ጭንቅላታችንን በሙሉ እዛ ላይ ባደረግን ቁጥር ራሳችን ላይ ተጨማሪ ጭንቀትና ድብርት እንጨምራለን።

ሰዎች ስለስራቸው አብዝተው ሲጨነቁ እና ነገሮችን ለማስተካከል ሙሉ ጊዜያቸውን እዚያ ጉዳይ ላይ ባዋሉ ቁጥር ከሰዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት እየቀነሰ ይመጣል። የሚያስደስታቸውን ነገር ማድረግም ቢሆን ያቆማሉ።

ምናልባት በርተን የሰዎችን አስተሳሰብ የተመለከተበትና ያጠናበት መንገድ ያረጀ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እርሱ ተውሶ ያመጣቸው የግሪክ ፈላስፋዎች አስተሳሰብና ህክምናዎች አሁንም ድረስ ጥቅም ላይ መዋል የሚችሉ ናቸው።

ራስን ማወቅ፣ መዋኘት፣ ተፈጥሮ፣ ማህበረሰብ እና ማንበብ ከዛሬ 400 ዓመት በፊት ከሰሩ አሁን ላይ ለእኛስ የማይሰሩበት ምክንያት አለ?

source -BBC News

የስብዕና ልህቀት
Join: @Human_Intelligence
12.8K viewsedited  16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-20 06:41:22 ፍቅርና ተቀባይነት!

አንድ ሰው እንዲህ ሲል የተናገረው ትዝ አለኝ፣ “በሕይወታችን የምናደርጋቸው አብዛኛዎቹ ነገሮች ፍቅርንና ተቀባይነትን ለማግኘት ነው ወይም ላጣነው ፍቅርና ተቀባይነት ማካካሻ ፍለጋ ነው”፡፡ የሚገርም ምልከታ!

ከዚህ በፊት በጣም የተጎዳችሁበትን ሁኔታ አስታውሱት፡፡ ከዚህ በፊት ከእናነት በራቁ ቁጥር የተከታተላችኋቸው ሰዎች አስቧቸው፡፡ በአሁን ወቅት ስሜታችሁን የረበሸውን ነገር አስቡት፡፡ በአሁን ወቅት ከአእምሯችሁ አልወጣ ስላለው ሰው አስቡት፡፡ በአሁን ወቅት የተነሳሳችሁለትን ድንገተኛ ውሳኔ አስቡት፡፡ አብዛኛውን ነገር ከፍቅርና ከተቀባይነት ፍለጋ ጋር ተያይዞ ታገኙታላችሁ፡፡

ሰው የሚረጋጋው ፍቅርንና ተቀባይነትን የመሆኑን ያህል፣ ሰው መረጋጋትን የሚያጣው ፍቅርና ተቀባይነትን ማግኘት ከማይችልበት ሰውና ስፍራ ያንን በመፈለግ ሲንገላታ ነው፡፡

ሰው የሚረጋጋው መወደድንና ተቀባይነትን የሚያስገኝ ባህሪይ ካዳበረ በኋላ ሰዎች የራሳቸው ምርጫ እንዳላቸው አምኖ ሲቀበል የመሆኑን ያህል፣ ሰው መረጋጋትን የሚያጣው ከሰዎች የሚጠባበቀውን ሁኔታ ሚዛናዊ አድርጎ ካልያዘው ነው፡፡  

ሰው የሚረጋጋው ከማንም ሰውና ሁኔታ ውጪ መኖር እንደሚችል ውስጡን ሲያሳምነው የመሆኑን ያህል፣ ሰው መረጋጋት የሚያጣው የሸሸውንና ተቀባይነት የነፈገውን ሰው ሁሉ ሲከታተል ውሎ ሲያድር ነው፡፡

ሰው የሚረጋጋው ከምን አይነት ሰው ምን አይነት ፍቅርና ተቀባይነት እንደሚያገኝ ለይቶ ሲያውቅ የመሆኑን ያህል፣ ሰው መረጋጋትን የሚያጣው ከአንዱ ያጣውን ፍቅርና ተቀባይነት ከሌላ ሰው ለማግኘት ሲጦዝና ደረጃውን ዝቅ ሲያደርግ ነው፡፡

መልካም ቀን!

ዶ/ር እዮብ ማሞ

@Human_intelligence
12.6K views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-08 21:28:45
12.7K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-10-06 08:27:10 የራእይ ጉልበት!

ታዋቂው ጸሐፊ ስቲቨን (Stephen Covey)  First Things First በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ስለአንድ ቪክቶር (Viktor Frankl) ስለሚባል የአውስትራያዊ የስነ-ልቦና ባለሞያ ታሪክ ይናገራል፡፡ ይህ የስነ-ልቦና ባለሞያ ከናዚ (ጀርመን) የሞት ካምፕ የተረፈ ሰው ነው፡፡ ቪክቶር በናዚ የሞት ካምፕ ውስጥ ታሽገው ከነበሩ ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ በሞት ሲያልፉ አንዳንዶቹ ግን እንዴት ያንን ለሞት የሚዳርግ ሁኔታ አሸንፈው ሊወጡ እንደቻሉ በምርምር ደረሰበት፡፡

በጥናቱ ብዙ ነገሮችን ተመልክቷል - የጤንነታቸው ሁኔታ፣ የቤተሰባቸው ሁኔታ፣ ብልህነታቸው፣ ችግርን የመቋቋም ብቃት እና የመሳሰሉት፡፡ በመጨረሻ የደመደመው፣ ከእነዚህ ነገሮች መካከል አንዱም እንኳን ለእነዚህ ሰዎች በሕይወት መኖር ምክንያት እንደልሆነ ነበር፡፡ በዚያ ከባድ ሁኔታ ውስጥ በሕይወት የቆዩት ሰዎች አንድ የጋራ ነገር ነበራቸው፡፡ ይህ ነገር የወደፊት ራእይ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች በሕይወት የመኖርን ነገር ጠንክረው እንዲይዙ ያደረጋቸው ብቸኛውና ጉልህ የሆነው ምክንያት በፊታቸው ገና ያላከናወኑት ራእይ እንዳላቸው የማመናቸው ሁኔታ ነበር፡፡

ጸሐፊው እንደ ቬትናም እና የመሳሰሉት ብዙ የጦር ምርኮኞች በስቃይ በሚታጎሩባቸው ካምፖችም ውስጥም ተመሳሳይ ሁኔታ እንደታየ ይናራል፡፡ አሳማኝ እና ወደፊት ላይ ያተኮረ ራዕይ ብዙዎቹን በህይወት እንዲኖሩ ያደረጋቸው ዋና ሃይል ነበር (ምንጭ፡- Stephen Covey, First Things First, p 103)፡፡

•  አንድ ሰው የሚሞተው ጤናው ሲጠፋ ብቻ አይደለም … ራእይ ሲጠፋም ጭምር ነው!

•  አንድ ሰው የሚከስረው ስራ ሲበላሽ ብቻ አይደለም … የራእዩ ሁኔታ ሲበላሽም ጭምር ነው!

•  አንድ ሰው ብቸኝነት የሚሰማው ሰው ሲርቀው ብቻ አይደለም … ራእይ ሲርቀውም ጭምር ነው!

•  አንድ ሰው ተስፋ የሚቆርጠው ሁኔታዎች አልታይ ሲሉት ብቻ አይደለም … ራእይ አልታይ ሲለውም ጭምር ነው!

•  አንድ ሰው ውዳቂ የሚሆነው ስለወደቀ ብቻ አይደለም … ራእዩን ሲጥል ጭምር ነው!

. . . እያለ እውነታው ይቀጥላል፡፡ ይህ እውነታ እንደሚያሳየን አንድ ሰው ምንም እንኳን በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ ሲያልፍ የዚያን ሁኔታ ውጤት መቅመሱ ባይቀርም፣ የመጨረሻውን ውሳኔ ከሚያስተላልፉትና በብርታትና በደካማነት መካከል ከሚወስኑት ሁኔታዎች መካከል አንጋፋው ራእይ የመኖሩና ያለመኖሩ ጉዳይ ነው፡፡

አሁን ከምታልፉበት አስቸጋሪና ተስ አስቆራጭ ነገር ባሻገር እንድትሄዱ ሊያደርጋችሁ የሚችል ዋነኛው የፈጣሪ ስጦታ ራእይ ይባላል፡፡ 

ራእያችሁን አግኙና እሱን በመኖር አሁን ያለውን ከባድ ዘመን አሳልፉት!

ዶ/ር እዮብ ማሞ
@Human_intelligence
@Human_intelligence
12.6K viewsedited  05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ